ar
Feedback
ፈገግታ vibe

ፈገግታ vibe

الذهاب إلى القناة على Telegram

🪐እንኳን ደና መጣችሁ ወደ መርጡ channel🎯እንደምትወዱት🥇 ምንም ጥርጥር የለንም💯 post በምናደርገው ማንኛውም ነገር ለናንተ ትምህርት🤌, ፍቅር ገላጭ♥️❤️‍🩹,እንዲሁም አስቂኝ ነገሮች😊 ደስ እንደምትሰኙ እምነት አለን ከ channelu left🗑️ባለማለት ወዳጅነታችሁን አሳዩን🔐 🙏🫴 share like አደራ እና mute🔇 አታርጉ🙏

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ፈገግታ vibe

تُعد قناة ፈገግታ vibe (@topc_vibe) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 146 969 مشتركاً، محتلاً المرتبة 190 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 176 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 146 969 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 29 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -4 278، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -188، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 0.61‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 0.16‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 892 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 241 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 14.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
🪐እንኳን ደና መጣችሁ ወደ መርጡ channel🎯እንደምትወዱት🥇 ምንም ጥርጥር የለንም💯 post በምናደርገው ማንኛውም ነገር ለናንተ ትምህርት🤌, ፍቅር ገላጭ♥️❤️‍🩹,እንዲሁም አስቂኝ ነገሮች😊 ደስ እንደምትሰኙ እምነት አለን ከ channelu left🗑️ባለማለት ወዳጅነታችሁን አሳዩን🔐 🙏🫴 share like አደራ እና mute🔇 አታርጉ🙏

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 30 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

146 969
المشتركون
-18824 ساعات
-1 1367 أيام
-4 27830 أيام
أرشيف المشاركات
Repost from Pp of Pp ꨄ
ጥሩ ኑሮ ሳይኖርህ ልጅ ባለመዉለድ ለልጅህ ዉለታ ዋልለት!
ጥሩ ኑሮ ሳይኖርህ ልጅ ባለመዉለድ ለልጅህ ዉለታ ዋልለት!

raul_and_hatim_6_paragraphs_each_260730_121744.pdf0.84 KB

ያ እንቅልፋችሁን መስዋት አድርጋችሁ የተፃፃፋችሁት text ምን ላይ ደረሰ ንገሩን እስኪ ምን ላይ ደረሳችሁ

💙   የመኖር አካፋይ የመሞት ሲሶ መንገድ መሃል🌹🔸                           ክፍል 2⃣2⃣ «ሚስትና መሬቴን አለ ይሄ እንከፍ?» የሚል ድምፅ ለመኝታ ቤቱ ቀርቦ ተሰማኝ። ቁጥራቸውን መገመት የሚቸግረኝ ሌሎች ሳቅ ተከተለ። እናቴ ትለምናቸዋለች። የምትለምንበት ድምፅ ሆዴን ረበሸው። መሸነፍ፣ ተስፋ መቁረጥ፣ ረዳት ማጣት…….. ሆድ የሚደበላልቅ ልመና ነው። የእናቴ ልመና ፍርሃቴን አስዋጠኝ። ምን ሊፈጠር እንደሚችል የማስብበት የብስለት ልክም አልነበረኝም ይሆናል። ኪዳንን ከአልጋው ስር ወደየትም ንቅንቅ እንዳይል አስጠንቅቄው በቀስታ እየተንፏቀቅኩ ገርበብ ያለው የመኝታ ቤት በርጋ ደረስኩ። እግሬ የቆመበት ተተክሎ ቀረ። ልሳኔም የተቆለፈ መሰለኝ። ከእናቴ ጋር ተያየን። መሬቱ ላይ በጀርባዋ ወድቃ የለበሰችው ሻማ ቀሚስ እስከደረቷ ተገልቦ አንደኛው ካኪ የለበሰ ሰውዬ በማሸነፍ ስሜት ቀበቶው ተፈትቶ ወደታች ዝቅ ባለ ሱሪው ቂጡ እየታየ እላይዋ ላይ ይፈነጫል። ሌላኛው ደግሞ የመሳሪያውን አፍ ወደ እርሷ አዙሮ ነውር እያየ ሳይሆን ትክክል ነገር ዓይኑ ስር እየሆነ ይመስል እየገለፈጠ ያያቸዋል። ፊታቸው ከእኔ በተቃራኒ አቅጣጫ ስለሆነ አያዩኝም። ሌላ ማንም የለም ሳሎኑ ውስጥ። አባቴ የት ሄዶ ነው እሷ የሚደርስላት አጥታ የተዋረደችው? አትታገልም! አትንቀሳቀስም! አፉ ብቻ ነበር የሚለምነው። እኔን ስታይ እሱንም ተወችው። በሚያሳዝን አስተያየት አየችኝ። ልመና ያለበት አስተያየት። እንዳያት አልፈለገችም! ልመናዋ ዞር እንድልላት ነው።  ይሄኔ ኪዳን ከየት መጣ ሳልለው አጠገቤ ደረሰ። እየሆነ ያለውን እንዳያይ አይኑን ከደንኩት። ይሄኔ ሌላ አንድ ሰው ከውጪ ገባ። ቀና ቢል ስለሚያየኝ ኪዳንን ይዤ በበሩ ተከልዬ ማጮለቅ ቀጠልኩ። ሰውየው ሲገባ እናቴ ያቆመችውን ልመና በለቅሶ ታጅባ ቀጠለች። የሰማት አይመስልም። ቢሰማትም ግድ አልሰጠውም። ይልቅ እንደመቆጣት እያለ « ስንት ነገር እያለብን አንተ እዚህ ወገብህን ታላቅቃለህ? ተነስ ወደዚያ!» ብሎ አምባረቀ። አለቃቸው ነገር ይመስላል። መሳሪያውን ይዞ የቆመው ሰውዬ «መሬቱን ወስደንበታል። ሚስቱንም እንቅመስለት ብለንኮ ነው!» ብሎ አስቀያሚ ሳቅ እየሳቀ ከእናቴ ላይ መነሳት ሲጀምር ሰውየውን በልቤ አመስግኜ ሳልጨርስ እሱም የአጋንንት ሳቅ የመሰለ ቃጭል ማስካካት አስካክቶ «እንዲያ ነው …..» ብሎ ሱሪውን መፍታት ሲጀምር ከእኔ የሚበልጥ እልህ እና መጠቃት ሰውነቴ ውስጥ ነደደ። ወዲያው ከውጪ የሆነ ሰው ተጣራ «ሙሉሰው? ሙሉሰው?» ይሄኔ ሊፈታ የጀመረውን ሱሪ ወደቦታው እየመለሰ በተሸከመው መሳሪያ እነርሱም እንዲወጡ ምልክት አሳይቷቸው ወጣ። መሳሪያ ይዞ በመቆም ሲያጅብ የነበረው ሰውዬ ወዲያው ተከተለው። እናቴ ላይ ሆኖ ሲያሰቃያት የነበረው ግን ቆሞ አዘቅዝቆ እያያት በፀያፍ ንግግር ይዘልፋት ጀመር። እያየኋት እንደሆነ አውቃለች። ፊቷን ወደበሩ አዙራ በስቃይ ታያለች። ከየት በመጣ ጉልበቴ እንደሆነ አላውቅም ኪዳንን ሽክም አድርጌ አልጋው ላይ ወሰድኩት እና በጩኸት እኔ እስክመለስ ንቅንቅ እንዳይል አስጠነቀቅኩት። እየተንሰቀሰቀ በጭንቅላቱ እሺ አለኝ። አልጋው አጠገብ የተቀመጠውን ሳጥን ከፍቼ ከሳጥን ውስጥ አነስ ያለች ቦርሳ አነሳሁ። ጠባብ ዚፕ ኪሱ ውስጥ ያለ ቁልፍ ወስጄ አልጋው እራስጌጋ ያለውን መሳቢያ ከፈትኩ። ከፍቼው ውስጡ ያለውን ሽጉጥ ሳየው ተርበተበትኩ። በሚንቀጠቀጥ እጄ ወጥተው ተበትነው የተቀመጡ ቀለሃዎቹን ሰካክቼ ወደሳሎን ሄድኩ። አንስቼ ሊወጣ የነበረው ሰውዬ ላይ ቀስሬ ስጠጋ እናቴ ከመሬት ብድግ አለች። አልተኮስኩም። ልተኩስ የነበረ ይመስለኛል ግን እጄ እየተንቀጠቀ ያቃተኝ። ሰውየው መርበትበቴን እና ህፃንነቴን አይቶ መሰለኝ ምንም ሳይመስለው በንቀት ወደእኔ ሲመጣ እናቴ ከለለችኝ። ግንድ በሚያክል እጁ ሲገፈትራት ተንገዳግዳ ወደቀች። እጄ መንቀጥቀጡን አቁሞልኝ ልስብ ስል የወደቀችው እናቴ ከየት እንዳገኘችው ያላየሁትን የቡና ዘነዘና አንስታ ጭንቅላቱን ከኋላ መታችው። ሰውየው ተገንድሶ ደሙ እየተንዠቀዠቀ እሱን ዘወር ብላ ሳታይ ዘላ የያዝኩትን ሽጉጥ እየቀማችኝ። «ለእድሜ ልክ የሚበቃሽን ክፋት አይተሻል። ደግሞ ነፍስ አጥፍተሽ ስትቃዢ ልትኖሪ?» ያለችው ለእራሷ እንጂ ለእኔ አይመስልም። የተቀበለችኝን ሽጉጥ ይዛ የተገነደሰው ሰውዬ አጠገብ ዘፍ አለች። ደንዝዛ በድኗ እየተንቀሳቀሰ ነው የሚመስለው። ሰውየው ደሙ መስመር እየሰራ ወደበሩ ይፈሳል። አይንቀሳቀስም። እሮጬ ወደ ውጪ የወጣሁት አባቴን ፍለጋ መሰለኝ። መሬቱ ላይ ተዘርሮ ያገኘሁት። እናቴን የአባቴ ሬሳ ላይ ትቻት የፈረጠጥኩት <እንዳትንቀሳቀስ> ያልኩት ኪዳን ፈርቶ ወደሳሎን ቢመጣ የወደቀውን ሰውዬ አይቶ ይደነግጣል ብዬ ነው። ካስቀመጥኩት ቦታ አልተነሳም። የሄድኩት እሱን ልጠብቀው ነበር። አልጋው ላይ አስጨንቄ አቅፌው ስወዘወዝ ምን ያህል ደቂቃዎች እንዳለፉ አላውቅም። ብቻ ወተት እንደሚንጥ ሰው ከፊት ወደኋላ ስናጥ የእናቴ ወንድም እያለቀሰ ገብቶ ኪዳንን ከጀርባ እኔን ከፊት አፋፍሶ ተሸክሞን ወጣ  ……… እዚህ ድረስ ያለው ምስል ምንም ብዥ ሳይል ነው ያስታወስኩት የሚቀጥለው ግን ብዥታ አለው አጎቴ እንደተሸከመን «ወየው ወንድሜን!» እያለ ድምፅ አውጥቶ እያለቀሰ የሆነ መንገድ የሄድን ይመስለኛል። ላስታውሰው ስሞክር ይጠፋብኛል። እዛው የመኝታ ቤት ውስጥ ቆሻሻ ተሞልቶ የተቀመጠ ማዳበሪያ ላይ ጭብጥ ብዬ ተቀምጫለሁ። «እያስጨነቅሽኝ እኮ ነው። ምንድነው ያስታወስሽው? ሰውነትሽኮ ያንቺ አይደለም!» ይለኛል ጎንጥ። ከደቂቃዎች በኋላ እሩጫ እና እርምጃ እየደባለቅኩ እናቴጋ ደረስኩ እና ተጠመጠምኩባት። ገባት! እሪሪሪ ብላ ማልቀስ ጀመረች። ስላስታወስኩ  «ምንአልኩህ አምላኬ? ለልጄ አዲስ ህይወት ሰጠህልኝ ብዬ አመስግኜ ሳልጨርስ?» እያለች አምላኳን መውቀስ ጀመረች። የሚሰማኝን ስሜት መለየት ከበደኝ። ከነበሩኝ ጥሩ ቀኖች ተለይቶ አስፈሪ ቅዠት የመሰለ የህይወቴን ክስተት ማስታወስ ሊያሳብደኝ አልነበር የሚገባው? ቁጣ፤ ንዴት፣ ጥላቻ ፣ ፍርሃት ፣ ሀዘን ……. አልነበር ሊሰማኝ የሚገባው? የሚሰማኝ የሆነ ቅዝቅዝ ያለ ፀጥተኛ ስሜት ነው። «ከእናቶች ሁሉ በላይ እናት ነሽ!!» አልኳት እናቴን እንዳቀፍኳት ብዙ ከቆየሁ በኋላ። አመሻሽ ለእራት ስንሰበሰብ ማስታወስ የቻልኩት ያቺን ቀን ብቻ እንደሆነ ነገርኳቸው። የነገርኳቸው የሆነ አስደንጋጭ ነገር ይመስል ገበታውን የከበበው ሁሉ ረጭ አለ። አጎቴ ሊጎርስ የጠቀለለውን እንጀራ የመወርወር ያህል ትሪው ላይ ጣለው። «መቼም ከዚህ የባሰ የስቃይ ቀን አለ አትሉኝማ? ምንድነው?» ብዬ ስጮህ «እንደዛ አይደለም። ለሁላችንም ከባድ የጨለማ ቀን እሱ ነበር። እንደው …… » እያለ ፊደሎቹን አፉ ውስጥ ያውደለድላቸዋል። ከብዙ ንትርክ በኋላ የተፈጠረውን ነገሩኝ።                 ........ ይቀጥላል ........ ✍ ፀሀፊ ሜሪ ፈለቀ ክፍል 2⃣3⃣ ከ 1⃣5⃣0⃣ Vote♥ በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍ሼር ማድረግ አይርሱ።       ‌‌‌‌‌ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!

💙   የመኖር አካፋይ የመሞት ሲሶ መንገድ መሃል🌹🔸                           ክፍል 2⃣2⃣ «ሚስትና መሬቴን አለ ይሄ እንከፍ?» የሚል ድምፅ ለመኝታ ቤቱ ቀርቦ ተሰማኝ። ቁጥራቸውን መገመት የሚቸግረኝ ሌሎች ሳቅ ተከተለ። እናቴ ትለምናቸዋለች። የምትለምንበት ድምፅ ሆዴን ረበሸው። መሸነፍ፣ ተስፋ መቁረጥ፣ ረዳት ማጣት…….. ሆድ የሚደበላልቅ ልመና ነው። የእናቴ ልመና ፍርሃቴን አስዋጠኝ። ምን ሊፈጠር እንደሚችል የማስብበት የብስለት ልክም አልነበረኝም ይሆናል። ኪዳንን ከአልጋው ስር ወደየትም ንቅንቅ እንዳይል አስጠንቅቄው በቀስታ እየተንፏቀቅኩ ገርበብ ያለው የመኝታ ቤት በርጋ ደረስኩ። እግሬ የቆመበት ተተክሎ ቀረ። ልሳኔም የተቆለፈ መሰለኝ። ከእናቴ ጋር ተያየን። መሬቱ ላይ በጀርባዋ ወድቃ የለበሰችው ሻማ ቀሚስ እስከደረቷ ተገልቦ አንደኛው ካኪ የለበሰ ሰውዬ በማሸነፍ ስሜት ቀበቶው ተፈትቶ ወደታች ዝቅ ባለ ሱሪው ቂጡ እየታየ እላይዋ ላይ ይፈነጫል። ሌላኛው ደግሞ የመሳሪያውን አፍ ወደ እርሷ አዙሮ ነውር እያየ ሳይሆን ትክክል ነገር ዓይኑ ስር እየሆነ ይመስል እየገለፈጠ ያያቸዋል። ፊታቸው ከእኔ በተቃራኒ አቅጣጫ ስለሆነ አያዩኝም። ሌላ ማንም የለም ሳሎኑ ውስጥ። አባቴ የት ሄዶ ነው እሷ የሚደርስላት አጥታ የተዋረደችው? አትታገልም! አትንቀሳቀስም! አፉ ብቻ ነበር የሚለምነው። እኔን ስታይ እሱንም ተወችው። በሚያሳዝን አስተያየት አየችኝ። ልመና ያለበት አስተያየት። እንዳያት አልፈለገችም! ልመናዋ ዞር እንድልላት ነው።  ይሄኔ ኪዳን ከየት መጣ ሳልለው አጠገቤ ደረሰ። እየሆነ ያለውን እንዳያይ አይኑን ከደንኩት። ይሄኔ ሌላ አንድ ሰው ከውጪ ገባ። ቀና ቢል ስለሚያየኝ ኪዳንን ይዤ በበሩ ተከልዬ ማጮለቅ ቀጠልኩ። ሰውየው ሲገባ እናቴ ያቆመችውን ልመና በለቅሶ ታጅባ ቀጠለች። የሰማት አይመስልም። ቢሰማትም ግድ አልሰጠውም። ይልቅ እንደመቆጣት እያለ « ስንት ነገር እያለብን አንተ እዚህ ወገብህን ታላቅቃለህ? ተነስ ወደዚያ!» ብሎ አምባረቀ። አለቃቸው ነገር ይመስላል። መሳሪያውን ይዞ የቆመው ሰውዬ «መሬቱን ወስደንበታል። ሚስቱንም እንቅመስለት ብለንኮ ነው!» ብሎ አስቀያሚ ሳቅ እየሳቀ ከእናቴ ላይ መነሳት ሲጀምር ሰውየውን በልቤ አመስግኜ ሳልጨርስ እሱም የአጋንንት ሳቅ የመሰለ ቃጭል ማስካካት አስካክቶ «እንዲያ ነው …..» ብሎ ሱሪውን መፍታት ሲጀምር ከእኔ የሚበልጥ እልህ እና መጠቃት ሰውነቴ ውስጥ ነደደ። ወዲያው ከውጪ የሆነ ሰው ተጣራ «ሙሉሰው? ሙሉሰው?» ይሄኔ ሊፈታ የጀመረውን ሱሪ ወደቦታው እየመለሰ በተሸከመው መሳሪያ እነርሱም እንዲወጡ ምልክት አሳይቷቸው ወጣ። መሳሪያ ይዞ በመቆም ሲያጅብ የነበረው ሰውዬ ወዲያው ተከተለው። እናቴ ላይ ሆኖ ሲያሰቃያት የነበረው ግን ቆሞ አዘቅዝቆ እያያት በፀያፍ ንግግር ይዘልፋት ጀመር። እያየኋት እንደሆነ አውቃለች። ፊቷን ወደበሩ አዙራ በስቃይ ታያለች። ከየት በመጣ ጉልበቴ እንደሆነ አላውቅም ኪዳንን ሽክም አድርጌ አልጋው ላይ ወሰድኩት እና በጩኸት እኔ እስክመለስ ንቅንቅ እንዳይል አስጠነቀቅኩት። እየተንሰቀሰቀ በጭንቅላቱ እሺ አለኝ። አልጋው አጠገብ የተቀመጠውን ሳጥን ከፍቼ ከሳጥን ውስጥ አነስ ያለች ቦርሳ አነሳሁ። ጠባብ ዚፕ ኪሱ ውስጥ ያለ ቁልፍ ወስጄ አልጋው እራስጌጋ ያለውን መሳቢያ ከፈትኩ። ከፍቼው ውስጡ ያለውን ሽጉጥ ሳየው ተርበተበትኩ። በሚንቀጠቀጥ እጄ ወጥተው ተበትነው የተቀመጡ ቀለሃዎቹን ሰካክቼ ወደሳሎን ሄድኩ። አንስቼ ሊወጣ የነበረው ሰውዬ ላይ ቀስሬ ስጠጋ እናቴ ከመሬት ብድግ አለች። አልተኮስኩም። ልተኩስ የነበረ ይመስለኛል ግን እጄ እየተንቀጠቀ ያቃተኝ። ሰውየው መርበትበቴን እና ህፃንነቴን አይቶ መሰለኝ ምንም ሳይመስለው በንቀት ወደእኔ ሲመጣ እናቴ ከለለችኝ። ግንድ በሚያክል እጁ ሲገፈትራት ተንገዳግዳ ወደቀች። እጄ መንቀጥቀጡን አቁሞልኝ ልስብ ስል የወደቀችው እናቴ ከየት እንዳገኘችው ያላየሁትን የቡና ዘነዘና አንስታ ጭንቅላቱን ከኋላ መታችው። ሰውየው ተገንድሶ ደሙ እየተንዠቀዠቀ እሱን ዘወር ብላ ሳታይ ዘላ የያዝኩትን ሽጉጥ እየቀማችኝ። «ለእድሜ ልክ የሚበቃሽን ክፋት አይተሻል። ደግሞ ነፍስ አጥፍተሽ ስትቃዢ ልትኖሪ?» ያለችው ለእራሷ እንጂ ለእኔ አይመስልም። የተቀበለችኝን ሽጉጥ ይዛ የተገነደሰው ሰውዬ አጠገብ ዘፍ አለች። ደንዝዛ በድኗ እየተንቀሳቀሰ ነው የሚመስለው። ሰውየው ደሙ መስመር እየሰራ ወደበሩ ይፈሳል። አይንቀሳቀስም። እሮጬ ወደ ውጪ የወጣሁት አባቴን ፍለጋ መሰለኝ። መሬቱ ላይ ተዘርሮ ያገኘሁት። እናቴን የአባቴ ሬሳ ላይ ትቻት የፈረጠጥኩት <እንዳትንቀሳቀስ> ያልኩት ኪዳን ፈርቶ ወደሳሎን ቢመጣ የወደቀውን ሰውዬ አይቶ ይደነግጣል ብዬ ነው። ካስቀመጥኩት ቦታ አልተነሳም። የሄድኩት እሱን ልጠብቀው ነበር። አልጋው ላይ አስጨንቄ አቅፌው ስወዘወዝ ምን ያህል ደቂቃዎች እንዳለፉ አላውቅም። ብቻ ወተት እንደሚንጥ ሰው ከፊት ወደኋላ ስናጥ የእናቴ ወንድም እያለቀሰ ገብቶ ኪዳንን ከጀርባ እኔን ከፊት አፋፍሶ ተሸክሞን ወጣ  ……… እዚህ ድረስ ያለው ምስል ምንም ብዥ ሳይል ነው ያስታወስኩት የሚቀጥለው ግን ብዥታ አለው አጎቴ እንደተሸከመን «ወየው ወንድሜን!» እያለ ድምፅ አውጥቶ እያለቀሰ የሆነ መንገድ የሄድን ይመስለኛል። ላስታውሰው ስሞክር ይጠፋብኛል። እዛው የመኝታ ቤት ውስጥ ቆሻሻ ተሞልቶ የተቀመጠ ማዳበሪያ ላይ ጭብጥ ብዬ ተቀምጫለሁ። «እያስጨነቅሽኝ እኮ ነው። ምንድነው ያስታወስሽው? ሰውነትሽኮ ያንቺ አይደለም!» ይለኛል ጎንጥ። ከደቂቃዎች በኋላ እሩጫ እና እርምጃ እየደባለቅኩ እናቴጋ ደረስኩ እና ተጠመጠምኩባት። ገባት! እሪሪሪ ብላ ማልቀስ ጀመረች። ስላስታወስኩ  «ምንአልኩህ አምላኬ? ለልጄ አዲስ ህይወት ሰጠህልኝ ብዬ አመስግኜ ሳልጨርስ?» እያለች አምላኳን መውቀስ ጀመረች። የሚሰማኝን ስሜት መለየት ከበደኝ። ከነበሩኝ ጥሩ ቀኖች ተለይቶ አስፈሪ ቅዠት የመሰለ የህይወቴን ክስተት ማስታወስ ሊያሳብደኝ አልነበር የሚገባው? ቁጣ፤ ንዴት፣ ጥላቻ ፣ ፍርሃት ፣ ሀዘን ……. አልነበር ሊሰማኝ የሚገባው? የሚሰማኝ የሆነ ቅዝቅዝ ያለ ፀጥተኛ ስሜት ነው። «ከእናቶች ሁሉ በላይ እናት ነሽ!!» አልኳት እናቴን እንዳቀፍኳት ብዙ ከቆየሁ በኋላ። አመሻሽ ለእራት ስንሰበሰብ ማስታወስ የቻልኩት ያቺን ቀን ብቻ እንደሆነ ነገርኳቸው። የነገርኳቸው የሆነ አስደንጋጭ ነገር ይመስል ገበታውን የከበበው ሁሉ ረጭ አለ። አጎቴ ሊጎርስ የጠቀለለውን እንጀራ የመወርወር ያህል ትሪው ላይ ጣለው። «መቼም ከዚህ የባሰ የስቃይ ቀን አለ አትሉኝማ? ምንድነው?» ብዬ ስጮህ «እንደዛ አይደለም። ለሁላችንም ከባድ የጨለማ ቀን እሱ ነበር። እንደው …… » እያለ ፊደሎቹን አፉ ውስጥ ያውደለድላቸዋል። ከብዙ ንትርክ በኋላ የተፈጠረውን ነገሩኝ።                 ........ ይቀጥላል ........ ✍ ፀሀፊ ሜሪ ፈለቀ ክፍል 2⃣3⃣ ከ 1⃣5⃣0⃣ Vote♥ በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍ሼር ማድረግ አይርሱ።       ‌‌‌‌‌ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!

💙   የመኖር አካፋይ የመሞት ሲሶ መንገድ መሃል🌹🔸                           ክፍል 2⃣3⃣ እንደዚያ ደም ያቃባቸው ፀብ ለዘመናት የከረመ የጎሳ ፀብ ነበር። ለዘመናት ያንተ ጎሳ ገላመጠኝ ፣ ያንተ ጎሳ ድንበሬን አልፎ ሽንቱን ሸና ዓይነት ገለባ ሰበብ እየመዘዙ ሲጣሉ ነበር የኖሩት። የአባቴ ዘመን ከፀቡ ሁሉ የከፋው ነበር። ፀቡ ፖለቲካዊ ይዘት እንዲኖረው ተደረገ። የእነዛ ወገን በቁጥር የምንበልጠው እኛ ብንሆንም ሰፊ ለም መሬት የያዙት እነዛ (የአባቴ ወገኖች) በመሆናቸው የመሬት ይገባኛል ነጠላ ጥያቄ ይዞ ነበር የተነሳው። ሲቀጥል ገበያውን የኛ ሰዎች ይቆጣጠሩት ፣ ሲቀጣጠል በማእከላዊ ደረጃ በአብላጫው ስልጣን ላይ ያሉት  የአባቴ ወገኖች መሆናቸው ሌላ ዘመናዊ የመሰለ የፀብ ድፍድፍ ጋገረ። ፀቡ በከረረ ቁጥር ከላይ ወታደር ይመጣል። ለቀናት ጋብ ይላል። ደግሞ ተመልሶ ይጋጋላል። አባቴ ነው አሉ የእኛን ጎሳ የሚመራው። አጓጉል ጉልበት መለካካት። የእኔ እበልጣለሁ ፉክክሩ ጦዞ ከተማ እስከማቃጠል ዘለቀ። የመጨረሻው ፀባቸው አባቴ ህይወቱን የገበረበት ነው። ራሴን እስክፈራው ድረስ ሰውነቴ ውስጥ የሞቀ ደም እንዲሮጥ ያደረገው መጨረሻው ነው። የእነዛ ጎሳዎች ሽማግሌ ላኩ። ከዚህም ወገን ሽማግሌ ተቀመጠ። ታረቁ!! የተበደልኩ ዓይነት ስሜት ተሰማኝ። እነርሱ ተጣሉ ከዛ ታረቁ። እኔስ በአስራ ሶስት ዓመቴ አባቴ ሲሞት እናቴ ስትደፈር ያየሁት እኔስ? እኔን ይቅርታ ጠይቀውኛል? እናቴስ? በአንድ ቀን ባሏንም ክብሯንም ያጣችው እናቴስ? ስትደፈር ያየቻትን ልጇን ዓይን እያዩ መኖር ስቃይ ሆኖባት መኖሪያዋን ጥላ የጠፋችው እናቴስ? በቃ! እነሱ እንደቀልድ ታረቁ? ማንም ላጠፋው ቅጣቱን ሳይቀበል ታረቁ! በሰላም ኖሩ! ተጋቡ! ተዋለዱ! የሚባለው የሰው ነፍስ እንዴት ሲናቅ ነው? እኔ እና የዛን ቀን የህይወት ሚዛናችንን የሳትን እኩዮቼስ? ንዴቴ ይንቀለቀል ጀመር። ከነቃሁ ጀምሮ ይሄን ስሜት አላውቀውም! እናቴ ትለምነኝ ጀመር። አጎቴ የፈራው ነገር የደረሰ ዓይነት ተሳቆ ሲያየኝ ቆይቶ ያኔም ልክ እነሱ ታረቁ ተብሎ በሰላም መኖር ሲጀምሩ እንዲህ መሆኔን እና ከዛ በኋላ ህፃንዋ ሜላት ድራሽዋ ጠፍቶ አስፈሪዋ ሜላት ማደግ መጀመሯን ነገረኝ።           ………………. አልጨረስንም ……….. ማሳሰቢያ እና ማሳወቂያ! እያንዳንዱን ኮመንታችሁን እንደማነብ የማታውቁ ካላችሁ 1000 ኮመንት ቢኖርም አነበዋለሁ። አብዛናዎቻችሁ ዘገየ ብላችሁ ንጭንጭ ማለታችሁን ተከትሎ። (እርግጥ በሰዓቱ ለምን አልተለቀቀም! ወጥ ሰዓት አበጂ፣ ምንድነው ስራ የምታስፈቺን ……. ዓይነት ሁሉ አለውኮ) ለማታውቁ ተፅፎ የተቀመጠ አይደለም የምለጥፍላችሁ። በየቀኑ ነው የምፅፍላችሁ! አንድ እና ሁለት ሰዓት ተቀምጬ በየቀኑ ለመፃፍ እንደቲቪ ፕሮግራም ወጥ የሆነ ሰዓት ማበጀት ከባድ ነው። ቲቪዎች እንጀራቸው ነው። እኔ እንጀራዬን ስጋግር ውዬ ነው በተጨማሪ የምጽፍላችሁ። እና ቁጣችሁን በረድ አድርጉት!! በተቻለኝ መጠን በቀን አንዴ እየለጠፍኩላችሁ እቀጥላለሁ። ከቻልኩ ጠዋት ጠዋት አደርገዋለሁ። ቃል ግን አልገባም!!                 ........ ይቀጥላል ........ ✍ ፀሀፊ ሜሪ ፈለቀ ክፍል 2⃣ከ 1⃣5⃣0⃣ Vote♥ በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍ሼር ማድረግ አይርሱ።       ‌‌‌‌‌ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!

Kefel 23

አብረናቹ አመሸን አብራችሁን ስለነበራቹ እናመሰግናለን ..       መልካም mesht🙏

የቱንም ያክል ልቤ ቢሰበር ግርግዳ ተደግፌ በ slow motion እየተንሸራተትኩ አሎርድም😝

ፈጣሪዬ 20 ሚሊየን ብር እና ጤናዬን ብቻ ስጠኝ ቅንጦት ኑሮ አልፈልግም😁 #አሜን በሉ

አንዳንድ ሰዎችን ግን ... 🪨    ╰🤨︿     ,︿)      〈 በዚ ነበር ማለት

💙   የመኖር አካፋይ የመሞት ሲሶ መንገድ መሃል🌹🔸                           ክፍል 2⃣1⃣ ከተቀመጥኩበት ሳልነሳ ለደቂቃዎች ቆየሁ። ምን ያህሉን እንዳስታወስኩ ባላውቅም ደጁን እያየሁት ምስሎቹ ጭንቅላቴ ውስጥ ቅርፅ እየሰሩ ተደረደሩ። ከቤት ተንደርድሬ ስወጣ በዛ ያሉ መሳሪያ የታጠቁ ወንዶች በድል አድራጊነት እየተወጣጠሩ ጊቢያችንን አልፈው እየወጡ፣ የመጨረሻው ሰውዬ አባቴ በወደቀበት ተራምዶት ሲያልፍ ፣ ዘልዬ አጠገቡ ስደርስ የቱጋ እንደተመታ እንኳን እንዳይለይ ሆኖ ልብሱ በደም ርሶ በእጁ የያዛትን የሲጋራ መለኮሻ መጨበጥ አቅቶት እጁ ሲዝል፣ እሪሪሪ ብዬ ስጮህ  እንኳን መንደርተኛው ባለመሳሪያዎቹን ፈርቶ ስለተሸሸገ ብቅ ያለልኝ ጠፍቶ ባለመሳሪያዎቹ ተመልሰው ቢደፉኝ እንኳን ግድ ሳይለኝ ድምፄ እስኪዛጋ ስጮህ እና ስሳደብ ……… የጎረቤታችን ቤት በእሳት ተያይዞ እየነደደ የእነርሱ ጩኸት ከእኔ ቢብስም ሊረዳቸው ብቅ ያለ አልነበረም። እናቴ እግሯንም ቅስሟንም እየጎተተች ከቤት ውስጥ ብቅ ስትል አባቴ ነፍሱ ወጥታ ነበር። አላለቀሰችኝም። አጠገቡ መሬቱ ላይ ቁጭ ብላ በደም የራሰ ደረቱ ላይ ተኛች። ጩኸቴን አቁሜ አየኋት። አታወራም ፣ አታለቅስም፣ ምንም ስሜት አይታይባትም። ከአባቴ ፊት ይልቅ የሞተ የሚመስለው የእርሷ ፊት ነበር። ብርግግ ብዬ ተነስቼ ወደ ቤት ውስጥ ሮጥኩ። በቃ እዚህ ድረስ ብቻ ነበር ለጊዜው የታየኝ። ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ሀረግ ወደወረረው ቤት ውስጥ ገባሁ። ደጁ ላይ የበቀሉት አረሞች እሾህ ያላቸው ስለነበሩበት ልብሴን እየያዘኝ ነበር ያለፍኩት። ጎንጥ አንዴ ፊት ፊቴን አንዴ መንገድ መንገዱን እያየ በዝምታ ይከተለኛል። ቤቱ ውስጥ ሳሎን አሮጌ አግዳሚ ወንበር እና የተበታተኑ ቆሻሻዎች አሉ። እንደገመትኩት አንዳንዱ ሰፈርተኛ ቆሻሻውን እያመጣ እዚህ ይጥላል። በቆሻሻ እና በዓይነምድር የሞሉትን ክፍሎች እየዞርኩ ግማቱ እንኳን አልታወቀኝም። ያ ቤት ያደግኩበት ልጅነቴ መሆን አለበት። ነገር ግን አንድም ከልጅነቴ ጋር የተያያዘ ትውስታ አልመጣልኝም። የዛን ቀን የሆነው ግን አንድ በአንድ የአሁን ያህል ሰውነቴን እስኪወረኝ ታወሰኝ። ጭንቅላቴ የፈለገውን መርጦ አንዲት ክስተት ብቻ አስታውሶ ነው ወይስ ቦታው ላይ ስገኝ ሌሎቹንም ትውስታዎቼን አገኛቸዋለሁ? አልገባኝም! ከሆነም ለምን ልጅነቴን አላስታወስኩም? ዶክተር እንዳለኝ አስፈሪ ገጠመኞቼን ከደበቀበት እያወጣ ሊሆን ይችላል ……. ጭንቅላቴ ራሱ ክፋቱ እንጂ ወይ ሙሉውን ባያስታውሰኝ አልያም እናቴ አውርታ የማትጠግበውን ደጉንም ልጅነቴን ቢያስታውሰኝ ምን ነበረበት? የዛን ቀን ከሆነው ውስጥ ያላስታወስኩት ይኑር አይኑር የማረጋግጥበት ምንም ማመሳከሪያ የለኝም። ያስታወስኳቸው ምስሎች ግን የጎደለ የሚመስል ትዕይንት የላቸውም። አባቴ እና እናቴ ሲጨቃጨቁ ሌላኛው ክፍል ከኪዳን ጋር ሆነን እንሰማቸዋለን። እናቴ አባቴ ላይ ትጮሃለች። «እኔ የምልህን አንዴ ሰምተኸኝ ቢሆን ይሄ ሁሉ አይመጣም!! ያንተ ፉከራ ዛሬ ከምን እንደሚያድንህ እናያለን! እሺ ልጆቼን ምኔ ውስጥ ልደብቃቸው? ሄዳችሁ ባትተነኩሷቸው ዛሬ አሳቻ ሰዓት ጠብቀው መንደራችንን ባልወረሯት ፤ እሺ አሁን ምንድነው የምሆነው?» በበሩ አጮልቄ አያቸዋለሁ። እሷ ወገቧን ይዛ እየተንጎራደደች ነው። እሱ ትልቅዬ መሳሪያ ወደበሩ አነጣጥሮ መንደራችንን ወረሯት የተባሉትን ሰዎች በሩን አልፈው ቢገቡ ሊቀልባቸው ይመስል ይጠብቃል። እናቴ አታቆምም። «እናንተ የእነሱን መንደር ሄዳችሁ አቃጥላችሁ <ጉሮ ወሸባዬ> እያላችሁ ስትመለሱ እጃቸውን አጣጥፈው የሚቀመጡ ነበር የመሰላችሁ?» «አንቺ ብዙ የማይገባሽ ነገር አለ አስካል! የአያት የቅድመአያቴን መሬት ካልፈነጨሁበት ሲሉ እኔስ ኑና በላዬ ዘብጡ ብዬ ዘንባባ አንጥፌ እንድቀበላቸው ነው ምኞትሽ?» እየጮኸ ነው እሱም የሚመልስላት። ከውጪ የብዙ ወንዶች ዘፈን ይሁን ፉከራ ያልለየለት ድምፅ እየቀረበ እየቀረበ ይሰማል። በመሃል የሚያወሩት በትክክል ባይሰማም ጮክ ያሉ ድምፆች ትእዛዝ ሲያስተላልፉ ይሰማል። ደግሞ ያጨበጭባሉ። ደግሞ አንዴ ሆ ብለው የደስታ ጩኸት ይጮሃሉ። እናቴ እሮጣ መጥታ ከሽቦ አልጋው ስር እንድንገባ ታደርገናለች። «ምንም ቢፈጠር እንዳትወጡ! ምንም ብትፈሩ ድምፅ እንዳታሰሙ!» እያለችን መሬቱ ላይ በደረቷ ተደፍታ እያየችን እጇ ይንቀጠቀጣል። ኪዳን ማልቀስ ጀምሯል። ጆሮዎቹን በእጄ ደፍኜ ይዤለት እሹሩሩ እንደማለት እየወዘወዝኩት ወደራሴ አጣብቄ ያዝኩት። ከውጪ የሚሰማው ሁከት መስኮታችን ጋር ደረሰ። እናቴ የመላእክትን ሁሉ ስም በሹክሹክታ እየጠራች ትፀልያለች። አባቴ እኛ ወዳለንበት ብቅ ብሎ «አንቺም ከእነርሱ ጋር ተሸሸጊ! እነርሱ የሚፈልጉት እኔን ነው!» አላት በትእዛዝ «ያንተ ሚስትኮ ነኝ አይምሩኝም! እኔን ሲፈልጉ ልጆቼን ካገኟቸው ይገድሉብኛል። እኔን ካገኙኝ ግን ልጆቼን አይፈልጓቸውም በፍፁም አልሸሸግም! የመጣ ይምጣ!» አለች እንጂ ሰውነቷ እየራደ ነው። ላቤ ከጀርባዬ ወደቂጤ ሲወርድ ይሰማኛል። የልቤ ትርታ ሁከተኞቹ ድረስ የሚሰማ ነው የሚመስለው። ብዙም አልቆየም! ድብልቅልቅ ያለ ጩኸት ፣ የበሩ መገንጠል፣ ተኩስ ድብልቅልቁ ወጣ። ሽንቴን እላዬ ላይ ለቅቄ እንዲያ ሰውነቴ የእኔ እስከማይመስለኝ በድኖብኝ ኪዳንን አልለቀቅኩትም። ድንጋጤው በዝቶበት ነው መሰለኝ ትንፋሽ እንደሌለው ሰው ዝም አለ። እናቴ ከአልጋው አጠገብ ተነስታለች ግን አትታየኝም። ፍርሃቴ ሽባ ስላደረገኝ የመነቃነቅም ድፍረቱ አልነበረኝም። ሳሎኑ ውስጥ የተፈጠረው ምን እንደሆነ ባላውቅም ድብልቅልቁ የወጣ ትዕይንት እንደሆነ ከድምፆቹ ያስታውቃል። ከሳሎን ድምፁ እየቀለለ የተወሰኑ ሰዎች ድምፅ ብቻ መሰማት ሲጀምር የእናቴ እሪታ ተከተለ። ነፍስ ከስጋዬ የተላቀቀች መሰለኝ። የሞት ሞቴን ለማየት ስሞክር መኝታ ቤቱ ውስጥ ማንም የለም።                 ........ ይቀጥላል ........ ✍ ፀሀፊ ሜሪ ፈለቀ ክፍል 2⃣2⃣ ከ 1⃣5⃣0⃣ Vote♥ በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍ሼር ማድረግ አይርሱ።       ‌‌‌‌‌

ሁሉም ሰው የራሱ የሆነ ችግር አለበት...አንተ ምን አለብህ አይባልም💔🥀

Kefl 21 zegju

ቤተሰቦች 🫶 አንዳንድ በሮች የተዘጉት እንዳትገቡ አይደለም እንዳትጎዱ እንጂ... ❤️‍🩹

iphone 17promax ገዛሁ ብዬ ፌስቡክ ላይ ደስ ብሎኛል ብዬ ፖስት ከማረጌ የሰፈራችን ማጅራት መቺዎች ላይክ እያረጉልኝ ነው ኮሜንትም ላይ እንኳን አብሮ ደስ አለን እያሉኝ ነው🤗🤗   ግን ምን አስበው ይሆን🤔🥹

        ተቀበይ . . . ውበትሽን አይቼ ልትዳር ባጭሽ ቆማጣ ያስሮጣል ለካ ፀባይሽ😄 #Ere_like የታለ

አታጠኑም  ምንባልበት ጊዜ አለፈና አታገቡም የምንባልበት ጊዜ መጣ አግቡ እንጂ ቤተሰብ 😁

ተማሪ ሁነን የመጨረሻው ክፍለ ጊዜ አላልቅ ብሎን በስንት መከራ አልቆ መምህሩ ሊወጣ ሲል ቀለሜዉ ተማሪ ጥያቄ 🙋 አለኝ ይላል 🤬💔😭 ህመሙን የሚያዉቀዉ 🤙🤙🤙

.💙   የመኖር አካፋይ የመሞት ሲሶ መንገድ መሃል🌹🔸                           ክፍል 2⃣0⃣ « የእኔ አበባ አባትሽን የገደሉትን ሰዎች አድገሽ አንድ በአንድ ተበቅለሻቸዋል። አታስታውሺው ይሄ ይቅርብሽ!! » አለችኝ በልመና። «አባቴ ሲሞት ስንት ዓመቴ ነበር?» አልኳት ውስጤን የአባቴን መልክ የማስታወስ ከፍተኛ ፍላጎት እያተራመሰው። ወዲያው ቀጥዬ «አባቴ ምን ይመስል ነበር?»                «13 ዓመትሽ ነበር። አባትሽ ሲሞት 13 ዓመትሽ ነበር። አባትሽ አንቺን ነበር የሚመስለው። መልካችሁ ብቻ መሰለሽ? ቁመትሽ ሳይቀር የሱ ነው። ነገረ ስራሽ የእርሱ ቅጂ መሆንሽ አይጣል ነው።» አለችኝ ለቅሶዋን ገታ አድርጋ። ከዚህ በኋላ የምጠይቃት ነገር ሁሉ ከእርሱ ሞት ጋር የተያያዘ እና የሚያስለቅሳት ስለመሰለኝ ምን ዘልዬ ምን እንደምጠይቃት ግራ ተጋባሁ። «ኪዳን የዘጠኝ ዓመት ልጅ ነበር። እሱ እንዳንቺ ጠንካራ አልነበረም። (ቅስስ ብላ ነው ይሄን የምታወራው) ክፉ እንዳያይ ጠበቅሽው፤ ክፉ እንዳይነካው ጠበቅሽው። እህትም እናትም ሆንሽው።» ብላኝ ፊቷን አዞረች። «አንቺስ? እንዴት ነው ከህይወቴ የጎደልሽው? ለምን ተለያየን? ኪዳን አሁን የት ነው?» አልመለሰችልኝም። ፊቷን ከእኔ መደበቅ ነው የፈለገችው። በእጇ አልጋ ልብሱን ጨመደደችው። ከአባቴ ሞት በላይ ሀዘኗን የሚያበዛ ሌላ ነገር መኖሩ ገባኝ። «እ? ንገሪኝ ምንድነው የተፈጠረው? » አልኳት «ኪዳን ካናዳ ነው ያለው። ዶክተር ሆኗል አልሽኝ። አሁንም ትምህርቱን ቀጥሎ የጭንቅላት ቀዶ ህክምና እየተማረ ነው ያለው አልሽኝ መሰለኝ በትክክል ካስታወስኩ።» አለችኝ ፊቷን ሳታዞር «አንቺስ? ምንም ቢሆን ንገሪኝ እና ታሪኬን የተሟላ አድርጌ ልገጣጥመው።» ልበላት እንጂ በምንም መርፌ የማልሰፋው ብዙ የተቦጫጨቀ ጎዶሎ እንዳለው ገብቶኛል። «አባትሽ ከሞተ በኋላ (ዝም አለች ለሆነ ሰከንዶች። ተገቢውን ቃል እየፈለገች መሰለኝ) አባትሽ ከሞተ በኋላ አቃተኝ። እናት መሆን አቃተኝ። ያንቺን ፊት በየቀኑ ማየት አቃተኝ። ለአጎታችሁ ትቻችሁ ከተማ መጣሁ። ይኸው ነው!! እኔ የማልረባ እናት ስለሆንኩ ነው የተለያየነው። ራስ ወዳድ ስለነበርኩ ነው ከህይወታችሁ የጎደልኩት።» እያለች ትንሰቀሰቅ ጀመር። የሚሰማኝ ስሜት ተደበላለቀብኝ። ምንም ቢሆን ይቅር ብዬሻለሁ እንዳልኳት አልቀለለኝም። አባታቸው የሞተባቸው ልጆችዋን እንዴት ትታን ትሄዳለች? ልቤ የለመደው ብርድ በረደው። ውስጤ ተከፋባት ግን ደግሞ ከነገረችኝ ታሪክ የተለየ ያልነገረችኝ ምክንያት እንዳለ ይሰማኛል። «በቃ? ይሄ ብቻ ነው ምክንያትሽ? ለምንድነው ያልነገርሽኝ ሌላ ነገር እንዳለ የሚሰማኝ? እ?» ከዚህ በኋላ የጠየቅኳትን ጥያቄ አንዱንም አልመለሰችልኝም። እቤቴ ይዣት ልሄድ ብለምናትም እንቢ አለችኝ። ልቀየማትም እፈልጋለሁ ልታረቃትም ያምረኛል። እሺ ልጅ ሆኜ ትታኝ ሄደች አሁን እንኳን በሞቷ አፋፍ ላይ ሆና የቀራትን ቀናት ፍቅሯን እንደተራብኩ እንዴት አይገባትም? ያልጠገብኩት እቅፏ እንደሚያስፈልገኝ እንዴት አትረዳም? ልጮህባትም ያምረኛል። ደግሞ እቅፏ ውስጥ ገብቼ ለሰዓታት ጠረኗን መማግም ያምረኛል። ለብዙ ደቂቃዎች ያለምንም ንግግር ዝም ብለን ቆየን። ትቻት ብወጣ ስመለስ የማላገኛት ዓይነት ስሜት እየተሰማኝ ከልክ በላይ ከፋኝ። ከየት መጣ ሳልለው እንባዬ ገነፈለ። «ምንም አልጠይቅሽም። ምንም አትመልሽልኝ። አጠገቤ ብቻ ሁኚልኝ። የቀረሽ ቀን ቀንድም ቀን ይሁን አንድ ዓመት አብረሽኝ ሁኚ። አንድ ቀንም ቢሆን እማዬ ልበልሽ? አንዲት ሰዓትም ቢሆን ልጅሽ ልሁን?» ብዬ እሪሪሪ ስልባት እሷ ከእኔ ባሰች። በጭንቅላቷ ንቅናቄ እሺ አለችኝ። ከነመድሃኒቶቿ ይዣት ወደ ቤት ተመለስኩ። ለቀናት ከእሷ ውጪ ስለምንም ነገር ማሰብ አልፈለግኩም። ህመሟ እየፀናባት ስለሆነ ብዙም አትንቀሳቀስም። ምግብ ለመብላትም ታስቸግራለች። ምንም አልጠይቃትም። እሷም ከአባቴ ሞት በፊት ስለነበረን ውብ የልጅነቴ ጊዚያት አንዳንድ ነገር ከማውራት የዘለለ አለመጠየቄ የተመቻት ይመስላል። አብሬያት እተኛለሁ። እሷን ከማጣጣም ውጪ ሌሎች ጥያቄዎቼን እና እውነታዎችን ሆነ ብዬ ችላ አልኩ። እሷ ስለኪዳን እኔ ከነገርኳት ውጪ የምታውቀው መረጃ የለም። እሷ እንደምትለኝ እንደዛ የምወደው እህቱ ከነበርኩ እንዴት ይሄን ሁሉ ጊዜ አይፈልገኝም? የሚለው ሀሳብ በመሃል ይጠልፈኛል። የጎንጥን ሽጉጥ መታጠቅም ልቤ አልረሳውም። አሁን ግን ከእናቴ ውጪ ምንም ነገር ላይ መጠመድ ስላልፈለግኩ ችላ አልኩኝ። ከቀናት በኋላ እናቴ ስትፈራ ስትቸር ቆይታ «ከሀገሬ ከወጣሁ በኋላ ድጋሚ አልተመለስኩም። ከመሞቴ በፊት ቀዬዬን ብረግጠው ፣ ቤተኞቼን በአይኔ ባያቸው፣ ያ ከርታታ ወንድሜ ምን ላይ እንዳለ ባውቅ፣ ኸረ እንደው ሞቴም እዛ ቢሆን አይከፋኝ። እዛው በአፈሬ ብቀበር። » አለችኝ እንደ እሩቅ ምኞት ምን ሊፈጠር እንደሚችል ሂሳብ አልሰራሁም። የመጀመሪያው ሀሳቤ የእናቴን ምኞት መሙላት ነው። የሆነኛው ልቤ ውስጥ ግን ናፍቆት አለው። ያ የሳር እርጥበት፣ ያ ቤቴ የሚመስለኝ አረንጓዴ አውድማ …… ልጅነቴ ….. ያደግኩበት መንደር ….. የማላውቀው ግን የማልቆጣጠረው ናፍቆት ……. እናቴ ተቀምጣ ብዙ መጓዝ ስለማትችል የሚመቻት መኪና ተከራየን እና ጎንጥ እየነዳ ከአዲስ አበባ ርቀን ወጣን። ሰው የሚፈልገውን ነገር እንዴት ይፈራዋል? እዛ አውድማ ላይ ስቆም ትውስታዬ እየተግተለተለ የሚመጣ እየመሰለኝ ፍርሃት ያንቀኛል። አውድማው ላይ ስቆም እንዳሰብኩት ትውስታዬ አልመጣም። አውድማው እንደፎቶው አረንጓዴ አይደለም። እናቴ እና ወንድሟ ሲገናኙ የተሰበሰበውን ሰፈርተኛ በእንባ ያራጨ ትእይንት ሆነ። በየቤቱ እየተዞረ የተነገራቸው ይመስል ግልብጥ ብሎ ለመጣው ሰፈርተኛ ሁሉ ጭንቅላቴ ስለማያስታውስ አላውቃችሁም ብሎ ማስረዳት አድካሚ ስለነበር እያቀፉ የሳሙኝን ሁሉ በፈገግታ እያቀፍኩ ስስም ቆየሁ። እናቴ ቀስ በቀስ የትኛው የስጋ ዘመዴ የትኛው ጎረቤት መሆኑን አስረዳችኝ። መንደሩን ለቅቄ ወንድሜን ይዤ የወጣሁት በ19 ዓመቴ እንደነበር አወቅኩ። የቤቱ ግርግር ሲሰክን እናቴም ድካሟ ጠንቶ ስትተኛ ከቤት ወጥቼ እግሬ ወደመራኝ ዘወር ዘወር ማለት ጀመርኩ። ጎንጥ እየተከተለኝ እንደሆነ ሳውቅ ቆሜ ጠበቅኩትና እኩል መሄድ ጀመርን። የሆነች ትንሽዬ ቤተክርስቲያን አልፈን፣ እጅብ ያሉ ቤቶች ካሉበት አለፍ ብለን የሆነ የፈረሰ ቤትጋ ስደርስ ቆምኩ። ለዘመናት ማንም እንዳልኖረበት የሚያስታውቅ፣ አረም እና ሀረግ የበቀለበት ግድግዳ ፣ የወለቀ በር፣ ደረቴን ደቅቶ ያስቆመኝ የሆነ ነገር ያለ ይመስል ቆምኩ። ጎንጥ ደንግጦ ያዝ አደረገኝ እና «ምነው?» አለኝ። አፌ ቃል አላወጣም። እግሬ የዛለ ስሜት ስለተሰማኝ ዘጭ አልኩ መሬቱ ላይ በቂጤ። «ይሄ ቤታችን ነበር። አባቴ እዛጋ ነው የሞተው።» አልኩት በጣቴ እየጠቆምኩት።                 ........ ይቀጥላል ........ ✍ ፀሀፊ ሜሪ ፈለቀ ክፍል 2⃣1⃣  ከ 1⃣5⃣0⃣ Vote♥ በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍ሼር ማድረግ አይርሱ።       ‌‌‌‌

ፈገግታ vibe - إحصائيات وتحليلات قناة تيليجرام @topc_vibe