የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን/Federal Tax Appeal Commission
الذهاب إلى القناة على Telegram
864
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+37 أيام
+530 أيام
أرشيف المشاركات
የፍትህ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች የኢቢሲን የሚዲያ ኮምፕሌክስን ጎበኙ፡፡
********************
ፌታይኮ
የፍትህ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች አዲስ አበባ ሸጎሌ የሚገኘውን የኢቢሲ ሚዲያ ኮምፕሌክስን ህዳር 11/2017 ዓ.ም. ጉብኝት አድርገዋል።
በተለያዩ በዓለም አቀፍና በአገር ውስጥ ቋንቋዎች አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘው ኢቢሲ ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ የሚጠቀምና ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች የተዋቀረ መሆኑን መመልከት ተችሏል፡፡
ኢቢሲ ከተቋቋመበት እስከ አሁን ድረስ ሲጠቀምባቸው የነበሩትን መሣሪያዎች እና በፎቶግራፍ የተደገፉ የተለያዩ መረጃዎች የያዘውን በኢቢሲ ሙዚየም ጉብኝት የተደረገ ሲሆን ለተነሱ ጥያቄዎች በባለሙያ ገለጻና ማብራሪያ ተሰጥቷል።
ነፃና ገለልተኝነት ለፍትሐዊ የታክስ ስርዓት !
ስለ ፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛ አድራሻችንን ይጠቀሙ ፡-
ፌስ ቡክ 👇
https://www.facebook.com/ftacofficial
ቴሌግራም 👇
https://t.me/ftac_official
ትዊተር 👇
https://twitter.com/federal_appeal
ድረ ገፅ 👇
http://ftac.gov.et/en-us/
ዩ ቱብ 👇
https://www.youtube.com/channel/UCzpuuuXybdHh7BlgWXMVIGw
አድራሻችንን follow, join, subscribe, like, comment, and share በማድረግ ህብረተሰቡ ስለ ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ትክክለኛ መረጃ እንዲያገኝ የድርሻዎን ይወጡ
ተለዋጭ ቀጠሮ ስለማሳወቅ
ህዳር 06/2017 ዓ.ም ተቀጥረው የነበሩ የከሰዓት ቀጠሮዎች ወደ ህዳር 17/2017 ዓ.ም ከሰዓት የተዛወሩ መሆናቸውን እየገለፅን በተጨማሪም ሰኞ 09/03/2017 ዓ.ም. የነበረው የጠዋት ቀጠሮ ወደ ህዳር 17/2017 ዓ.ም. ጠዋት የተዛወሩ መሆናቸውን በአክብሮት እንገልፃለን ፡፡
ነፃና ገለልተኝነት ለፍትሐዊ የታክስ ስርዓት !
ስለ ፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛ አድራሻችንን ይጠቀሙ ፡-
ፌስ ቡክ 👇
https://www.facebook.com/ftacofficial
ቴሌግራም 👇
https://t.me/ftac_official
ትዊተር 👇
https://twitter.com/federal_appeal
ድረ ገፅ 👇
http://ftac.gov.et/en-us/
ዩ ቱብ 👇
https://www.youtube.com/channel/UCzpuuuXybdHh7BlgWXMVIGw
አድራሻችንን follow, join, subscribe, like, comment, and share በማድረግ ህብረተሰቡ ስለ ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ትክክለኛ መረጃ እንዲያገኝ የድርሻዎን ይወጡ
የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ዳኞች ፣ አመራሮች እና ሰራተኞች በሀገራዊ የ100 ቀናት እቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሄዱ፡፡
********************
ፌታይኮ
ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም.
የኮሚሽኑ ዳኞች አመራሮች እና ሰራተኞች በ2017 በጀት ዓመት ሀገራዊ የ100 ቀናት እቅድ አፈጻጸም ላይ በተቋሙ የችሎት አዳራሽ ውይይት አካሂደዋል፡፡
ሀገራዊ የ100 ቀናት ዕቅድ አፈጻጸም ውይይቱን የመሩት የኮሚሽኑ ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ሙሉጌታ አያሌው ፤ በሀገራችን እየተከናወኑ ያሉ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች እና የሪፎርም ውጤቶች ላይ ሠራተኛው በቂ ግንዛቤ እንዲያገኝ ስለሚያስችል እንዲህ አይነት ውይይቶች ሠራተኞችን ማሳወቅ እና በየጊዜው ያለማቋረጥ ጊዜ ተመድቦለት የሚከናወን ሊሆን እንደሚገባው ተናግረዋል፡፡
በ100 ቀናት የእቅድ አፈፃፀም መድረክ የተነሱ ዋና ዋና ነጥቦች
o አለም አቀፍ የፖለቲካል ኢኮኖሚ አዝማሚያና ለኢትዮጵያ ያለው አንድምታ
o የሪፎርሙ ተጠባቂ ፋይዳዎች እና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፋይዳዎች
o ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢ መፍጠር
o ያደገ ምርትና ምርታማነትን ማረጋገጥ
o ያደገ የውጭ ምንዛሬ ግኝት መፍጠር
o የተረጋጋ የማክሮ ኢኮኖሚ፣ የዘርፎች ምርታማነትና ተወዳዳሪነት መፍጠር
o የመንግስትን ገቢ ማሳደግ
o ዋና ዋና የሸቀጦች ፣ የወርቅ ፣ የመአድን ፣ የኤክስፖርት አፈጻጸም
o የስራ እድል ፈጠራ አፈፃፀም
o ተኪ ምርት መፍጠር
o የመንግስት አገልግሎት እና የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ
o የዋና ዋና ፕሮጀክቶች አፈፃፀም
o ከህዳሴው ግድብ እና የኮሪደር ልማት
የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የአገልግሎት የጥራት መርሆዎች
የተገልጋዩ ባለቤትነትና ተደማጭነት ማረጋገጥ ፣
የደንበኞች እርካታና የአገልግሎት ቀጣይነት ማሳደግ ፣
ትክክለኛ፣ ሀቀኛ፣ ግልፅነትና ፍትሐዊ ከስህተት የፀዳ አገልግሎት መስጠት ፣
ጥራት ያለው ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ፣
ለተሰጡ ውሳኔዎችና አገልግሎቶች ተጠያቂ መሆን ፣
ለተቋማዊ እሴቶቻችን መገዛት ፣
የአገልግሎት ተደራሽነትና ተቀባይነትን ማሳደግ ፣
የሠራተኞች ተነሳሽነትና ውጤታማነት ማሳደግ፡፡
የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ክብርት ወ/ሮ ሃና አርዓያሥላሴ የፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር ሆነው ስለተሾሙ እንኳን ደስ አሎት እያለ መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንልዎ ይመኛል!
