ar
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد
1 745
المشتركون
+124 ساعات
+57 أيام
-130 أيام
أرشيف المشاركات
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ  በዘንድሮ የትምህርትና ስልጠና ዘመን የተቀበላቸውን አዲስ ገቢ ሰልጣኝ ተማሪዎች ወደ መደበኛ ስልጠና ከመግባታቸው አስቀድሞ ሰልጣኞችን በሁሉም ረገድ ዝግጁ የሚያደርጋቸውን የLife Skill ስልጠና በዛሬው እለት መስጠት ጀመረ።  በስልጠናው ሰልጣኝ ተማሪዎቹ ከ Life skill ስልጠናው በተጨማሪም ስለ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ፖሊሲና እስትራቴጂ እንዲሁም በዘርፉ ስለሚሰጡ የሙያ መስኮች ሰፉ ያለ ማብራርያ የሚሰጣቸው መሆኑም ተገልጿል:: በዚህም ሰልጣኝ ተማሪዎቹ ሰለ ቴ/ሙ/ት/ስ ዘርፍ እንዲሁ እሁን ላይ ያለውን የገበያ ፍላጎት በጥልቅ ከተረዱና ግንዛቤውን ካገኙ በኃላ ለመሰልጠን የወሰኑትን የሙያ መስክ ምርጫቸውን ለማስተካከል በእጅጉ እንደሚረዳቸውም ይትመናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ህዳር 24/2016 ዓ.ም

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ስራ ሂደት ከስራና ክህሎት ቢሮ ጋር በመተባበር በአስተዳደሩ ለሚገኙ ጀማሪ ኢንተርፕራይዞች መሰረታዊ የኢንተርፕረነርሺፕ ስልጠና ሰጠ:: በዚህ ለ 4 ቀን በቆየው ስልጠና 38 የሚሆኑ ጀማሪ የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የተሳተፉ ሲሆን ለተሳታፊዎች  በስራ ፈጠራ እና ንግድ ክህሎት ዙሪያ ያተኮረ ስልጠና መሰጠቱንና ይህም ኢንተርፕራይዞች በሚያደርጉት የእድገት ሽግግር ላይ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረውም ተገፅጿል:: ሰልጣኞች በበኩላቸው ይህን ስልጠና ወስደው በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸው ውስጥ ተግባራዊ እንደሚያደርጉት በመግለፅ በቴክኖሎጂ ሽግግርና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት የሚደረጉላቸው የድጋፍ ማእቀፎችን ለመጠቀምና ራሳቸውን ለማሳደግ ፍላጎትና ተነሳሽነት እንደፈጠራላቸው ተናግረዋል። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ህዳር 21/2016 ዓ.ም

መረጃውን በማድረስ ይተባበሩን!! ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባወጣው የቅጥር ማስታወቂያ ላይ ተመዝግባችሁ የፅሁፍ ፈተና ያለፋችሁ የከተማችን ወጣቶች የኢንተርቪው ፈተና ህዳር 25/2016 ዓ
+5
መረጃውን በማድረስ ይተባበሩን!! ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባወጣው የቅጥር ማስታወቂያ ላይ ተመዝግባችሁ የፅሁፍ ፈተና ያለፋችሁ የከተማችን ወጣቶች የኢንተርቪው ፈተና ህዳር 25/2016 ዓ.ም ጀምሮ በሰንጠረዡ በተጠቀሰው ሰዓት ስለሚሰጥ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እንድትገኙ ጥሪ ተላልፏል።

"ብዝሃነትና እኩልነት ለአገራዊ አንድነት!" የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አመራሮችና ሠራተኞች 18ኛውን የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን አከበሩ። በዓሉ በፓናል ውይይት የተከበረ ሲሆን፣ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር የዘንድሮው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን "ብዝሃነትና እኩልነት ለአገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል የሚከበር መሆኑን አውስተው፣ አገራዊ አንድነትን ለማጽናት ሕገ መንግሥቱን መሠረት በማድረግ ጥያቄዎችን በሰላማዊ አግባብ የሚያስተናግድ ሥርዓት መገንባት ቀዳሚ የመንግሥት ትኩረት እንደሆነ ተናግረዋል። የቢሮው ምክትል ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ትምህርና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በበኩላቸው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት እና የጋራ መብታቸው የተረጋገጠበት ሕገ መንግሥት የጸደቀበትን ኅዳር 29 ቀን መነሻ በማድረግ የሚከበር መሆኑንና በሕገ መንግሥቱ የተረጋገጡ መብቶችን አስጠብቀን ልንጓዝ የምንችለው ተግባራዊ ለማድረግ ሁላችንም የድርሻችንን ስንወጣ ይሆናል ብለዋል፡፡ የውይይቱ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት የብሔር ብሔረሰቦች ቀን መከበሩ የሕዝቦችን እኩልነትና ኅብረ ብሔራዊ አንድነት ለማጠናከር ጠቀሜታው የጎላ እንደሆነ ገልጸው፣ አንድነትን ለማጠናከር ሰላምን የሚያደፈርሱ አጀንዳዎችን የማስወገድ ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አሳስበዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 17/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+7

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አመራር ፑል በISO 9001:2015 QMS አተገባበር ዙሪያ ውይይት አካሄደ:: በመድረኩ የ ISO 9001:2015 QMS ትግበራ እንደ ኮሌጅ በተሰሩት የተለያዩ ስራዎች ያሉበትን ደረጃ የተገመገመ ሲሆን በቀጣይ በአጭር ጊዜ ውስጥ ኮሌጁን የሰርቲፊኬት ተሸላሚ ለማድረግ ሁሉም የስራ ክፍሎችና የአመራር ፑሉ አባላት ስራተኛውን በማስተባበር እንዲሁም ለትግበራው የቅድሚያ ቅድሚያ በመስጠት በቁርጠኝነት መሠራት እንዳለበትና እጅግ ባጠረ ጊዜ ትግበራውን አጠናቆ እንደ ኮሌጅ ሚጠበቀውን ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባም ተገልጿል:: ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 15/2016 ዓ.ም

በጀርመን ሀገር ሚገኘው የአድራ ጀርመኒ የፕሮጀክቱ ዋና ስራ አስፍፃሚ ልኡካን ቡድናቸውን በመያዝ በአድራ ኢትዮጵያ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጉብኝት እካሄዱ:: አድራ ኢትዮጵያ ከአድራ ጀርመኒ ጋር በመተባበር በጀርመን መንግስት ድጋፍ የሶላር ፒቪ ዝርጋታ እና ጥገና የሚሆን ወርክሾፕ በማደራጀት እና ስልጠናውን ለመስጠት የሚያስችል አቅም በመፍጠር በአሁን ሰአት ከገጠር እና ከከተማ የተመለመሉ ሰልጣኞች 23 ከገጠር 20 ከከተማ በድምሩ 43 ሰልጣኞችን በመያዝ ስልጠናውን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ስልጠናውን በመስጠት ላይ ይገኛል:: ልኡካን ቡድኑም በቅድሚያ በአዲስ መልክ የተደራጀውን የፕሮጀክቱን ማሰልጠኛ ወርክ ሾፕ ተዝዋውረው የጎበኙ ሲሆን በዚህም ሰልጣኞቹ የመግቢያ ፈተና ወስደው በተገኘው ውጤት መሰረት የ Life Skill ስልጠና ካገኙ በኋላ መሰረታዊ የኤሌክትሪክ እና የኮምፒውተር ስልጠና በመውሰድ ላይም እንደሚገኙ ተመልተው በቀጣይም ሰልጣኞቹ ወደ ሶላር ስልጠና እንደሚያመሩ ከአስተባባሪዎች ገለፃ ተደርጎላቸዋል:: የአድራ ጀርመኒ ዋና ስራ አስፈፃሚና ልኡካቸው በኮሌጁ የተገኙት ይህንን ጨምሮ በፕሮጀክቱ የተሰሩ አጠቃላይ ስራዋችን ለመገምገም እና የግብአት ጉድለቶችን ለማሟላት የሚያስችል ሁኔታዋችን ለመፍጠር እንዲሁም ሰልጣኞች ያሉበትን ሁኔታ ለማየት ሲሆን በፕሮጀክቱ የታዩትን ተግዳሮቶች እና በቀጣይ ሊሰሩ የሚችሉ ተግባራትን ከኮሌጁ ዲኖች እና ከአሰልጣኝ መምህራኑ ጋር በጥልቅ ተወያይተዋል:: በመጨረሻም ልዑካኑ ከአድራ ሶላር core string comittee ጋር በመገናኘትና ውይይት በማድረግ ፕሮጀክቱ ያለበትን ሁኔታ በመገምገም ያሉትን ማነቆዎች በማውጣት ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ናቸው ያሏቸውን በዝርዝር ለይተው አስቅምጠዋል:: በተሰጠውም ግብረመልስ በፕሮጀክቱ አፈፃፀምና አጠቃላይ እንቅስቃሴ ልዑካን ቡድኑ በእጅጉ መደሰቱበመግለፅ ለኮሌጁ ምስጋናቸውን ይቀረቡ ሲሆን በቀጣይም የኢትዮጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በሶላር ዘርፍ በምስራቁ ክፍል center of exellence ሊሆን የሚችልበትን ሁኔታ ና አቅም ለመፍጠር ዝግጁ መሆናቸውንም ገልፀዋል:: ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 14/2016 ዓ.ም