ar
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

الذهاب إلى القناة على Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

إظهار المزيد
1 160
المشتركون
+124 ساعات
+27 أيام
+130 أيام
أرشيف المشاركات
እህቶች ብቻ የተጋሩት ታሪክ! በ እህቶች ብቻ የታበሰ እምባ! 💭ዝምተኛው ትግል! 🔥ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከ ሙተነቂቦች መንደር 1 ልክ እንደ ትናንት ከ 3 ዓመት በፊት አንዷ እህቴ ላይ የደረሰውን ነገር ሳይ ነበር ውስጤ የ ትግል እሳት የተቀጣጠለው! ግቢ መግብያ 2 ሰዓት ነበር። በ ሰዓቱ በማላስታሰው ምክኒያት ሙስሊም ተማሪዎች የምንጠቀመው ከ መስጅዳችን(ሙሃጂሪን) ፊት ለፊት ያለውን የ መግብያ በር መጠቀም እንደማንችል እና በ ዋናው በር እንድንዞር ተደረገ፣ ሄድንም! ከዛ ጥበቆች ፊታችሁን እየከፈታችሁ ... አሉን። በጊዜው ብዙ በ ኒቃብ ኒያህ ማስክ ሚጠቀሙ፣ በ ግቢው ፍርሃት ኒቃብ ማይለብሱ እህቶች ነበሩ። ነገር ግን አንዲት ብቸኛና ጠንካራ ሙተነቂብ ጓደኛችን ነበረች፣ ቀላል ባይሆንም ከ ID ያችን ጋር እያስተያዩን እኛ እንደምንም ገባን፣ ቀድሚያት ስለነበር ኒቃቢስት ጓደኛችንን ወደ ሗላ ዞሬ ሳገኛት ከ ድንጋጤ የተነሳ ትንፋሿ ይቆራረጥ ነበር፣ ሁኔታዋ አሁንም ከ አዕምሮዬ አይጠፋም! በጋለ ስሜት ለምን ሚለውን 'መልስ የሌለውን ጥያቄ' ጠየኩ፣ ለምን ?! እንዴት ሂጃብ መልበስ ሀበሻ ውስጥ ይከለከላል!? አልኩ... ግን መልስ የለም!!! የዛች ቀን ለኔ ትልቅ ማንቂያ እና ለ ጽናትም ሰበቤ ነበረች! ዓመቱ ID ሲቀማ፣ ሲመለስ፣ ሲፈረም እንደምንም አለቀ። ጊዜ ጊዜን ተክቶ ወደ ግቢ መመለሻ ጊዜያችን ደርሶ እኛም ተመለስን፣ ግቢውም ያደርስ የነበረውን በደል አክርሮ እና አጠናክሮ ጠበቀን! መሳቀቅ ዚክርና ዱዓ እያረጉ ገብቶ መውጣት፣ መሰደብ፣ መደበቅ የዚህ ዓመት ዋና ስራችን ሆነ ሲመታ እንደሚጠነክር ሚስማር እንደሚባለ የ ኒቃቢስቶች ቁጥር ከ 1 ወደ 2, 3 እየጨመረ መጣ! ቢሆንም ከ ስድብና እንግልታቸው የተነሳ ማስክ ለብሰን እንኳ ብቻችንን መንቀሳቀስ ለኛ ሰቀቀን ነበረ፣ ክላስ ካፌ፣ የግቢ በር ብቻችንን መግባት ልክ እንደ ምድር ጀሀነም ነበር ለኛ። የተማሪዎች ካፌ ቲከሩ "ፊታችሁን ካልከፈታችሁ አትገቡም" ብሎ የምሩን ከመለሰን ቀን ቦሃላ ድርሽ ብለን አናቅም ..... ወሰንንንንንን! ምናልባት ካፌ በመቅረት ውስጥ ከ ጥበቆቹ ፊትም ዞር እንል ይሆናል፣ በዚህ ሚቀንስልን ጭቅጭቅ እና መጋተት ካለ ብለን ድጋሜ ካፌ ላንመጣ ወስንን! በ ታሪክ ከተነገረን ግቢያችን በ ቁጥር በዛ ያሉ ወደ 43 ሚጠጉ ኒቃብስቶችን ፊታችሁን ሸፈናችሁ ብሎ ጠቅልሎ ያባረረበት ጊዜ ነበር፣ የኛ ሁኔታም ኒቃብ ከሚለብሱት እኩል ወደዛ ሚያቀና ይመስል ነበር...በዚም መልኩ ጊዜያት ያልፉ ነበር•• እናም 1 ቀን ወደ መስጂድ እየሄድን ሳለን ወደ መውጫው በር እንደተቃረብን የየቀን ዱዓችን ውስጥ ሚኖረው የጥበቃው ኃላፊ አገኘን፣ ከብዙ ስድብ፣ አድካሚና አሰልቺ ንግግር ቦሃላ "ቆይ ግን አሁን አንቺ አዲስ እዚ ያመጣሽው ነገር ነው እንጂ ታች ሀገርሽ ስትማሪ እንዲ ትለብሺ ነበር?!" አለ ወደ ለበስኩት ማስክ እየጠቆመ .. ጓደኛዬ እጄን ጥብቅ እያረገች ዝም በይው ትለኛለች፣ "አዎ እኔ እንዲው ለብሼ ነው የተማርኩት አዲስ ነገር አደለም!" አልኩት የ ጥላቻ ንዝነዛውን እንደቀጠለ "እሺ አሁን አንቺ ጁንታ ሁኚ ሸኔ ሁኚ ፋኖ ሁኚ በምንድነው ማቀው?!" ሕያው ምስክር ~ 1 የ ፊታችን ጁምዐ ማታ ከ ምሽቱ 3 ሰዓት ይጠብቁን ! @aaumsu

ጥያቄዎቻችን የፍትሕ፤ የእኩልነት እና የዜግነት ጥያቄዎች ናቸው! በቲክቶክ https://vt.tiktok.com/ZSVrkmnYF/ በመግባት ለሁሉም ይደርስ ዘንድ ኮፒሊንክ ሪፖስት ያድርጉ። @aaumsu

እስቲ ራሳችንን እንጠይቅ፦ ሀገራችን ኢትዮጵያ ዜጎቿን ያለ ልዩነት በእኩልነት እያገለገለች ነው? ዜጎች ሀገራቸውን በእኩልነት ያገለገሉ ዘንድ እድሎች አሉን? የሀገር ተቋማት ላይ እኩል ውክልና አለን? የሀገር ሀብት በፍትሐዊነት ተከፋፍሏልን? የሀገር መገለጫዎች ሁሉንም ይገልፃሉን?! መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ በቲክቶክ https://vt.tiktok.com/ZSVMj5B8o/ በመግባት ሪፖስት ያድርጉ። @aaumsu

ሕያው ምስክር - 1 የ11 አመታት ችግሮች የተፈቱበት የ11 ሌሊቶች ትግል በዲላ ዩኒቨርስቲ ! ከጥንት እስከ አሁን፤ ከትላንት እስከ ዛሬ፤ ከድሮ እስከ ዘንድሮ ከደቡብ እስከ ሰሜን፤ በምስራቁም ሆነ
ሕያው ምስክር - 1 የ11 አመታት ችግሮች የተፈቱበት የ11 ሌሊቶች ትግል በዲላ ዩኒቨርስቲ ! ከጥንት እስከ አሁን፤ ከትላንት እስከ ዛሬ፤ ከድሮ እስከ ዘንድሮ ከደቡብ እስከ ሰሜን፤ በምስራቁም ሆነ በምዕራቡ የኢትዮጵያ ክፍል በዳዮች ሰበብ እየፈጠሩ ሙስሊም ተማሪዎችን ሲያንገላቱ፤ መብቶቻቸውን እየጣሱ፤ ከትምህርት እያፈናቀሉ ዘልቀዋል። በዚህም ሕዝበ ሙስሊሙ በማህበራዊ መስተጋብር፤ በኢኮኖሚ እንቅስቃሴ፤ በፖለቲካዊ ተሳትፎ መድረስ ካለበት ሳይደርስ አሁንም ድረስ ስለመብቱ እየጠየቀ፤ እየታገለ፤ ስለ ዘላቂ መፍትሔ እየተጓዘ አለ። ጨቋኝን ጨቋኝ የመውረሱን ያክል የነፃነት ታጋይንም ስለነፃነቱ የሚጠይቅ ትውልድ ወርሶ በደል ባለበት ቦታ ሁሉ ጥያቄ አለን እያልን፤ ስለመብታችን እየታገልን፤ መብታችንንም እያስከበርን አለን። የጥያቄ አለን ትውልድ የሚዘነጋው ትግል የለምና በእኛ ትውልድ በደቡቡ የሀገራችን ክፍል በዲላ ዩኒቨርስቲ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የደረሰን በደል፤ የተደረገን እልህ አስጨራሽ ትግል፤ ለአስራ አንድ ቀናት ከግቢ ውጪ ታድሮ የተፈፀመን ገድል በሕያው ምስክር - 1 የምንቃኝ ይሆናል። እንግዳችን፦ ኡስታዝ ኑረዲን አብደላህ (በሰዓቱ የዲላ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት አሚር) መድረክ መሪ፦ ዘይድ ሷዲቅ (የቀድሞ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ፀሐፊ) ቀን፦ ነሐሴ 15 / 2018 ዓ.ል ሰዓት፦ ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ መድረኩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል (@aaumsu) ላይ ነው። @aaumsu

#ሚሽካት የመጀመሪያ ታሪካችን ይሄን ይመስል ነበር። ቀጣይ በ አላህ ፍቃድ የተሻሉ እና የተለያዩ የታሪክ ገጾችን የሚዳስሱ ጠቃሚ እና አስተማሪ ታሪኮችን በማቅረብ የምንቀጥል ይሆናል። በመሃል ደግሞ ልዩ ልዩ ሰርፕራይዞችም ስለሚኖሩን በንቃት ተከታትላችሁ እንድትጠቀሙ እንጠይቃለን ✨ 🍂ከመጀመሪያው ታሪካችን የወሰዳችሁት ትምህርት፣ የተፈጠረባችሁ ጥያቄ እንዲሁም ተጨማሪ ያገኛችሁት ግንዛቤ ካለ ከታች ባለው  'comment section' ልታጋሩን ትችላላችሁ። @aaumsu

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ኅብረት ከሩፋይዳ የሴቶች ፋውንዴሽን ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ ! በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሙስሊም ሴት ተማሪዎችን መብት ለማስጠበቅ፣ ማህበራዊ ግንዛቤን ለማሳደግ እና አቅማቸውን ለመገንባት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ኅብረት ከሩፋይዳ የሴቶች ፋውንዴሽን ጋር ተፈራርሟል። ይህ አጋርነት ተማሪዎች በግቢው ውስጥ የሀይማኖት ማንነታቸውና መብታቸው እንዲከበር፣ የስነ-ልቦና እና የጤና ድጋፍ እንዲያገኙ፣ እንዲሁም ሌሎች ተመሳሳይ ዝግጅቶችን በአንድነት ለማመቻቸት ያለመ ነው። በፊርማው ስነ-ስርዓት የኅብረቱ ፕሬዚዳንት ሙሐመድ ኢድሪስ አሊ፤ የፋውንዴሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ሀንጋቱ አብዱልዋሀብ እንዲሁም ሌሎች የህብረቱና የፋውንዴሽኑ አመራሮች የተገኙ ሲሆን ወደፊት በሚሰሩ ዝርዝር ተግባራትም ውይይት ተደርጓል:: አላህ ለመልካም ለውጥ እና ለተሻለ ሁኔታ ሰበብ ያደርገው ዘንድ ዱዓችን ነው ! ! ! @aaumsu

ከታሪክ ገጾች📖…እስካለንበት ተጨባጭ ✍️ ✨በማይፈራው ፣ጽኑው ሰዒድ እና በግፈኛው ገዢ ሐጃጅ መካከል የተደረገ የታሪክ ምልልስ✨            የመጨረሻው ክፍል ሰኢድ ቢን ጁበይር (ረሕመቱላህ ዐለይህ) በርግጥም ከታላላቁ ኡለማዖች መሀከል አንዱ ነበር። እንዲሁም ከአብደላህ ኢብኑ አባስ ውድ ባልደረቦች ሲሆን በጣም አዋቂ ፣አላህን ፈሪ ፣ኢባዳን የሚያበዛ ፣እንደውም በ2 ሌሊቶች ቁርአንን ያኸትም እንደነበርና እሱ ባለበት ሌላው አካል ፈትዋ እንዲሰጥ የማይፈለግበት ደረጃ ድረስ አላህ ከፍ ያደረገው ምርጥ ሰው ነበር። ኢብኑ ዐባስን ሰዎች መጥተው ጥያቄ ሲጠይቁት እንኳ ፦ "በመካከላችሁ ሰኢድ ቢን ጁበይር የለምን?" በማለት ደረጃውን ከፍ አድርገው ይመለከቱት ነበር። ሰዒድ ኢብኑ ጁበይርም ከዓመታት በኋላ፣በግፈኛው ሐጃጅ ኢብኑ ዩሱፍ ፊት እስረኛ ሆኖ ቀረበ።  ይህም ፍትሕ የጎደለውን አስተዳደር በመቃወም በተነሳው እንቅስቃሴ ውስጥ ስለተሳተፈ ነበር። በሰዐቱ ሰኢድ ከዐብዱርረሕማን ቢን ሙሐመድ ቢን አል-አሽዐስ ጋር አብሮ ነበር። በሰራዊቱ አጠቃላይ ወጪ ዙሪያ ሀጃጅ ኃላፊ አድርጎ የሾማቸው የነበረ ቢሆንም አብዱራህማን እንዲሁም ሰኢድ የሃጃጅ አካሄድ ትክክለኛ እና ስርአት ያለው እንዳልሆነ በመረዳት ከሱ ተቃራኒ በሆነ መልኩ ተንቀሳቅሰው ነበር። ስለዚህ ከጊዜያት በኋላ ሀጃጅ ከዐብዱራህማን ጋር በነበረው ጦርነት ላይ ድልን ሲቀዳጅ ሰኢድ ተፈላጊ ሆነ፤ በመጨረሻም ተይዞ ወደ ሐጃጅ ተላከ። ያ ምንም ዓይነት የጦር ኃይል ወይም ስልጣን የሌለው ታላቅ ሊቅ በግፈኛው ገዥ ፊት ቆመ። ሐጃጅ ያለፈውን እያስታወሰ፡ "በአደራዬ አላካፈልኩህም ነበርን? ሥራ አልሰጠሁህም ነበርን? እንዲህ እንዲህ አላደረኩልህምን?" በማለት ጠየቀው። ሰኢድም በተረጋጋ መንፈስ፡ «አዎ» እያለ መለሰ። ከዚህ በኋላ ሐጃጅ ሊደርስበት ወደሚፈልገው ዋናው ጥያቄ አለፈ፡ «ታዲያ በእኔ ላይ እንድትነሳና የአሚሩል ሙእሚኒንን ቃል ኪዳን እንድታፈርስ ምን አነሳሳህ?» ሰኢድም፡ «ከኢብኑ አል-አሽዐስ ጋር  ለመቀጠል የታማኝነት ቃል ኪዳንን ይዤ ነበረ» በማለት መለሰ። ሐጃጅ በጽኑ ተቆጣ። ከዚህ ቀደም ለዐብዱልመሊክ ቢን መርዋን ሰጥቶት የነበረውን ታማኝነትና ቃል ኪዳን እያስታወሰ፣ እንዴት ከእሱ ጋር የነበረውን ሁለት ቃል ኪዳኖችን ትቶ የኢብኑ አል-አሽዐስን ብቻ እንደሚይዝ በመገረም ወቀሰው። ውይይቱ ወደ ከረረ ደረጃ ሲሸጋገርም ሐጃጅ በስሙ ላይ በመጫወት እንዲህ አለ፦ "አንተ 'ሸቂይ ኢብኑ ኩሰይር' ነህ!" ("ሰዒድ"ማለት ደስተኛ፣ ዕድለኛ ሲሆን "ሸቂይ" ደግሞ እድለ ቢስ ማለት ነው።  "ጁበይር" ማለት የተሰበረን የሚጠግን፣ የተበላሸን የሚያስተካክል ሲሆን "ኩሰይር" ደግሞ ሰባሪ ማለት ነው።) በዚህ የጭንቀት ሰዓትም ቢሆን ሰኢድ ከራሱ ላይ እርጋታው እንዲወገድ አልፈቀደም፣እንደዛው ረጋ ባለ መልኩ ቀጠለ ፣ጽናቱንም አልለቀቀም። ሐጃጅ፡ «ወላሂ እገድልሃለሁ!» ብሎ በዛቻና በቁጣ ሲጮህበት… ሰዒድም፡ “ያን ጊዜማ እናቴ የሰየመችኝ ስም እውነት ይሆናል፤ እኔም (ለእውነት ሞቼ) በእርግጥም ደስተኛ (ሰዒድ) እሆናለሁ!» በማለት የሞትን ጥላ እንደ ክብርና እንደ እውነተኛ ድል ተቀበለው።” ሐጃጅ ሰኢድ እንዲገደል አዘዘ፤ አንገቱም ተቀላ (ረሕመቱላህ ዐለይህ)። ግና ሰኢድ አካሉ ሄደ እንጂ ታሪኩና ስሙ አልሞተም። ከዚህ ግድያ በኋላ ሐጃጅ ረጅም ዕድሜ አልኖረም። በተኛበት ሕልሙ ሰኢድ እየመጣ የልብሱን ጫፍ በመያዝ፡ “አንተ የአላህ ጠላት፣ በምን ምክንያት ገደልከኝ?" እያለ ይጠይቀው ነበር። ሐጃጅ በቅዠት እየተረበሸ፡ "የእኔና የሰኢድ ቢን ጁበይር ጉዳይ ምን አገናኘን! ምን አገናኘን!" በማለት ፀፀቱን ይገልፅ ነበር። ከዚህ ክስተት በኋላም ሐጃጅ ከዚያ በፊት በሰዎች ላይ ያሳየውን ግፍ ማሳየት እንዳቆመ ይነገራል። የዚህ ታሪክ ፍጻሜ እዚህ ላይ ቢያከትምም፣ ትምህርቱ ግን ገና ጀምሯል። ሰኢድ ከሐጃጅ ፊት የቆመው ሞት የማይቀር ውሳኔ መሆኑን ተረድቶ፣ የሰው ልጅ እውነተኛ ዋጋ የሚለካው ፍርሃት ሲጫነውና ከመርሆቹ እንዲወርድ ሲጠየቅ በሚያሳየው አቋም መሆኑ ስለገባው ነው። ለዚህም ነው የሰኢድ ቢን ጁበይር ስም ከዘመናት በኋላም ህያው የሆነው፤ የሐጃጅ ኃይልና ስልጣን ግን ጠፍቷል። ዘመናት ሊለወጡ፣ የፈተና መልክና ቅርጽ ሊቀያየር ይችላል፤ ነገር ግን የጽናት ትርጉም ከቶውን አይለወጥም። ዛሬም ቢሆን፣ ማንኛውም ሰው እምነቱን፣ መርሆቹን ወይም የሚያምንባቸውን እሴቶች ከባድ ፈተና፣ ግፊት ወይም ፍርሃት ውስጥ ወድቀው ሲያገኛቸው የሰኢድ ቢን ጁበይርን ታሪክ ሊያስታወስ ግድ ይላል። መንገዱ ቀላል አልነበረም፤ ጽናትም ያለ ዋጋ አልመጣም፤ ነገር ግን አንዳንድ አቋሞቻችን ጋር አስፈላጊ ሲሆን መከራንም ጭምር ተቀብለን ለአላህ ብለን መቆም እና መፅናት እንደሚገባን ያስገነዝበናል። ትምህርቱ ሰኢድ የኖረበትን ዓይነት ሁኔታዎች ማለፋችን ወይም በዘመናችን ያለውን ልዩነት ሁሉ ከእርሱ ታሪክ ጋር ማመሳሰላችን አይደለም። ይልቁንም ከታሪኩ የምንወስደው ቁምነገር ሰው በእምነቱ ላይ ሲፈተን እንዲጸና፣ በአላህ እንዲታገዝ፣ አላህም ትዕግሥቱን እንደሚመለከት እና ፈተናው ቢረዝምም ማብቂያ እንዳለው ማወቁ ነው። ዛሬም ቢሆን፣ አንድ ሙስሊም በሃይማኖቱ መጽናት ከባድ በሆነበት ፈተና ውስጥ ሲያልፍ፣ የሰኢድ ቢን ጁበይር ታሪክና የጽናት መንገዱ ከቶውንም በምቾት የተነጠፈ እንዳልነበር ያስታውሰናል። ትዕግሥት ሁሌ መንገዱ ይቀላል ሳይሆን ፣ ሰውየው ለምን ዓላማ መከራን መቀበል እንደሚገባው ማወቁን ያሳያል። እርግጥ ነው ሰኢድ ሞቷል፤ አቋሙ ግን እንደ ትምህርት ዘልቆ ኑሯል። ዘመናትን ቢሻገሩም የጽናት ትርጉሙ አልተለወጠም። የአላህ እዝነት በሰኢድ ላይ ይስፈን፤ ታሪኩንም ከእርሱ በኋላ ለሚመጡት ሁሉ መማሪያ ያድርግለት። በእውነት ላይ መጽናት በሰላምና በምቾት ሰዓት የሚወራ ባዶ ቃል ሳይሆን፣ ለጽናት እውነተኛ ዋጋ መከፈል በሚጀምርበት ሰዓት ላይ የሚገለጥ ጽኑ አቋም መሆኑን አስተምሮናል። ©aaumsu @fivekjemaa

2) ኢትዮጵያስ ሁሉንም ዜጎቿን በእኩልነት እያገለገለች ነውን? 3) የኢትዮጵያ የሆኑ ነገሮች ሁሉ በእኩልና በፍትሃዊ መልኩ ሁሉም እየተወከሉበት፣እኩል ተጠቃሚ ሆነውበታል? ሁሉንስ ከግምት ያስገቡ ሆነው ተዋቅረዋልን? የሙስሊሞች ጥያቄ ከመስጂድ ቅጥር ውጭ ይዘልቃል። ወደ ታሪክ አካታችነት ይሄዳል። ወደ ትምህርት ስርዓትና አተገባበር ያመራል። ወደ አካታች ኢኮኖሚም ይገባል። ወደ የቅርስና የባህል ጥበቃ ይሄዳል። ወደ ሀገራዊ ምልክቶችና መገለጫዎችም ይደርሳል። ወደ ሴቶችና ህፃናት መብትም ይዘልቃል። የ ሰብዓዊ መብት ጉዳይም ነው። ወደ አሳታፊና አካታች የተቋማት ግንባታ ይሄዳል። ፍትሃዊ ውክልናንም ይመለከታል። ወደ ፍትሕ ስርዓቱ ይገባል። በዜግነት ጉዳዮች በኩል ይመዘዛል። ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የሚጠይቋቸው ጥያቄዎች ከመስገድና ከመነገድ በላይ የዘለቁ ጥያቄዎች የፍትሕ፣ የእኩልነት፣ የውክልና እና የሙሉ ዜግነት ጉዳዮች ናቸው! ይህ የሙስሊሞች ጥያቄ ብቻ አይደለም። ይህ የኢትዮጵያ የሀገር ግንባታ ጥያቄዎች ናቸው። የአካታችነትና በሁሉም እርከን በፍትሃዊነት የመወከል ጥያቄ ነው። የሀገር ባለቤትነት ጥያቄ ነው። ይድረስ ለኮሚሽነሮቹ! 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 በሀገራዊ የምክክር ሂደት ውስጥ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን ጥያቄዎች በስምንቱ አጀንዳዎች ዉስጥ የተዘረዘሩትን ሰብስቦ በአንድ “የሃይማኖት ጉዳይ” ሳጥን ውስጥ መክተት የመፍትሔ መንገድ ሳይሆን የመዋቅራዊ ችግሩን ሥር የሚያስቀጥል አካሄድ ነው። እውነተኛ ሀገራዊ መግባባት የሚገኘው የዜጎችን መብት በአስተዳደራዊ ማጣሪያዎች ወይም በሃይማኖታዊ ሳጥኖች ውስጥ በመክተት ሳይሆን፣ እውነተኛ አካታችነት ማለት የሙስሊሞችንም ሆነ የየትኛውም ወገንን በየተነሱበት አጀንዳዎች ስር ከነአውዳቸው ሳይሸፋፈኑና በጥቅል ገለጻ ስር ሳይደበቁ በዚያው በተጠቀሱበት አኳኋን ምክረ ሀሳቦቹ በየተገቢው አጀንዳ ውስጥ ማስቀመጥና መፍትሄ እንዲያገኝ ማድረግ ሲቻል ብቻ ነው። እውነተኛ ፍትሕ ማለት በየተቋሙ ያለውን መዋቅራዊ እንቅፋት መለየትና ማስወገድ ነው። እውነተኛ ሀገር ግንባታ ማለት ሁሉም ዜጎች በሀገራቸው ውስጥ እኩል ባለቤትነት እንዲሰማቸው ማድረግ ነው።

በእውነት የሚገርመው ምንድን ነው? አንዲት ሙስሊም ተማሪ በሂጃቧ ምክንያት ብትገለል፣ ይህ የሴቶች መብት ጉዳይ ነው ወይስ የመጅሊስ ጉዳይ? የሙስሊሞች ታሪካዊ ቅርሶች በብሔራዊ ትረካ ውስጥ ቢጠፋ፣ ይህ የባህልና ቅርስ ጉዳይ ነው ወይስ የሃይማኖት ጉዳይ? ከወለድ ነፃ ፋይናንስ በበቂ ሁኔታ አለመዳረሱ የአሳታፊ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ጉዳይ ነው ወይስ የሃይማኖት ጉዳይ? አንድ ሙስሊም ዜጋ በመንግሥት ተቋማት ውስጥ እኩል ዕድል እንዲኖረው ሲጠይቅ ይህ የዜግነት ጥያቄ ነው ወይስ የሃይማኖት? በፌደራልም ሆነ በክልል በቢሮክራሲ፣ በዳኝነት፣በሕዝብ ተወካዮች ተቋማት ወይም በውሳኔ ሰጪ መድረኮች የሚነሱ የውክልና ጥያቄዎች የሃይማኖት ጉዳይ ናቸውን? እነዚህ ጥያቄዎች መልሳቸው ግልጽ ነው። ችግሩ የሃይማኖት ተቋማት ችግር አይደለም። ችግሩ የሀገራዊ ተቋማት አካታችነት ችግር ነው። "ጥያቄ ስታነሱ ሴኩላሪዝም ትዝ አለኝ" 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 በሀገራችን የታዘብኩት አንድ የቆየ አሳሳቢ አዝማሚያ አለ። የኢትዮጵያ ሙስሊሞች በታሪክ፣ በፍትሕ፣ በውክልና፣ በትምህርት፣ በኢኮኖሚ፣ በሰብዓዊ መብቶች፣ በተቋማት አካታችነት ወይም በሕገ-መንግሥታዊ መብቶች ዙሪያ ማንኛውንም ጥያቄ ሲያነሱ፣ ወዲያውኑ “ሴኩላሪዝም” ትዝ የሚላቸው መገኖች አሉ። በሁሉም መስክና ስፍራ እኩልነት በተግባር ጥያቄ ሲነሳ እነዚህ ወገኖች ሴኩላሪዝምን (የመንግስት ነፃ በመሆን ዓለማዊነትን) ጉዳይ በማንሳት ውይይቱን ወደ “ሃይማኖት ጉዳይ” ብቻ ለመግፋት የሚሞክሩ አካላትን ደጋግመን ታዝበናል። እነዚህ አካላት ጉዳዩን በዜግነት፣ በሰብዓዊ መብት፣ በሕገ-መንግሥታዊ እኩልነት፣ በተቋማዊ ፍትሕ ወይም በሀገር ግንባታ ማዕቀፍ ከማየት ይልቅ ወደ ሃይማኖታዊ ማዕቀፍ ብቻ ለማሳነስ ይሞክራሉ። በዚህ ሂደት የሙስሊሞች ጥያቄ ዜጎች የሚያነሱት ሀገራዊ ጥያቄ ሳይሆን የአንድ ሃይማኖት ውስጣዊ ጉዳይ እንደሆነ ለማቅረብ ይሞክራሉ። ይህ ግን ለሴኩላሪዝም ጥብቅና መቆም አይደለም፤ የዜግነት ጥያቄን ባህሪ መቀየርና በሴኩላሪዝም ስም ማፈን ነው። ሴኩላሪዝም ማለት መንግሥት ሃይማኖት ሳይኖረው በገለልተኛነት የሁሉምና ለሁሉም የሚመች፣ ሁሉም ዜጎች በእኩልነት በሀገራቸው ጉዳዮች እንዲሳተፉ የሚያስችል የገለልተኝነት መርህ እንጂ ማንኛውንም ማህበረሰብ ከሀገራዊ ጉዳዮች ማግለል ወይም ጥያቄዎቹን ወደ ሃይማኖት ሳጥን ውስጥ መክተት አይደለም። የሙስሊሞችን ማንኛውንም ጥያቄዎች ወደ “ሃይማኖት” ማውረድ የእኩል ዜግነትን ክርክር ከመሰረቱ ማዛባት ነው። የሀገራዊ የምክክሩ ትምህርት 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 በቅርቡ በተካሄዱ ሀገራዊ ውይይቶች አንድ አሳሳቢ አዝማሚያ ታይቷል። ከሙስሊሙ ማህበረሰብ የሚነሱ የታሪክ፣ የፍትሕ፣ የውክልና፣ የኢኮኖሚ፣ የሴቶች መብት፣ የትምህርት፣ የባህል፣ የመሬት አጠቃቀም፣ የፋይናንስ፣ የሲቪክ ተሳትፎ እና የተቋማት አካታችነት ጥያቄዎችን በሙሉ “የሃይማኖት ጉዳይ” በሚል ርዕስ ስር ለማጠቃለል የተደረገ ጥረት ታይቷል። ይህ ከቀላል የአጀንዳ አመዳደብ ስህተት በላይ ነው። ይህ የታሪካዊ ማግለል ዘመናዊ ቅጂ ነው። ጥያቄዎችን “ባለቤት አልባ” ማድረግ ኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች የተደራጁ በርካታ ሚኒስቴሮችና ተቋማት አሏት። የንግድ ጉዳይ የንግድ ተቋማትን ይመለከታል። የባህልና ቱሪዝም ጉዳይ ተቋማቱን ይመለከታል። የትምህርት ጉዳይ የትምህርት ተቋምን ይመለከታል። የሙስሊም ሴቶች መብት ጉዳይ የሴቶች ጉዳይ ሚኒስትርን ይመለከታል። አይመለከተኝም ካለ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ስያሜውን "የሙስሊም ያልሆኑ ሴቶች ጉዳይ ሚኒስቴር" ብሎ ይቀይር።የሙስሊም ሴቶች ጉዳይ የመጅሊስ ጉዳይ ብቻ የሚሆንበት ሁኔታ ማብቃት አለበት። የአካታች ፋይናንስ ጉዳይ የፋይናንስ ተቋማትን ይመለከታል። የተቋማት አካታችነት ጉዳይ የመንግሥት ተቋማትን ይመለከታል። እነዚህን ሁሉ በ“ሃይማኖት” ስም ወደ አንድ ተቋም መግፋት ማለት ጥያቄውን ከሚመለከተው ዋና ተቋም የማራቅ ስልት ነው። በዚህ ሁኔታ ተጠያቂ የሆኑ ተቋማት ከኃላፊነታቸው ይሸሻሉ።በተጨማሪም ጥያቄው መፍትሔ የሚያገኝበትን መንገድ ያጣል። ምክንያቱም የሃይማኖት ጉዳይ ተቋም በካቢኔ ውክልና፣ በመከላከያ ፖሊሲ፣ በትምህርት ሥርዓት፣ በመሬት አጠቃቀም ወይም በብሔራዊ ታሪክ አጻጻፍ ላይ ውሳኔ የመስጠት ሕጋዊ ሥልጣን የለውም። ስለዚህ ጥያቄው ከአንድ ቢሮ ወደ ሌላ ሲዘዋወር ይቆያል፤ መፍትሔ ግን አያገኝም። የታሪክ ጥያቄ የኢትዮጵያ ታሪክ ሲጻፍ ሙስሊሞች በምን ያህል ተካተዋል? የሀገሪቱ የንግድ ታሪክ፣ የስልጣኔ ታሪክ፣ የሙስሊም ሊቃውንት ታሪክ፣ የሙስሊም መሪዎች አስተዋጽኦ፣ የሙስሊም ማህበረሰቦች የሀገር ግንባታ ሚና በብሔራዊ ትረካ ውስጥ ምን ያህል ቦታ አግኝተዋል? ይህ የሃይማኖት ጥያቄ አይደለም። ይህ የታሪክ ፍትሕ ጥያቄ ነው። "ሙስሊሞች እኩል ዜጎች ከሆኑ" ✅✅✅✅✅✅✅✅✅ 1) በሀገራዊ ታሪክ ውስጥ እኩል ተወክለዋልን? 2) በባህልና ቱሪዝም ተቋማት ሥራዎች ውስጥ እኩል ተካተዋልን? 3) በትምህርት መጻህፍት ትረካዎች ውስጥ እኩል ተገልጸዋልን? 4) በፖሊሲ ውሳኔዎች ውስጥ እኩል የመወሰን ድምፅ አላቸውን? 5) በተቋማት ውስጥ እኩል ውክልና አላቸውን? 6) በውሳኔ ሰጪ መድረኮች ውስጥ እኩል ተሳትፎ አላቸውን? 7) በሀገራዊ ምልክቶችና መገለጫዎች ውስጥ እኩል ታይተዋልን? 8) በብሔራዊ ትረካዎች ውስጥ እኩል ቦታ አግኝተዋልን?... በርካታ ጥያቄዎችን ጨምሩበት። እነዚህን ጥያቄዎች ማንሳት ልዩ ጥቅም መጠየቅ አይደለም። እነዚህን ጥያቄዎች ማንሳት የእኩል ዜግነት ጥያቄ ነው። የሙስሊሞች ጉዳይ የሃይማኖት ጉዳይ ነውን? ⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕ የጥያቄውን ትክክለኛ ባህሪ መለየት አስፈላጊ ነው። አንድ ሙስሊም ዜጋ ሀገሩን በወታደራዊ ተቋማት ለማገልገል ሲፈልግ ከእምነቱ ወይም ከሙስሊምነቱ አንዳንድ መገለጫዎች እንዲተው ከተጠየቀ፣ ይህ የሃይማኖት ጉዳይ ብቻ አይደለም፤ የተቋማት አካታችነት፣ የእኩል ዕድል እና የዜግነት ጥያቄ ነው። አንዲት ሙስሊም ሴት በአለባበሷ ወይም በሃይማኖታዊ ማንነቷ ምክንያት በሥራ ቦታ ዕድል ከተነፈገች፣ ይህ የሠራተኛ መብት፣ የእኩልነት እና የሕገ-መንግሥታዊ መብት ጉዳይ ነው። አንድ ሙስሊም ተማሪ በሙስሊምነቱ ወይም በሃይማኖታዊ መገለጫው ምክንያት ከትምህርት ቤት ከተገለለ፣ ይህ የመጅሊስ ጉዳይ ሳይሆን የትምህርት መብት፣ የዜግነት እና የሕግ የበላይነት ጉዳይ ነው። መስጂዶች ሲቃጠሉ፣ሲፈርሱ ወይም ኢማሞች ሲገደሉ፣ ይህ የሀገሪቱ የሰላምና የደህንነት አጀንዳ እንጂ የሙስሊሞች ጉዳይ አይደለም። የሕግ ማስከበር እና የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ ግዴታ ያለባቸው ተቋማትን የሚመለከት ጉዳይ ነው። በአጠቃላይ ጥያቄውን የሚወስነው ጉዳዩን ያነሳው ሰው ሙስሊም መሆኑ ሳይሆን የተጣሰው መብት፣ የተፈጠረው ችግር እና መፍትሔ የሚሰጠው ተቋም ነው። ስለዚህ ሙስሊሞች የሚያነሱትን እያንዳንዱን ጥያቄ “የሃይማኖት ጉዳይ” ብሎ መፈረጅ የጥያቄውን እውነተኛ ባህሪ መሸፈን እና ከተጠያቂ ተቋማት ማራቅ ነው። ኢትዮጵያ እኩል የሁላችንም ነች? ከቃል ባሻገር በተግባር እንዴት ይገለጻል? 🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒 “እስላም ከሰገደና ከነገደ ሌላ ምን ይፈልጋል?” የሚለው ጥያቄ በመሠረቱ የተሳሳተ ጥያቄ ነው። መቅረብ ያለባቸው ጥያቄዎች የሚከተሉት ናቸው። 1) ኢትዮጵያውያን ሀገራቸውንና ወገናቸውን የማገልገል እኩል እድል አግኝተዋልን?

"እስላም ከሰገደና ከነገደ ሌላ ምን ይፈልጋል?" 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 የዜግነት ጥያቄዎችን በ“ሃይማኖት ጉዳዮች” ሳጥን ውስጥ የማፈን መዋቅራዊ አደጋ እና የተቋማዊ ማግለል አሰራር አደጋ። 📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶 በአሕመዲን ጀበል 🔴🔴🔴🔴🔴🔴 “እስላም ከሰገደና ከነገደ ሌላ ምን ይፈልጋል?” የሚለው አባባል አዲስ አይደለም። በዘመናት የተወረሰ፣ በትውልዶች የተደጋገመ፣ ዛሬም በይፋ ባይነገርም በተለያዩ መንገዶች የሚገለጽ የሚታይ አመለካከት ነው። በቀድሞ ዘመን በቀጥታ ይነገር ነበር፤ ዛሬ ግን በተቋማት አሰራር፣ በፖሊሲ አቀራረብ፣ በሚዲያ ትረካዎች፣ በሀገራዊ ውይይቶች እና በውሳኔ ሰጪ መድረኮች ውስጥ በዘመናዊ መልክ ተሸፍኖ መቀጠሉን እናያለን። ይህ አስተሳሰብ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን ጥያቄዎች ወደ መንፈሳዊና ኢኮኖሚያዊ ብቻ የማድረግ ስልታዊ ማግለል መገለጫ ነው። በምክክሩ ሙስሊሞች የገጠማቸው ተግዳሮቶች 📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶 እየተካሄደ ባለው ሀገራዊ ምክክር ሙስሊም ተሳታፊዎችን ከገጠሟቸው ተግዳሮቶች አንዱና ዋነኛው በርካቶች ዘንድ "ሙስሊም ከሰገደና ከነገደ ሌላ ምን ይፈልጋል?" የሚለው እይታ መኖሩን መታዘቡና ከዚሁ እይታ የተነሳ ሙስሊሞች ከሃይማኖት ጉዳዮች አጀንዳ ውጭ ባሉ ጉዳዮች የሚያነሷቸው ጥያቄዎችና ምክረ ሀሳቦች በሚያዙ ቃለጉባኤዎች ዉስጥ እንዳይካተቱ የሚታገሉ አካላትን በግልጽ መጋፈጣቸው ነው። የሚገርመው አብዛኞቹ መሰል አካላት የራሳቸው አንዳች አጀንዳዎች፣ጥያቄዎች የሌላቸውና የነርሱ አጀንዳ የሙስሊሞች አጀንዳ እንዳይካተት ማድረግ እስኪመስል ራሳቸውን አጋልጠዋል። በዚህ ስንኩል አመለካከት ባለቤቶች መካከል በሀላፊነት ላይ ያሉትም ጭምር ሆነው መገኘታቸው አሳዛኙ ሁኔታ ነው። ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በሀገር ግንባታ፣ በሀገር ባለቤትነት ጉዳዮች፣በታሪክ ፣የጋራ ሀገራዊ ማንነት እና እሴቶች፣ብዝኃነት እና አስተዳደር ጉዳዮች፣ የባህል፣ ታሪክ እና ቅርስ ጥበቃ ጉዳዮች ጥያቄዎች አሏቸው። በመንግሥት ምሥረታ፣ በተቋም ግንባታ፣ሰላም ግንባታ፣ግጭት መንስኤዎች እና አፈታት መንገዶች፣ ማህበራዊ ኢኮኖሚ እንዲሁም የአርሶ አደሮች እና አርብቶአደሮች ጉዳዮች፣ህገ መንግስታዊ እና ህጋዊ ማዕቀፍ በሰብአዊ መብቶች ጥበቃ፣የመልካም አስተዳደር ችግር እና የሙስና ጉዳዮች ምክረሀሳብ አሏቸው። ሙስሊሞች በ8ቱም አጀንዳዎች የሚያነሷቸው ጥያቄዎችና ምክረ ሀሳቦች ከየአጀንዳዎቹ ስር ተሰርዘው ወደ ሃይማኖት አጀንዳ ብቻ ይሂዱ የሚለው እይታ የተሳታፊዎች ብቻ አልነበረም። ኮሚሽኑ በመደባቸው ጥቂት አወያዮች፣ አስተባባሪዎችና ጥቂት ኮሚሽነሮች ዘንድም ተንጸባርቋል። ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በየአጀንዳዎቹ ሥር ያነሷቸውን ምክረ ሀሳቦች ለቃቅሞ ወደ የሃይማኖት አጀንዳ ሥር ለመውሰድ መሞከር ማለት ተራ የአሰራር ጉዳይ አይደለም።እንድምታው አደገኛ ነው። "ከሀገራዊ አጀንዳዎች ለማራቅ ወደ ሃይማኖት ጉዳዮች ግፏቸው!" ✅✅✅✅✅✅💢💢💢💢💢💢💢 አንድም የናንተን ሀሳብ ከሃይማኖት አንፃር ብቻ ነው የምናየው እያሉ ነው።አልያም ከሃይማኖት ጉዳይ በቀር ስለሌላው አይመለከታችሁም ፣ወይም ከሃይማኖት አጀንዳ እንድትወጡ አንፈቅድላችሁም ነው። ይህ በራሱ ሌላ ሀገራዊ ምክክር የሚፈልግ ሸውራራ እይታ ነው። በመጀመሪያ እይታ ይህ አባባል ቀላል ጥያቄ ሊመስል ይችላል። ግን በውስጡ ጥልቅ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና መዋቅራዊ እሳቤ ይዞ ይመጣል። ለምን? ምክንያቱም ይህ አስተሳሰብ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን ከሀገሪቱ አጠቃላይ ጉዳዮች እየገፋ ወደ “ሃይማኖት” ብቻ ለመወሰን ይሞክራል። በፍትሕ ላይ ጥያቄ ቢያነሱ ወደ ሃይማኖት ይገፋሉ። በታሪክ ላይ ቢናገሩ ወደ ሃይማኖት ይገፋሉ። በኢኮኖሚ ላይ ቢጠይቁ ወደ ሃይማኖት ይገፋሉ። በተቋማት ውክልና ላይ ቢወያዩ ወደ ሃይማኖት ይገፋሉ። የጥያቄው ርዕስ ቢቀየርም የሚቀርበው መልስ አንድ ነው፤ “ይህ የሃይማኖት ጉዳይ ነው” የሚለው።ነገር ግን ይህ የችግሩ መፍትሔ አይደለም፤ የችግሩ መሸፈኛ ነው። ሁለቱ አደገኛ እሳቤዎች ❌❌❌❌❌❌❌ “እስላም ከሰገደና ከነገደ ሌላ ምን ይፈልጋል?” የሚለው አባባል ሁለት አደገኛ እሳቤዎችን ይሸከማል። ሀ) ሙስሊሞችን ማሳነስ 🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶 ይህ አባባል ሙስሊሞችን ከሀገር ግንባታ፣ ከእውቀት ምርት፣ ከሳይንስ፣ ከፖለቲካ፣ ከባህል፣ ከተቋማት ግንባታ፣ ከውሳኔ ሰጪነት እና ከሀገራዊ አጀንዳዎች ውጭ ያሉ ሰዎች እንደሆኑ ያቀርባቸዋል። ሙስሊሙ እንደ መምህር አይታይም። እንደ ሳይንቲስት አይታይም። እንደ ዳኛ አይታይም። እንደ ፖሊሲ አውጪ አይታይም። እንደ ታሪክ ባለቤት አይታይም። እንደ ሙሉ ዜጋም አይታይም። እንደ ሃይማኖታዊ ማህበረሰብ ብቻ እንዲታይ ይደረጋል። ለ) ሙስሊሞችን በሁለት መስኮች ብቻ መገደብ 🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺 ሁለተኛው አደገኛ እሳቤ ሙስሊሞችን በሁለት መስኮች ብቻ በመስገድና በመነገድ ለመገደብ ያለ ፍላጎት ነው። ይህ አመለካከት ሙስሊሞች በመስጂድ ውስጥ እንዲቆዩ ወይም በንግድ እንዲሰማሩ ሊፈቅድ ይችላል። ነገር ግን በታሪክ አጻጻፍ፣ በሀገራዊ ትረካ፣ በትምህርት ፖሊሲ፣ በተቋማት ግንባታ፣ በመከላከያ፣ በዳኝነት፣በሲቪል ሰርቪስ፣ በሚዲያ ፣ በባህል ተቋማት፣ በውሳኔ ሰጪ መድረኮች፣ በሀገራዊ ምልክቶች እና በሀገር ባለቤትነት ስሜት ውስጥ እኩል ተሳታፊ እንዳይሆኑ በተዘዋዋሪ መንገድ ይገፋፋል። የዜግነት ጥያቄን ወደ ሃይማኖት ነጻነት ማውረድ ⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕ የችግሩ መሠረት አንድ ነው፤ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የሚያነሱትን ማንኛውንም ጥያቄ እንደ “ሃይማኖታዊ ጥያቄ” ብቻ መመልከት። ነገር ግን እውነተኛው ጥያቄ ይህ ነው፦ ሙስሊሞች በዚህች ሀገር ላይ የሚያነሱት ጥያቄ የሃይማኖት ጥያቄ ብቻ ነውን? መልሱ ግልጽ ነው። አይደለም። ሙስሊሞች የሚያነሱት ጥያቄ የዜግነት ጥያቄ ነው። ስለ ፍትሕ ሲናገሩ፣ ስለ ተቋማዊ ውክልና ሲጠይቁ፣ ስለ ታሪክ አጻጻፍ ሲከራከሩ፣ ስለ ባህል ቅርስ ሲጠይቁ፣ ስለ ኢኮኖሚ ተሳትፎ ሲወያዩ፣ ስለ ኢስላማዊ ፋይናንስ ሲነሱ፣ ስለ እኩል ትምህርት ዕድል ሲናገሩ፣ ስለ አሳታፊ የሥራ ዕድል ሲጠይቁ፣ ስለ ሴቶች መብት ሲያነሱ፣ ስለ ሰብዓዊ መብቶች ሲወያዩ፣ ስለ መሬት አጠቃቀም ሲከራከሩ፣ ስለ ተቋማት አካታችነት ሲጠይቁ፣ ስለ ውሳኔ ሰጪነት ሲወያዩ፣ የሚያነሱት ጥያቄ የዜግነት ጥያቄ ነው። ይህ የመስጂድ ጥያቄ ብቻ አይደለም። ይህ የሂጃብ ጥያቄ ብቻ አይደለም። ይህ የመጅሊስ ጥያቄ ብቻ አይደለም። ይህ የእኩል ዜግነት ጥያቄ ነው። የጥያቄውን ባህሪ የመቀየር አደገኛነት 💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥 አንድ ማህበረሰብ የሚያነሳውን የመብት ጥያቄ “ሃይማኖታዊ” ብቻ ብሎ መፈረጅ በእውነቱ የጥያቄውን ባህሪ መቀየር ነው። የፍትሕ ጥያቄ የሃይማኖት ጥያቄ አይደለም። የኢኮኖሚ ተሳትፎ ጥያቄ የሃይማኖት ጥያቄ አይደለም። የባህልና ቅርስ ጥያቄ የሃይማኖት ጥያቄ አይደለም። የታሪክ ውክልና ጥያቄ የሃይማኖት ጥያቄ አይደለም። የመንግሥት ተቋማት አካታችነት ጥያቄ የሃይማኖት ጥያቄ ሊሆን አይችልም። የሙስሊም ይሁን የክርስቲያን የሴቶች መብት ጥያቄ የሃይማኖት ጥያቄ አይደለም። የትምህርት ፖሊሲ ጥያቄ የሃይማኖት ጥያቄ አይደለም። የውክልና ጥያቄ የሃይማኖት ጥያቄ እንዴት ሊሆን ይችላል? እነዚህ ሁሉ የዜግነት፣ የፍትሕ፣ የእኩልነት እና የሀገር ግንባታ ጥያቄዎች ናቸው።

🌙✨ የሙሀደራ ፕሮግራም ✨🌙 መውሊድ — ያልተነገረው ገጽታ ጉዳዩን በግምት ሳይሆን፣ በቁርአን፣ በሐዲስ፣ በዑለማዎች ንግግርና በፊቅህ መርሆች በመመርመር እንመለከታለን። 🔎 በዚህ ሙሀደራ የሚነዳሰሱ ነጥቦች ፦ ❓ መውሊድ በማን ተጀመረ? ❓ መውሊድን የሚፈቅዱ ዑለማዎች ማስረጃቸው ምንድነው? ❓ አንድ ተግባር በመልካም ዓላማ መፈጸሙ ብቻ ለሸሪዓ የተፈቀደ ያደርገዋልን? ❓ ነቢዩ ﷺ አንድን ነገር አለማድረጋቸው (الترك) በራሱ የተግባሩ መከልከል ማስረጃ ነውን? ❓ “መልካም ቢድዓ” የሚለው አባባል በምን ይተረጎማል? ዑለማዎችስ ምን ይላሉ? 🎙️ አቅራቢ፦ ኡስታዝ ዘንጀቢል ━━━━━━━━━━━━━━ 📅 የፕሮግራሙ ቀን፦ የፊታችን ሰኞ — ነሐሴ 10 ⏰ ሰዓት፦ ከምሽቱ 3 ሰዓት ━━━━━━━━━━━━━━ 🌿 ጉዳዩን በጥልቀት ለመረዳት፣ የተለያዩ የዑለማዎችን አቋም ለማወቅና በማስረጃ ላይ የተመሠረተ ግንዛቤ ለመያዝ ይሳተፉ። 🔥 “ከመውሊድ ጀርባ ያለውን እውነት ለማወቅ… ይህን እድል አያምልጦ!” 📢 ለሌሎችም ያጋሩት!

Zenjebil.m4a6.22 KB

🔥نحن قومٌ أعزَّنا اللهُ بالإسلام! 🔊አዲስ መድረክ፣ አዲስ ግንዛቤ፣ አዲስ ከፍታ! 🗯 ሕያው ምስክር❕🗯 የ ስኬት መጎናጸፍያ ጎዳና የሆነው እስልምና ላይ እስከ ዘመናችን ድረስ
🔥نحن قومٌ أعزَّنا اللهُ بالإسلام! 🔊አዲስ መድረክ፣ አዲስ ግንዛቤ፣ አዲስ ከፍታ!             🗯 ሕያው ምስክር❕🗯 የ ስኬት መጎናጸፍያ ጎዳና የሆነው እስልምና ላይ እስከ ዘመናችን ድረስ በመንገዱ ከቀደሙን ታላላቅ ሰዎች ስንቅ እንወስድ ዘንዳ ጉዟቸውን፣ ትግላቸውንና ልምዳቸውን ምንቃኝበት ታላቅ መድረክ!! በ ሀገራችን ውስጥ የተለያዩ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ስለ እውነት፣ ስለ መብት፣ ስለ ማንነት፣ ስለ እስልምና ሲደረጉ የነበሩ መሰል ጉዞዎች፣ ስለ ሙስሊሙ ማህበረሰብ እና ስለ ተማሪዎች ጥያቄ፣ ስለተደረገው ትግል እና ስላስገኘው ውጤት በ ጥልቀት ምናይበት፣ እንዲሁም በተለያዩ ጽንሰ ሃሳቦች ዙርያ ዕይታን በማስፋት ረገድ አንገብጋቢ የሆኑ ርዕሶች ላይ ግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራሞች ሚቀርቡበት፣ ወደ ሗላ ራቅ ብሎም እስልምና ለመፍጠር ሚተጋለትን ማህበረሰብ በተግባር ኖረው ካሳዩን ወርቃማ ትውልድ እና ጊዜያት በተለያዩ ምሁራን አማካኝነት ምንቃኝበት ፕሮግራም ነው። ሕያው ምስክር በየ ሶስት ሳምንቱ በ አአዩሙተህ ይፋዊ ቴሌግራም ቻናል በ ቋሚነት ሚቀርብላችሁ ልዩ የ ቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም ! የመጀመሪያው ታሪካዊ መድረካችን መቼ ነው ?! በምን ዙሪያስ ይሁን ሚቀርበው ?! በቅርብ ቀን ይጠብቁን✨ @aaumsu

ሀገራዊ ምክክሩ ዘመናትን ለተሻገረው የሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄ ዘላቂ መፍትሔ እንዲያመጣ እንጠይቃለን። መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ በኢንስታግራም https://www.instagram.com/reel/Db_G8VCMmHu/?igsh=aHJiMHNvMmZyaGs2 በመግባት ያሰራጩ። @aaumsu

#ሕያው_ምስክር❕ 🔥 ••በ ቅርብ ቀን ይጠብቁን•• 🔥 @aaumsu
#ሕያው_ምስክር❕ 🔥 •በ ቅርብ ቀን ይጠብቁን•• 🔥 @aaumsu

የትምህርት ሚኒስቴሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ኢንትራንስ የሚፈተኑ ተማሪዎችን ከመፈተኛ አዳራሽ ገብቶ እየዘየረ ኒቃቢስት ተማሪዎች አትገቡም ተብለው አንድ ሙሉ ፈተና እስኪያልፋቸው ድረስ ከውጭ እንዲቆዩ
የትምህርት ሚኒስቴሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ኢንትራንስ የሚፈተኑ ተማሪዎችን ከመፈተኛ አዳራሽ ገብቶ እየዘየረ ኒቃቢስት ተማሪዎች አትገቡም ተብለው አንድ ሙሉ ፈተና እስኪያልፋቸው ድረስ ከውጭ እንዲቆዩ ተደርገው ነበር። የሗላ ሗላ ኒቃባቸውን ጥለው በማስክ እንዲገቡ ቢሆንም ከዚያ ቀን ቡሃላ ግን ማስኩንም እንደተከለከሉ ተናግረዋል። ይህ እና ሌሎች ነጥቦች፤ ብሎም የመፍትሔ አቅጣጫዎች በሱመያዎቹ ፖድካስት ተዳሷል። https://youtu.be/dwCvc9NIA90?si=p53yOcEtaA-m5mlq በመግባት ተመልከቱ። ለሌሎችም አሰራጩ። @aaumsu

የኒቃቢስቷ ጥሪ፦ ኢማሞች በመስጂድ እንድንለብስ ያስተማራችሁንን ዩኒቨርስቲ ስንገባ እየተከለከልን ነው። ስለመብታችን ሊታገል የቆመው መጅሊስ ባለበት አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሙስሊም ተማሪዎችን መብት ሲጥስ ከርሟል። ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ሁሉም ሀላፊነቱን ሊወጣ ግድ ነው። የአዳማ ከተማ መጅሊስ፦ ሁላችንም በያለንበት መታገል ግዴታችን ነው። መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ https://vt.tiktok.com/ZS4cKLF1Y/ በመግባት ሪፖስት አድርጉ። @aaumsu

በምርቃታቸው ቀን ታሰሩ። ከተመረቁ ቡሃላ ደግሞ ዲግሪያቸውን ተከለከሉ። ይህ ሁሉ "ኒቃብ መልበስ መብት ነው!" - የሚል መልዕክት በለበሱት ሪቫን ላይ በማስቀመጣቸው ነው። ይህ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እያደረሰ ያለውን ቀጣይነት ያለው የመብት ጥሰት ያሳያል። የሐይማኖት ነፃነት መብታችንን እስኪያከብር ጥያቄ አለን። የመናገር ነፃነት መብታችንን እስኪያከብር ጥያቄ አለን። ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ጥያቄ አለን ! መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ https://vt.tiktok.com/ZS4nuKTRG/ በመግባት ሪፖስት አድርጉ። @aaumsu