fa
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

رفتن به کانال در Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

نمایش بیشتر
1 162
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+37 روز
+730 روز
آرشیو پست ها
🌙✨ የሙሀደራ ፕሮግራም ✨🌙 መውሊድ — ያልተነገረው ገጽታ ጉዳዩን በግምት ሳይሆን፣ በቁርአን፣ በሐዲስ፣ በዑለማዎች ንግግርና በፊቅህ መርሆች በመመርመር እንመለከታለን። 🔎 በዚህ ሙሀደራ የሚነዳሰሱ ነጥቦች ፦ ❓ መውሊድ በማን ተጀመረ? ❓ መውሊድን የሚፈቅዱ ዑለማዎች ማስረጃቸው ምንድነው? ❓ አንድ ተግባር በመልካም ዓላማ መፈጸሙ ብቻ ለሸሪዓ የተፈቀደ ያደርገዋልን? ❓ ነቢዩ ﷺ አንድን ነገር አለማድረጋቸው (الترك) በራሱ የተግባሩ መከልከል ማስረጃ ነውን? ❓ “መልካም ቢድዓ” የሚለው አባባል በምን ይተረጎማል? ዑለማዎችስ ምን ይላሉ? 🎙️ አቅራቢ፦ ኡስታዝ ዘንጀቢል ━━━━━━━━━━━━━━ 📅 የፕሮግራሙ ቀን፦ የፊታችን ሰኞ — ነሐሴ 10 ⏰ ሰዓት፦ ከምሽቱ 3 ሰዓት ━━━━━━━━━━━━━━ 🌿 ጉዳዩን በጥልቀት ለመረዳት፣ የተለያዩ የዑለማዎችን አቋም ለማወቅና በማስረጃ ላይ የተመሠረተ ግንዛቤ ለመያዝ ይሳተፉ። 🔥 “ከመውሊድ ጀርባ ያለውን እውነት ለማወቅ… ይህን እድል አያምልጦ!” 📢 ለሌሎችም ያጋሩት!

Zenjebil.m4a6.22 KB

🔥نحن قومٌ أعزَّنا اللهُ بالإسلام! 🔊አዲስ መድረክ፣ አዲስ ግንዛቤ፣ አዲስ ከፍታ! 🗯 ሕያው ምስክር❕🗯 የ ስኬት መጎናጸፍያ ጎዳና የሆነው እስልምና ላይ እስከ ዘመናችን ድረስ
🔥نحن قومٌ أعزَّنا اللهُ بالإسلام! 🔊አዲስ መድረክ፣ አዲስ ግንዛቤ፣ አዲስ ከፍታ!             🗯 ሕያው ምስክር❕🗯 የ ስኬት መጎናጸፍያ ጎዳና የሆነው እስልምና ላይ እስከ ዘመናችን ድረስ በመንገዱ ከቀደሙን ታላላቅ ሰዎች ስንቅ እንወስድ ዘንዳ ጉዟቸውን፣ ትግላቸውንና ልምዳቸውን ምንቃኝበት ታላቅ መድረክ!! በ ሀገራችን ውስጥ የተለያዩ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ስለ እውነት፣ ስለ መብት፣ ስለ ማንነት፣ ስለ እስልምና ሲደረጉ የነበሩ መሰል ጉዞዎች፣ ስለ ሙስሊሙ ማህበረሰብ እና ስለ ተማሪዎች ጥያቄ፣ ስለተደረገው ትግል እና ስላስገኘው ውጤት በ ጥልቀት ምናይበት፣ እንዲሁም በተለያዩ ጽንሰ ሃሳቦች ዙርያ ዕይታን በማስፋት ረገድ አንገብጋቢ የሆኑ ርዕሶች ላይ ግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራሞች ሚቀርቡበት፣ ወደ ሗላ ራቅ ብሎም እስልምና ለመፍጠር ሚተጋለትን ማህበረሰብ በተግባር ኖረው ካሳዩን ወርቃማ ትውልድ እና ጊዜያት በተለያዩ ምሁራን አማካኝነት ምንቃኝበት ፕሮግራም ነው። ሕያው ምስክር በየ ሶስት ሳምንቱ በ አአዩሙተህ ይፋዊ ቴሌግራም ቻናል በ ቋሚነት ሚቀርብላችሁ ልዩ የ ቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም ! የመጀመሪያው ታሪካዊ መድረካችን መቼ ነው ?! በምን ዙሪያስ ይሁን ሚቀርበው ?! በቅርብ ቀን ይጠብቁን✨ @aaumsu

ሀገራዊ ምክክሩ ዘመናትን ለተሻገረው የሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄ ዘላቂ መፍትሔ እንዲያመጣ እንጠይቃለን። መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ በኢንስታግራም https://www.instagram.com/reel/Db_G8VCMmHu/?igsh=aHJiMHNvMmZyaGs2 በመግባት ያሰራጩ። @aaumsu

#ሕያው_ምስክር❕ 🔥 ••በ ቅርብ ቀን ይጠብቁን•• 🔥 @aaumsu
#ሕያው_ምስክር❕ 🔥 •በ ቅርብ ቀን ይጠብቁን•• 🔥 @aaumsu

የትምህርት ሚኒስቴሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ኢንትራንስ የሚፈተኑ ተማሪዎችን ከመፈተኛ አዳራሽ ገብቶ እየዘየረ ኒቃቢስት ተማሪዎች አትገቡም ተብለው አንድ ሙሉ ፈተና እስኪያልፋቸው ድረስ ከውጭ እንዲቆዩ
የትምህርት ሚኒስቴሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ኢንትራንስ የሚፈተኑ ተማሪዎችን ከመፈተኛ አዳራሽ ገብቶ እየዘየረ ኒቃቢስት ተማሪዎች አትገቡም ተብለው አንድ ሙሉ ፈተና እስኪያልፋቸው ድረስ ከውጭ እንዲቆዩ ተደርገው ነበር። የሗላ ሗላ ኒቃባቸውን ጥለው በማስክ እንዲገቡ ቢሆንም ከዚያ ቀን ቡሃላ ግን ማስኩንም እንደተከለከሉ ተናግረዋል። ይህ እና ሌሎች ነጥቦች፤ ብሎም የመፍትሔ አቅጣጫዎች በሱመያዎቹ ፖድካስት ተዳሷል። https://youtu.be/dwCvc9NIA90?si=p53yOcEtaA-m5mlq በመግባት ተመልከቱ። ለሌሎችም አሰራጩ። @aaumsu

የኒቃቢስቷ ጥሪ፦ ኢማሞች በመስጂድ እንድንለብስ ያስተማራችሁንን ዩኒቨርስቲ ስንገባ እየተከለከልን ነው። ስለመብታችን ሊታገል የቆመው መጅሊስ ባለበት አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሙስሊም ተማሪዎችን መብት ሲጥስ ከርሟል። ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ሁሉም ሀላፊነቱን ሊወጣ ግድ ነው። የአዳማ ከተማ መጅሊስ፦ ሁላችንም በያለንበት መታገል ግዴታችን ነው። መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ https://vt.tiktok.com/ZS4cKLF1Y/ በመግባት ሪፖስት አድርጉ። @aaumsu

በምርቃታቸው ቀን ታሰሩ። ከተመረቁ ቡሃላ ደግሞ ዲግሪያቸውን ተከለከሉ። ይህ ሁሉ "ኒቃብ መልበስ መብት ነው!" - የሚል መልዕክት በለበሱት ሪቫን ላይ በማስቀመጣቸው ነው። ይህ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እያደረሰ ያለውን ቀጣይነት ያለው የመብት ጥሰት ያሳያል። የሐይማኖት ነፃነት መብታችንን እስኪያከብር ጥያቄ አለን። የመናገር ነፃነት መብታችንን እስኪያከብር ጥያቄ አለን። ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ጥያቄ አለን ! መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ https://vt.tiktok.com/ZS4nuKTRG/ በመግባት ሪፖስት አድርጉ። @aaumsu

ከታሪክ ገጾች📖…እስካለንበት ተጨባጭ ✍️ ሁሉም ትውልድ የራሱ ሀጃጅ ሲኖረው፤ ሁሉም ሀቅም የራሱ ባለቤት አለው። ✨ ክፍል 2 እውነትን ግፍ የተከተለበትና የሁለት ተቃራኒ ጎዳናዎች የተገናኙበት ታሪክ ነው። ፍሰቱን የጠበቀ በሚመስል መልኩ የጽናት ተምሳሌት የሆነውና እውነትን ለመናገር ሕይወቱን የሰጠታቢዒይ 💫 አቡ ዐብደላህ ሰዒድ ኢብኑ ጁበይር አል-አሰድይ በተወለደ በ2 አመቱ ነበር ስልጣኑን በግፍ የጠመቀው ገዥ ሀጃጅ ኢብን ዩሱፍ አስ-ሰቀፊይ የተወለደው። አላህ ዱንያ ላይ የትኛውንም አይነት ፈተናን ለአንድ አማኝ ባሪያው መስጠቱ ግልጽ ሆኖ ሳለ፣ ባለህ ስልጣን ወይም ደግሞ በተቀመጥክበት ሃላፊነት ላይ ሌሎች ውድ የአላህ ባሮች ጋር መገናኘት ግድ ይሆንና ስልጣንህን ተጠቅመህ በደልህን በመዝራት ኢ- ፍትሃዊነትን ያሰፈንክ እለት ፈተናህን መውደቅህ ብቻ ሳይሆን እረፍት የሌለውና ዘላቂ የሆነ የቅጣት ማእበል ላይ ዘውታሪ እንደምትሆን ማሰቡ ደግ ነው።ሐጃጅ ኢብን ዩሱፍም ምናልባት ፈተናው ይህ ነበር❗️ ስልጣንን ለማግኘት ያለው መንገዱ ገራለት፣እያደገ ሲሄድም ከተወለደበት ከተማ ከጣኢፍ ወደ ሻም ተጓዘ።በዚያም ከኸሊፋው ዐብዱል መሊክ ኢብኑ መርዋን ጋር ተገናኘ። ዐብዱልመሊክ የሐጃጅን ጥንካሬና ቆራጥነት በማየት ከፍተኛ ኃላፊነት ሰጠው። በዚያን ዘመን በመካ የሙስሊሞች መሪ  የነበረው ታላቁ ሶሐቢ ዐብዱላህ ኢብኑ ዙበይር (ረድየላሁ ዐንሁ) ነበር። እርሱ የታላቁ ሶሐቢ ዙበይር ኢብኑል ዐዋም ልጅ ሲሆን፣ እናቱም የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየላሁ ዐንሁ) ልጅ አስማእ (ረድየላሁ ዐንሃ) ነበረች። ዐብዱል መሊክ ሐጃጅን የሙስሊሞች መሪ  የነበረውን ታላቁን ሶሐቢ ዐብዱላህ ኢብኑ ዙበይር እንዲገድል ወደ ሒጃዝ ላከው።ታላቅ ሠራዊት አሰልፎ በመሄድም ዐብዱላህ ኢብኑ ዙበይርን ገደለ፤ የእርሱንም አስተዳደር አበቃ። ከዚያ በኋላ ዐብዱል መሊክ ሐጃጅን የሒጃዝ (መካ፣ የመዲና፣ የጧኢፍ)፤ በኃላም የዒራቅ አስተዳዳሪ አደረገው። ከዚያ ጀምሮ ሐጃጅ ሥልጣኑን በጥብቅ እጅ ማስፈጸም ጀመረ። ፊትነቱል-ቁራእ በተባለው ፊትና የተሳተፉ የታቢዒዮችን ዑለሞች ማሳደድ፣ማሰርና መግደል የዘወትር ሥራው ሆነ ፣በዚህ አደገኛ የስም ዝርዝር ውስጥም ሰዒድ ኢብኑ ጁበይር ይገኛል።     ሐጃጅ ሰዒድን ለመያዝ የጀመረው ፍለጋ አንድ ቀን ወይም አንድ ወር አልነበረም። 🔸 ከስምንት ዓመታት በላይ የቀጠለ ነበር። በቃ እውነታው ይህ ነው፤ዛሬ ላይ ምናልባት አንተ ለያዝከው ሀቅ ከምትከፍለው መስዋእትነት በላይ እጅ እንድትሰጥ፣ እንድትደክም እና ተስፋ እንድትቆርጥ ጠላት በጣም በተደራጀና እጥፍ በሆነ መልኩ ዝቅ ሊያደርግህ ይለፋ፣ ይተጋ ይሆናል። ነገር ግን አይደለም 1 ፣ 2 አመት ጽናቱ ካለህና በአላህ ከታገዝክ ፈተናህ የብዙ አመታት ቢሆን እንኳን ትወጣዋለህ። እናም ሀጃጅ ሰኢድን ማሰስ ከጀመረ ከ8 አመታት በኋላ በወታደሮቹ አማካኝነት በመካ አገኘው እነርሱም አሰረዉት ወደ ሐጃጅ ይዘውት መጓዝ ጀመሩ። በመንገድ ላይ ግን ልብን የሚሰብር ክስተት ተፈጠረ።ሴት ልጁ ከፊት ለፊቱ ተከትላ እየሮጠች ታለቅስ ጀመር።ሰዒድም እንደምንም ራሱን ለማጠናከር ከራሱ ጋር እየታገለ "ልጄ ሆይ! እናትሽን በአላህ ፈቃድ ጀነት ውስጥ እንገናኝ በያት!" አላት። እርሱ የሚሄደው ወደ እስር ብቻ እንዳልሆነ፣ ወደ ሸሂድነት ጉዞ መሆኑን ያውቅ ነበር… ሁኔታው በእርግጥ ከባድ ነው። ነገር ግን ዱንያ ላይ ያለ ነገር በሙሉ እንደ መስዋእትነት ቀርቦ ሀቅ ላይ መጽናት እንዳለብን የተማርንበት ትልቅ ክስተት ነበር። ዛሬ ላይ የአመታትን ልፋት እና ሌሎች ብዙ ነገሮችን ሊያስከፍለን ይችላል። ጽናትና ኢኽላስ ካለ ግን ከአላህ ጋር ሁሉም ይሳካል። የእውነት ድምጽ በስልጣን ፊት ምን ይመስል ይሆን? ክፍል 3 ይቀጥላል……… ✍️ታሪኩን በምን መልኩ ወሰዳችሁት ?! ✍️ምን ትምህርት አገኛችሁበት?! ✍️ ምንስ አስተዋላችሁበት ?! ከታች ባለው ሊንክ አስቀምጡልን @Niqab_issueBot @aaumsu

ከታሪክ ገጾች📖…እስካለንበት ተጨባጭ ✍️ ለመፈተን የመጀመሪያዎቹ አይደለንም፤ለመጽናትም የመጨረሻዎቹ አንሆንም። ክፍል 1 << ዘንድሮ >> በውስጡ << ድሮ >> የሚለውን ቃል ይይዛል። ታሪክ ሲተረክ በድሮ ጊዜ ✍️እየተባለ ነው አይደል? ብዙ ድሮዎች ደግሞ አልፈዋል። ግን ያ ያማረው ፣ ድንቁና ወርቃማው በታሪክ ማህደር ውስጥ ውድ ሳሃቦችንና ታቢዒዮችን ያሰፈረው ድሮ ከሌላው በጣም የተለየ ነው። እንደ አንድ ዲኑን ለማወቅ የሚታትር፣ እስልምና ከፍ ብሎ ማየትን የሚሻ እንዲሁም መብቱን አስከብሮ መኖርን በራሱ ላይ ግዴታ ያደረገ ሙስሊም ደግሞ ዘንድሮም እንዳለፈው ድሮ ደምቆ ይሰፍር ዘንድ ካለፈው ታሪክ ያጤናል፣ ትምህርቱን ወስዶ የዛሬውን ጉዞ መስመሩ በተስተካከለው የቀደምቶች መንገድ ላይ ይቀጥላል….. ሂጃብ ለብሶ መማር መሰናክል ሲሆን፣ እህቶች በየመግቢያ በሩ ፣ካፌ እና ላይብረሪ ላይ ሲፈተኑ ማየት ከዛ ደግሞ ያለንበት እውነታን አለም ተረድቶ መፍትሄ ይሰጠን ዘንድ ስንቋምጥ አንድም በታወሩ ልቦች ሁለትም ውሸትን ቀለብ ባደረጉ ህሊናዎች ምን ሆናችሁ? ምን ነካችሁ? መባልና መካድ በጣም ያማል። ይህ ህመም ይሽር ዘንድ መድሃኒቱ የእውነት ደምቆ መታየት መሆኑ ደግሞ እሙን ነው። ግና ምን ያህል ዋጋ ያስከፍለን ይሆን? ለመክፈልስ ዝግጁ ነን❓ ……………………. ለእውነት ሲል በእውነት ላይ ከሞተ 1 ታላቅ ስብእና ፣ የእውነት ሰው እና የጽናት ተምሳሌት የምንወስደው ቁም ነገር አለ። ነገሩ እንዲህ ነው👇 በ38ተኛው ዓ.ሂ በኩፋ ከተማ አንድ ሕፃን ተወለደ። ይህ የሆነው በአራተኛው ኸሊፋ፣ በዐሊይ ኢብኑ አቢ ጧሊብ (ረድየላሁ ዐንሁ) ዘመን ነበር። በዚያን ጊዜ ማንም ይህ ሕፃን በኋላ ከታቢዒዮች እና ታላላቅ ዑለማዎች አንዱ እንደሚሆን፣ በተፍሲር፣ በሐዲሥና በፊቅህ ውስጥ የማይረሳ ስም እንደሚተው፣ እውነትንም ለመጠበቅ እስከሞት ድረስ እንደሚቆም አያውቅም ነበር። ……………………. ከሁለት ዓመታት በኋላ ደግሞ በጧኢፍ ሌላ ሕፃን ተወለደ። አንዱ በእውቀትና በኢማን ይታወቃል፤ሌላው በኀይልና በጭካኔ አንዱ ሰዎችን ወደ አላህ ይጠራል፤ሌላው በሥልጣኑ ያስፈራራል። የሁለቱ መንገድ ከዓመታት በኋላ ይገናኛል፤ ያ ግንኙነትም በእስልምና ታሪክ ውስጥ በጣም አስደናቂና ትምህርት የሞላበት ክስተት ይሆናል። የዚህ ባለሁለት መንገዱ አስደናቂ ታሪክና ክስተት ባለቤት የሆኑት ሁለቱ ህጻናት እነማን ይሁኑ?🤔 ክፍል 2 ይቀጥላል… @aaumsu

🔵 ( الدُنيا تَقولُ بِمِلءِ فيها حَذارِ حَذارِ مِن بَطشي وَفَتكي وَلا يَغرُركُم حُسنُ اِبتِسامي فَقَولي مُضحِكٌ وَالفِعلُ مُبكي)
 ⚪️ ​هِيَ الدُنيا تَقولُ بِمِلءِ فيها ⚫️ ያቺ ዱንያ በሙሉ አፏ አውጥታ (በጎላ ድምፅ) ትናገራለች፦ ⚪️ ​حَذارِ حَذارِ مِن بَطشي وَفَتكي ⚫️ «ተጠንቀቁ! ተጠንቀቁ ከኃይሌና ከጥቃቴ (ከጥፋቴ)! ⚪️ ​وَلا يَغرُركُم حُسنُ اِبتِسامي ⚫️ በፈገግታዬ ማማርና ውበት አትታለሉ፤ ⚪️ ​فَقَولي مُضحِكٌ وَالفِعلُ مُبكي ⚫️ ንግግሬ የሚያስቅ ቢሆንም፥ ድርጊቴ ግን የሚያስለቅስ (የሚያስከፋ) ነውና።»

አሰላሙዓለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ 👋 የዐቂደቱ ጠሀዊያ ኪታብ ተጠናቋል ‼️ አልሃምዱሊላህ በጋ ላይ ተጀምሮ የነበረው የኢማም አቡ ጃዓፋር አጠሃዊ የአቂዳ ኪታብ የሆነችው ኪታቡ ዐቂደቱ ጠሀዊያ ተጠናቃለች። በመጀመሪያ አስጀምሮ ላስጨረሰን ጌታ ሹክር እያቀረብን ፤ ጊዜያቸውን ለእኛ በመስጠት ኪታቧን እያዋዙ በተነሱት ርዕሶች ዙሪያ ብዙ ቃኢዳዎችን እያስጨበጡን ለወራት ሲያስቀሩን ለነበሩት ኡስታዛችን ኡስታዝ ዘንጀቢል ላቅ ያለ ምስጋና እያቀረብን፤ ባሳወቁን እያንዳንዱ እውቀት አላህ ታላቅ ምንዳን እንዲፅፍላቸው እንከጅላለን ፣ ኡስታዝ ሲያስቀሩን የሚሉን ነገር አለ " ሁሌም ከፍታን ለመውጣት በማሰብ ብዙዎች ይጀምራሉ ግን በጣም ጥቂቶች ብቻ  ከከፍታው ጫፍ ይደርሳሉ" ይሉናል። ደርሱን በአግባብ ስትከታተሉ የነበራችሁ ተማሪዎች ከደርሱ ጅማሮ አንስቶ እስከ መገባደጃው በፅኑ አላማ እና ብርታት ያጠናቀቃችሁ ትልቅ ዕውቀትን እንደጨበጣችሁ ተስፋ እናደርጋለን ፤ ሙራጃ ማድረጉን አትርሱ። አቂዳን በአግባቡ ማወቅ  በአኺራ ብቻ ሳይሆን ፣ በዱንያ ላይም እንኳን ቢሆን ያለው ጠቀሜታ ላቅ ያለ ነው ፣  አላህ  በሱራ  Adh-Dhariyat (56–58) እንዲህ ይለናል፦
﴿وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ ۝ مَا أُرِيدُ مِنْهُم مِّن رِّزْقٍ وَمَا أُرِيدُ أَن يُطْعِمُونِ ۝ إِنَّ اللَّهَ هُوَ الرَّزَّاقُ ذُو الْقُوَّةِ الْمَتِينُ﴾ ጋኔንንና ሰውንም ሊገዙኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም፡፡ ከነርሱም ምንም ሲሳይ አልፈልግም፡፡ ሊመግቡኝም አልሻም፡፡አላህ እርሱ ሲሳይን ሰጪ የብርቱ ኀይል ባለቤት ነው፡፡
ደርሱን ያጠናቀቃቹ ተማሪዎች አላህ ባወቃችሁት ላይ ይጨምርላችሁ የምትሰሩበት ብሎም ለሌሎች የምታሳውቁበት ያድርጋችሁ። 👉 ኢንሻአላህ online ቂርዓታችን የሚቀጥል ይሆናል 5 ኪሎ ጀማዓ ቂርዓት channel  ይቀላቀሉ ‼️ @fivekjemaa

‹‹በታሪካቸው ውስጥ ለአእምሮ ባለቤቶች በእርግጥ መገሠጫ ነበር፡፡›› (ዩሱፍ 12፡ 111) የሕይወት መመሪያና መርህ የሆነው ቁርኣን፣ አንድ ሦስተኛው ያህል በተለያዩ ታሪኮች የተሞላ ነው። ታሪኩን ከ
‹በታሪካቸው ውስጥ ለአእምሮ ባለቤቶች በእርግጥ መገሠጫ ነበር፡፡›› (ዩሱፍ 12፡ 111) የሕይወት መመሪያና መርህ የሆነው ቁርኣን፣ አንድ ሦስተኛው ያህል በተለያዩ ታሪኮች የተሞላ ነው። ታሪኩን ከተረከልን በኋላ ከትረካው እውቀት እንቀስም ዘንድ ያመላክተናል ‹‹ይህን ሁሉ (የቀደምት) መልእክተኞች ታሪክ በርሱ ልብህን ልናፀና ተረክንልህ።›› (ሁድ 11፡ 120) (አስተዋይ) ልቦና ላለው፣ (ተግሳጽንም ለማድመጥ) ጆሮውን ለከፈተ፣ (እውነትን) ለመሰከረ በዚህ (ታሪክ) ውስጥ ተግሳጽ አለበት::›› (ቃ9: 50:37) 🍂ከትናንት ጥልቀት የተገኙ፣ ዛሬን የሚያበሩ•• 🍂ህይወትን በአዲስ መልክ ማየትን የሚያስችሉ ልዩ ታሪኮች! 💥ከ ዛሬ ጀምሮ ዘውትር ቅዳሜ እና እሁድ ይከታተሉ ~> @aaumsu መልካም ሙሉ ሰው መሆኛ ጊዜ!!@aaumsu

ደርሷል... ነገ ማታ እንገናኝ! ሚሽካት!!! ©aaumsu @fivekjemaa
ደርሷል... ነገ ማታ እንገናኝ! ሚሽካት!!! ©aaumsu @fivekjemaa

ደርሷል... ነገ ማታ እንገናኝ! ሚሽካት!!! @aaumsu
ደርሷል... ነገ ማታ እንገናኝ! ሚሽካት!!! @aaumsu

🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉 ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا
🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉 ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ ﷺ 🌟🌟اللهم صل على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم في العالمين إنك حميد مجيد🌟🌟 ۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦ ➊ መታጠብ ➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች) ➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም ➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ ➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት "ሱረቱል ካህፍን በጁምዓ ቀን መቅራት፤ በሁለቱ ጁምዓዎች መካከል የሚበራ ብርሃን (ኑር) ይሆንልሃል/ ይሆንልሻል።" ይህ ማለት አላህ እስከሚቀጥለው አርብ ድረስ ልባችንን በብርሃን ይሞላዋል፣ ትክክለኛውንና ስህተቱን የምንለይበትን ጥበብ ይሰጠናል ማለት ነው። ➏ በጊዜ መስጂድ መግባት ➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ በውዱ ነብያችን ላይ ሶለዋት ማብዛትንም አንርሳ❤️ اللهم صلِّ وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد وعلى آله وصحبه وسلم تسليماً كثيراً ﷺ 🌟 መልካም ጁምአ🌟 @fivekjemaa

abdul-wadood-haneef-018.mp329.05 MB

"የራበን ፍትሕ እንጂ ዳቦ አይደለም።"- የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ይህ በዘንድሮው አመት ሙስሊም ተማሪዎች ያሳለፉትን በጥቂቱ የሚያስቃኝ ነው። https://www.tiktok.com/@aaumsu/video/7670594379068820744?is_from_webapp=1&sender_device=pc በመግባት ለሁሉም ይደርስ ዘንድ ሪፖስት ያድርጉ። @aaumsu

💭ሚሽካት!! የ ታሪክን ገጾች ስላደመቁ ጊዜያት እና ስብዕናዎች ምንመለከትበት ልዩ መድረክ ✨ ታሪክ•• ታሪክ ትናንትን ለማወቅ፤ ዛሬን ለመረዳትና ለነገ ለማቀድ ያግዛል። ታሪክ ያለው ሕዝብ በአግባቡ
💭ሚሽካት!! የ ታሪክን ገጾች ስላደመቁ ጊዜያት እና ስብዕናዎች ምንመለከትበት ልዩ መድረክ ታሪክ•• ታሪክ ትናንትን ለማወቅ፤ ዛሬን ለመረዳትና ለነገ ለማቀድ ያግዛል። ታሪክ ያለው ሕዝብ በአግባቡ ከተጠቀመበት ታሪክ ይሠራል! ወደፊት መጓዝ የፈለገ መጀመሪያ ወደ ኋላ ተመልሶ ታሪኩን ይፈትሻል:: የአባቶቹንና የአያቶቹን ገድል ሲረዳ በምን ሁናቴ ውስጥ እንዳለፉ ግልጽ ብሎ ይታየዋል። የዛሬው እርሱነቱ የበርካታ ሂደቶች ውጤት መሆኑን ይረዳል፡፡ የአባቶቹንም ስህተት አይደግምም! የነርሱ ጠንካራ ተሞክሮ ኃይል ይሆነዋል። እሴቶቻቸውን ለማስከበር ስለከፈሉት መስዋዕትነት ሲያነብ የርሱ ድርሻ ምን እንደሆነ ይረዳል፡፡ ታሪክ ትናንትን እየነገረን ነገ ወዴት እንደሚሄድ ያመላክተናል፡፡ ትናንትን የማያውቅ ትውልድ ዛሬን እርግጠኛ አይደለም። ስለነገውም ቢሆን ግልጽ እይታ የለውም፡፡ ይላሉ Dr. አህመዲን ጀበል ! إِنَّ ٱللَّهَ لَا يُغَيِّرُ مَا بِقَوْمٍ حَتَّىٰ يُغَيِّرُوا۟ مَا بِأَنفُسِهِمْ ۗ
አላህ በሕዝቦች ዘንድ ያለውን ጸጋ በነፍሶቻቸው ያለውን (ኹኔታ) እስከሚለውጡ ድረስ አይለውጥም፡፡
"ውስጣቸው ያለውን ሁኔታ እስኪለውጡ ድረስ" ተብለናል! እነሆ እኛም ከተለያየ ዘመን ክፍል፣ ውስጣችንን ሊገነቡ ይችላሉ ብለን ያሰብናቸውን ታሪኮች በ ተከታታይ ፕሮግራም ልናቀርብላችሁ ወደድን። 🗓 ቀን: ዘውትር ቅዳሜ እና እሁድ! @aaumsu