ሀገረ ማርያም መሰረተ ተዋሕዶ ሰ/ት/ቤት
الذهاب إلى القناة على Telegram
ይህ የሀገረ ማርያም ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን መሠረተ ተዋሕዶ ሰንበት ት/ት ቤት አባላት መማሪያና መልእክት መጋሪያ ብቻ ይሆን ዘንድ የተዘጋጀ አውታር ነው።
إظهار المزيد944
المشتركون
-124 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
+230 أيام
أرشيف المشاركات
ቅዱስ አምብሮስ፦ "የሃይማኖት ትምህርትን መማር ማለት የሕይወትን መሪ ማግኘት ማለት ነው። ማዕበል በበዛበት የዚህ ዓለም ባሕር ላይ መጻሕፍትና የአባቶች ትምህርት እንደ ኮምፓስ (አቅጣጫ ጠቋሚ) ሆነው ይመሩሃል።"
ተመዝግቦ በመማርና Share በማድረግ ሃይማኖታዊ ግዴታዎን ይወጡ !!!
ቅዱስ አምብሮስ፦ "የሃይማኖት ትምህርትን መማር ማለት የሕይወትን መሪ ማግኘት ማለት ነው። ማዕበል በበዛበት የዚህ ዓለም ባሕር ላይ መጻሕፍትና የአባቶች ትምህርት እንደ ኮምፓስ (አቅጣጫ ጠቋሚ) ሆነው ይመሩሃል።"
Repost from ዲ/ን ወ/አረጋዊ
አስራት ምንድን ነው?
አስራት ማለት ከሰው ገቢ፣ ምርት ወይም ንብረት አስረኛውን (10%) ለእግዚአብሔር መለየት ማለት ነው። "አስራት" የሚለውም ቃል ከ"አስር" የተገኘ ነው።
የአስራት ታሪክ
1. ከሕግ በፊት በአብርሃም ዘመን
አስራት የጀመረው በሙሴ ሕግ አይደለም። ከሙሴ በፊት በብሉይ ኪዳን አባቶች ዘመን ይታያል።
አብርሃም ነገሥታትን ድል ካደረገ በኋላ ከያዘው ምርኮ አስረኛውን ለመልከ ጼዴቅ ሰጠ (ዘፍጥረት 14፥20)።
ይህ የሚያሳየው አስራት ከሕግ በፊትም እንደ ምስጋናና እንደ አምልኮ መቅረቡን ነው።
2. በያዕቆብ ዘመን
ያዕቆብ በቤቴል እግዚአብሔርን ሲማጸን፦
"ከምትሰጠኝ ሁሉ አስረኛውን ለአንተ እሰጣለሁ"
ብሎ ተሳለ (ዘፍጥረት 28፥22)።
ይህም አስራት ከእግዚአብሔር በረከት ጋር የተያያዘ መሆኑን ያሳያል።
3. በሙሴ ሕግ
እግዚአብሔር ለእስራኤል ሕዝብ አስራትን እንዲያቀርቡ አዘዘ።
የአስራት ዓላማዎች፦
ሀ. ለሌዋውያን
ሌዊ ወገን ለቤተ መቅደስ አገልግሎት ተለይቶ ነበር፤ የራሱ የመሬት ርስት ስላልነበረው ሕዝቡ ከአስራታቸው ይደግፉት ነበር። (ዘኍልቍ 18፥21)
ለ. ለቤተ መቅደስ አገልግሎት
የመቅደስ አገልግሎት፣ መሥዋዕት እና ሌሎች ቅዱሳን ሥራዎች በአስራት ይደገፉ ነበር።
ሐ. ለድሆች
በየሦስት ዓመቱ የሚሰበሰብ አስራት ለመጻተኞች፣ ለድሆች፣ ለድሀ አደጎችና ለመበለቶች ይውል ነበር (ዘዳግም 14፥28-29)።
4. በነቢያት ዘመን
ሕዝቡ አስራት መስጠት ሲተው እግዚአብሔር በነቢዩ ሚልክያስ አማካኝነት እንዲህ አለ፦
"ሙሉ አስራቱን ወደ ጎተራ አምጡ" (ሚልክያስ 3፥10)
ይህ የተነገረው ሕዝቡ የቤተ መቅደስን አገልግሎት ችላ ስላለ ነበር።
5. በአዲስ ኪዳን
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስራትን በቀጥታ አልሻረውም፤ ነገር ግን ከአስራት ይልቅ ፍትሕ፣ ምሕረትና እምነት እንዳይረሱ አስተማረ።
"እነዚህን ማድረግ ሳይተዉ ያንንም ማድረግ ይገባችኋል" (ማቴ 23፥23)
በሐዋርያት ዘመን ምዕመናን ከአስረኛ በላይ እንኳ ንብረታቸውን ለችግረኞችና ለቤተ ክርስቲያን ያካፍሉ ነበር (ሐዋ. 4፥32-35)።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ቤተ ክርስቲያኒቱ አስራትን እንደ ቅዱስ ልማድ ትቀበላለች። ምዕመናን ከገቢያቸው አስረኛውን ለቤተ ክርስቲያን፣ ለካህናት አገልግሎት፣ ለድሆች እና ለወንጌል ሥራ እንዲያወጡ ትመክራለች።
ነገር ግን አስራት በፍርሃት ወይም በግዴታ ሳይሆን፣ በፍቅርና በምስጋና መሰጠት አለበት። ቅዱስ ጳውሎስም፦
"እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፤ በኀዘን ወይም በግድ አይደለም፤ እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጥን ይወዳል" (2ኛ ቆሮ. 9፥7)።
የአባቶች ማብራሪያ
የኦርቶዶክስ አባቶች አስራትን እንደ "የምስጋና መጀመሪያ ፍሬ" ይመለከቱታል። ሰው 100% ያለው ሁሉ የእግዚአብሔር ስጦታ መሆኑን በመቀበል 10% በመለየት ለፈጣሪው ምስጋና ያቀርባል።
ስለዚህ በኦርቶዶክስ አስተምህሮ አስራት የገንዘብ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የእምነት፣ የምስጋና እና የታዛዥነት ጉዳይ ነው።
በንስሐ ውስጥ ያላችሁ ራሳችሁን ዝቅ ዝቅ አድርጉ
ይ.ዲ፦
❝እለ ውስተ ንስሐ ሐሎክሙ አትሕቱ ርዕሰክሙ — በንስሐ ውስጥ ያላችሁ ራሳችሁን ዝቅ ዝቅ አድርጉ❞ትርጓሜ፦ ዲያቆኑ «ራሳችሁን ዝቅ ዝቅ አድርጉ» ማለቱ ልቡናችሁን ከትዕቢት ለዩ ማለት ነው፡፡ ይኸውም ዮሐንስ መጥምቅ ትዕቢትን በተራራና በኮረብታ መስሎ ሲናገር፦
❝ተራራውም፣ ኮረብታው ሁሉ ዝቅ ይበል፤ ሰንከልካላውም የቀና ጥርጊያ ይሁን ወጣ ገባ መንገድም ይስተካከል❞— ብሏል (ሉቃ ፫፥፭-፯) ይህም ማለት ተራራ/ኮረብታ የተባለው ትዕቢተኛ ልቡና፤ ሰንከልካላ ወጣ ገባ መንገድ የተባለው ደግሞ የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት የሚጠራጠር ተጠራጣሪ ልብ ነው። ስለዚህ ከጥርጥርና ከትዕቢት፣ ተለይታችሁ በፍጹም ትሕትና ሁናችሁ ካህኑ የሚለውን አድምጡ ለማለት ነው። ካህኑም አያይዞ ለምዕመናኑ፦
❝አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ በንስሐ ውስጥ ወዳሉት ወገኖችህ ምዕመናን ተመልከት እንደ ይቅርታህም ብዛት ይቅር በላቸው፤ እንደ ቸርነህትህ ብዛት በደላቸውን አጥፋላቸው፤ ከክፉ ነገርም ሁሉ ጠብቃቸው፥ ሰውራቸውም፡፡ የቀደመ ሥራቸውን ይቅር ብለህ በሰላም ነፍሳቸውን አድን❞— እያለ ሲጸልይላቸው ልቡናቸው ከትዕቢት የለዩ ሰዎች ሁሉ ጸሎቱ ይደርሳቸዋል፡፡ ጸሎቱ እንዲደርሰው የሚፈልግ ሁሉ ልቡናችሁን ሊያዋርድ ይገባዋል ማለት ነው፤ ጸጋ እግዚአብሔር በትዕቢት አትገኝም። ራስን ዝቅ ዝቅ በማድረግ፥ ጌታዬ ሆይ በአንተ ምህረት እንጂ እንደ ስራዬ ቢሆንማ በመቅደስህ መገኘት ቀርቶ ልጅህ ለመባል ስንኳ ባልተገባኝ ነበር እያሉ ከልብ ራስን ዝቅ ዝቅ በማድረግ ሲሆን ግን ያኔ ትገኛለች።
❝ራሱን ከፍ ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳል፤ ራሱንም የሚዋርድ ይከብራል❞— እንዲል ቅዱስ መጽሐፍ (ሉቃስ ፲፰፥፲፫-፲፰)። ከዚህ በኋላ ዲያቆኑ፣ ካህኑና ሕዝቡ በንባብ «ተንሥኡ ለጸሎት» ፥ «እግዚኦ ተሣሃለነ» ፤ «ሰላም ለኩልክሙ» ፥ «ምስለ መንፈስከ» ይላሉ፡፡ ይህም በተለየ ሁኔታ በንባብ ብቻ መባሉ መንፈስ ቅዱስ ሕብስቱን ለውጦ ሥጋ ወልደ አምላክ አምላክ፥ ወይኑንም ለውጦ ደመ አምላክ አድርጎ በቅዳሴው ጊዜ ምን ሰዓት እንደሚለውጠው አለመታወቁን ያስገነዝበናል፤ ዜማ እንደሚታወቀው የጩኸት ነው ከሩቅ ይሰማል፤ በትሑት ዜማ ወይም በንባብ ከሆነ ግን ጩኸቱ ብዙ አይደለምና በዜማ ጮክ ብሎ ያለመሰማቱ መንፈስ ቅዱስ ሥጋ ወደሙን ሲለውጥ እዚህ ሰዓት ላይ ነው የሚለውጠው ተብሎ አለመታወቁን ያሳስባል። ከዚህ ቀጥሎ ኅብስቱ ተለውጦ ሥጋ ወልደ አምላክ፤ ወይኑም ተለውጦ ደመ ወልደ አምላክ መሆኑን ካህኑ ይመሰክራል፤ እምነቱንም ይገልጣል፡፡ ዲ/ን ኃይለራጉኤል
ሁሉም ካህናት የእግዚአብሔር ላይሆኑ ይችላሉ
ሁሉም ካህናት የእግዚአብሔር ላይሆኑ ይችላሉ በሁሉም ካህናት ግን እግዚአብሔር ይሠራል ።
ሳይገባቸው የተቀበሉ እና ተቀብለውም እንደሚገባቸው የማይኖሩ አሉና።
ከዚህም በላይ ክህነቱን እና ክርስትናን ጭምር የሚያስነቅፋ አሉ።
ካህናት በሚቻላቸው መጠን ለተሰጣቸው ክብር በሚገባ መጠን ለመኖር መትጋት ይኖርባቸዋል ።
ክህነቱን አቅልለው በሚያስቅፋ መልኩ የሚኖሩ ከሆነ ከእግዚአብሔር ቅጣት በሥጋም በነብስም አያመልጡም ።
ምዕመናን ግን ካህናት በእግዚአብሔር እንደሚሾሙ ተረድተው የሥነምግባር ጉድለት ቢኖርባቸውም ክህነቱን እስካላቸው ድረስ ለካህን እንደሚገባ የማክበር ግደታ አለባቸው ።
https://t.me/felege_yohanis
ለሃይማኖት ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ!
የቡሌ ሆራ ፈለገ ዮርዳኖስ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወልደታ ለማርያም ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት፤ ልዩ የክረምት መንፈሳዊ ትምህርት (ስልጠና) አዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል።
📌 የሚሰጡ የትምህርት ዓይነቶች፦
ትምህርተ ሃይማኖት
የቤተ ክርስቲያን ታሪክ
ነገረ ድኅነት
📅 የትምህርት ጊዜ ሰሌዳ፦
የትምህርቱ ቆይታ፦ ከሰኔ 15 እስከ ነሐሴ 30 ቀን
የመማሪያ ቀናት፦ ዘወትር ከሰኞ እስከ ረቡዕ
የመማሪያ ሰዓት፦ ከቀኑ 10:30 - 12:00
ትምህርቱ የሚጀመርበት ቀን፦ ሰኔ 15 ቀን
📍 ቦታ፦ በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ
📝 የምዝገባ መረጃ፦
የምዝገባ ቀን፦ ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 14 ቀን
📞 ለበለጠ መረጃ በነዚህ ስልኮች ይደውሉ፦
0979823772
0706874979
📱 የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ፦
https://t.me/felege_yohanis
"የእግዚአብሔር ቃል ይደርሳችሁ ዘንድ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!"
ስለዚህ ራስሽን ተገቢ ባልሆነ መንገድ ለመሸለምና ለመኳኳል አትጣጣሪ። ጎደሎ የኾነ የእግዚአብሔር ሥራ የለምና፤ ወይም በአንቺ አማካኝነት መስተካከል የሚሻው ግብር የለምና።
በእንተ makeup ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የማቴዎስ ወንጌል ማብራሪያ ክፍል ሁለት ገጽ 123
ከክርስቶስ ጋር አንድ እንደ ሆንሽ አስቢና ከዚህ የማይገባ ነገር ራስሽን አርቂ። ጌታሽ ክርስቶስ በእነዚህ መቀባባቶች ደስ አይሰኝምና፤ ይልቅስ እርሱ የሚፈልገው ሌላ ውበትን ነው - እርሱ እጅግ አብዝቶ የሚሻው የነፍስሽን ውበት ነው። ነቢዩ ደስ ትሰኚበት ዘንድ ያዘዘሽም ይህንን ነው፤ እንዲህ በማለት:- “ንጉሥ ውበትሽን ወዶታልና” (መዝ.44:11)።
ስለዚህ ራስሽን ተገቢ ባልሆነ መንገድ ለመሸለምና ለመኳኳል አትጣጣሪ። ጎደሎ የኾነ የእግዚአብሔር ሥራ የለምና፤ ወይም በአንቺ አማካኝነት መስተካከል የሚሻው ግብር የለምና።
የእግዚአብሔር መልአክ ይቅርና የአንድ ንጉሥ ሐውልትም ተሠርቶ ከቆመ በኋላ ማንም መጥቶ የራሱን ነገር ለመጨመር ቢደፍር ከዚያ በኋላ ከባድ ቅጣት ያገኘዋል እንጂ ደኅና ኾኖ አይኖርም። ሀቅም... ሰው በሠራው ላይ እንዲህ መጨመር አትችዪም። ታዲያ እግዚአብሔር የሠራውን ለማሻሻል ትደፍሪያለሽ? እንዲህ ለማድረግ ስታስቢ አንዳች የእሳት ገሃነም ጥቂትስ እንኳን ትዝ አይልሽም? የነፍስሽን ጥፋት አይታሰብሽምን? በዚህ ምክንያት ቸል ብለሻል፤ ድካምሽን ዅሉ በሥጋሽ ላይ ባክኗል።
ስለ ነፍስ የምንናገረው ለምንድን ነው? ለገዛ ሥጋሽም ቢኾን የሚገኘው አንቺ ካሰብሽው ዅሉ በተቃራኒ ነው። እስኪ ተመልከቺ! መልካ መልካም መኾንን ነው አይደለም የምትፈልጊው? ይህ ግን መልካም መልካም ኾነሽ እንድትታዪ አያደርግሽም። ባልሽን ደስ ማኘት ነው አይደለም የምትፈልጊው? እንደዚህ ማድረግሽ ግን ያሳዝነዋል። ባልሽን ብቻም አይደለም፤ ሌሎች ባዕዳን ሰዎችንም ጭምር አንቺን እንዲንቁሽ ያደርጋቸዋል...
Repost from ዲ/ን ወ/አረጋዊ
በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስ ለምን ዓላማ ወረደ?
፩. ኀይልን ለመስጠት
ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ በሰጣቸው ተስፋ መሠረት በበዓለ ሃምሳ ለደቀዛሙርቱ መንፈስ ቅዱስን ስለላከላቸው፣ ደቀ መዛሙርቱ በመንፈስ ቅዱስ ኀይል ድኩማን የነበሩ ኀያላን፤ ፈሪዎች የነበሩ ደፋሮች ሆነው በራቸውን ዘግተውና ተደብቀው ከነበሩበት ቤት በድፍረት ወጥተው በቤተ መቅደሱ አካባቢ በተለያዩ ሥፍራዎች ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ በይፋ ያለ አንዳች ፍርሃት ማስተማር ጀምረዋል። በዚያ የተሰበሰቡት የአይሁድ ሕዝቦች በሁለት ነገር እጅግ ተደነቁ፣ አንደኛ ሐዋርያት ለእነሱ እንግዳ የሆነ ስለ ክርስቶስ አዲስ ትምህርት ማስተማራቸው ሲሆን፣ ሁለተኛ ደቀ መዛሙርቱ በተለያዩ ቋንቋዎች ሲነጋገሩ ማየታቸውና መስማታቸው ነበር። ፈሪ ልብ የነበራቸው ሐዋርያት ይህንን አልጫውን ዓለም በወንጌል ጨውነት ለማጣፈጥ ጨለማውን ዓለም ወደ ብርሃን ለመለወጥ ከአርያም ልዩ ኀይል ያስፈልጋቸው ስለነበር ጎይልን ሊያለብሳቸው ወርዷል። ጌታችን ሊያርግ ሲል እንዲህ ብሎ ተስፋ ሰጥቷቸው ነበር፦
❝እነሆም አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ አልክላችኋለሁ፣ እናንተ ግን ከላይ ኀይል እስክትለብሉ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ❞— ብሏቸው ስለነበር በዚያ ቃል ኪዳን መሠረት መንፈስ ቅዱስ ኀይል ሰማያዊ ሊያጎናጽፋቸው ወረደላቸው (ሉቃ ፳፬፥፵፱ ፤ የሐዋ ፩፥፰)። ፪. ሐሰተኛውን ዓለም ለመውቀስ ሽፍታው በርባን እንዲፈታላት ጻድቁ ክርስቶስ እንዲሰቀልላት አብዝታ የጮኸችው ሐሰተኛዋ ዓለም መንፈስ ቅዱስና መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ሰው ካልሆነ በስተቀር ደፍሮ ሊወቅሳት የሚችል ኀይል አልነበረም:: ምክንያቱም በውስጧ የሚኖሩ ሐስተኞች ናቸውና:: ለበርባን ነጻነትን፣ ለክርስቶስ ሞትን የደገሰችውን ዓለም መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት አድሮ ወቅሷታል። ጌታችን በቅዱስ ወንጌሉ፦
❝እርሱም መጥቶ ስለኀጢአት ስለጽድቅም ስለፍርድም ዓለምን ይወቅሳል❞ — ብሎ በተናገረው መሠረት መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት አንደበት ይህቺን ግፈኛ ዓለም ወቅሷታል - (ዮሐ ፲፮፥፲፪)። በእውነተኛው ጌታ አለማመን፤ ድል ስለተነሣው ጠላት ስለዲያብሎስ ውድቀት አለማወቅ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቀደመ ክብሩ መመለሱን አለማመን ትልቅ በደል ስለሆነ ይህንኑ በሐዋርያት ላይ አድሮ ግልጥ አድርጎ ለመውቀስ መንፈስ ቅዱስ ወረደ:: ስለዚህ ድንቅ ምሥጢር ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ ሲዘምር፦
❝አውጽኦሙ አፍአ እስከ ቢታንያ እንሥእ አዴሁ ወባረኮሙ ወይቤሎሙ ሰላም ለክሙ አዐርግ ሰማየ ኀበ አቡየ ወእቡክሙ ካዕበ እመጽእ ወእነሥአክሙ እነ እሄሉ ምስሌክሙ እፌኑ ለክሙ ጰራቅሊጦስሃ መንፈስ ጽድቅ — እስክ ቢታንያ አወጣቸው እጁን አንሥቶ ባረካቸው ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው ወደ አባቴ ወደ አባታችሁ ዐርጋለሁ፤ ዳግመኛም እመጣለሁ እወስዳችኋለሁ፤ እኔ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ፤ የእውነት መንፈስ ጰራቅሊጦስንም አልክላችኋለሁ❞ — በማለት ተቀኝቷል፡፡ ፫. ሰዎችን ወደ እውነት ለመምራት ሕይወታችንን ወደ እውነት የሚመራን መንፈስ ቅዱስ ነው፤ ወይም በእውነት ጸንተን ስለእውነት እንድንመስክር የሚያደርገን መንፈስ ቅዱስ ነ
ው። ❝ወይቤሎሙ እፌኑ ለክሙ መንፈሰ ጽድቅ ጸራቅሊጦስሃ ዘይሄሉ ዘልፈ ምስሌክሙ ኢየጎድገክሙ ዕጓለ ማውታ ትኩኑ ዘኢይክል ዓለም ነሢኦቶ — ከእናንተ ጋር የሚኖር የእውነት መንፈስ ጰራቅሊጦስን እልክላችኋለሁ፤ እንደ እጓለ ማውታ አልተዋችሁም❞ ነቢዩ ዳዊት ወደ ጽድቅ ጎዳና ወደ እውነት ቦታ የሚመራ መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ ሲ
ዘምር፦ ❝ወመንፈስከ ቅዱስ ይምርሐኒ በምድረ ጽድቅ — ቅዱስ መንፈስህ ወደ ጽድቅ ምድርይምራኝ❞ — ብሎ እግረ ነፍሳችንን ወደ መንስተ ሰማያት፣ እግረ ልቡናችንን ወደ ወንጌል የሚያቀናልን መንፈስ ቅዱስ ነው! አሁን መንፈስ ቅዱስ ወደ እውነት ይመራል ሲባል ያለፈቃዳችን ይወስዳል ማለት አይደለም፤ ልቡናችን በጎ ሐሳብ እንዲያስብ ያደርገዋል፣ ሐሳብ ያሰበ ልቡና ደግሞ ወደ በጎ ስፍራ ይሄዳል ማለት ነው (መዝ ፻፵፩፥፲) ፤ ወደ እውነት የሚመራን መንፈስ ቅዱስ በመሆኑ ሁላችንም በዚህ መንፈስ ምሪት ልንጓዝ ያስፈልጋል። እውነተኞች ክርስቲያኖች ያለመንፈስ ቅዱስ ቅኝት በራሳቸው ምኞት አንዳችም ነገር አያደርጉም፤ የክርስቲያኖች የሕይወት አቅጣጫ ጠቋሚያቸው መንፈስ ቅዱስ ነው። ሐዋርያው ቅዱስ
ጳውሎስ፦ ❝እናንተ ግን የእግዚአብሔር መንፈስ በእናንተ ቢኖር በመንፈስ እንጂ በሥጋ አይደላችሁም የክርስቶስ መንፈስ ከሌለው ግን የእርሱ ወገን አይደለም፣ ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ ቢሆን ሰውነታችሁ በኀጢአት ምክንያት የሞተ ነው፤ መንፈሳችሁም በጽድቅ ምክንያት ሕያው ነው❞ — በማለት መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ሰው በምድርም ቢኖር ኑሮው ግን ሰማያዊ ነው፤ በሥጋ ቢታይም ሕይወቱ ግን መንፈሳዊ መሆኑን ነግሮናል። ለኀጢአት ሙ መሆን ማለት ኀጢአት አለመሥራት ማለት ነው፣ ለጽድቅ ሕያው መሆን ማለት ደግሞ ለጽድቅ ሥራ መትጋት ማለት ነው (ሮሜ ፰፥፱)። ልጅነታችንን ከምናስመስክርበት ወይም ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅር ከምናሳይበት መንገድ አንዱ በምንኖረው ኑሮ ውስጥ በእግዚአብሔር መንፈስ መመራት መቻላችን ነው፤ ሐዋርያው ቅ
ዱስ ጳውሎስ፦ ❝በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመራ ሁሉ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸው❞ — ሲል ያስረዳናል (ሮሜ ፰፥፲፬)። አባቶቻችን «ጻድቃንን ወደ ገዳም ሰማዕታትን ወደ ደም የሚወስድ መንፈስ ቅዱስ ነው»፡፡ ይላሉ:: ይህ ማለት ጸድቃን በገዳማት ሰማእታት በምስክርነት ጸንተው እንዲኖሩ ኀይል ብርታት የሚሰጥ መንፈስ ቅዱስ ነው ለማለት ነው (ዮሐ ፲፮፥፲፫ ፤ ዮሐ ፳፩፥፲፰)። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሐዋርያት ከዕርገቱ በፊት እንዲህ ሲል ተስፋውን
ነግሯቸው ነበር፦ ❝እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ይመራችኋል የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ ከራሱ አይናገርምና፤ የሚመጣውንም ይነግራችኋል፤ እርሱ ያከብረኛል፤ ለእኔ ካለኝ ወስዶ ይነግራችኋልና❞ — በማለት ሐዋርያት ለእውነትና በእውነት መኖር እንዲችሉ በሥራቸው ሁሉ መንፈስ ቅዱስ እንደማይለያቸው ነግሯቸዋል (ዮሐ ፲፮፥፲፫)። መንፈስ ቅዱስ ኀጢአተኞችን ወደ ንስሐ ይመራል (መዝ ፲፬፥፰)። በክርክር ጊዜም እውነቱን ይገልጣል (ማቴ ፲፥፳ ፤ ዮሐ ፲፬፥፮ ፤ ፩ኛ ቆሮ ፲፪፥፫)። ፬. ስለ እግዚአብሔር ወልድ ለመመስከር ዓለም እግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስን ስላላወቀው ስለ ወልደ እግዚአብሔር በሐዋርያት አድሮ ለመመስከር ተገለጠ:: ስለዚህ አንድ ሰው መንፈስ ቅዱስ ምሥጢሩን ካልገለጠለት በቀር ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ጌትነት ማወቅና መመስከር አይችልም (ዮሐ ፲፭፥፳፮)። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ስለጌታችን ስለኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ ልጅነት፥ ጌትነትና ከሃሊነት መመስከር የሚቻለው በመንፈስ ቅዱስ ኀይል
እንደሆነ ሲናገር፦ ❝ስለዚህ ማንም በእግዚአብሔር መንፈስ ሲናገር ኢየሱስ የተረገመ ነው የሚል እንደሌለ፤ በመንፈስ ቅዱስ ካልኾነ በቀር ኢየሱስ ጌታ ነው ሊል አንድ እንኳን እንዳይችል አስታውቃችኋለሁ❞ — በማለት ያለመንፈስ ቅዱስ ገላጭነት የክርስቶስን ጌትነት መመስከር እንደማይቻል ተናግሯል (፩ኛ ቆሮ ፲፪፥፫)።
Repost from የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
"የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ ፬;፫
እንኳን ለዓመታዊው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በሰላም አደረሳችሁ!
የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በጋራ ጉባኤ በአንድነት ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሚመክሩበት፣ የትውልዱን መጻኢ ጉዞ የሚተልሙበት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለነገው ትውልድ ሊያሻግሩ የሚችሉ ዐውደ ሐሳቦች ለውይይት የሚቀርቡበት ታላቅ በዓል ነው። ይህ በቅዱስ ሲኖዶስ ዕውቅና ተሰጥቶት በየዓመቱ እየተከናወነ የሚገኘው የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ዘንድሮ በሀገራዊ ጉዳይ ምክንያት በመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ደረጃ ጠቅላላ ጉባኤውን በበዓለ ጰራቅሊጦስ ማከናወን ባይችልም በሁሉም አህጉረ ስብከት፣ በየወረዳው እና በየአጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ዕለቱ በደማቅ ሁኔታ "የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ ፬;፫ በሚል መሪ ቃል ተከብሮ ይውላል።
ቅዱስ ጳውሎስ "የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ብቻ አይደለም ያለን ይህንንም የመንፈስ አንድነት እንዴት መጠበቅ እንዳለብን በመንገርም ጭምር ነው እንጂ። ይኸውም በፍጹም የዋሕነት፤ ራሳችሁን ዝቅ አድርጋችሁ፣ እየታገሣችሁ፣ ለወንድሞቻችሁም እሺ እያላችሁ፣ በፍቅር እየተጋችሁና እየተባበራችሁ በማለት ነው። የአንድነታችንንም ዓላማ እንዳንዘነጋ ሲገልጽልን “ለአንዱ ተስፋችሁ እንደመጠራታችሁ” ይለናል። እኛም የ15ኛ ዓመት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ቀንን ስናከብር ከወትሮ በላቀ የመንፈስ አንድነታችንን ለመጠበቅ መትጋት እንዲገባን ይህን የቅዱስ ጳውሎስን ምክር መርሐችን አድርገናል። ከሁል ጊዜው በላይ ዓለምም ሆነ ሀገራችን እየተጓዘችበት ካለው አስፈሪ የጥፋት ጉዞ ትውልዱን መጠበቅ፣ ማዳንና ማሰማራት የሚቻለው የመንፈስ አንድነታችንን ለመጠበቅ ስንተጋ ብቻ ነው።
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ትውልዱን በቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር ለመጠብቅ የመንፈስን አንድነት መርሕ ይዞ የሚጓዝ መዋቅር ነው። ታዲያ ይህንን አንድነታችንን ከውስጥም ከውጭም ፈተናዎች ለመጠበቅ እየታየ ያለውን በጎ ፍሬ ለማስቀጠል ትጋትን ገንዘብ ልናደርግ ይገባናል እንላለን። ምንም እንኳን በበዓለ ጰራቅሊጦስ የዘንድሮውን ዓለም አቀፋዊ ጠቅላላ ጉባኤያችንን ማከናወን ባንችልም በያለንበት መዋቅር ዕለቱን ልንዘክረው ይገባናል። በመጨረሻም የዘንድሮውን ዓለም ዓቀፍዊ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ የሚከናወንበትን ዕለት በቅርቡ የምናሳውቅ መሆኑን እየገለጽን እንኳን ለዓመታዊው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በሰላም አደረሳችሁ እንላለን።
የመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
ግንቦት 22/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
