5killo Jem'a official Channel
Відкрити в Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Показати більше1 161
Підписники
Немає даних24 години
+37 днів
+730 день
Архів дописів
ነፍሷን አሸንፋ እርቃኗን ከመሆን:
ራሷን አብቅታ ለመትረፍ ለወገን::
መማርን ፈልጋ ልታለማ አገሯን:
በእውቀት አለንጋ አባራ ጅህልናን:
ለሃገር ግንባታ ለማስቀመጥ ጡቧን::
ተፍ ተፍ ስትል ለመሻት እውቀትን:
ከሐገር ለማጥፋት ችግር ድህነትን::
የሰው ቀዬ ሳትደርስ ሳትጋፋ ሌላን:
መራቆትን ጠልታ በመያዟ እምነቷን::
የእህቴን ክብር የዛች የጥብቋን:
በ'ምባ እየተሞላች ገፈፏት ሑርማዋን::
⭐️⭐️⭐️
« አላ ሹለት የዱን » እህቴን የነካች:
የንፅህናን ልክ በቅጥ ያልተረዳች:
በጥላቻ ሰክራ ድንበር የዘለለች:
የእህቴን ካባ ክብሯን የደፈረች::
ያቺ እጅ ትረገም ሐቅን የረገጠች:
ኒቃብን አውልቃ እርቃን ያነገሰች::
የእህቴን ካባ ክብሯን የደፈረች:
ራቁት አስፈትና ለባሽ ያባረረች:
ፍትህን በመጣስ ሚዛን ያጓደለች::
⭐️⭐️⭐️
ሁሉ ሲሰለጥን ሗላ የዘገዩ :
በክፋት ጥላቻ ተነክረው የቆዩ:
ቀለም መንካት እንጂ መማርን ያላዩ::
በ'ድሜ ቢሆን እንጂ ከልጅ ያልተለዩ:
ከሽበት በስተቀር ክፋ ደግ ያልለዩ::
በየ ሴክተሩ ላይ ተሰግስገው ያሉ:
ስንት ሰዎች አሉ አድገው ያልበሰሉ::
የተቀመጡበት ከስር ያለው ወንበር:
ከነሱ ይሻላል በግልጋሎት ግብር::
⭐️⭐️⭐️
ምን ይሆን ክሳችሁ ከቶ ምን አጠፋች?!
ራሴን ጠብቄ እማራለሁ ባለች:
ለ'ምነቷ ዘብ ሆና ፀንታ ስለቆመች::
ጨርቃቸውን ጥለው ሲቆዝሙ ሌሎች:
ክብሯን ችላ ብላ ልብሷን ስላልጣለች::
የቱ ነው ጥፋቷ መብቷን በጠየቀች?:
የራሷን ነው እንጂ የሰው መብት አልነካች::
ከጥላቻ በቀር ምክንያት ካላችሁ:
አይዟችሁ ንገሩኝ በሉ እስኪ ልስማችሁ:
ንገሩን ሰበቡን ድምፅ ከፍ አርጋችሁ::
የክልከላው ምክንያት ከተዋጠላችሁ:
ኑ እስኪ ተናገሩት ካላሳፈራችሁ::
⭐️⭐️⭐️
የኔው ነው ጥፋቱ የኔው ነው ስህተቱ:
ይሰማኝ ይመስል ሙታን መጣራቱ::
መንቃት ያልፈለገን አውቆ የተኛን ሰው:
እሳት ቢሆን እንጂ ውሃ ላያነቃው::
ያፄዎቹን ትርክት ጠጥቶ የሰከረን:
ወደ ፊቱን ትቶ ሗላ ላይ የቀረን::
እውነታውን ገፍቶ መረዳት ዘመኑን:
በጨለማው ዘመን ሰምጦ የቀረውን::
ቅን መሆንን ትቶ ጥላቻን ያዘለን:
ጭቆናን እንደ ድል ስኬት የቆጠረን::
ምን ብዬ ልንገረው እንዴትስ ላስረዳው?!
የጥላቻ ቆፈን ሐቅን ከጋረደው::
የሰው ልጅ ወቃሹ የገዛ ህሊናው:
እሱ የሌለውን ሰው ብለህ አትጥራው::
ይህን ለመረዳት ካልሆነህ ትምርትህ:
ጥላቻን ካስቀደምክ አመክንዮን ትተህ:
ጥቅሙ ምኑ ላይ ነው ቀለም የመንካትህ::
ፕሮፌሰር : ዶክተር : ምሁራን መባልህ:
Master , phD , degree መሸከምህ::
@aaumsu
"መጅሊስ በሂጃብ ጉዳይ ከ Retroactive( እሳት አጥፊነት) ነፃ የሚሆነው መች ነው?" - (ጠበቃ ሙስጠፋ ሺፋ እንደፃፈው)
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሸሪዓ ፍርድ ቤትን አዋጅ ለማሻሻል ከመንግሰት ጋር በመቀናጀት አንድ እምርታ እንዳስመዘገበው ሁላ ስለ ሂጃብ ኢ ህገ መንግስታዊ ብሎም የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሲፈፀም በተለይ የፈተና ወቅትን እየጠበቁ ባልተፃፈ ህግ የሙስሊም ተማሪዎችን ስነ ልቦና ለመጉዳት ሆን ተብሎ በጥቂት የመንግስት ተሿሚዎች ስልጣንን አላግባብ በመጠቀም በአንደኛ ደረጃ፣ በሁለተኛ ደረጃና በከፍተኛ የትምህርት ተቋም እየተፈፀመ ያለውን በደል መጅሊስ ልክ ድርጊቱ ሲፈፀም መግለጫ ከማውጣትና ድርጊቱ ወደ ተፈፀመበት ስፍራ አቅንቶ ለዛሬ ይሁን ዓይነት ሽንገላ ተነጋግረናል ተወያይተናል ይባልና ጉዳዩ ችላ እንደተባለ ከሆነ ጊዜ ቆይታ በኋላ አሁንም ሲያገረሽ መጅሊስ retroactive ( እሳት ማጥፋቱ) ይቀጥላል። ግን እስከ መቼ?
ሒጃብ ሃይማኖታዊ ነው። ይህን ሃይማኖታዊ መብት ከኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀፅ 27(1) አኳያ እንዲከበርና እንዲጠበቅ ዘንድ በደንብና በመመሪያ ጥሰት ፈፃሚዎች ተጠያቂ እንዲሆኑ ሃይማኖታዊ መብትን ብሎም ህገ መንግስታዊ ጥበቃ የተሰጠውን መብት በዘለቄታነት ተከብሮ እንዲዘልቅ መጅሊስ ስር ነቀል ለውጥ እንዲመጣ ዘንድ ጥሰት ሲፈፀም ለጊዜያዊነት ማስታገሻ እየወሰዱ ከመዝለቅ ይልቅ ስር ነቀል ለውጥ ለማምጣት ህግ እንዲከበር አበክሮ ካልሰራ ትላንትም፣ዛሬም ነገም ስለ ሂጃብ ክብር እየተደፋፈነ እንግልቱ ወደ ትውልድ መቀባበሉ ይቀጥላል።
መጅሊስ በአዋጅም ሆነ በህገ መጅሊሱ የህዝበ ሙስሊሙን ሃይማኖታዊ መብት ማስከበርና ማስጠበቅ አበይት ተግባሩ ነው።
@aaumsu
"እምነቴን ልተው?
ወይስ ትምህርቴን?" - አቡ አብደላህ እንደፃፈው
ይህ ዛሬ ብዙ የሙስሊም ሴት ተማሪዎች የሚጠየቁት ከባድ ጥያቄ ሆኗል።
ኒቃብ ለብሳ መማር የፈለገች ተማሪ ከትምህርት ክፍል ውጭ ስትቀር፣ ፈተና እንዳትፈተን ስትከለከል፣ የሚጎዳው አንድ ግለሰብ ብቻ አይደለም፤ የሀገራችን ፍትሕ፣ እኩልነት እና የሕግ የበላይነትም ጭምር ነው።
እኛ የምንጠይቀው ልዩ መብት አይደለም። ሕገ መንግሥቱ የሚያረጋግጠው የእምነት ነፃነት እና የትምህርት መብት በአንድነት እንዲከበሩ ብቻ ነው።
የደኅንነት ወይም የማንነት ማረጋገጫ ካስፈለገ፣ ያንን የሴት ሠራተኛ በሚያረጋግጥበት ሥርዓት መፈጸም ይቻላል። ነገር ግን በኒቃብ ምክንያት ትምህርትን መከልከል ተገቢ መፍትሔ አይሆንም።
ለመንግሥት ያለን ጥሪ፦
የሁሉንም ዜጎች መብት በእኩልነት የሚያስከብር፣ የእምነት ነፃነትንና የትምህርት መብትን የሚያጣጥም ግልጽ መመሪያ እንዲወጣ እንጠይቃለን።
ለመጅሊስ ያለን ጥሪ፦
ይህ የብዙ ሙስሊም ሴት ተማሪዎችን የሚመለከት ጉዳይ ነው። ከመንግሥት፣ ከትምህርት ተቋማት እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመወያየት ሕጋዊ፣ ሰላማዊ እና ዘላቂ መፍትሔ እንዲገኝ የሚጠበቅበትን ሚና እንዲወጣ እንጠይቃለን።
የሙስሊም ሴት ተማሪ ኒቃብ የትምህርቷ ጠላት አይደለም።
እምነትም ሆነ ትምህርት ሁለቱም መብቶች ናቸው፤ አንዱ ሌላውን ሊያስቀር አይገባም።
#ኒቃብ_ወንጀል_አይደለም
#የትምህርት_መብት
#የእምነት_ነፃነት
#ፍትሕ_ለሁሉም
@aaumsu
"ክብሯን አስወለቋት!"
የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ኒቃቡን ካላወለቃችሁ ተብለው ማውለቅ ጀመሩ። በአደባባይ ክብራቸውን እንዲያወልቁ ተደረጉ። እስካሁን ባለው መፍትሔ ተብሎ የተሰጠው ማስክ ለብሰው መግባትን ነው። ኒቃብም ማስክም ፊትን ይሸፍናሉ። ኒቃቡን አስወልቀው ማስክ ማስለበስን ለምን ፈለጉ? ማስክ አስለብሰው ኒቃቡን ማስወለቅ ለምን ፈለጉ?! ጥላቻ! ለኢስላማዊ እሴት ያለ ጥላቻ!! ሌላ ምንም ምክንያት የለም። አሁንም ቢሆን ተማሪዎች ክብራቸውን በአደባባይ ሳይጥሉ፤ ከእነ ኒቃባቸው እንዲፈተኑ መጅሊስ እና የሚመለከተው የመንግስት አካል ይስራ። አሁንም ቢሆን ይህንን ውንብድና የፈፀሙ አካላት ተጠያቂ እንዲደረጉ መንግስት እና መጅሊስ ይስሩ።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
ዛሬም ኒቃባቸውን በአደባባይ አውልቀው እንዲገቡ ተገደዋል!
በትላንትናው እለት የ12ተኛ ክፍል ኢንትራንስ ተፈታኝ ተማሪዎች በአብርሆት ቤተመፅሐፍት እየተፈተኑ ባለበት ከ20 በላይ ሙስሊም ተማሪዎችን "ኒቃባችሁን ካላወለቃችሁ አትገቡም!" - ተብለው ጓደኞቻቸው ውስጥ እየተፈተኑ እና በትምህርት ሚኒስቴሩ ሚንስትር ብርሃኑ ነጋ እየተጎበኙ ለ3 ሰዓታት ያክል ከውጪ እንዲሆኑ ተደርጎ ነበር። የሗላ ሗላ እንዲገቡ ቢደረግም ኒቃባቸውን አውልቀው እና ጥለው በማስክ ነበር። መፍትሔ እንደሚመጣ የተገለፀ ቢሆንም በዛሬው እለትም በተመሳሳይ ኒቃባቸውን በአደባባይ እያወለቁ እንዲገቡ ነው የተደረጉት።
ይህ ግልፅ የሆነ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው። ይህ ግልፅ የሆነ የሀይማኖት መብት ጥሰት ነው። ይህ ግልፅ የሆነ የነፃነት መብት ጥሰት ነው። ኒቃብን መልበስ መብት ነው። መብት ስለሆነም ለብሳው ስትማር ነበር። አሁን ላይ እየተፈፀመ ያለው ውንብድና ተማሪዎችን የስነ-ልቦና መቃወስ ውስጥ እየከተታቸው ነው። ተማሪዎችም አስቸኳይ መፍትሔ እንዲመጣላቸው እየጠየቁ ነው። መጅሊስ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ ይስራ። መንግስት ተጠያቂ መደረግ ያለባቸውን አካላት ተጠያቂ ያድርግ። ዘላቂ መፍትሔም ይምጣ!!!
@aaumsu
ይህ ምስል፣ ልብን በሀዘንና በቁጭት የሚሰብር የታሪክ ጠባሳ ነው! (በኡስታዝ ነስሩ ኸዲር)
መሬት ላይ ተጥሎ የሚታየው ተራ ጨርቅ አይደለም፤ የአንዲት እህታችን ክብር፣ ማንነት እና የእምነት መብት እንጂ!
ተማሪዎች ነገ ሀገር ለመረከብ በሚፈተኑበት አዳራሽ ደጃፍ ላይ እምነታቸውን በግድ እንዲያወልቁ መገደዳቸው እጅግ አሳዛኝ ሥርዓት አልበኝነት ነው።
ሂጃብ ለሙስሊም ሴት ልጅ ውጫዊ ጌጥ ሳይሆን፣ የማንነቷ አካልና የእሴታችን መገለጫ ነው።
ይህ ድርጊት በአዲስ አበባ ከተማ እምብርት ላይ ሲፈጸም፣ የሚመለከታቸው የመፍትሄ አካላት እስካሁን ድረስ ግልጽና የማያሻማ እርምጃ አለመውሰዳቸውና በዝምታ ማለፋቸው ተጠያቂነትን ያጠፋ የተቋማት ዳተኝነት ነው።
ትምህርት ቤት የነፃነትና የእኩልነት ማዕከል መሆን ሲገባው፣ የተማሪዎችን ስነ-ልቦና የሚሰብር አግላይ መድረክ ሊሆን አይገባም።
ይህንን በደል ዝም ብሎ ማየት አብሮነትን ማፍረስ በመሆኑ፣ የሚመለከተው አካል አስቸኳይ ማስተካከያ እንዲያደርግና ጥፋተኞችን ተጠያቂ እንዲያደርግ በጽኑ እንጠይቃለን።
@aaumsu
🔖በ4ኪሎ የቂርዐትና ደዕዋ ክፍል የተዘጋጀ አዲስ የክረምት ደርስ
📚 ሲራ (የረሱልﷺን የህይወት ታሪክ) የተመለከተ
══━━━።◈።━━━━══
📚اَلْفُصُولُ فِي سِيرَةِ الرَّسُولِ
📝የመልእክተኛው የሕይወት ታሪክ ምዕራፎች
📌የቂርዐት አይነት ፦ ኦንላይን(Online)
⏰ሰዐት፦ዘወትር ሰኞ እና ማክሰኞ ከኢሻ በኋላ(2:45)
⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻
https://t.me/Qirat4k/835
📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ።
https://t.me/Qirat4k
✴️ይህንን ኪታብ ምን ለየት ያደርገዋል???
🔵 የኪታቡ አዘጋጅ ኢብኑ ከሲር ሙፈሲር ፣ ሙሀዲስ ናቸው እንደሌላው የሲራ ኪታብ ደካማና አስተማማኝ ያልሆኑ ዘገባዎችን የሌለበት ፣ በትክክለኛ ዘገባዎች ላይ የተመሠረተ ነው።
🔴 የኪታቡ አፃፃፍ ከሌላው ለየት የሚያደርገው የነቢዩን (ﷺ) የሕይወት ታሪክ ፣ባህሪቸውን ፣ ሀዲሶች እና አህካሞችን በአንድ የያዘ ኪታብ ነው።
⚫️ ረጅም ታሪኮችን ዋና ሀሳባቸውን ሳይተው በአጭርና ግልጽ በሆነ አቀራረብ ያቀረበ፤
ለጀማሪዎች እና ዕውቀትን በፍጥነት ለመገንባት ምቹ በሆነ ማጠቃለያ የተዘጋጀ ነው።
🔷በመጨረሻም በአጫጭርና በተደራጁ ምዕራፎች የተከፋፈለ በመሆኑ፤
ለማንበብ፣ ለመረዳትና መረጃን በቀላሉ ለመፈለግ እጅግ ቀላል ነው።
✳️ ኪታቡ(ደርስ) የሚጀመረው 23/10/2018 ማክሰኞ ማታ 2:45
@aau4kilomsj
"መመሪያው መማር ማስተማሩን የሚረብሹ እና ስነ-ምግባርን ያልተከተሉ ብሎ እንደሚያስቀጡ ከገለፀ ቡሃላ ከእነዚህ መካከል በአንቀፅ 1.3 እና 2.3 ላይ 'ፊትን በሙሉ የሚሸፍን (ኒቃብ) መልበስ አይፈቀድም ይላል።" - የሆፕ ኢንተርፕራይዝ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ሙስሊም ተማሪዎች
የኮሌጁ ሙስሊም ተማሪዎች ይህ መመሪያ ኒቃብን ስነ-ምግባርን ያልተከተለ ብሎ ማስቀመጡ እምነትን እና ማንነትን የሚያንቋሽሽ ነው በማለት ገልፀዋል። ይህንንም ተከትሎ በኒቃቢስት ተማሪዎች ላይ የተለያዬ ክልከላ እና እንግልት እየደረሰባቸው እንደሆነ አስቀምጠዋል። መፍትሔ ይመጣ ዘንድም ለኮሌጁ፤ ለአዲስ አበባ እና ፌደራል መጅሊስ ደቤዳቤ ያስገቡ ቢሆንም እስካሁን ድረስ መፍትሔ እንዳልመጣ በመግለፅ መመሪያው የሙስሊም ተማሪዎችን መብት ባከበረ መልኩ ይስተካከል ዘንድ እና ይህንን ያደረጉ አካላት በሕግ አግባብ እንዲጠየቁ ይሰራ ዘንድ ጠይቀዋል።
@aaumsu
🔖በ4ኪሎ የቂርዐትና ደዕዋ ክፍል የተዘጋጀ አዲስ የክረምት ደርስ
📚 ሲራ (የረሱልﷺን የህይወት ታሪክ) የተመለከተ
══━━━።◈።━━━━══
📚اَلْفُصُولُ فِي سِيرَةِ الرَّسُولِ
📝የመልእክተኛው የሕይወት ታሪክ ምዕራፎች
📌የቂርዐት አይነት ፦ ኦንላይን(Online)
⏰ሰዐት፦ዘወትር ሰኞ እና ማክሰኞ ከኢሻ በኋላ(2:45)
⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻
https://t.me/Qirat4k/835
📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ።
https://t.me/Qirat4k
✴️ይህንን ኪታብ ምን ለየት ያደርገዋል???
🔵 የኪታቡ አዘጋጅ ኢብኑ ከሲር ሙፈሲር ፣ ሙሀዲስ ናቸው እንደሌላው የሲራ ኪታብ ደካማና አስተማማኝ ያልሆኑ ዘገባዎችን የሌለበት ፣ በትክክለኛ ዘገባዎች ላይ የተመሠረተ ነው።
🔴 የኪታቡ አፃፃፍ ከሌላው ለየት የሚያደርገው የነቢዩን (ﷺ) የሕይወት ታሪክ ፣ባህሪቸውን ፣ ሀዲሶች እና አህካሞችን በአንድ የያዘ ኪታብ ነው።
⚫️ ረጅም ታሪኮችን ዋና ሀሳባቸውን ሳይተው በአጭርና ግልጽ በሆነ አቀራረብ ያቀረበ፤
ለጀማሪዎች እና ዕውቀትን በፍጥነት ለመገንባት ምቹ በሆነ ማጠቃለያ የተዘጋጀ ነው።
🔷በመጨረሻም በአጫጭርና በተደራጁ ምዕራፎች የተከፋፈለ በመሆኑ፤
ለማንበብ፣ ለመረዳትና መረጃን በቀላሉ ለመፈለግ እጅግ ቀላል ነው።
✳️ ኪታቡ(ደርስ) የሚጀመረው 23/10/2018 ማክሰኞ ማታ 2:45
@aau4kilomsj
ልዩነቱን ተመልከቱ
አንዱ ከቤተ- መንግስት ፊት ለፊት ሲሆን ሌላኛው ደግሞ በወራቤ ዩኒቨርስቲ ነው። ሁለቱም ለኢንትራንስ ተማሪዎችን እያስፈተኑ ሲሆን ከቤተ- መንግስት ፊት ለፊት ያለው በትምህርት ሚኒስቴሩ ብርሃኑ ነጋ ኒቃባቸውን ገፍፎ ከመሬት ሲጥል፤ በወራቤ ያለው ደግሞ ክብራቸውን ጠብቆ ስርዓቱን በተከተለ መልኩ ፈትሾ አስፈትኗቸዋል።
@aaumsu
ከአራት ቀን በፊት ነበር "ኒቃቧን እንደለበሰች ትማራለች!" - የሚል ፅሁፍ ያለበትን ሪቫን የለበሱ 12 የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተመራቂ ተማሪዎች በምርቃታቸው ቀን ከእስር ቤት እንዲውሉ የተደረገው። ዛሬ ደግሞ ኢንትራንስ የሚፈተኑ ተማሪዎች "ኒቃብ ስለለበሳችሁ ልትገቡ አትችሉም!" - ተብለው ጓደኞቻቸው እየተፈተኑ ባለበት ከውጪ እንዲቀመጡ ተደረገ።
What are we waiting for? ምን እስኪደርስ ነው የሚጠበቀው? የክብራችን ዋጋ ምን ያክል ነው? የእስልምናችን ዋጋ ምን ያክል ነው?
@aaumsu
ማስክም ኒቃብም ፊትን የሚሸፍኑ ሆነው ሳለ ኒቃባቸውን አስወልቀው በማስክ አስገቧቸው። እንዳሉት ለደህንነት ጉዳይ ቢሆን ኖሮ ማስኩም ፊትን ስለሚሸፍን መለበስ አልነበረበትም። ሆኖም ግን ምክንያታቸው ሙስሊም ጠልነት ስለሆነ ፍላጎታቸው ኒቃቡን በማስወለቅ ማዋረድ፣ መጨቆን፣ ከእምነቷ ማራቅ ነው፤ አደረጉትም።
መብቷን ማስጠበቅ የነበረበት መጅሊስም ከቦታው ተገኝቶ ማስክ ገዝቶ ሰጣት።
@aaumsu
ክብራችንን ነው የገፈፉት
መብታችንን ነው የጣሉት
ነፃነታችንን ነው በማስክ የቀየሩት
ጨርቅ ነው ብለው ከወሰዱ ስህተት ነው። ሱና ነው ብሎ ያብራራም ካለ ውርደት ነው። ይህ እንደ ሀገር፤ እንደ ኢትዮጵያዊ፤ እንደ ዜጋ መብታችን የሆነ ነገር ነው። የክብራችን መገለጫ፤ የሐይማኖት መብታችን ዋስትና ነው።
ሆኖም ግን ገፈፏቸው
ሆኖም ግን አስወለቋቸው
ሆኖም ግን ከመሬት ጣሉት
ይህ በእኔ እና በአንተ ዘመን እየሆነ ያለ ነው!
@aaumsu
+1
ኒቃባቸውን በዚህ መልኩ ሰብስበው ከመለሱ ቡሃላ ማስከ አስለብሰው ነው ያስገቧቸው። ይህ ነው ጊዜያዊ መፍትሔ? ይህ ነው መፍትሔው?! ይህ እኮ ውርደት ነው ወገን!!!
@aaumsu
መጅሊስ የሙስሊም ተማሪዎችን መብት ለማስከበር ቁርጠኝነት ካለው የሚከተሉትን ነገሮች ያድርግ፦
፨ የመብት ጥሰት እየፈፀሙ ያሉ አካላትን በሕግ አግባብ እንዲጠየቁ ያድርግ
፨ ለሙስሊም ተማሪዎች መብት እውቅና የሚሰጥ መመሪያ ይወጣ ዘንድ በቁርጠኝነት ይስራ
@aaumsu
መንግስት ከሙስሊሙ ማህበረሰብ የመብት ጥያቄ ጋር ችግር ከሌለበት እና ችግሩ የብርሃኑ ነጋ ብቻ ከሆነ የሚከተሉትን ያድርግ፦
1ኛ፦ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ ተደጋጋሚ የመብት ጥሰት እንዲፈፀም እያደረገ ያለውን ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከሀላፊነቱ ያንሳ፤ በሕግ አግባብም ተጠያቂ እንዲሆን ይስራ
2ኛ፦ ለሙስሊም ተማሪዎች ሕገ- መንግስታዊ መብቶች እውቅና የሚሰጥን መመሪያ ያውጣ
@aaumsu
የሙስሊም ተማሪዎች መብቶች ማስከበር ለእነሱ የሚደረግ ውለታ አይደሉም። ከአላህ ለሁላችንም በቦታችን ልክ የተሰጠ አደራ፣ ህጋዊ ኃላፊነት እና የማህበረሰብ ግዴታ ናቸው። ሙስሊም ተማሪዎችን መደገፍ በጎ አድራጎት (ሰደቃ) አይደለም፤ አማናን (አደራን) መወጣት ነው።
@aaumsu
የትምህርት ሚኒስቴርን በሚኒስትርነት እንዲመራ የተቀመጠው ሰው ገብቶ እየጎበኘ ካለበት የፈተና ማዕከል በር ላይ ነበር ኒቃቢስት ተማሪዎች አትገቡም ተብለው ለሶስት ሰዓታት ያክል ከበር የተቀመጡት። ይህንን ሰው ነው መንግስት በትምህርት ላይ ለውጥ እንዲያመጣ ያስቀመጠው? ተማሪዎቹ እንዲገቡ ቢደረግም እንዲገቡ የሆነው ኒቃባቸውን አውልቀው በማስክ ብቻ ነው። ጊዜያዊ መፍትሔ የሚባለው ይህ ነው? ኒቃብ ማውለቃቸው ለምን ተፈለገ? በማስክ መሆኑን ለምን ፈለጉት?! አሁንም ጥንቃቄ እና ዘላቂ መፍትሔ ያስፈልጋል።
@aaumsu
+1
ግንቦት 7 ወ ሰኔ 23
ከ46 ቀናት በፊት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች በኒቃብ ምክንያት እየደረሰባቸው ስላለው መጠነሰፊ የመብት ጥሰት፣ እንግልት እና ጭቆና አቤት ለማለት ከዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ፊት ለፊት ቆመው ነበር። ሆኖም የሚያወያያቸው አካል እንኳ ሳይኖር ከምሽቱ 4:30 ደረሰ። የዚያኔም ከሰላም ሚኒስቴር፤ ሀይማኖት ተቋማት ጉባዔ፤ አዲስ አበባ ፀጥታ ጽ/ቤት፤ መጅሊስ እና ከዩኒቨርስቲው የመጡ አካላት ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት ውይይት እንደሚካሄድ በተማሪው ፊት ቃል ገብተው ተማሪው ተበተነ።
ከ46 ቀናት ቡሃላ በሰኔ 23 / 2018 ዓ.ል የ12ተኛ ክፍል ተማሪዎች ኒቃባችሁን ካላወለቃችሁ አትፈተኑም ተብለው ከጧቱ 2:00 እስከ 5:00 ድረስ ቆሙ። ከሰላም ሚኒስቴር፤ መጅሊስ፤ አዲስ አበባ ፀጥታ ወዘተ ... የመጡ ሰዎችም እንዲገቡ አደረጓቸው።
አሁንም ግን ዘላቂ መፍትሔ አልመጣም። አሁንም ግን ተማሪዎች ላይ እንግልት የፈፀሙ አካላት ተጠያቂ አልተደረጉም። እስከ መች? ቀጣይስ የት ይሆን? የት ይሆን ችግር የሚፈጥሩት? መች ይሆን የሚያስጮሁን? መች ይሆን ጊዜያዊ መፍትሔ መጣ የሚል ዜና የሚሰራው?!
መሰል እሽክርክሪት መቀጠል የለበትም። ለጥያቄዎቻችን ዘላቂ መፍትሔ እንሻለን። መጅሊስም መንግስትም ዘላቂ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ በቁርጠኝነት ይስሩ።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !!!
@aaumsu
