ar
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

الذهاب إلى القناة على Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

إظهار المزيد
1 160
المشتركون
-124 ساعات
+17 أيام
+530 أيام
أرشيف المشاركات
እስክርቢቶ የጣለ? ሊያስጥሉኝ ያስባሉ። ሊያስጥሉኝም እየሞከሩ ነው። ግን አልጣልኩም፤ አልጥልምም። ፌደራሎች እያስፈራሩ፤ ተማሪውን እየገፈታተሩ፤ ተማሪው የፈራ የተጨነቀ በመሰላቸው ሰዓት ከአንድ ወንድ
እስክርቢቶ የጣለ? ሊያስጥሉኝ ያስባሉ። ሊያስጥሉኝም እየሞከሩ ነው። ግን አልጣልኩም፤ አልጥልምም። ፌደራሎች እያስፈራሩ፤ ተማሪውን እየገፈታተሩ፤ ተማሪው የፈራ የተጨነቀ በመሰላቸው ሰዓት ከአንድ ወንድም ጮክ ብላ የተሰማች ንግግር ነበረች። መልዕክቱ ጥልቅ ነበር። የእኛ ትኩረት ሊነጥቁን፣ ሊወስዱብን፣ ሊያሳጡን እየሞከሩ ያሉትን ብዕር በፅናት መያዝ ላይ እንደሆነ ያመለክታል። ከፊት ለፊታችን የነበረው ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት የሴራው ጠንሳሽ ሲሆን፤ እኛ ደግሞ ብዕራችንን እንደያዝን ለሴራው ሳንበገር ከዚያው ቆመን ነበር። በአላህ ፈቃድ መብታችን በመመሪያ እስኪፀና፤ ብዕራችንን ለመንጠቅ የሚሞክሩ ሰዎች በሕግ ፊት ተጠያቂ እስኪሆኑ ድረስ እንደፀናን እንቆያለን። መብት በትግል እንጂ በልመና አይገኝምና! @aaumsu

እስኪርቢቶ የጣለ? ፍትህ እንደራበኝ እንደተጠማሁኝ ፣ ጁሙዐን ሰግጄ ቶሎ አሰላመትኩኝ ፣ ሀጃ አለብኝ እና... በፍጥነት ወጣሁኝ ፤ መንገዱን ተጉዤ ጫፍ እንደደረስኩኝ ፣ መብቴን ለመጠየቅ ከቢሯቸዉ ቆምኩኝ :: የእህቴን ስቃይ እንግልት አይቼ፣ ህመሟ ተሰምቶኝ ግፉን ተመልክቼ :: ነፃነትን ሽቼ... ከስኬት ለመድረስ ፣ ስለ ፍትህ ቆምኩኝ መብቷን ለማስመለስ:: ታዲያ በቆምኩበት እዛው ስብሰለሰል ፣ ላቤ ግጥም አለ ጭንቀቱ ነው መሰል ? ግራ ተጋባሁኝ 'ምን ሆኘ ነው ዛሬ?' የውሸት ነው እንዴ ቢላህ መመስከሬ ? ነብዩን መውደዴ ኢስላምን ማፍቀሬ ? በጭራሽ አይሆንም! የምን ጥርጣሬ ፣ በላብ ያጠመቀኝ... ያውና ሚስጥሬ ... ለካስ ፀሀዩ ነው መጨነቄ አይደለም፣ ትንሽ ሞቆኝ እንጂ ያሳሰበኝ የለም :: ጠራራው በረደ ፀሀይም ጠለቀች ፣ መግሪብ ተሰገደ ልቤም ተፈተነች:: ፊትለፊቴ ቁሞ ግብዳው ፌደራል ፣ ጥቁር ጎማ ይዞ ሲዝት ይሰማኛል ፤ ታዲያ ሰውነቴ መንቀጥቀጡን ያዘው ፣ እኔም ግራ ገባኝ 'እንዴ! ምን ሆኜ ነው?':: እውነት አልነበረም ለአሏህ መስገዴ ? መቆም መቀመጤ ማጎንበስ መውረዴ ? አካሌ ሲከዳኝ እንዲሁ መፍቀዴ ... በፍፁም አይደለም! ላስረዳችሁ አንዴ :: ለካስ ነፋሱ ነው የአመሻሽ ብርዱ ፣ ፈርቸ አልነበረም የነቢ ልጅ ወንዱ ፤ "አንዴ ሁላችሁም ሶለዋት አውርዱ" በዱዐ ወጥሬ በዚክር ባውራዱ፣ ንቅንቅ አላልኳትም አገዘኝ ሶመዱ :: በዚህ ሁኔታ ላይ እዛው ተቀምጬ፣ ሳወርድ ሳወጣ በሀሳብ ተውጬ:: መጋፋት ጀመሩ... ፌደራል ፖሊሱ ፣ ከበው አስፈራሩ "ተበተን" "ተነሱ" ጭንቀቴ አገረሸ ጀግንነት ተረሳ ፣ ያኛው "ግደሉን" ሲል ለነብሱ ሳይሳሳ ፤ ያንኛው ሲቀመጥ... ያንኛው ሲነሳ ፣ ግራ ተጋባሁኝ 'አወይ የኔ አበሳ!':: በዛ መሀል ነበር ይች ቃል ተሰማች ፣ "እስኪርቢቶ የጣለ...?" ሰኪናን አመጣች ፤ አንዱ ወንድማችን ይህን ከማለቱ ፣ ብዙ መልክት አለው ሁሉም በመስማቱ ፤ የጣለውን እቃ ይውሰድ ባለ ሀቁ ፣ ምንም አያመጡ በፅናት ጠይቁ  ፣ አብሽሩ ማለት ነው አትጨናነቁ ፣ ወዳው ሲገባቸው ወንድሞችም ሳቁ ፤ እንደማንመለስ እነሱም አወቁ :: እኔ ግን የቆጨኝ... በራሴ መፍረዴ ፣ ያችን ጥቁር ዱላ ሳልቀምሳት መሄዴ፣ ኡስታዝን አምኜ... ለጊዜው መውደዴ ፣ መፍትሄው ሊርቀኝ ጥያቄ መስደዴ፣ ዘላቂ እንደማይሆነ እያወቀው ሆዴ :: "ሽርጡን የጣለ"... ይህ ነው ጨርቄ ማቄ፣ ለምን ነበር ታዲያ ምሽጌን መልቀቄ ፣ "መስገጃ የጣለ"... በቂ ነበር ስንቄ ፤ ቅር አለኝ በእውነት... ውይ አለማወቄ :: ©Sefere Selam Muslum Students Jeme'a ©aaumsu

© ለፈገግታ 😁 ትዝ የሚለው ካለ ፅናትን፣ ጥንካሬንና ከአቋም አለማፈግፈግን ያየንበት አጋጣሚ!! @aaumsu
© ለፈገግታ 😁 ትዝ የሚለው ካለ ፅናትን፣ ጥንካሬንና ከአቋም አለማፈግፈግን ያየንበት አጋጣሚ!! @aaumsu

በትላንትናው እለት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቅጥር ግቢ ውስጥ የተከሰተውን ክስተት አስመልክቶ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የወጣ መግለጫ “መብት በልመና አይገኝም!” ይህ በታላቅ
+3
በትላንትናው እለት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቅጥር ግቢ ውስጥ የተከሰተውን ክስተት አስመልክቶ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የወጣ መግለጫ “መብት በልመና አይገኝም!” ይህ በታላቅ ትዕግስትና ፅናት ያለፉትን 19 ወራት (ከ620 ቀናት በላይ) መዋቅራዊ በደልና ማግለል የተጋፈጠው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ድምፅ ነው ። ህገ-መንግስታዊ መብትን በሚጥስና በተለይም የሙስሊም ሴት ተማሪዎችን ሂጃብና ኒቃብ በግቢው ውስጥ ሙሉ በሙሉ በሚከለክል አድሏዊ መመሪያ ምክንያት እህቶቻችንና ወንድሞቻችን በየቀኑ ሲንገላቱ፣ አካዳሚያዊና ስነ-ልቦናዊ ጥቃት ሲፈጸምባቸው ኑረዋል ። ትናንት ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ል. በዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ፊት ለፊት በሰላማዊ መንገድ በመሰባሰብ፣ በብርድ፣ በጨለማና በረሃብ ውስጥ ሆነው የታየው የመቶዎች ፅናት ይህ ትውልድ ማንነቱን፣ እምነቱንና ክብሩን ለምንም አሳልፎ የማይሰጥ መሆኑን በተግባር ያረጋገጠበት ታሪካዊ ክስተት ነው ። ከሃይማኖት መሪዎቻችን (መጅሊስ) ጋር በተደረገው ስምምነትና በተሰጠው ቃል መሠረት ጉዳዩን በኃላፊነት እንዲይዙት ሌሊት ላይ ተማሪው ወደ ማደሪያው ቢበተንም ፣ ይህ ትግሉ ተጠናቀቀ ማለት ሳይሆን መመሪያው በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲሻሻል የተሰጠ የጊዜ ገደብ ነው ። መብታችን በግልፅ ተረጋግጦ፣ የታተመ የመመሪያ ለውጥ በይፋ እስካልመጣ ድረስ ሰላማዊ ትግላችን በበለጠ ስፋትና ጉልበት ይቀጥላል! መላው ፍትህ ፈላጊ ማህበረሰብም ከተበደሉ ተማሪዎች ጎን እንዲቆም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ። በዱዓ፣ በንቃትና በአንድነት ቆመን የመጨረሻውን ፍሬ እናያለን! “ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን!” @aaumsu

አሥሩ የዚል-ሒጃ ቀናት! | ~አላህ ሲያስብልን፣ ሲወደን እና ሊጠቅመን ሲፈልግ ምንዳዉና ችሮታው የሚነባበርባቸዉን ቀናትና ጊዜያት ጠቆመን፡፡ አስተዋይ ልቦና የሠጠው ሰው በትኩረት ይጠቀምባቸዋል፡፡ እንደዋዛ አያሳልፋቸዉም፡፡ ~አሥሩ ምርጥ ቀናት ነገ ወይም ከነገ ወዲያ  ይገባሉ፡፡ ስለ ምርጥነታቸው በቁርኣን ተመስክሮላቸዋል፣አላህ ምሎባቸዋል፣ የአላህን ቤት ጎብኝዎች ወደተከበረዉና የተቀደስው ሥፍራ መካ እና ዙርያው በመጉረፍ የሐጅን ሥርዓት ያከናዉኑባቸዋል፡፡ ታድያ እኛ በቀናቱ ዉስጥ ምን መሥራት እንችላለን? 1- ከልብ ተፀፅቶ ወደ አላህ መመለስ፤ 2- አላህን ማውሳት ማብዛት፣ 3- መፆም፣ 4- ኢስቲግፋር ማብዛት፣ 5- ሰደቃ መስጠት 6- ዱዓእ ማድረግ፣ 7- ሶላትን በወቅቱ መስገድ፣ 8- ከ ወንጀል መራቅ፣ 9- ስለ ቀናቱ ምርጥነትና እንዲጠቀሙባቸው ሌሎችን ማስታወስ፣ 10- በነቢዩ ላይ ሶላዋት ማውረድ… ➜ እንዳጠቃላይ መልካም ሥራዎችና ንግግሮች ላይ መትጋት ያስፈልጋል። 👉አሁን ላይ የተጋረጠብንን ችግር አላህ ዘላቂውን መፍትሄ ያመጣልን ዘንድ ካሉብንም ውጥረቶች ይፈርጀን ዘንድ አጥብቀን በዱዓ እንበርታ፣ ኒቃብ መልበስ መብት ነው ፣ እህታችንም ለብሳ ትማራለች ኢንሻአላህ ለዚህም ዘላቂ መፍትሄ እንዲመጣ ወደ አላህ ጥሪያችን የበዛ ይሁን!!

አልሐምዱሊላህ __ ታድለናል ! ‎ገና ባልጠና ጉልበታችን፥ የብዙዎች ያልተሰራ የቤት ሥራ በጫንቃችን ላይ ተጣለብን። ‎ ‎ታድለን ... ‎የትውልድን ክብር በመጠበቅ ላይ ኃላፊነት ወሰድን። ‎ ‎ታድለን... ‎የእህታቸው ክብር እየተነካ፥ በሰላም ተኝተው የማያድሩ ዓይኖች ተሰጡን። ‎ ‎ታድለን... ‎ፍትሕ ስትቀበር «በእኔን ከተመቸኝ ይሁንታ» የማይቀበል አዕምሮ ተሰጠን። ‎ ‎ታድለን... ‎ቀን እስኪያልፍ የሚጎድልን ክብር የማይታገስ ልብ ተቸርን። ‎ ‎ታድለን... ‎ሌሎች የፈሩበትን ነገር በድፍረት የመጋፈጥ ወኔ ተሰጠን። ‎ ‎ታድለን... ‎«አዳኝ» እስኪመጣ ሳንጠብቅ፥ ኃላፊነታችንን የምንወጣበት ተቆርቋሪነት ተሰጠን። ‎ እንደኛ የታደለ አለ እንዴ?! ‎ ‎ታድለን... ‎ፍትሕ መጓደል አመመን። ‎የመብታችን መጣስ ቆረቆረን። ‎ጭቆና አንገሸገሸን። ‎ ‎ደግሞ እንደኛ የታደለ አለ እንዴ?! ‎ ‎ታድለንማ'ኮ... ‎ታሪክ "ካላጎነበሱት" መካከል መዘገበን። ‎መስዋዕትነት ከገባቸው፤ ‎ትውልዳቸውን ለመታደግ ቁርጠኛ ከሆኑት መሃል መዘገበን። ‎ ‎ደግሞ እንደኛ የታደለ አለ እንዴ?! ‎ ‎ታድለንማ'ኮ... ‎በአላህ ላይ ከሚመኩት፣ ‎ለመንገዱ ከሚታመኑት፤ ‎ድልንም ከርሱ ብቻ ከሚጠብቁት ሰራዊቶቹ መሃል አደረገን። ‎ ‎ደግሞ እንደኛ የታደለ አለ እንዴ?! ‎ለኛ የተሰጠው ለማን ተሰጥቷል?! - ዙሪያችሁን አትመለከቱምን?! ‎ ‎በህይወታችን ካየናቸው ብዙ ብዙ ብቸኝነቶች ውስጥ፥ በዚህ የትግል መንገድ ላይ ያለ ብቸኝነትን ያህል ዋጋ ያለው ብቸኝነት የት እናገኛለን?! ‎አላህ የሚያየው፣ የሚመሰክርለት ብቸኝነት! ‎ወደ ድል እንጂ የማይደርስ፣ ውድቀት የሌለበት ብቸኝነት!! ‎ትርጉሙ ጥልቅ፣ ክፍያው ብዙ ብቸኝነት!!! ‎ ‎ይህ እንደዋዛ 'ሚገኝ ነው እንዴ 'ሚመስለን?! ‎በፍጹም። ‎ለዚህ ብቸኝነት መመረጥ ያሻዋል። ‎ ‎ይህ'ኮ ታላቅ ጸጋ እንጂ ሌላ አይደለም። ‎አልሐምዱሊላህ!!! ‎ ‎ሐስቡነላህ ወኒዕመል ወኪል!!! @aaumsu

በዚህ ምሽት የተማሪውን ቁርጠኝነት ያስተዋለ ማንም ሰው ተማሪው ስለመብቱ ያለውን ግንዛቤ፤ ለመብቱ ሊከፍለው የሚችለውን መስዋዕትነት፤ እስኪያስከብር ድረስ ሊሄድ የሚችልበትን ርቀት ይረዳል። ተማሪው እ
በዚህ ምሽት የተማሪውን ቁርጠኝነት ያስተዋለ ማንም ሰው ተማሪው ስለመብቱ ያለውን ግንዛቤ፤ ለመብቱ ሊከፍለው የሚችለውን መስዋዕትነት፤ እስኪያስከብር ድረስ ሊሄድ የሚችልበትን ርቀት ይረዳል። ተማሪው እየተራበ፣ ብርድ እየመታው፣ እንደበድብሃለን እየተባለ ነበር የቆየው። ሆኖም ሁሉም ማስፈራሪያ ምንም ነበር። ይባስ ብሎም ከውጪ የነበረው ተማሪ ካልተቀላቀልን፣ አብረን ካልሆን ብሎ እየታገለ ነበር። ነገሩ ኻሊድ ኢብኑ ወሊድ (ረድየላሁ ዐንህ) "እናንተን ሞትን የምትሸሹትን ያክል የእኔ ወታደሮች ይፈልጉታል።" - እንዳለው ነው። እንደ ድንገት ሳይደርሱ የቀሩት ተማሪዎች ቁጭት እና መልዕክት ደግሞ "ምነው ከእናንተ ጋር በሆንን!" - የሚል ቁጭት ነበር። ጥንካሬያችንም ይኼው ነው። ብርታታችንም ይኼው ነው። የተማሪው ቁጭት፣ ግንዛቤ፣ ቆራጥነት እና መስዋዕትነት ማለት ነው። ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! @aaumsu

በሏቸው፦ መጀመሪያ እናንተ ጋር ያለውን የተሸፈነ ማንነት ግለጡ _ የዚያኔ የእኛ መሸፈን ክብር እንደሆነ ይገባችሗል። @aaumsu

እኛን ሊያስሩን ይችላሉ ... ጥያቄዎቻችንን ግን ሊያስሩ አይችሉም ... ወንድሞቻችንን ሊያስሩ ይችላሉ ... ወደሗላ እንድንተዋቸው ግን ሊያደርጉን አይችሉም ... በአንድነት በአንድ ድምፅ ወንድማችንን እንዳስፈታነው በጋራ በሕብረት በአንድነት ጥያቄያችንም ይፈታል። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! @aaumsu

ወንድማችን ተፈቷል! ©aaumsu @fivekjemaa

ተማሪ ኡስማን ዓሊ በሕግ ትምህርት ቤት የአራተኛ አመት ተማሪ ሲሆን ትላንት ተማሪዎች በሰላማዊ መንገድ እየጠየቁ ባለበት ሰዓት እንዲታሰር ሆኗል። የጀመዓ አሚሮች ለመጠየቅ የሄዱ ቢሆንም አሁን ሊለቁት
ተማሪ ኡስማን ዓሊ በሕግ ትምህርት ቤት የአራተኛ አመት ተማሪ ሲሆን ትላንት ተማሪዎች በሰላማዊ መንገድ እየጠየቁ ባለበት ሰዓት እንዲታሰር ሆኗል። የጀመዓ አሚሮች ለመጠየቅ የሄዱ ቢሆንም አሁን ሊለቁት እንደማይችሉ ገልፀው መልሰዋቸዋል። ወንድማችንን ፍቱት። ጥያቄያችን ሰላማዊ ነው _ በሰላማዊ መንገድ እየጠየቁ ያሉ ተማሪዎችን በእስር ማስፈራራት ትክክል አይደለም። @aaumsu

ወንድማችንን ፍቱት ! ተማሪው በሰላማዊ መንገድ ጥያቄውን እየጠየቀ ባለበት ሰዓት ለተማሪዎች ምግብ ለመግዛት የወጣን ተማሪ ፖሊሶች ይዘው ከእስር ቤት አሳድረዋል። ይህ ትክክለኛ ያልሆነ እና ተማሪው ችግሮችን በውይይት ለመፍታት እየሄደ ያለበትን መንገድ የሚያደፈርስ፤ ዩኒቨርስቲውንም እንደከዚህ ቀደም እንዳናምነውና የተገቡት ቃሎችን ለመፈፀም ቁርጠኝነት እንደሌላቸው እንድናስብ የሚያደርግ ነው። ጥያቄያችን ሰላማዊ ነው _ የጠየቅነው መብታችን ይከበር ዘንድ ነው _ ሒጃብ ይለበስ ብሎ ለጠየቀ አካል እስር መልስ አይሆንም _ ወንድማችንን ፍቱት ! ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! @aaumsu

አልሃምዱሊላህ ! ዛሬ ሁሉም ተማሪ በሰላም ወደ ዶርሙ ተመልሷል። ከቀኑ 7 ሰዓት ጀምሮ በፅናት ለቆያችሁ እና በዱዓም ስታግዙን ለነበራችሁ ሁሉ አላህ ኸይር ጀዛችሁን ይክፈላችሁ። ኢንሻ አላህ በቀጣይ በሰፊ ፅሁፍ እንመለስበታለን!

Update! ከመጅሊስ በኩል ኡስታዝ አቡበከር አሕመድ፣ ኡስታዝ አዩብ ደርባቸው፣ ኡስታዝ ሸሃቡዲን ሸኑራን ጨምሮ 5 ልዑካን አባላት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተገኝተው ከጀማዓው ተወካዮች እንዲሁም ከአጠቃላይ ተማሪዎች ጋር ውይይት ካደረጉ በኃላ በነገው ዕለት ከዩኒቨርሲቲው ጋር ውይይት እንደሚደረግ፤ ይህንንም ጉዳይ በኃላፊነት እንደሚይዙት በመናገር ተማሪዎች እንዲበተኑ ሆኗል። አሁንም የመጅሊስ አመራሮች ለተማሪዎች የገባችሁትን ቃል አክብሩ! ተማሪው እናንተን አምኖ ጥያቄየን ታሳካላችሁ ብሎ አማና ሰጥቷችኃል። ይህን አማና መብላት አላህ ፊት፤ ተማሪው ፊት፤ ህዝብ ፊት እንዲሁም ታሪክ ፊት ተጠያቂ ያደርጋችኃልና አማናችሁ ተወጡ! ተጨማሪ በቅርቡ የምንመለስ ይሆናል። @aaumsu

ተማሪውን ለማረጋጋት እየተሞከረ ቢሆንም ግን ተማሪው አቋሙን አለቅም በሚል ቀጥሏል። ለጥያቄዬም መልስ ሳይሰጠኝ የትም አልሄድም በሚል አቋሙ ጸንቶ ነው ያለው። አሚሮች ከመጅሊስ አካላት ጋር ንግግር እያደረጉ ይገኛሉ! @aaumsu

አሁንም አቋማችን ግልጽ ነው! ለጥያቄያችን ተገቢ ምላሽ ሳይሰጥ ምንም አይነት ቀጠሮ፣ ምንም አይነት ሽንገላ አንቀበልም። ከማንም ቢመጣ! @aaumsu

በአሁን ሰዓት ኡስታዝ አቡበከር የደረሰ ሲሆን ከተማሪዎች ጋር እየተነጋገሩ ነው። @aaumsu

"አንድ ሰው እናግኝና ጭፍልቅ ነው የምናደርጋችሁ!" - ከተወሰኑ ደቂቃዎች በፊት ከነዚህ አካላት ጋር ንግግርም ቀጠሮም አንቀበልም! መብታችን ሳይከበር፤ ጥያቄያችን ሳይመለስ ወዴትም አንቀሳቀስም! @aaumsu

መፍትሄ እንጂ ቀጠሮ አንቀበልም! @aaumsu
+2
መፍትሄ እንጂ ቀጠሮ አንቀበልም! @aaumsu

በአሁን ሰዓት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ እና የአዲስ አበባ መጅሊስ ጸሐፊ ኡስታዝ ሺሃቡዲን ሸይኽ ኑራ ወደግቢው እየመጡ ይገኛሉ። የዩኒቨርሲቲውም ፕሬዝዳንት እዚያው ግቢ ውስጥ ይገኛል። አሁንም ቢሆን ለጥያቄያችን ፍትኃዊ ምላሽ እስኪሰጥ ድረስ የትም አንቀሳቀስም! @aaumsu