Assaye Derbie
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Assaye Derbie
تُعد قناة Assaye Derbie (@asayede) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 355 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 646 في فئة المدوّنات والمرتبة 2 354 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 355 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 22 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -133، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -3، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 38.76%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 11.78% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 562 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 691 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 34.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 23 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة المدوّنات.
14 355
المشتركون
-324 ساعات
-387 أيام
-13330 أيام
أرشيف المشاركات
14 355
ከስር ያለውን ሊንክ በመጠቀም Live ትከታተሉን ዘንድ ጋበዝን!
https://www.youtube.com/live/mjxAQUcRjOs?feature=share
14 355
ያለ ግጭት እና ጦርነት መኖር የማይችለው ሥርዓት የአማራ ልዩ ሃይልን ትጥቅ ማስፈታት ከቻለ ወደ አማራ ፋኖ እና ሚኒሻ ይሸጋገራል እንጂ ወደ ሌላ ክልል ሄዶ ግብ ግብ የሚገጥመው ልዩ ሃይል አይኖርም።
እናም ይሄንን በሕግ ያልተደገፈና ሕዝብን ያላሳተፈ የጥጋብ ዘመቻ መላው አማራ በአንድነት ቁሞ መመከት ካልቻለ ከዚያ በኋላ የ "አማራ" የሚባል ክልል ይኖራል ተብሎ አይታሰብም።
እነ ባሕርዳር፣ ጎንደር፣ ደሴ እና ደብረ ብርሐንም የድንበር ተሻጋሪ ወንበዴዎች መፈንጫ ምሽጎች እንጂ ነዋሪዎቻቸው ሠርተው የሚያድሩባቸው ሰላማዊ ከተሞች ሆነው ሊቀጥሉ አይችሉም።
14 355
የግፉአን ልሳን የሆኑ ብሎም ለሙያቸውና ለወገናቸው የታመኑ ጋዜጠኞችን የማፈን ዘመቻው ተጧጡፏል።
እንዲያም ሆኖ ግን.... ልክ እንደ ገነት አስማማው፣ አባይ ዘውዱና ጌትነት አሻግሬ እውነትን የሚናገሩ፣ ለሙያቸው ያደሩ ብሎም የማይበገሩ ልሳኖችን የማፈን ተግባሩ ቁሞ መረሸን ካልተጀመረ በቀር እነዚህ አርአያ ሰቦች በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚሸለሙበት ጊዜ እንደሚመጣ አልጠራጠርም።
14 355
ከስር ያለውን ሊንክ በመጠቀም Live ትከታተሉን ዘንድ ጋበዝን!
https://www.youtube.com/live/BzVo-2pOFs8?feature=share
14 355
የእነ ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቼውን ክስ ስመለከት... ያለ ምንም የቃላት ለውጥ በወቅቱ ታስረው ከነበሩ የትግራይ ተወላጆች ክስ ላይ የተገለበጠውና እንዲህ የሚለው የወንጀል ክሴ ትዝ አለኝ።
"በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አሸባሪ ተብሎ ከተፈረጀው የህውሓት ከፍተኛ አመራሮች ተልዕኮ ተቀብሎ ወደ መሀል አገር መጥተው ንጹሐንን የሚጨፈጭፉበትን እና የሚዘርፉበትን መንገድ በማመቻቸት ተጠርጥሮ ስለተያዘ..."
የሚገርመው ነገር ታዲያ በህውሓት ተላላኪነት ተጠርጥሬ የተያዝኩት ከመጠን በላይ የምጠየፈውና እንደ እናቴ ገዳይ የምመለከተው የሽብር ድርጅት "በአማራና በአፋር ሕዝብ ላይ የፈጸማቸው ሰብዓዊና ቁሳዊ ውድመቶች ተድበስብሰው መቅረት የለባቸውም" በሚል አቋም በርካታ የሰነድና የምሥል ማስረጃዎችን የያዘ መጽሐፍ ባሳተምኩ ማግስት መሆኑ ነው። 😃
14 355
አቶ አዲስ አረጋ ኪጋሊ ሆኖ በሮዋንዳ እልቂት ዙሪያ ያስተላለፈው እጅግ አደገኛ መልዕክት ባጭሩ ሲታይ፦
🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸
➽"የኪጋሊ ከተማ ባለፈ ታሪኳ ዙሪያ ለአዲስ አበባ እና ለሥልጣን ልንጠቅ ባዮች ጮኽ ብላ የምትናገረው ማስጠንቀቂያ አላት" በሚል ማስፈራሪያ የሚጀምር...
➽ለሮዋንዳ እልቂት መከሰት ዋነኛው ምክንያት የሮዋንዳውን ፕሬዝዳንት የጫነችው ሄሊኮፍተር ተመትታ መከስከሷ ነው" ብሎ ከተናገረ በኋላ ያ እልቂት እንዳይከሰት መላዕከ ሞትን ገዝቶ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ዘላለማዊ ሕልውና ማረጋገጥ እንደሚገባ የሚመክር፤
➽የኢትዮጵያን ሕልውና ከአምላክ ቀምቶ ከዐቢይ መዳፍ ስር የሚያኖር
➽የሮዋንዳ እልቂት መነሻ አንዱ ምክንያት ማጆሪቲ ከሆነው የሁቱ ማሕበረሰብ የወጡና ወደ ሥልጣን የመጡ ጽንፈኛ ልሂቃን የሥልጣን ተቀናቃኛችን በሚሉት በቲትሲ ማሕበረሰብ ላይ የነዙት የጥላቻ ትርክት" መሆኑን ክዶ አማራን ተጠያቂ ለማድረግ ሲል ብቻ እልቂቱን ያመጡት ልክ እንደኛ "የሥልጣን ልቀቅ፥ ሥልጣን ልንጠቅ" አጀንዳ የሚያራግቡ ልሒቃን ናቸው" በሚል ውሸት ቱትሲዎችን የሚወነጅል የውሸት ታሪክ የሚናገር፤
➽ከሩዋንዳ እልቂትም ሆነ ከአገራዊ ፍርሰት ለመዳን "ንጉስ ሆይ ሺ ዓመት ይንገሱ" እያሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ከየትኛውም ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ አደጋ መጠበቅ እንደሚገባ የሚናገር፤
➽አንዱ ወገን ኢንተር ሐሞይን ለመሆን የሚያበቃ በቂ ምክንያት እንዳለው አምኖ፤ ሌላው ወገን የቱትሲን እጣ እንዳይጋራ የሥልጣን ይልቀቁ ጥያቄ ማንሳት የለበትም" በማለት የሚያስጠነቅቅ፤
➽በመንግሥታዊ መዋቅር ተደግፎ ድምጽ አልባ በሆነ መልኩ ሲፈጸም የከረመውን የሮዋንዳ እልቂት ክዶ "እንዳይደገም" እያለ የሚሳለቅ፤
➼ወደ ኪጋሊ አምርቶና የመታሰቢያ ሙዚየሙን ጉብኝቶ የተማረውን መልካም ነገር ለአገር በማስተላለፍ ፈንታ አማራን እና አዲስ አበባን ጠፊም አጥፊም አድርጎ ስልታዊ በሆነ መልኩ የዘር ፍጅትን የሚያውጅ
.
.
.
በመሆኑም አቶ አዲሱ አረጋ የለጠፈውን እጅግ አደገኛ ጽሑፍ በሰነድ መልክ ጠርዞ ለሚመለከታቸው ዓለም አቀፍና አገር በቀል ተቋማት ማድረስ ይገባል እላለሁ።
አሳዬ ደርቤ
share
14 355
ኤርሚያስ ለገሰን "በሐሳብ ሞግተው" ባላችሁኝ መሠረት ኤርሚያስን ለመተቸት ያበቁኝን አሳማኝ ምክንያቶች በቪዲዮ ማስረጃ አስደግፌ አቅርቤያለሁ። 👇
https://www.youtube.com/live/gzsA4Zhg0fI?feature=share
14 355
ከስር ያለውን ሊንክ በመጠቀም Live ትከታተሉን ዘንድ ጋበዝን!
https://www.youtube.com/live/gzsA4Zhg0fI?feature=share
14 355
"አስቴር" በሚል ሥሟ ጠርተህ ስህተቷን ስትነግራት "ይሄ ሁሉ ትችት የበዳኔ ልጅ በመሆኔ ነው ትልኻለች።
"ወዳጄ ኤርሚያስ ለገሰ" ብለህ ስትጠራው "እኔ የዋቅጅራ ልጅ ያንተ ወዳጅ ሆኜ አላውቅም" ይልኻል። 😂
እውነት ለመናገር የአባቶቻችሁን ሥም ሳስታውስ "ደርቤ" የሚለውን የአባቴን ሥም "ድሪባ" ባደርገው ደስታዬ 😆
14 355
ከአምስት ደቂቃ በኋላ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያለንን ሐሳብ ልንገልጽ Live ስለምንገባ ስር ያለውን ሊንክ በመጠቀም ትከታተሉን ዘንድ ጋበዝን!
https://www.youtube.com/live/_TK7BhE0uG0?feature=share
14 355
የልጆቿን አባት ገድላችሁ ከራሔል ኀዘን የከፋ ብርቱ ኀዘን ያመጣችሁባት እኩዮች ሆይ ይሄውና ስኬታችሁ...ይሄውና ደስታችሁ...!
በእናንተ ዘንድ ፍቅር ማለት ሌሎችን መጥላት ነውና..
"ይህቺን የካሕን ሚስት የልጇቿን አባት ገድለን በጉንጯ ላይ እንባ ሳይሆን ደም እንዲንዠቀዠቅ ማድረግ ቻልን" የሚል ገድላችሁን ለእናቶቻችሁ ነግራችሁ ደስ አሰኟቸው።
የንጹሐንን ሞት ሕይወታችሁ፣ የእናቶችን ኀዘን ሐሴታችሁ፣ የዜጎችን ስቃይ ሲሳያችሁ፣ የሌሎችን ቤት አልባነትና ድሕነት ስኬታችሁ ያደረጋችሁ የወቅቱ ገዢዎች ሆይ ይሄን ፎቶ ዳውንሎድ አድርጉና ከታሪክ መጽሐፋችሁ ጋር አሳትሙት።
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
