ar
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

الذهاب إلى القناة على Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

إظهار المزيد
1 160
المشتركون
-124 ساعات
+17 أيام
+530 أيام
أرشيف المشاركات
ይህ ትላንት የሆነ ነው!!! ‎ለውይይት የተገባው ቃል 4 ቀን ካለፈው በኋላ ማለት ነው። ‎ "አንቺ ለምንድን ነው ያስገባሻት? አልሸባብ ብትሆንም አሸባሪ ብትሆንም እንደዚህ ነው የምታስገቢያት? ምን ማለት ነው?" - የ6ኪሎ ጥበቃ ‎ ‎   አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ ለ20 ወራት ሲያካሂድ የነበረውን የመብት ጥሰት በውይይት ለመፍታት ፍቃደኛ ባለመሆኑ ግንቦት 7 / 2018 ዓ.ል ከዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ፊት ለፊት በመሰባሰብ ጠይቀን ነበር። ውይይትን የተጠየፉት የዩኒቨርስቲው አመራሮች ለተማሪዎች ምንም አይነት ምላሽ ሳይሰጡ ምሽት አራት ሰዓት ሲያልፍ ከሰላም ሚኒስቴር፤ ከኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት ጉባዔ፤ ከፌደራል እና አዲስ አበባ መጅሊስ የመጡ አመራሮች ባሉበት ቅዳሜ ውይይት ተደርጎ ዘላቂ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ እንደሚሰራ ተገልፆ ነበር። ይህንንም ተከትሎ በማግስቱ ቅዳሜ እንዲሁም ሰኞ እለት ከመጅሊስ አመራሮች ጋር ጥልቅ እና ፍሬያማ ውይይት የተደረገ ሲሆን የመንግስት አካላት በዚህ ሳምንት የውይይት መድረኮችን ሊያዘጋጁ ቃል እንደገቡ ተገልፆ ነበር። ‎ ‎   ሆኖም ይህ በእንዲህ ባለበት በዛሬው እለት በ6ኪሎ የሚገኙ ጥበቆች በኒቃቢስት ተማሪዎች ላይ እላፊ ንግግሮችን ሲናገሩ እና ተማሪዎች ላይ እንግልት ሲፈፅሙ ነበር። ጥበቃዎቹ ኒቃቢስት ተማሪዎችን እንዳይገቡ ሲከለክሉ አንዲት እህት እርሷ በከፈተችው በር እንዲገቡ ማድረጓን ተከትሎ "አንቺ ለምንድን ነው ያስገባሻት? አልሸባብ ብትሆንም አሸባሪ ብትሆንም እንደዚህ ነው የምታስገቢያት? ምን ማለት ነው?" - እያሉ ሲወርፏት ተስተውሏል። ‎ ‎   ይህ ፍፁም አግባብነት የሌለው፤ ዩኒፎርምን ከለበሰ የጥበቃ አካል የማይጠበቅ ድርጊት ነው። መሠል ሕገ- ወጥ ተግባራት እየተፈፀሙ ያሉት ዩኒቨርስቲው ባፀደቀው ሕገ- ወጥ መመሪያ ምክንያት ነውና ችግሩ በውይይት እንደሚፈታ ቃል የገቡ የመንግስት አካላት ውይይቱን በቶሎ አድርገው ዘላቂ መፍትሔ እንዲያመጡ እንጠይቃለን። ‎ ‎ለተማሪዎቻችን፦ ስነ-ምግባር የጎደለው እና ፀያፍ ንግግርን ለሚናገሩ የዩኒቨርስቲው አካላት ምላሽ አትሰጡ። በአላህ ፈቃድ በሕግ ፊት ተጠያቂ እንዲሆኑ የምናደርግ ይሆናል። ‎ ‎ለሰላም ሚኒስቴር፤ የኢትዮጵያ ሐይማኖት ተቋማት ጉባዔ እና ለሚመለከታቸው በሙሉ፦ ተማሪው በአደባባይ የወጣው ለ20 ወራት ያክል ከቢሮ ቢሮ ተንከራቶ ፍትሕን ስለተነፈገ ነው። በዚያ ምሽት ከተማሪ ፊት የገባችሁትን ቃል በመፈፀም ሀገር የጣለችባችሁን ሀላፊነት ትወጡ ዘንድ ጥሪያችን ነው። @aaumsu

‎Update ! ‎ ‎እስከአሁኗ ሰዓት ሰዓት ድረስ ከዩኒቨርሲቲው በኩል ለውይይት የተከፈተ በር የለም!!! - ያንን ተከትሎም ዩኒቨርሲቲው ከዚህ ሳምንት የቀሩትን ቀናት በመጠቀም ራሱን ለውይይት ብቁ እንዲያደርግ ለመጨረሻ ጊዜ ጥሪ እናቀርባለን። ያ ሳይሆን ቢቀር ግን የውይይት በር ሲዘጋ ለሚከፈቱት ሌሎች በሮች ሁሉ ዩኒቨርሲቲው ተጠያቂነቱን የሚወስድ ይሆናል። ‎ ‎እንደሚታወቀው ሰኞ ዕለት ከፌደራል መጅሊስ አመራሮች ጋር ከቅዳሜው የቀጠለ ውይይት ነበረን። ውይይቱ ፍሬያማ የነበረ ሲሆን፥ በዚህ ሳምንት ውስጥ የመንግስት አካላት የውይይት መድረክ አዘጋጅተው ዘላቂ መፍትሔ የሚመጣበት መንገድ እንደሚኖር ተገልጿል። ‎ ‎ውይይቱ ይካሄዳል የተባለው ጁምዓ ምሽት ከተማሪዎች ፊት ሆኖ ሳለ እስካሁንም መዘግየቱ ቅሬታ ፈጥሯል። አሁንም ቢሆን በተማሪው ፊት የተገባው ቃል ተግባራዊ ሆኖ ዘላቂ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ እንጠይቃለን። ‎ ‎በቀጠሮ የሚዘገይ ፍትሕ ሊኖር አይገባም። ጨቋኙ የዩኒቨርስቲው መመሪያ ይሻሻል። ድንበር አልፈው እምነታችንን ያንቋሸሹ እና ተማሪዎችን ያንገላቱ አካላት ተጠያቂ ይሁኑ። ‎ ማስታወሻ፦ ‎ ‎ይህንን ለማስተካከል የሰጠነው ጊዜ፥ ይሄኛው ሳምንት ብቻ ነው። እስከዚህ ሳምንት መጨረሻ ድረስ ባሉ የሥራ ቀናት፥ በተገባው ቃል መሰረት ከግቢው በኩል ምላሽ የማናገኝ ከሆነ ትግላችን ተጠናክሮ ይሆናል። ‎ ‎ተማሪዎቻችን፦ ‎ ‎ይህንን ሳምንት በተመለከተ... ያሉ ሂደቶችንና ውጤቶቻቸውን በትዕግስት እንድትጠብቁና በተጠቀሱት ቀናት ምንም ውጤት የማይመጣ ከሆነ፥ ራሳችሁን ተደራሽነቱን ለሚያሰፋው ትግል እንድታዘጋጁ ስንል እንጠይቃለን። ‎ ‎ቀኑ መቁጠር ጀምሯል። በሚነጉዱት ሰዓታት ፍጥነት ልክ ራሳችሁን እያዘጋጃችሁ ጠብቁ! ‎ ‎ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! @aaumsu

የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ የቀድሞ ኢንፎርሜሽን ሴክተር አሚር አቡበክር "ፍትሕ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች!" - ሲል መልዕክቱን አድርሶናል። ጥያቄው የሁሉም ነው _
የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ የቀድሞ ኢንፎርሜሽን ሴክተር አሚር አቡበክር "ፍትሕ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች!" - ሲል መልዕክቱን አድርሶናል። ጥያቄው የሁሉም ነው _ ፍትሕ እስኪመጣ በሁሉም መንገድ እንጠይቃለን _ በአደባባይም ቢሮ ውስጥም እንጠይቃለን _ በሚዲያም በአካልም እንጠይቃለን! ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! @aaumsu

‎አለማወቅ... 4! ‎ ‎ማስፈራሪያው የበገረው ‎ቃልኪዳኑን ያጓደለ፣ ‎የድል ድርሳን መክተቢያውን ‎«እስክሪብቶ» ... የጣለ አለ?! ‎ ‎በዚያች ቦታ ... ‎የዚያን ጊዜ ... ‎ ‎ታሪክ ዝንቱን
አለማወቅ... 4! ‎ ‎ማስፈራሪያው የበገረው ‎ቃልኪዳኑን ያጓደለ፣ ‎የድል ድርሳን መክተቢያውን ‎«እስክሪብቶ» ... የጣለ አለ?! ‎ ‎በዚያች ቦታ ... ‎የዚያን ጊዜ ... ‎ ‎ታሪክ ዝንቱን የማይረሳው ‎የሚዘከር ገድል ሲጻፍ፣ ‎"ጸንቶ መቆም" ጎልቶ ጩኋል ‎"ሂዱ" ከሚል የጨቋኝ አፍ። ‎ ‎በዚያች ቦታ ... ‎የዚያን ጊዜ ... ‎ ‎"እስክሪብቶ የጣለ አለ"ን ‎"ተበተኑ" ካለው በላይ፣ ‎እንደሰማን ማን ይንገረው ‎ያለመፍራት ልኩን እንዲያይ። ‎ ‎ለነገሩ... ማን ይፈርዳል?! ‎ ‎ሐቅን ይዞ 'ፍርሃት' ላይኖር ‎ከሙእሚን ልብ መዝገበ ቃል፣ ‎'መፍራት' ቃሉን እንደማናውቅ ‎ይህን እርሱ በምን ያውቃል?! ‎ ‎ባወቀማ... ባልሞከራት! ‎ ‎እንድንፈራው ነበር መሰል ‎ዱላ ይዞ የከበበን፣ ‎እሳት ዱላን ፈርቶ ሲቆም ‎የት እንዳየው በነገረን?! ‎ ‎አለማወቅ! ‎ ‎በነገ ገጽ የምንከትበው ‎'ክብርን ማውለቅ' ስለሌለው፣ ‎ስለዚህ ነው ቢያስፈራሩን ‎እስክሪብቶ የማንጥለው። ‎ ‎ማስፈራሪያው የበገረው ‎ቃልኪዳኑን ያጓደለ፣ ‎የድል ድርሳን መክተቢያውን ‎«እስክሪብቶ» ... የጣለ አለ?! ‎ ‎••• ከየት መጥቶ?! ‎ #ዘመቻ_ዙልሒጃ! #በሂደት_ላይ... #አሁንም_ዝግጁ?! @aaumsu

ዩኒቨርስቲ አዕምሮን ማበልፀጊያ እንጅ ማንነትን መደፍጠጫ አይደለም። ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች እንዲያስቡ፣ እንዲመራመሩ፣ ባህላቸውን እንዲያሳድጉ፣ ሐይማኖታቸውን እንዲጠብቁ፣ መከባበርን እንዲያደብሩ ማገዝ አለበት እንጂ ጨፍላቂ መሆን የለበትም። የሚወጡ ሕጎች መማር ማስተማሩን ሊያሻሽሉ ሲገባ የተማሪዎችን ማንነት ከጥያቄ ውስጥ የሚያስገቡ መሆን የለባቸውም። @aaumsu

አሰላሙዓለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካትሁ ​ባለፈው ጁምዓ በፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ተሰባስባችሁ ከነበራችሁ ወንድሞች እና እህቶች መካከል በምስሉ ላይ የሚታዩትን ፓወር ባንክ (Power Bank) እና መ
+1
አሰላሙዓለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካትሁ ​ባለፈው ጁምዓ በፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ተሰባስባችሁ ከነበራችሁ ወንድሞች እና እህቶች መካከል በምስሉ ላይ የሚታዩትን ፓወር ባንክ (Power Bank) እና መስገጃ የረሳችሁ (የጣላችሁ) ካላችሁ እቃዎቹን መውሰድ ትችሉ ዘንድ ከታች በተቀመጠው ቦት አማካኝነት ያናግሩን። 👇 ​ @MediasectorFeedback_botማሳሰቢያ፦ እቃዎቹ የእርስዎ መሆናቸውን እርግጠኛ ለመሆን በሚያናግሩን ወቅት ጥቂት ማብራሪያ (ለምሳሌ፦ የፓወር ባንኩን ብራንድ ወይም መስገጃው ያለበትን የተለየ ምልክት) ቢጠቅሱልን ኸይር ነው። ​እባክዎ ለሌሎችም እንዲደርስ ሼር ያድርጉት። ጀዛኩሙላሁ ኸይረን! ©AAU6kilojemea @aaumsu

በነዚህ ቀናት ሊበዙ የሚገባቸው ምርጥ ተግባራት 🔊​የአላህ አፍቃሪዎች ሆይ! በዚህ ወቅት የሚከተሉትን መልካም ስራዎች አብዝ፦ 🪾​አምልኮቶችና ሰደቃ ሶላቶችን፣ ቁርኣን መቅራትን፣ ጾምን እንዲሁም ሰደቃን አብዙ። 🪾​ለወላጆች በጎ መዋል ወላጆችን በተለያዩ መንገዶች በጥሩ ሁኔታ መንከባከብ፣ እንዲሁም ካለፉ በኋላ የነሱን ወዳጆችና ዘመዶች በመዘየር (በመጠየቅ) በጎነትን ማሳየት። 🪾​ዝምድናን መቀጠል የደም ትስስር ያላቸውን ዘመዶች መጎብኘት። 🪾​ማህበራዊና ዲናዊ ኃላፊነት ምስኪኖችን ፈልጎ ማገዝ፣ የዘነጉትን (ጋፊሎችን) ወደ አላህ መንገድ መጣራት፣ ዲንን መርዳት እና የተበደሉና የተጨቆኑ ሙስሊም እህት/ወንድሞቻችንን መደገፍ። 🪾​ዚክር ማብዛት፦ በቤቶቻችሁ፣ በመንገዶች ላይ፣ በጉዞአችሁም ሆነ በትርፍ ጊዜያችሁ ሁሉ ተክቢራ (አላሁ አክበር)፣ ተህሊል (ላ ኢላሀ ኢልለላህ) እና ተህሚድ (አልሐምዱሊላህ) ማለትን አብዝቱ። 🪾​ተውበት ማድረግ ወንጀልና ስህተት ያለበት ሰው ሁሉ በአስቸኳይ ከእሱ ይራቅና ወደ ጌታው ይመለስ። 🪾ዱዓ Lአላህ ለእኛም ለእናንተም በእነዚህ ቀናት ውስጥ በረከቱን ይክፈትልን፤ በውቦቹ የጀነት የንአይም ገነቶችም ውስጥ በአንድነት ይርሰን።

በዙልሒጃ አስርቱ ቀናት የሚደረግ         መልካም ስራ ደረጃከጂሃድ የሚበልጥ ስራ፦ ከነቢያችን (ሰ.ዐ.ወ) በተረጋገጠው ሐዲስ ላይ እንዲህ ብለዋል፦ ​
"በነዚህ (በአስሩ የዙልሒጃ) ቀናት ውስጥ ከሚሰሩ መልካም ስራዎች ይልቅ አላህ ዘንድ ይበልጥ ተወዳጅ የሆኑ መልካም ስራዎች የሚሰሩባቸው ቀናት የሉም።" ሶሃቦችም፦ "የአላህ መልክተኛ ሆይ! በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሃድም ቢሆን አይበልጠውም?" አሉ። ነቢያችንም (ሰ.ዐ.ወ)፦ "በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሃድም ቢሆን አይበልጠውም፤ በነፍሱና በገንዘቡ ወጥቶ ከዚያ ነገር በምንም ሳይመለስ የቀረ (የተሰዋ) ሰው ቢሆን እንጂ" አሉ።
​👉 ይህ የዙልሒጃ ወቅት እኛ የምናተርፍበት፣ በአዛኙና የልዑልነት ባለቤት በሆነው ጌታችን ዘንድ መቃረብን የምናገኝበት፣ እንዲሁም የወንጀሎቻችንን ዕዳ የምንከፍልበት (የምናባብስበት) ወርቃማ ወቅታችን ነው። ስለዚህ አላህንና መልክተኛውን የምትወዱ ሁሉ! ትጋት.. ትጋት ይኑራችሁ!

‎አለማወቅ... 3! ‎ ‎ዱላ አስከተለ አሉ ‎አልቻልህ ቢለው፥ በአፉ ዝም ማስባል፣ ‎እንዴት በገዛ እጁ ‎ሰው ለራሱ መጥፊያ፥ ቃታውን ይስባል?! ‎ ‎አጃኢብ'ኮ ነው። ‎ ‎በምድራዊ ጉልበት ‎ሙእሚን
አለማወቅ... 3! ‎ ‎ዱላ አስከተለ አሉ ‎አልቻልህ ቢለው፥ በአፉ ዝም ማስባል፣ ‎እንዴት በገዛ እጁ ‎ሰው ለራሱ መጥፊያ፥ ቃታውን ይስባል?! ‎ ‎አጃኢብ'ኮ ነው። ‎ ‎በምድራዊ ጉልበት ‎ሙእሚንን ሊረታ፥ ህልም የወጠነ 'ለት፣ ‎ሽንፈቱን ጀምሯል ‎ያኔ ነው ውድቀቱ፥ ያን ጊዜ አበቃለት። ‎ ‎ትላንትን አያይም?! ‎ ‎የብርሃኑን ችቦ ‎ለማጥፋት አስቦ፥ እጁን የሰደደ፣ ‎አቀጣጠለ እንጂ ‎መች እንደተመኘው፥ እሳት አበረደ?! ‎ ‎እሳቱ ተፈጥሮው ‎የመጥፋት ዘመኑ፥ ድሮ ስላለፈ፣ የነካካው ጊዜ ‎ከፊቱ የባሰ፥ አንድዶት አረፈ። ‎ ‎አጠፋለሁ ብሎ ‎የቆሰቆሰበት፥ ጸጸቱ ቢያውከው፣ ‎ወላፈኑ ከብዷል ‎የሰደደውን እጅ፥ ዳግመኛ እንዳይልከው። ‎ ‎አርፈው ቢቀመጡ ‎ተቃጥሎ ከመውደም፥ በገዛ ሥራቸው፣ ‎አላህን የያዘ ‎መጥፋት እንደማይችል፥ ማን በነገራቸው?! ‎ ‎አለማወቅ!!! ‎ይህን እሳት፥ አለማወቅ!!! #ዘመቻ_ዙልሒጃ! #በሂደት_ላይ... #አሁንም_ዝግጁ?! @aaumsu

አለማወቅ 2! ‎ ‎ተረት ተረት ... ‎ ‎አንዲት ጦጣ ሙዙን ሰርቃ ‎በጫካው ውስጥ ብትደበቅ፣ ‎ሰው «ተይ» አለ በመልካም ቃል ‎የሀገር ሰላም ለመጠበቅ። ‎ ‎ጦጣ ሆዬ መቼ ሰምታ ‎ቢለሳለስ ሞኝ አለችው፣ ‎ከዛፉ ላይ ተደብቃ ‎በማጮለቅ ታዘበችው። ‎ ‎አልታየችም በሷ ሃሳብ ‎ከፍ ማለት ከልሏታል፣ ‎ፍትሕ ምሳር ሆኖ ሲገኝ ‎የሚምራት ይመስላታል?! ‎ ‎ከዛፉ ጋር አብሮ ጣላት ‎ተበዳዩ ጊዜው ደርሶ፣ ‎ለጭቆናም መቋጫ አለው ‎የነቁ ቀን ጥርስን ነክሶ። ‎ ‎በሰው ክብር ተረማምዶ ‎መንጠላጠል የናፈቀው፣ ‎ከዛፉ ጋር አንድ ላይ ነው ‎ተገንድሶ የሚወድቀው። ‎ ‎ገና መቼ?! ‎ ‎ገና መቼ ተቀጣጥሎ ‎ሊያስፈራራ ከምን በቃ፣ ‎ልንለኩሰው ስንዘጋጅ ‎የሚሸሹን በደቂቃ?! ‎ ‎ገና'ኮ ነው። ‎ ‎እሳት ንቆ የከረመው ‎ፍንጣሪ ሸሸ ቢባል፥ ‎ያየው እንጂ የማያውቀው ‎አሁን ይሄን እንዴት ያምናል?! ‎ ‎ገና መቼ?! ‎ ‎ከነግርማው ተሰይሞ ‎ከፊታችን ሰደድ እሳት፣ ‎ምን ይባላል ለጨረፍታው ‎መንጠላጠል በር መዝጋት?! ‎ ‎ገና'ኮ ... መለኮሱ ነው ... ‎የነደደ መስሏቸው ነው?! ‎ወይ እሳቱን አለማወቅ!!! #ዘመቻ_ዙልሒጃ! #በሂደት_ላይ... #አሁንም_ዝግጁ?! ቪድዮ፦ ከተማሪ ፊት ለፊት መጥተው ምላሽ መስጠት የነበረባቸው የፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ሰዎች በመስኮት አጮልቀው ተማሪዎችን ሲመለከቱ። @aaumsu

አለማወቅ... 1! ‎ ‎በርሱ'ማ ቤት ‎ዝም ሊያስብል ‎ ‎በርሱ'ማ ቤት ‎ሊያስፈራራ... ‎ ‎አልነገሩት ‎ቃል እንዳለን ‎ ‎ከአላህ በቀር ‎እንዳንፈራ! ‎ ‎ትላንትን አያይም?! ‎እፍፍፍ... አለ
አለማወቅ... 1! ‎ ‎በርሱ'ማ ቤት ‎ዝም ሊያስብል ‎ ‎በርሱ'ማ ቤት ‎ሊያስፈራራ... ‎ ‎አልነገሩት ‎ቃል እንዳለን ‎ ‎ከአላህ በቀር ‎እንዳንፈራ! ‎ ‎ትላንትን አያይም?! ‎እፍፍፍ... አለ አሉ ‎ስንጠፋ ሊያይ ‎ ‎ሻማ መስለን ‎ብንታየው፣ ‎ ‎እፍታውን ‎ረገማት ‎ ‎አሳት ደርሶ ‎ቢያደባየው። ‎ ‎አለማወቅ!!! ‎ይህን እሳት፥ አለማወቅ!!! #ዘመቻ_ዙልሒጃ! #በሂደት_ላይ... #አሁንም_ዝግጁ?! @aaumsu

🗣🗣🗣🗣🗣🗣🗣🗣🗣🗣 بِسۡمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحۡمٰنِ ٱلرَّحِيۡم           اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ‎👋👋        🗣🗣 የማይቀርበት ሳምንታዊ የዳዕዋ ፕሮግራም !!!!! ✴️ዳዕዋው : በወንድም ሙስዐብ አህመድ 🔥" القرأن منهاج الحياة " "ቁርአን የህይወት መመሪያ!" በሚል ርዕስ ይቀርባል። 🍀 ለቀልባችን ስንቅ ለሳምንታችን ማነቃቂያ የሆነው ተናፋቂው እና ተወዳጁ ሳምንታዊ የዳዕዋ ፕሮግራማችን እነሆ ዛሬም የሚቀጥል ይሆናል። 👌 ሁላችንም ከጓደኞቻችን ጋር ከመሆን በቦታው ላይ በመገኘት ተጠቃሚ እንሁን። 👉 መልዕክቱን ላልሰሙት እናሰማ!!!!!! 🕰 ሰዓት: መግሪብ-ኢሻ 🗓 ቀን: ሰኞ ግንቦት 10 /2018 🕌 ቦታ: 4ኪሎ ተማሪዎች መስጂድ ©aau4kilomsj

🗣🗣اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ‎👋👋 ✅ኢንሻአላህ ዛሬ (ሰኞ ) የሰሂህ አል-ቡኻሪ ሙኽተሰር የሆነውን التجريد الصريح لأحاديث الجامع الصحيح ደርስ ይኖረናል ።  6ኪሎ እና 5ኪሎ የምንገኝ ሙስሊም ተማሪዎች በጊዜ እንገኝ ሌሎችንም በማስከተል  ቡዙ እናተርፍለን። ⏰ሰዓት: ከመግሪብ - ኢሻ 🕌ቦታ፡ 6ኪሎ አቅሳ መስጅድ 📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ። https://t.me/durus_at_aqsa ⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻 https://t.me/durus_at_aqsa/4306/4934 @fivekjemaa

#ዘመቻ_ዙልሒጃ! ‎ ‎ትግላችን ወደቀጣይ እርምጃ የሚሸጋገርበት አዲስ ነገር ••• !!! ‎ ‎አላህ (ሱ.ወ) ከዱንያ ቀናት ሁሉ ያከበራቸው እነዚህ ቀናት፥ የተከበረ የሆነውን የርሱን ሃይማኖት ለመጠበቅ አመቺ ዕድሎች ናቸው።... መንገዱ በነዚህ የዙልሒጃ ቀናት ይበልጥ ትርጉሙን ያገኛል።... አጅሩም በዚያው ልክ እጥፍ ድርብ ይሆናል!!! - እኛን ሊያከብር ኃላፊነት ያሸከመንና በተለያዩ አጋጣሚዎች ምንዳችንን የሚያበዛው እንዲሁም ድልን ሊያቀዳጀን ቃልኪዳኑ የሆነው ጌታችን ምስጋና ይገባው። አልሐምዱሊላህ። ‎ ‎ከምንም በላይ ለድላችን መፋጠን ሰበብ በሚሆኑ መልካም ስራዎች፥ በተለይ በዱዓ በመበርታት ላይ ሁላችሁንም አደራ እንላለን። ‎ ‎የጭቆና ውድቀት የሚጀምረው፥ ሰዎች ሁኔታውን በግልጽ የተረዱበት ጊዜ ላይ ነው።... እኛም አሁን ላይ ገብቶናል። በሕገ-ወጥ መመሪያ ሽፋን የሚፈጸምን በደል እንረዳለን። የእስልምናና የሙስሊሞች ጥላቻ ያለባቸው አካላት የሚመርጡትን ሂደት እናውቀዋለን።... እኛ ወደ ድል እንደምንጓዝም ጭምር። ‎ ‎የተነካው የአላህ (ሱ.ወ) ዲን፣ የረሱሉ (ሰ.ዐ.ወ) መንገድ፣ የምዕመናን ባጠቃላይ ክብር ነውና፥ ወደኋላ ለመመለስ የሚያስችለን ሁኔታ የለም። ከጅምሩ ወደኋላ ለመመለስ የሚያስበው ለቀለለ ነገር የሚታገል እንጂ ሌላ ማን ነው?!... ይህንን ዓለም የሚሻገር የገዘፈ ዓላማ ባለቤት የሆነ፣ ወደ ድል እንጂ ወዴትም እንደማይሄድ ያረጋገጠ ሰው እንዴት ብሎ ወደኋላ ስለመሄድ ያስባል?! - መንገዳችንማ ወደፊት ብቻ ነው!!! ‎ ‎የርሱ ባሪያዎች አድርጎ፥ ፍርሃትን በኛ ላይ ጉልበት ያሳጣው ጌታችን ምስጋና የተገባው ይሁን። ‎ ‎እናንተ የአላህ ባሮች ሆይ፦ ‎ ‎በነዚህ የመስዋዕትነት አየር ከሌላው ጊዜ በተለየ መልኩ በሙእሚኖች ልብ ላይ በሚነፍስበት ወቅት፥ የኢስማዒልን (ዐ.ሰ) አላህን የመታዘዝና፥ በመንገዱ ላይም ራስን ለመስዋዕትነት የማዘጋጀት ጉዞ በጋራ እንጓዝ ዘንድ ምን ያህል ዝግጁ ናችሁ?! ‎ ‎እናንተ የአላህ ባሮች ሆይ፦ ‎ ‎ጌታችን በነጻነት የማይመለክበት ቦታ ላይ እንደመቀመጥ የሚቆረቁር ነገር አለን?! - ታዲያ ነገ በአላህ ፊት የምትጠየቅ ነፍሳችን፥ ትመልሰው ቃል እንዳታጣ የሚያደርጋትን ተግባር ለማከናወን ምን ያህል ዝግጁ ናችሁ?! ‎ ‎እናንተ የአላህ ባሮች ሆይ፦ ‎ ‎ወደኋላ መመለሳችን፥ ከፊት ከሚጠብቁን ፈተናዎች በላይ አስፈሪ በሆነበትና መመለስ በማይታሰብበት በዚህ ጊዜ... ከባዱን ግን አስተማማኙን የድል መንገድ ለመምረጥ ምን ያህል ዝግጁ ናችሁ?! ‎ ‎••• ይኼኛውን ዒድ ከብዙ ትርጉሞች ጋር የምናከብረው ስንሆን (በአላህ ፈቃድ) ••• @aaumsu

በስልጤ ዞን የዳሎቻ ወረዳ ማህበረሰብ ስለ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ድምፃቸውን አሰምተዋል። ጥያቄው የሕዝበ ሙስሊሙ ነው። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! @aaumsu

ሸይኽ ሙሐመድዘይን ዘህረዲን የኒቃብ ክልከላን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል። "አሚና ኒቃብ ለብሼ ልግባ ስትል በቀለች በአንቺ ትቀናና ሌላ ነገር ታመጣለች አይባልም። ካመጣች ሐይማኖቶ ከሆነ ለምንድን ነው የማይፈቀድላት? ይህ ሀገር እኮ የሐይማኖተኞች ሐገር ነው። ሐይማኖተኞች መከበር አለባቸው። ጥቁር ለበሰች ነጭ ለበሰች ለትምህርት ጎድቶት አይደለም። እኔ አስተማሪ ነበርኩ። አዕምሮን አይደል የምትለውጡት? እንደ ምሁራን ተሰባስባችሁ መልበስ ይጠቅማል አይጠቅምም ተብሎ ሊወራ አይገባም።" @aaumsu

🌟የዙልሒጃ አስርቱ ቀናት ታላቅነትና ልቅና ​✨✨ መለኮታዊ ክብር፦ እነዚህ አላህ (ሱ.ወ) ደረጃቸውን ከፍ ያደረጋቸው ታላላቅ ቀናት ናቸው። አላህን ማክበራችን የሚገለጸው ደግሞ እርሱ ያላቃቸውን ምልክቶችና ቀናት ስናከብር ነው፤ አላህ እንዲህ ይላል፦ ​
(ይህ የተባለው ነገር ነው) የአላህንም ምልክቶች የሚያከብር ሰው እርሷ (ማክበሯ) ከልቦች አላህን መፍራት ናት። (ሐጅ: 32)
የአላህ መሃላ፦ የልዑልነት ባለቤት የሆነው ጌታችን በእነዚህ ቀናት ምሏል፦ ​
በጎህ እምላለሁ፤ በአስሩም ሌሊቶች እምላለሁ። (ፈጅር: 1-2)
። እነዚህም የዙልሒጃ የመጀመሪያዎቹ አስር ሌሊቶች ናቸው። ስለዚህ እነዚህን ቀናት ልክ እንደማንኛውም ተራ ቀን እንዲሁ እንዲያልፉ ፈጽሞ መፍቀድ የለብንም። ወትሮ ከምንሰራቸው ኢባዳዎች በመጨመር ከምን ጊዜውም በላይ ልንጠናከርና ወደ አላህ ልንቃረብ ይገባናል። ወንጀላችን በዝቷል፤ ልባችን ደርቋል ፤ ኢባዳችን ጥፍጥናውን/ለዛ አጥቷል??...ወደ ኃያሉ ጌታችን አላህ ለመመለስ ጊዜው አሁን ነው በነዚህ ቀናት ለአሂራ ሸመታችን የበዛ እናድርገው ። የነቃ ነጋዴ በማትረፊያ ሰዓቱ (የገበያው ንግድ በተጧጧፈበት ጊዜ) አይተኛምና!!

የዙልሒጃ ጨረቃ ዛሬ ታይታለች። ዱንያ ላይ ካሉ ቀናቶች መካከል አስሩ አንድ ብለው ጀመሩ ማለት ነው። በዚህም ዒደል- አድሃ ግንቦት 19 ረቡዕ ቀን የሚውል ይሆናል። አላህ በእነዚህ በላጭ በሆኑ ቀናት
የዙልሒጃ ጨረቃ ዛሬ ታይታለች። ዱንያ ላይ ካሉ ቀናቶች መካከል አስሩ አንድ ብለው ጀመሩ ማለት ነው። በዚህም ዒደል- አድሃ ግንቦት 19 ረቡዕ ቀን የሚውል ይሆናል። አላህ በእነዚህ በላጭ በሆኑ ቀናት በላጭ የሆኑ ስራዎችን የምንሰራ ያድርገን። መብቶቻችን ተከብረው፤ የእህቶቻችን ስቃይ ቆሞ፤ በዳዮችም ተጠይቀው ፍትሕን የምናሰፍንበትን ብርታት ይስጠን። አሚን! ኢንሻ አላህ ይሳካል ! ! ! @aaumsu

ሐዲሰል ቁድሲ! ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ قالَ اللهُ تعالى:‐ ﴿يا ابنَ آدمَ إنّكَ ما دعَوتَني ورجَوتَني غفَرتُ لَكَ على ما كانَ فيكَ ولا أُبالي، يا ابنَ آدمَ لو بلغَت ذنوبُكَ عَنانَ السَّماءِ ثمَّ استغفرتَني غفرتُ لَكَ ولا أبالي، يا ابنَ آدمَ إنّكَ لو أتيتَني بقِرابِ الأرضِ خطايا ثمَّ لقيتَني لا تشرِكُ بي شيئًا لأتيتُكَ بقرابِها مغفرةً﴾ የላቀው አላህ እንዲህ ይላል፦ “አንተ የአደም ልጅ ሆይ! እስከጠራኸኝና ከእኔ ዘንድ እስከጠየቅክ ድረስ፤ ለሠራኸው ኃጢያት ይቅር እልሃለሁ ምንም ግድ አይሰጠኝም። አንተ የአደም ልጅ ሆይ! ኃጢአቶችህ ከሰማይ ቢደርሱ እንኳ እኔን ይቅር በለኝ ካልክ ይቅርታ አደርግልሃለሁ ምንም ግድ አይሰጠኝም። አንተ የአደም ልጅ ሆይ! ምድርን የሚሞላ ኃጢአቶች ይዘህ ወደኔ ብትመጣና ከዚያም ከእኔ ጋር አንድንም አካል ሳታጋራ ፊቴ ከቀረብክ ከወንጀልህ የሚልቅ ማህርታን ይዤ እመጣሃለው።” 📚ሲልሲለቱ አሶሂሃ: 127

Update! በትላንትናው ዕለት ቅዳሜ፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ተወካዮች ከመጅሊስ ተወካዮች ጋር ረጅም ሰዓታት የፈጀ፣ የችግሩን አሳሳቢነትና የእህቶቻችንን ስቃይ በዝርዝር
Update! በትላንትናው ዕለት ቅዳሜ፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ተወካዮች ከመጅሊስ ተወካዮች ጋር ረጅም ሰዓታት የፈጀ፣ የችግሩን አሳሳቢነትና የእህቶቻችንን ስቃይ በዝርዝር ያቀረብንበትን ውይይት አድርገናል። በዚሁ መሠረት፣ ይህንን ውይይት ይበልጥ በተጠናከረና ውጤት ተኮር በሆነ መልኩ ነገ ሰኞ ለመቀጠል ከስምምነት ላይ ተደርሷል። ነገር ግን ላለፉት 19 ወራት የተመገብናቸው የውሸት ተስፋዎችና የተሰበሩ ቃላቶች በልባችን ላይ የፈጠሩት ቁስልና ቁጣ አሁንም ትኩስ ነው! እነዚህ ውይይቶች የተማሪውን ቁጣ ለማብረድ፣ ጊዜ ለመግዛትና ድምፃችንን ለማጥፋት የሚደረግ ሌላው የተለመደ "የማደንዘዣ" እና የማስታገሻ ሙከራ እንዳልሆነ የምናምንበት ምንም ምክንያት የለንም። እኛ በውይይት ሰበብ የምንታለል ትውልድ አይደለንም፤ እኛ በወረቀት ላይ የሰፈረና የታተመ ውጤት የምንፈልግ ትውልድ ነን! በዚህ ጉዳይ ላይ እጃችሁን ላስገባችሁ አካላት ሁሉ፡ ለዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ ለመንግስት ተቋማትም ሆነ ለመጅሊስ የምናስተላልፈው መልዕክት አጭርና ግልጽ ነው፦
“ህጉን አስተካክሉ (መመሪያውን ቀይሩ) እንጂ ሰላማዊ ተማሪዎችን ለማታለልና ጊዜ ለመግዛት አትሞክሩ!” መብቱን የጠየቀን፣ ንፁህ እና ሰላማዊ ተማሪ በቢሮክራሲ ማድረቅና ማሸማቀቅ አይቻልም። ፍትህ በውይይት ቀጠሮዎች አይተካም!
ለተማሪዎቻችን፦ ንቃታችሁ ይባስ እንጂ ፈፅሞ አይቀንስ። በዱዓ እና በንቃት ቁሙ። ነገ ሰኞ የሚመጣውን ውጤት በንቃት እንጠብቃለን፤ ያ ውጤት ግን የታተመና የተፈረመ የፖሊሲ ለውጥ የሚያመጣ አቅጣጫ ካልሆነ፣ ትላንት በፕሬዝዳንቱ ጽ/ቤት ፊት ለፊት የነበረው ማዕበል በበለጠ ጉልበትና ስፋት የማይመለስበት ምንም ምክንያት የለም! አሁንም ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን! @aaumsu