ar
Feedback
Law students Union ️️️

Law students Union ️️️

الذهاب إلى القناة على Telegram

LSU is created mainly to inform you updated laws; useful teaching materials,References, exit exam files, shortnotes available;and to support law students 🎓LSU🎓 🎓GBS🎓 🎓ሕተህ🎓 📩 @LSU2012_bot lawstudentsunioneth2013@gmail.com For Accessibil of Laws!

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Law students Union ️️️

تُعد قناة Law students Union ️️️ (@lawstudentsunion) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 423 مشتركاً، محتلاً المرتبة 581 في فئة القانون والمرتبة 2 345 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 423 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 15 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 39، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 23.91‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 9.38‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 449 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 353 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 13.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
LSU is created mainly to inform you updated laws; useful teaching materials,References, exit exam files, shortnotes available;and to support law students 🎓LSU🎓 🎓GBS🎓 🎓ሕተህ🎓 📩 @LSU2012_bot lawstudentsunioneth2013@gmail.com For Accessibil of ...

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 16 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة القانون.

14 423
المشتركون
+124 ساعات
+397 أيام
+3930 أيام
أرشيف المشاركات
+6
Coffee quality Regu.pdf1.19 MB

Bunaan walqabatee Seerota bahanii jiran ስለ ቡና የተደነገጉ ሕጎች

Repost from Law School Media
ኒጀር ግብረ-ሰዶማዊነትን በህግ ከከለከሉ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ተርታ ተቀላቅላለች ። የኒጀር ወታደራዊ ሁንታ ግብረ-ሰዶማዊነትን በወንጀል የሚቀጣ አዲስ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ማውጣቱን አስታወ
ኒጀር ግብረ-ሰዶማዊነትን በህግ ከከለከሉ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ተርታ ተቀላቅላለች ።  የኒጀር ወታደራዊ  ሁንታ  ግብረ-ሰዶማዊነትን በወንጀል የሚቀጣ አዲስ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ማውጣቱን አስታወቀ። ከሀገሪቱ የፍትህ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ አዲሱ ህግ ከትናንት በስቲያ ሐሙስ ጀምሮ ገቢራዊ ተደርጓል።  ስራ ላይ የዋለው አዲሱ ህግ  ግብረ-ሰዶማዊነትን ወይም መሰል ድርጊቶችን የፈጸመ ወይም ለመፈጸም የሞከረ ማንኛውም ሰው ከ5 እስከ 10 ዓመት በሚደርስ እስራት እና በገንዘብ ይቀጣል። ቅጣቱ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸውን ሰዎች ጋብቻ ያስፈጸሙ ሰዎችን፣ ምስክሮችን፣ ጋብቻው እንዲፈጸም ፍቃድ የሰጡትን እንዲሁም የሰርጉን አዘጋጆች በሙሉ ያጠቃልላል ነው የተባለው። ከዚህ ቀደም በኒጀር ግብረ-ሰዶማዊነት በህግ የተከለከለ ባይሆንም፣ በህብረተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ማግለል ይደርስበት ነበር። ኒጀር ይህንን እርምጃ በመውሰድ ግብረ-ሰዶማዊነትን በህግ ከከለከሉ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ተርታ ተቀላቅላለች።  ግብረሰዶማዊነት በሴኔጋል፣ ኬንያ፣ ሴራሊዮን እና ታንዛኒያ እስከ 10 ዓመት እና ከዚያ በላይ በሆነ እስራት ያስቀጣል። በሶማሊያ፣ ዩጋንዳ እና ሞሪታኒያ ደግሞ የወንጀሉ ቅጣት እስከ ሞት ፍርድ ሊደርስ እንደሚችል ዘገባው አመልክቷል።

የሕግ ፈላስፋው Lon Fuller እ.ኤ.አ በ1964 ባሳተመውና የዘመኑ ቁንጮ በሆነው ''The Morality of Law'' (የሕግ የሥነ-ምግባር መሠረት) በተሰኘው ድንቅ መጽሐፉ፣ ለሕግ ፅንሰ-ሐሳባዊ ትንተና አዲስና ልዩ መስተጋብር አስተዋውቋል። ፉለር በህግ ፍልስፍና አለም ውስጥ “ተፈጥሯዊ የህግ አምላኪ” (Natural Lawyer) ተብሎ ይመደባል፤ ነገር ግን የእሱ አቀራረብ ከቀደሙት የሃይማኖት ወይም የሞራል ምሁራን የተለየ ነው። እሱ የሚያተኩረው በህጉ ይዘት (Substance) ላይ ሳይሆን ህጉ በሚወጣበትና ስራ ላይ በሚውልበት ሂደትና ቅርፅ (Procedure) ላይ ነው። ይህንን ነው “ውስጣዊ ግብረገብነት” የሚለው። ህግጋት ፍትሃዊ፣ ግልጽ እና ሊተገበሩ የሚችሉ ካልሆኑ የህግነት ባህሪያቸውን ያጣሉ። ፉለር ይህንን ሃሳብ ለማስረዳት (King Rex) የተባለውን ምናባዊ ንጉስ ታሪክ እንደ ምሳሌ ያነሳል። ንጉስ ሬክስ ፍጹም መልካም ፍላጎት ቢኖረውም፣ በስምንት ተከታታይ ስህተቶች ምክንያት የተሳካ የህግ ስርዓት መገንባት ሳይችል ቀርቷል። ➨The Eight Principles of Legality አንድ የህግ ስርዓት ህጋዊ ክብርና የሞራል ግዴታን ለመፍጠር ማሟላት ያለበት ስምንት ውስጣዊ መመዘኛዎች አሉት። እነዚህ መርሆች ሲጣሱ ህጉ ይከሽፋል፦ ▶አጠቃላይነት (Generality): ህግ ግለሰባዊ ውሳኔ ሳይሆን፣ በሁሉም ላይ በእኩልነት የሚተገበር አጠቃላይ መመሪያ መሆን አለበት። በግለሰብ ደረጃ የሚሰጡ በየቀኑ የሚቀያየሩ ውሳኔዎች ህግ ሊሆኑ አይችሉም። ▶ይፋዊነት (Promulgation): ህግ ለተፈፃሚዎቹ በግልጽ ሊታወቅና ሊታወጅ ይገባል። ህዝብ የማያውቀው ሚስጥራዊ ህግ የሰዎችን ባህሪ ሊመራ አይችልም። ▶ ወደኋላ የማይመለስ መሆን (Non-Retroactivity): ህግ ወደፊት ለሚፈጸሙ ድርጊቶች እንጂ፣ ትናንት በተደረገ ነገር ላይ ዛሬ ወጥቶ ሰውን ሊቀጣ አይችልም። ይህ የፍትህ መሰረት ነው። ▶ ግልጽነት (Clarity): የህግ ቋንቋ ህዝብ ሊረዳው የሚችል መሆን አለበት። ማንም ሊፈታው የማይችለው ረቂቅና ድብቅ ህግ መኖርና አለመኖሩ አንድ ነው። ▶ አለመቃረን (Non-Contradiction): በአንድ ስርዓት ውስጥ ያሉ ህግጋት እርስ በርሳቸው መጋጨት የለባቸውም። አንዱ ህግ “ፈቅጃለሁ” የሚለውን ሌላው “ከልክያለሁ” ካለ ህዝቡን ግራ ያጋባል። ▶ ሊተገበር የሚችል መሆን (Possibility of Compliance): ህግ ከሰው አቅም በላይ የሆነን ነገር እንዲያደርጉ ማዘዝ የለበትም። ለምሳሌ “ነገ ጠዋት ሁሉም ዜጋ መብረር አለበት” የሚል ህግ ቢወጣ ተፈፃሚነት ስለሌለው ህግ ሊባል አይችልም። ▶ ጽናት ወይም ቀጣይነት (Constancy): ህግ በየቀኑና በየሰዓቱ መለዋወጥ የለበትም። ሰዎች የወደፊት ህይወታቸውንና እቅዳቸውን ሊመሩበት የሚችል አንጻራዊ መረጋጋት ሊኖረው ይገባል። ▶በፅሁፍና በተግባር መካከል ያለው መጣጣም (Congruence): በይፋ የወጣው ህግና ፍርድ ቤቶች ወይም አስፈፃሚ አካላት በተግባር የሚተረጉሙት ህግ አንድ መሆን አለባቸው። ህጉ ወረቀት ላይ ብቻ ቀርቶ መሬት ላይ ሌላ አምባገነናዊ አሰራር ካለ ህጋዊነት የለም። የፉለር ፍልስፍና ዋና ረቂቅነት የሚገለጠው እዚህ ላይ ነው፤ እነዚህ ስምንት መርሆች የህግ መውጫ መንገዶች ብቻ ሳይሆኑ በራሳቸው የፍትህና የግብረገብነት ምሰሶዎች ናቸው። አንድ ገዢ አካል የፈለገውን ያህል ጨካኝ ቢሆን እንኳን፣ እነዚህን ስምንት መርሆች ጠብቆ ህግ ለማውጣት ከተገደደ፣ የስርዓቱ ውስጣዊ የሞራል ጥንካሬ ክፉና አድሏዊ ህግ እንዳይወጣ በራሱ ትልቅ ጋሻ ይሆናል። ህግ የሰዎችን ክብርና ነጻነት የሚጠብቀው ይዘቱ ብቻ ሳይሆን፣ የሚወጣበት ፍጹም ስነ-ስርዓታዊ ጥበብ ጭምር ነው። የህግ ውስጣዊ ሞራል ሲጣስ፣ የህግ ስርዓቱ ይፈርሳል። ህዝቡም ያንን ህግ የመታዘዝ የሞራል ግዴታው አብሮ ያበቃል። ህግ የሃይል መጫኛ ሳይሆን፣ በገዢና በተገዢ መካከል የሚደረግ የጋራ መከባበርና የታማኝነት ውል (reciprocal burden) ነው። #LegalPhilosophy #leadership #LegalEducation #Ethiopia @LawStudentsUnion telegram Channel

Paid Internship Opportunity: CEHRO The Consortium of Ethiopian Human Rights Organizations (CEHRO) is accepting applications for its paid internship program. Roles include supporting research, advocacy, workshops, and project implementation. The program offers hands-on experience, mentorship, and modest financial compensation. Requirements • Students or recent graduates • Passion for human rights and democracy • Good English skills ⏳Duration: 3 Months(possible extension) 📍Location: Addis Ababa 🔗Apply: https://forms.gle/LdzGbieF9LwHPQ6u6 For more: here Deadline: June 20, 2026 የሕግ መረጃ @legal_infoo

ኒጀር ግብረ-ሰዶማዊነትን በህግ ከከለከሉ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ተርታ ተቀላቅላለች ። የኒጀር ወታደራዊ ሁንታ ግብረ-ሰዶማዊነትን በወንጀል የሚቀጣ አዲስ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ማውጣቱን አስታወ
ኒጀር ግብረ-ሰዶማዊነትን በህግ ከከለከሉ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ተርታ ተቀላቅላለች ።  የኒጀር ወታደራዊ  ሁንታ  ግብረ-ሰዶማዊነትን በወንጀል የሚቀጣ አዲስ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ማውጣቱን አስታወቀ። ከሀገሪቱ የፍትህ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ አዲሱ ህግ ከትናንት በስቲያ ሐሙስ ጀምሮ ገቢራዊ ተደርጓል።  ስራ ላይ የዋለው አዲሱ ህግ  ግብረ-ሰዶማዊነትን ወይም መሰል ድርጊቶችን የፈጸመ ወይም ለመፈጸም የሞከረ ማንኛውም ሰው ከ5 እስከ 10 ዓመት በሚደርስ እስራት እና በገንዘብ ይቀጣል። ቅጣቱ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸውን ሰዎች ጋብቻ ያስፈጸሙ ሰዎችን፣ ምስክሮችን፣ ጋብቻው እንዲፈጸም ፍቃድ የሰጡትን እንዲሁም የሰርጉን አዘጋጆች በሙሉ ያጠቃልላል ነው የተባለው። ከዚህ ቀደም በኒጀር ግብረ-ሰዶማዊነት በህግ የተከለከለ ባይሆንም፣ በህብረተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ማግለል ይደርስበት ነበር። ኒጀር ይህንን እርምጃ በመውሰድ ግብረ-ሰዶማዊነትን በህግ ከከለከሉ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ተርታ ተቀላቅላለች።  ግብረሰዶማዊነት በሴኔጋል፣ ኬንያ፣ ሴራሊዮን እና ታንዛኒያ እስከ 10 ዓመት እና ከዚያ በላይ በሆነ እስራት ያስቀጣል። በሶማሊያ፣ ዩጋንዳ እና ሞሪታኒያ ደግሞ የወንጀሉ ቅጣት እስከ ሞት ፍርድ ሊደርስ እንደሚችል ዘገባው አመልክቷል። ======================

consti,pil,ethics_cr_pc,tort,_succe,EVI,_Family,labor,,cipc,lbo.doc1.66 KB

Model exam 2018 woliyta sodo university

📢 AUDIENCE REGISTRATION OPEN | HABEGAR QUIZ UNIVERSITY STUDENTS COMPETITION Would you like to be part of a live television a
📢 AUDIENCE REGISTRATION OPEN | HABEGAR QUIZ UNIVERSITY STUDENTS COMPETITION Would you like to be part of a live television audience and witness one of Ethiopia's exciting university quiz competitions? Applications are now open for audience members to attend the recording of the Habegar Quiz University Students Competition. 🎬 Program Details 📅 Thursday, June 18, 2026 – 100 Audience Members 📅 Friday, June 19, 2026 – 100 Audience Members 📍 Location: Addis Ababa 📺 Brodcast on EBC 🤝 Organized by Projust Institute of Research and Debebe Hailegebriel Law Office in collaboration with Abrhot Library. ✅ Eligibility • Must be available in Addis Ababa. 🎁 Benefits • Experience a live television production • Network with participants and audience members from diverse backgrounds • Be part of a nationally televised educational program 📝 Apply Here: https://forms.gle/L5ddAnApnbqqJSmK8 ⏳ Application Deadline Applications will remain open until all available audience seats are filled.

አካሌ ነፃ ይዉጣልኝ ( Habeas Corpus ) ምን ማለት ነው ? ◼️ ሰዎች በተለያዩ ቦታዎች እና ሁኔታዎች በወንጀል ተጠርጥረው ለእስር ሊዳረጉ ይችላሉ ። በወ/ስ/ስ/ህግ ሆነ በህገ _መንግስቱ ከተረጋገጡ መብቶች መካከል በ 48 ሰዓት ዉስጥ በአቅራቢያ ወደሚገኝ ፍርድ ቤት መቅረብ ይገኝበታል ። ይህ ሳይሆን ሲቀር ተጠርጣሪዉም ሆነ የእርሱ ተወካይ ያለ አግባብ መታሰራቸው ቀሪ እንዲሆን ወይም የአካሌ ነፃ ይዉጣልኝ አቤቱታ ማቅረብ ይችላሉ ። ◾️ Habeas Corpus  የሚለው ቃል የላቲን ሲሆን " Show me the body "  የሚል ትርጓሜ አለው ። ◾️ በዚህ ስርዓትም የታሠረዉን ግለሰብ ያሰረው አካል የማቅረብ ወይም  " to produce the body " ግዴታ አለበት ። ⚫️ የዚህ ዓይነቱ ክስ በየትኛው ፍርድ ቤት ይቀርባል ? የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን ስልጣን ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 1234/13  አንቀጽ 5 (1) (ኘ ) መሠረት አካሌ ነፃ ይዉጣልኝ አቤቱታ በፌዴራል ፍ/ቤቶች ይቀርባል ። ◼️ በህገ _ መንግስቱ ምዕራፍ 3 ላይ የተዘረዘሩት መሠረታዊ መብቶች እና ነፃነቶችን ለማስከበር ፍርድ ቤት ለመታየት ብቁ የሆኑ ጉዳዮችን ለመዳኘትም በዚሁ አዋጅ ለከፍተኛ ፍርድ ቤት ስልጣኑ ተሰጥቷል ። ⚫️ ይህ በእንዲህ እንዳለ ስለ አቤቱታ አቀራረቡ የፍትሐብሔር ስነ _ ስርዓት ህጋችን ምን ይላል ? የዚህ ህግ አንቀጽ 177_ 179 ያሉት ድንጋጌዎች የአካሌ ነፃ ይዉጣልኝ ክስ በማን ፣ የትኛው ችሎትና ማንን መክሰስ እንደሚቻል አብራርቶ ያስቀምጣል ። ◾️ አቤቱታው በራሱ በተጠርጣሪው ወይም ለእርሱ ሲል በሚቀርበው ሰው ፦ _ በቃለ _ መሀላ የተደገፈ _ የታሳሪዉን እና የአሳሪዉን ስም _ የተያዘበት ስፍራ እና _ ካሉም ይህንን የሚያስረዱ ምስክሮች ስም ያካተተ መሆን አለበት ። ፍርድ ቤቱም የተያዘውን ሰው በዋስ ወይም ያለ ዋስ እንዲለቀቅ አስፈላጊውን የግራቀኙን ክርክር ከሰማ በኋላ ሊወስን ይችላል ።                        ,,,,,,,,,,,✍️✍️✍️ @LawStudentsUnion

#ExitExamProtocols የ2018 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም ይሰጣል። የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ሊከተሏቸው የሚገቡ የስነ-ምግባር መመሪያዎች፦ ➫ ተፈታኝ ተማ
#ExitExamProtocols የ2018 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም ይሰጣል። የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ሊከተሏቸው የሚገቡ የስነ-ምግባር መመሪያዎች፦ ➫ ተፈታኝ ተማሪዎች በመፈተኛ ክፍል ውስጥ የሞባይል ስልክ፣ ሚሞሪ ያለው የእጅ ሰዓት፣ ሳይንቲፊክ ካልኩሌተር፣ የራስ ያልሆነ መታወቂያ እንዲሁም ማንኛውም አይነት የጦር መሳሪያ ይዘው መገኘት አይችሉም፡፡ ➫ ተፈታኝ ተማሪዎች ከ3ዐ ደቂቃ ቀድመው በተመደቡበት ክፍል መገኘት አለባቸው፡፡ ➫ ተፈታኞች ከተመደቡበት ክፍል ውጪ መፈተን ውጤት ያሰርዛል፡፡ ➫ ተፈታኝ ተማሪዎች የፈተና አስፈጻሚን ትዕዛዝ ማክበር ይጠበቅባቸዋል። ➫ ተፈታኞች የፋይዳ መታወቂያ እንዲሁም ራሳቸውን የሚገልፅ መታወቂያ መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ ➫ በሌላ ሰው ስም፣ መለያ ቁጥር እና የይለፍ ቃል መፈተን አይቻልም፡፡ @LawStudentsUnion @LawStudentsUnion

+7
Licensing of Insurance Surveyors Directive Number SIB/22/2002

Financial Inclusion Directives

Repost from N/a
የጭቃ ቤት ግንባታ ተከለከለ‼️ ለአዳዲስ የጭቃ ቤት ግንባታ ፈቃዶች መታገዳቸው ተገለጸ‼️ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ከተሞችን ዘመናዊ፣ ጽዱና ከአየር ንብረት ለው
+1
የጭቃ ቤት ግንባታ ተከለከለ‼️ ለአዳዲስ የጭቃ ቤት ግንባታ ፈቃዶች መታገዳቸው ተገለጸ‼️ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ከተሞችን ዘመናዊ፣ ጽዱና ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር የሚስማሙ ለማድረግ አዳዲስ የጭቃ ቤት ግንባታ ፈቃዶች በማዘጋጃ ቤቶች በኩል እንዳይጸድቁ በይፋ አገደ። የቢሮው ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ዘውዴ ዘታ ለዞን መዋቅሮችና ለከተማ አስተዳደሮች ባስተላለፉት መመሪያ መሠረት፣ እገዳው የደን መመናመንንና የተፈጥሮ አደጋዎችን ለመከላከል እንዲሁም የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግቦችን ለማሳካት ያለመ ነው። ከተሞች ይበልጥ እንዲዘምኑ ለማድረግ በማንኛውም ግንባታ ላይ ደረጃቸውን የጠበቁ የብሎኬት፣ የጡብና የዘመናዊ ሕንጻ ግብዓቶችን መጠቀም እንደሚገባ ተገልጿል። ይህ አዲስ መመሪያ ደብዳቤው በይፋ ከወጣበት ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በጥብቅ ተፈጻሚ የሚሆን ሲሆን፣ በማንኛውም ማዘጋጃ ቤት በኩል የጭቃ ቤት ግንባታ ፈቃድ ማጽደቅ ሙሉ በሙሉ የተከለከለ መሆኑ ታውቋል። https://t.me/ethiopianfuturejustice https://t.me/ethiopianfuturejustice https://t.me/ethiopianfuturejustice

Repost from N/a
+6
Employment law model exit exam.doc0.60 KB

Repost from N/a
+6
Employment law model exit exam.doc0.60 KB

Repost from N/a
የማስረጃ ምንነት 🇪🇹⚖️🇪🇹⚖️🇪🇹⚖️🇪🇹⚖️🇪🇹⚖️🇪🇹⚖️🇪🇹⚖️🇪🇹⚖️🇪🇹⚖️🇪🇹 ማስረጃ ማለት ማንኛውንም ፍሬ ነገር ወይም መደምደሚያን ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል የሚጠቅም መረጃ ነው፡፡በክስ ማሰማት ሂደትም በጭብጥ የተያዙ ፍሬ ነገሮችን ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል በሚል የሚቀርብ መረጃ ነው ፡፡ ማስረጃ የአንድን ነገር መፈጸም፣ወይም መፈጸም ግዴታ ሆኖ እያለ ባለመፈጸም ህግን መተላለፍ በወንጀል የሚያስጠይቅ በሆነ ጊዜ ድርጊቶቹ እውነት የተፈጸሙ መሆኑን ጉዳዩ ለሚቀርብለት ፍርድ ቤት ለማሳመን የሚቀርቡ ሲሆን በሌላ በኩል ተከሳሽም የቀረበበትን ክስ በተመለከተ ያለመፈጸሙን ለፍርድ ቤቱ በማረጋገጥ ለማስተባበል የሚያቀርባቸው መረጃዎች ናቸው፡፡ ለምሳሌ በስርቆት ወንጀል የተከሰሰ ሰው ድርጊቱን በእርግጥም ፈጽሞታል ወይስ አልፈጸመውም የሚለውን በፍርድ ቤት የሚያዝ ጭብጥ ለማስረዳት ማስረጃዎች ወሳኝ ናቸው፡፡በመሆኑም ድርጊቱን መፈጸሙን የሚያረጋግጡ የተለያዩ ማስረጃዎችን ማቅረብ የግድ ይሆናል ማለት ነው፡፡ ተከሳሽም ቢሆን ድርጊቱን ያልፈጸመ መሆኑን የሚያስረዱለትን የተለያዩ ማስረጃዎችን የማቅረብ እና የማሰማት መብት አለው፡፡ ማስረጃች እንደየባህርያቸው በተለያዩ መንገዶች የሚርቡ ሲሆን የሰው የምስክርነት ቃል ከሆነ ምስክሩን አቅርቦ በማሰማት፣ የሰነድ ማስረጃ ከሆነ ሰነዱን አቅርቦ ይዘቱን በማሳየት እንዲሁም በኤግዚሂቢትነት የሚቀርብ ዕቃ ከሆነ ይህንኑ ዕቃ በማቅረብ ፍርድ ቤቱ ግንዛቤ እንዲወስድ በማድረግ በጭብትነት የተያዘውን ፍሬ ነገር መኖር ለማስረዳት እና የመደምደሚያውን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ይቻላል፡፡ ምስክሮቹ የሰጡት ወይም የሚሰጡት ቃል፣ ከቀረበው ሰነድ ላይ ወይም ዕቃ ላይ የተወሰደው ግንዛቤ ወይም መረዳት ማስረጃ ስንለው እነኚህኑ ማስረጃዎች ፍርድ ቤት ለማቅረብ የተጠቀምንባቸው ማለትም ምስክሩ፣ ሰነዱ እና ዕቃው ማስረጃን የማቅረቢያ ዘዴ በማለት ለያይተን መመልከት እንችላለን፡፡ በሌላ በኩል ከላይ ከጠቀስነው ዝርዝር ሀሳብ አንጻር በመረጃ እና በማስረጃ መካከል ያለ ልዩነት በውል መታወቅ አለበት፡፡ ማስረጃዎች ሁሉ መረጃዎች ሲሆኑ መረጃዎች ሁሉ ግን ማስረጃ ሊሆኑ አይችሉም፡፡ማስረጃ ማለት ሰዎች ከጥናት፣ ከንባብ፣ ከሰዎች ጋር ከሚደረግ ግንኙነት፣ ቀድሞ ከነበረ እውነታ ወይም ፍሬ ነገር እና በተግባር ከተገኘ ልምድ የሚመነጭ የሰዎች እውቀት ማለት ነው፡፡ ማስረጃ ተፈጸመ የተባለን ወንጀል አፈጻጸም እና መችየት፣ የፈጻሚን ማንነት፣ በወንጀል ተግባሩ የተገኘው ጥቅም እና የደረሰን ጉዳት እና የመሳሰሉትን ፍሬ ነገሮች ለማረጋገጥ የምንጠቀምበት መረጃ ነው፡፡

Constitutional law Register and test your intelligence. Serve as a junior Juror Register here: https://forms.gle/aQJibRQUCyba
Constitutional law Register and test your intelligence. Serve as a junior Juror Register here: https://forms.gle/aQJibRQUCyba69qd9

+5
MoANR GTP II final draft base case scenario Amharic Final.pdf1.42 MB

MoA