ar
Feedback
Official Bole Gerji school ቦሌ ገርጂ ት/ቤት የወላጃ እና የተማሪ ቴሌግራም ቻናል

Official Bole Gerji school ቦሌ ገርጂ ት/ቤት የወላጃ እና የተማሪ ቴሌግራም ቻናል

الذهاب إلى القناة على Telegram

ቦሌ ገርጂ ት/ቤት የ ዩቲዩብ ቻናል 👉 https://www.youtube.com/@officialBolegerjischool 👈YouTube It's All About You And Education.

إظهار المزيد
1 394
المشتركون
+324 ساعات
+107 أيام
-230 أيام
أرشيف المشاركات
ሰላም እንደምን አመሻችሁ? ከዚህ በታች የተጠቀሳችሁ ብሎኮች የማህበሩ ሰብሳቢ፣ ምክትል እና ፀሐፊዎች ነገ ጠዋት 2:30 ጀምሮ ቤቶች አስተዳደር 11ኛ ፎቅ አዳራሽ እንድትገኙ እናሳስባለን። 1. አራብሳ 1= 2 እና 8 2. አራብሳ 5 = 3 እና 4 3. ፉሪ ሃና = 4 , 7 እና 8 4. ቦሌ በዋ=5, 6, 7, 8, 9, 10, 13, 15, 16 ,17, 18, 20, 21, 22 5. መንዲዳ= 1 , 4

Qabxiilee ijoo armaan gadii jala bultii qormaataa fi yeroo qormaatichaa milkii mirkaneessuuf hojiirra ooluu qabu:- 👉Boqonnaa gahaa argachuu: Sammuu kakaasuu fi dhiphina hir'isuuf yoo xiqqaate sa'aatii 7 hanga 8 hirriba gadi fagoo qabaachuun barbaachisaadha. 👉 Meeshaalee qorannoo qopheessuu: qubeessaa, , haqtuufi qartuu, waraqaa eenyummaa, fi meeshaalee barbaachisoo biroo dursanii  qophaa’uu qabu. 👉 Gamaaggama gabaabaa qofa godhi: Mata duree haaraa dubbisuuf yaaluu dhiisanii gabaabduu fi qabxiilee ijoo kanaan dura qophaa’an qofa gamaaggamuun gaariidha. 👉 Nyaata sirrii: Sammuun sirnaan akka hojjetu gochuuf nyaata salphaa, soorataa, fi fayya qabeessa nyaachuu qabda. 👉 Miira kee to'adhu: Yaaddoo qormaataa fi dhiphina hir'isuuf, garmalee yaaduu irraa fagaachuun, yaada gaarii qabaachuu, fi boqochuun barbaachisaadha. 👉 Iddoo qormaata beekuu: Bakki qormaataa fagoo yoo ta'e, karaa keessan dursanii karoorfachuu fi yeroon gahuun barbaachisaa dha. 👉 Qormaata waliin carraa gaarii!! 👉 Bu'aa gaarii! 👉 Carraa gaarii!

Repost from N/a
✔️
በፈተና ዋዜማ ተማሪዎች አእምሮን ለማዝናናት በቂ እንቅልፍ መተኛት፣ የተዘጋጁ ማጠቃለያዎችን ብቻ በአጭሩ መገምገም፣ የፈተና መገልገያ ቁሳቁሶችን ማዘጋጀት፣ ጤናማ ምግብ መመገብ እና አላስፈላጊ ጭንቀትን ማስወገድ አለባቸው።
⭐️በፈተና ዋዜማ እና የፈተና ጊዜ ስኬትን ለማረጋገጥ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች ተግባራዊ ማድረግ ይገባል🔤➖ 🔤በቂ እረፍት ማድረግ፡ አእምሮን ለማነቃቃት እና ጭንቀትን ለመቀነስ ቢያንስ ከ 7 እስከ 8 ሰዓታት የሚሆን ጥልቅ እንቅልፍ መተኛት ያስፈልጋል። 🔣የፈተና ቁሳቁስ ማሟላት እስክሪብቶ፣ እርሳስ፣ ማጥፊያ፣ መለያ (ID) እና ሌሎች አስፈላጊ ግብዓቶች አስቀድመው በቦርሳ መዘጋጀት አለባቸው። ⏰አጭር ግምገማ ብቻ ማድረግ፡ አዳዲስ ርእሶችን ለማንበብ ከመሞከር ይልቅ ቀደም ሲል የተሰሩ ማጠቃለያዎችን እና ዋና ዋና ነጥቦችን ብቻ ማየት ይበጃል። 🔤ትክክለኛ አመጋገብ፡ አእምሮ በተገቢው መንገድ እንዲሠራ ቀላል፣ ሰውነትን የሚያነቃቁ እና ጤናማ ምግቦችን መመገብ ይገባል። 🔤ስሜትን መቆጣጠር የፈተና ፍርሃትን እና ጭንቀትን ለመቀነስ ከመጠን በላይ ከማሰብ መቆጠብ፣ አዎንታዊ አስተሳሰብ መያዝ እና ዘና ማለት ያስፈልጋል። 🔤የፈተና ቦታን ማወቅ፡ የፈተናው ቦታ ሩቅ ከሆነ አስቀድሞ መንገድን በመለየት ሰዓት አክብሮ ለመገኘት እቅድ መያዝ ወሳኝ ጉዳይ ነው 📌መልካም ፈተና!! 📌 መልካም ውጤት! 📌መልካም እድል!

በቀን 5/10/2018 አ/ም በቦሌ ገርጂ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ለ6ኛ እና ለ8ኛ የቀንና የማታውን የሁለቱንም መርሃ ግብር ጨምሮ ኦሬንቴሽን ተሰጠ። በዕለቱ ገለፃውን የሰጡት የፈተና ጣቢያ ሃላፊው አቶ መሃመድ አህመድ ሲሆኑ በዕለቱ ማድረግ ያለባቸውን እና የተከለከሉ ነገሮችን ሰፊ ግዜ ወስደው አስገንዝበዋል። ከዚህ በተጨማሪም ለመፈተን ተመልምለው የመጡ መምህራንና የት/ት ቤቱ የኮማንድ ፖስት አባላት የዕለቱን ኦሬንቴሽን ተማሪዎች እንዲገነዘቡ እገዛና ቁጥጥር በማድረግ ተማሪዎቹም ያልገባቸውን በመጠየቅ ምላሽና ማብራሪያ በፈተና ጣቢያ ሃላፊው በኩል ተሰጧቸው የዕለቱን አጀንዳ አጠናቀዋል።

የተፈታኞች መብትና ግዴታ ✅ 📚 ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ደንብና ሥርዓት  አከባበር እንዲሁም የመልስ ወረቀት አጠቋቆርና   ተዛማጅ ሁኔታዎችን አስመልክቶ በሚሰጡ ገለፃዎች ላይ የመሣተፍ ግዴታ አለበት። 📚 ተፈታኙ በገለፃው ላይ ባለመሳተፉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ኃላፊነቱን ይወስዳል። 📚 ተፈታኙ/ኟ የሰራበትን የመልስ ወረቀት ለፈታኙ በመስጠት  የጥያቄ ወረቀቱን ይዞ መውጣት ይችላል 📚 ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ጥያቄዎቹን መስራት ከመጀመሩ በፊት በፈተና የመልስ መስጫ ወረቀት ላይ የግል መለያ መረጃዎችን በሙሉ ግልፅ በሆነ ሁኔታ በቅደም ተከተል ጽፎ ማጥቆር ይኖርበታል (በተለይ የመለያ ቁጥር እና የትምህርት አይነት ኮድ)። 📚 ማንኛውም ተፈታኝ የራሱን ችሎታና ዕውቀት ተጠቅሞ መስራት ይጠበቅበታል፡፡ 📚 የሚሠራባቸው የጥያቄና የመልስ መስጫ ወረቀቶች ለሌሎች ተፈታኞች ዕይታ የተጋለጡ እንዳይሆኑ ሸፍኖ መስራት ይኖርበታል 📚 ማንኛውም ተፈታኝ ሞባይል፣ ካልኩሌተርና የመሳሰሉ ማንኛውንም ዓይነት  የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ይዞ ወደ ፈተና ክፍል መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው ። 📚 እያንዳንዱ ተፈታኝ ይህንን አውቆ በቅድሚያ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ። 📚 ይህንን ባለማድረጉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ተፈታኙ  ራሱ ኃላፊነቱን ይወስዳል። 📚 ማንኛውም ተፈታኝ በመፈተን ላይ እያለ ፈተናውን እንዳይሠራ የሚያውኩ ሁኔታዎች ቢያጋጥመው በፈታኙ ሲፈቀደለት ችግሩን በመግለጽ አስፈላጊውን እርዳታ ማግኘት ይችላል ይሁንና በማንኛውም ምክንያት ለባከነ ጊዜ ተጨማሪ ሰዓት አይፈቀድም 📚 ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከሚጀመርበት ጊዜ ተኩል ሰዓት /30 ደቂቃ/ ቀደም ብለው ከመፈታኛው ቦታ በመገኘት መቀመጫቸውን መያዝ አለባቸው። 📚 ፈተናው ከተጀመረ ከ15 ደቂቃ በኋላ የሚመጣ ተፈታኝ ወደ ፈተናው አዳራሽ መግባት አይፈቀድለትም። 📚 ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ፈተናውን ሠርቶ ቢያጠናቅቅም እንዲወጣ አይፈቀድለትም። 📚 ይሁን እንጂ ፈተናው ከተጀመረ ከ45 ደቂቃ በኋላ ከፈተና አዳራሹ ለመውጣት   እንዲፈቀድለት ሲጠይቅ የመልስ ወረቀቱን ለፈታኙ አስረክቦ በጸጥታ እንዲወጣ ይፈቀድለታል። 📚 ፈተናው ሊጠናቀቅ ከ10 ደቂቃ ያነሰ ጊዜ ሲቀረው የሚጨርስ ተፈታኝ የሁሉም ተፈታኞች የመልስ ወረቀቶች እስኪሰበሰቡና ለፈተናው የተፈቀደው የጊዜ ገደብ አብቅቶ እስኪደወል ድረስ በቦታው ተቀምጦ እንዲቆይ ይደረጋል። 📚 ፈተናው በሚሰጥበት ጊዜ ማንኛውም ተፈታኝ ትክክለኛ ያልሆነ የተቀደደ ወይም የተበላሸ የፈተና ጥያቄ ጥራዝ ከገጠመው ወይም የተሰጠው የመልስ ወረቀት የተበላሸ ከሆነ ወይም በራሱ እጅ ቢበላሽበት እጁን አንስቶ በመጠየቅ ሲፈቀድለት ሊያስቀይር ይችላል። ለተፈታኞች የተፈቀዱ

Biiroo Barnoota Bulchiinsa Magaalaa Finfinnee, Kutaa Magaalaa Boolee, Aanaa 13, Mana Barumsaa Boolee Garjii BSTD, Sad.1ffaa fi Giddu-galeessaatti Qormaata Afaan Oromoo xumura Seemisteera 2ffaa kutaa 7ffaa bara 2018 Barattoota Guyyaaf qophaa’e. 40% Maqaa ………………… kutaa ………… Lakk….………………… saala………….

Kidane Tesfaye🦴: Addis Ababa City Administration Education Bureau Bole Sub-City District 13 Bole Gerji Pre-Primary, Primary and Middle School Second Semester June 2018 E.c English language Final Exam for Grade 7th (regular) students.(40%)       Time allotted 45 minutes Name........... Grade and section...... Roll No ..... Gender..... በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13  የቦሌ ገር ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2018 ዓ.ም የሁለተኛ መንፈቅ ዓመት የ7ኛ ክፍል ለቀን ተማሪዎች የተዘጋጀ የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት  ማጠቃለያ ፈተና። ከ40%                     የተፈቀደ ሰዓት ___ ደቂቃ ስም ..................... ክፍል እና ሴክሽን ...... ተራ ቁጥር ........ ጾታ -- የማጠቃለያ ፈተና ላይ ለሁሉም ወጥ እንዲሆን ከላይ በተፃፈው አርዕስት መሰረት እንዲደረግ እና ፈተናው በጣም እስከ አርብ 05 / 10 /2018 ዓ.ም 6:00 ሰዓት ድረስ ከት /ቢሮ በወረዳው የፈተና ቢጋር መሰረት ተዘጋጅቶ በትምህርት ክፍል ኃላፊ በኩል ገቢ እንዲደረግ እናሳስባለን ። ት/ቤት

[ ከፈታኝ መምህራን የሚጠበቅ ]
👉🏾 የተፈታኝ ተማሪዎችን ID በአግባቡ በማረጋገጥ ወደ ክፍል እንዲገቡ ማደረግ ይጠበቅባቸዋል። 👉🏾 ተፈታኝ ተማሪዎችን በሥም ዝርዝራቸው መሠረት ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል። 👉🏾 ፈታኝ መምራህን የተማሪዎችን አቴንዳንሰ ይወስዳሉ ፤ ተማሪዎችን ፊርማ ያስፈርማሉ። 👉🏾 በፈተና ክፍል ውስጥ ደምጽ እንዳይሰማ፣ ተማሪዎች ከቦታ ቦታ እንዳይዘዋወሩ ተገቢውን ቁጥጥር ማድረግ አለባቸው። 👉🏾 የፈተናው አጠቃለይ ሂደት በትኩረት መከታተል አለባቸው። 👉🏾 በህመም ምክንያት ተማሪዎች ከክፍል መውጣት ቢፈልጉ ከሱፐርቨዘር ጋር በመነጋገር አስፈላጊውን እርዳታ ያደርጋሉ። 👉🏾 ተማሪዎች በጎናቸው ያለውን ሌላ ተማሪ እንዳይመለከቱ እንዳይኮርጁ  መቆጣጠር አለባቸው። 👉🏾 ተማሪዎች ፈተናው ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በፊት እንዳይወጡ መቆጣጠር ይጠበቅባቸዋል። 👉🏾 ሲኮርጂ ወይንም ሲያስኮርጅ የተገኘ ተማሪ ከመፈተኛ ክፍል እንዲወጣ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። 👉🏾 ፈተናው ከጀመረ 30 ደቂቃ በኃላ የሚመጣ ተማሪ እንዲገባ ማድረግ የላባቸውም። 👉🏾 የፈተና አፈጻጸም ሪፖርት ለሱፐርቨዘር ማቅረብ

ለቦሌ ገርጅ ቅድመ 1ኛ ፣ 1ኛ እና መካክለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የክፍል ኃላፊ መምህራን እና የክበብ ተጠሪ መምህራን በሙሉ - በየወሩ የአንድ ለአምስት አደረጃጀት ሪፖርት ለቢሮ ገቢ ያላደረጋችሁ የክፍል ኃላፊ መምህራን ነገ በጠዋት ገቢ እንዲደረግ ፤ - በአዲሱ የአንድ ለአምስት አደረጃጀት አደራጅታችሁ ቢሮ ገቢ ያለደረጋችሁ የክፍል ኃላፊ መምህራን ነገ በጠዋት ገቢ እንድታደርጉ - የክበባት ተጠሪዎች በየወሩ የሰራችሁትን የክበብ ሪፖርት ፣ የሰጣችሁበትን የስልጠና ሰነድ ፣ ፎቶ እና ተያያዥ መረጃዎች ለቢሮ ገቢ ያላደጋችሁ የክበባት ተጠሪ መምህን ነገ በጠዋት ቢሮ ገቢ እንድታደርጉ እናሳስባለን ። ት/ቤቱ

ከላይ በማስታወቂያ የተገለፀው የማታ ትምህርት ያካተተ ስለሆነ ለሚመለከታችሁ መምህራን እናሳስባለን ።

ለቦሌ ገርጅ ቅድመ 1ኛ ፣ 1ኛ እና መካክልኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን በሙሉ ፤ ትምህርት ቤቱ የኢንስፔክሽን ምዘና ላይ መሆኑ ይታወቃል ፤ ስለሆነም :- 1ኛ በምዘና ወቅት ለመማር ማስተማር አስፈላጊ የተባሉ መረጃዎች ይዞ መገኘት እና ከመምህር የሚጠበቅ ነገሮችን ማድረግ 2ኛ, በት/ቤቱ ወጥቶ ከተለጠፈው የክፍለ ጊዜ ፕሮግራም ውጭ ክፍል ገብቶ ማስተማር በፍፁም የተከለከለ መሆኑን እየገለፅን ይኸን እና መሰል ከመማር ማስተማር ጋር በተያያዙ ያሉ ነገሮች ላይ ለማወቅም ሆነ ባለማወቅ ክፍተት የፈጠረ መምህር ተጠያቂ እንደሚሆን እናሳስባለን ። ት/ቤቱ

Repost from N/a
✅ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት  እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡ ✅ በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ ✅ ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም። ✅ በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን።

Repost from N/a
✔️የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የፈተና መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም ዙሪያ ሊያውቋቸው የሚገቡ ጉዳዮች ✅የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመ
+2
✔️የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የፈተና መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም ዙሪያ  ሊያውቋቸው የሚገቡ  ጉዳዮች ✅የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡ ✅ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) ብቻ ማጥቆር አለበት፡፡ ✅ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡ ✅ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን የአራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡ ✅በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ መልስ (የአራት ማዕዘን ቅንፍ/Square Bracket) ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡ ✅ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡ ✅ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ  በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ✅ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ ማጥፋት ይጠበቅባችኋል። ✅መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡

Repost from Yeka Education
✔️የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የፈተና መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም ዙሪያ ሊያውቋቸው የሚገቡ ጉዳዮች ✅የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመ
+3
✔️የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የፈተና መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም ዙሪያ ሊያውቋቸው የሚገቡ ጉዳዮች የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) ብቻ ማጥቆር አለበት፡፡ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን የአራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡ በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ መልስ (የአራት ማዕዘን ቅንፍ/Square Bracket) ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡ ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ  በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ ማጥፋት ይጠበቅባችኋል። መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት  እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡ በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም። በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን። #️⃣ሸር 📌 ለሁሉም ተፈታኞች መልካም የጥናትና የፈተና ጊዜ! 👏👏👏👏👏 🔠🔠🔠🔠 🔠🔠🔠 Our Channel ⬇️⬇️⬇️ https://t.me/dam76

ጥብቅ ማስታወቂያ በሁሉም መምህራን ! ሊተገብሩት የሚገባ በሚቀጥለው ሰኞ ጀምሮ እስከ እሮብ ወደ 4ኛ ደረጃ ውስጥ ለመግባት  ለሚደረገው ት/ቤት ምዘና እያንዳንዱ  መምህር በጥንቃቄ  የሚተገብራቸው ተግባራት እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል ። 1.ጠዋት እስከ 1:30 ት/ቤት ግቢ መገኘት 2. የክፍል ምልከታ 65ቱም ክፍል የሚታይ መሆኑን ( በ1 ክ/ጊዜ 2መ/ራን ) 3. ሁሉንም መረጃ በአግባቡ ክፍል ይዞ መግባት ማለትም 💧 አመታዊ እና እለታዊ እቅድ ሳይዛነፉ በተጣጣመ መልኩ መኖራቸውን እና በሃላፊዎች ማረጋገጣቸውን 💧የመ/ር/ት ማስታወሻ ደብተር 💧የተማሪዎች አቴንዳንስ በተሟላ መልኩ ይዞ መግባት 💧አሳታፊ የመማር ማስተማርና ሂደቱን በተግባር በተከፋፈለው ደቂቃ ተማሪዎቹ  መሳተፋቸውን የሚገልፅ በሆነ መልኩ ተግባራዊ ማድረግ 💧የመምህራን ስነ-ምግባርን ተላብሶ መገኘት 💧የተከታታይ  ምዘናን በስታንዳርዱ መሠረት አሟልቶ ከመያዝ  እና ዲፓርትመንት ተጠሪውና ስርአተ ትምህርት ሀላፊው ይፀደቀ መረጃ ይዞ ክፍል መግባት :: 💧ሁሉም ተማሪ የት/ት ግበአት እንዲይዞ ማድረግ ከዚህ በተጨማሪ የክበባት ተጠሪዎች 💧የክበባት እቅድ 💧ወርሃዊ ሪፖርት 💧ለአባላቱ የተሰጠ ስልጠና ፕሮፖዛል እና ማነዋል / የስልጠና ሰነድ 💧ቃለ ጉባኤ በተሟላ መልኩ መገኘት ያለባቸው  መሆናቸውንና ሌሎች ያልተገለፁ ተግባራትን በጥንቃቄ መያዝ እንዲሁም የዲፓርትመንት ተጠሪዎች 💧አመታዊ እቅድ 💧ወርሃዊ ሪፖርት 💧ለአባላቱ የተሰጠ ስልጠና ፕሮፖዛል እና ማነዋል / የስልጠና ሰነድ ተደራጅቶ እንዲያዝ  እናሳውቃለን :: ት/ቤቱ 29/09/2018 አ/ም

በቦሌ ገርጂ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪዎች የክህሎት ስልጠና ተሰጠ። ስልጠናውን የሰጡት ብዙ ልምድ ያካበቱና ክህሎትን በመተግበር የሚታወቁት ልዩ ተሰጥቶ ያላቸው የእንግሊዝኛ መምህር የሆኑት ሀይላይ ተክላይ ሲሆኑ ተማሪዎች ከዘመኑ ጋር የሚሄድ ሙያዊ ክህሎትን በማዳበር የተለያዩ ችግሮችን በማስወገድ ሳይንሳዊ ዘዴን መጠቀም እንዲችሉ ጥልቅ ስልጠናን አግኝተዋል። 28/09/2018 አ/ም