cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

مشاركات الإعلانات
587
المشتركون
+224 ساعات
+77 أيام
+1730 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

Photo unavailableShow in Telegram
የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ለሰራተኞቹ ከተረጂነት መላቀቅ በሚል ስልጠና ሰጠ፡፡ ******************** ፌታይኮ ሰኔ 18 ቀን 2016 ዓ.ም የኮሚሽኑ ዳኞች ፣ ከፍተኛ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት ከተረጂነት መላቀቅ በሚል ስልጠና ወሰዱ፡፡ ከተረጂነት መላቀቅ በሚል ስልጠና የሰጡት የኮሚሽኑ ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ሙሉጌታ አያሌው፤የተረጂነት አስተሳሰብ በመስበር ተረጂ የነበረ የህብረተሰብ አካልን ለይቶ በማወያየት በዘላቂነት ከተረጂነት በማላቀቅ እራሳቸውን እንዲችሉ ማድረግ እንደሚገባና ድህነትን ተከትሎ የሚመጣ ልመና ክብረ-ነክ በመሆኑ ልንፀየፈው እንደሚገባና የተቸገሩትን እንዴት በቋሚነት ማገዝና ከተረጂነት ወደ ምርታማነት እንደሚሸጋገሩ ሁሉም ተቋም በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ ይኖርበታል ብለዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ በቀጣይ በስራ ኢኮኖሚን ማጠናከር ፣ ነፃ ፖሊሲ ማዘጋጀት ፣ ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ ፣ ተረጂነትን የሚጠየፍ ትውልድ መገንባት ዋነኛ ስራችን አድርገን መንቀሳቀስ እንደሚኖርብን ተናግዋል፡፡
إظهار الكل...
የታሪፍ አመዳደብ የጉምሩክ ታሪፍ ምንድን ነው? የጉምሩክ ታሪፍ ማለት ወደ ጉምሩክ ክልል በሚገቡ እና ከጉምሩክ ክልል በሚወጡ ማናቸውም ዕቃዎች ላይ የሚከፈል ቀረጥን ለመወሰን የሚያስችል የዕቃዎች የቀረጥ ማስከፈያ ምጣኔ ነው፡፡ የታሪፍ አመዳደብ ምን ማለት ነው? በዕቃዎች ላይ ሊከፈል የሚችልውን የቀረጥ ምጣኔ ለማወቅ ዕቃዎችን በኤች ኤስ (የተጣጣመ የሸቀጦች መግለጫና መለያ ስርዓት) ወይም በታሪፍ መጽሀፍ ውስጥ በየትኛው ክፍል፣ ምዕራፍ አንቀጽና ንዑስ አንቀጽ ስር እንደሚመደብ ለማወቅ የሚደረግ ስራ ነው፡፡ የታሪፍ መጽሀፍ ወይም ኤች ኤስ (የተጣጣመ የሸቀጦች መግለጫና መለያ ስርዓት)ምንድን ነው? በንግድ ወይም በሌላ ምክንያት በዓለም ላይ የሚንቀሳቀሱና የሚዘዋወሩ ዕቃዎችን በቀላሉ፣ ቴክኒካዊ በሆነ ስልት እና ወጥነት ባለዉ መንገድ ለይቶ ለማወቅ ዕቃዎችን በክፍሎች በምዕራፎች፣ በአንቀጽና በንዑስ አንቀጾች በመለየት ተጠንቶ የተዘጋጀ ስርዓትን መሰረት ያደረገ ሰነድ/መጽሀፍ ነው፡፡ የዕቃዎችን ታሪፍ እንዴት መመደብ ይቻላል? በጉምሩክ አዋጅ 859/2006 አንቀጽ 102/3 ላይ የዓለም የጉምሩክ ድርጅት (World Customs Organization) ስለሸቀጦች አመዳደብ የሚያወጣው ሰነድ ስለዕቃዎች የታሪፍ አመዳደብ ወሳኝ ማስረጃ ተደርጎ ይወሰዳል ተብሎ ተደንግጓል፡፡ በዚህ መሰረት በአለም የጉምሩክ ድርጅት አባል ሀገራት ስምምነት የጸደቀው የተጣጣመ የዕቃዎች መግለጫና መለያ ስርዓት (Harmonized Commodity Description and Coding System) በኢትዮጵያ ለእቃዎች ታሪፍ አመዳደብ ጥቅም ላይ ይውላል ማለት ነው፡፡ በአለማችን ከሚገኙ እቃዎች ከ 95 በመቶ በላይ የሚሆኑ ዝርዝርን ከላይ በተገለጸው አግባብ ስልታዊና ወጥ በሆነ አግባብ ለይቶ ለማወቅ ይቻል ዘንድ እቃዎቹ በታሪፍ መጽሀፍ ውስጥ በክፍሎች፣ በምዕራፎች፣ በአንቀጽና በንዑስ አንቀጽ ተደራጅተው ይገኛሉ፡፡
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
የተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት መሪ እቅድ አቶ በላይሁን ይርጋ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ.ፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ እና የሥራ ባልደረቦቻቸው ፣ አቶ ሙሉጌታ አያሌው የኮሚሽኑ ፕሬዚዳንት እና የማኔጅመንት አባላት በተገኙበት ዛሬ ሰኔ 4 ቀን 2016 ዓ.ም. በፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የስብሰባ አዳራሽ ቀርቧል፡፡ ******************** የ2017 በጀት ዓመት የእቅዱ ዓላማ የታክስ ይግባኝ ስርዓቱ ፍትሐዊ እንዲሆን የቅሬታ መዛግብትን በሕግና በአሰራር በመመርመር ጥራቱን የጠበቀ ውሳኔ በመስጠት ፍትሐዊነቱን ማረጋገጥ ሲሆን ውስብስብ ባህሪ ያላቸውን የይግባኝ ጉዳዮች መለየትና በጥልቀት መመርመር ፣ ህግና አሰራርን መሰረት ያደረገ ውሳኔ የመስጠት አቅም 100% ማድረስ ፣ ተከራካሪ ወገኖችን በህግ አግባብ ማከራከር ፣ ቀልጣፋና ውጤታማ የሆነ የመዛግብት አከፋፈት ፣ አጠባበቅ ፣ የጉዳዮች አተገባበርና አቤቱታ አቀራረብ ሥርዓት መዘርጋት ፣ ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዩን እርካታ ማረጋገጥ ፣ የተዘረጉ አሰራሮችን በየጊዜው እየፈተሹ ማሻሻል እንደሚገባ ተገልጿል፡፡
إظهار الكل...
👍 2
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.