fa
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

رفتن به کانال در Telegram
1 739
مشترکین
-124 ساعت
+17 روز
-730 روز
آرشیو پست ها
photo content
+7

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አመራር ፑል በISO 9001:2015 QMS አተገባበር ዙሪያ ውይይት አካሄደ:: በመድረኩ የ ISO 9001:2015 QMS ትግበራ እንደ ኮሌጅ በተሰሩት የተለያዩ ስራዎች ያሉበትን ደረጃ የተገመገመ ሲሆን በቀጣይ በአጭር ጊዜ ውስጥ ኮሌጁን የሰርቲፊኬት ተሸላሚ ለማድረግ ሁሉም የስራ ክፍሎችና የአመራር ፑሉ አባላት ስራተኛውን በማስተባበር እንዲሁም ለትግበራው የቅድሚያ ቅድሚያ በመስጠት በቁርጠኝነት መሠራት እንዳለበትና እጅግ ባጠረ ጊዜ ትግበራውን አጠናቆ እንደ ኮሌጅ ሚጠበቀውን ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባም ተገልጿል:: ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 15/2016 ዓ.ም

በጀርመን ሀገር ሚገኘው የአድራ ጀርመኒ የፕሮጀክቱ ዋና ስራ አስፍፃሚ ልኡካን ቡድናቸውን በመያዝ በአድራ ኢትዮጵያ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጉብኝት እካሄዱ:: አድራ ኢትዮጵያ ከአድራ ጀርመኒ ጋር በመተባበር በጀርመን መንግስት ድጋፍ የሶላር ፒቪ ዝርጋታ እና ጥገና የሚሆን ወርክሾፕ በማደራጀት እና ስልጠናውን ለመስጠት የሚያስችል አቅም በመፍጠር በአሁን ሰአት ከገጠር እና ከከተማ የተመለመሉ ሰልጣኞች 23 ከገጠር 20 ከከተማ በድምሩ 43 ሰልጣኞችን በመያዝ ስልጠናውን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ስልጠናውን በመስጠት ላይ ይገኛል:: ልኡካን ቡድኑም በቅድሚያ በአዲስ መልክ የተደራጀውን የፕሮጀክቱን ማሰልጠኛ ወርክ ሾፕ ተዝዋውረው የጎበኙ ሲሆን በዚህም ሰልጣኞቹ የመግቢያ ፈተና ወስደው በተገኘው ውጤት መሰረት የ Life Skill ስልጠና ካገኙ በኋላ መሰረታዊ የኤሌክትሪክ እና የኮምፒውተር ስልጠና በመውሰድ ላይም እንደሚገኙ ተመልተው በቀጣይም ሰልጣኞቹ ወደ ሶላር ስልጠና እንደሚያመሩ ከአስተባባሪዎች ገለፃ ተደርጎላቸዋል:: የአድራ ጀርመኒ ዋና ስራ አስፈፃሚና ልኡካቸው በኮሌጁ የተገኙት ይህንን ጨምሮ በፕሮጀክቱ የተሰሩ አጠቃላይ ስራዋችን ለመገምገም እና የግብአት ጉድለቶችን ለማሟላት የሚያስችል ሁኔታዋችን ለመፍጠር እንዲሁም ሰልጣኞች ያሉበትን ሁኔታ ለማየት ሲሆን በፕሮጀክቱ የታዩትን ተግዳሮቶች እና በቀጣይ ሊሰሩ የሚችሉ ተግባራትን ከኮሌጁ ዲኖች እና ከአሰልጣኝ መምህራኑ ጋር በጥልቅ ተወያይተዋል:: በመጨረሻም ልዑካኑ ከአድራ ሶላር core string comittee ጋር በመገናኘትና ውይይት በማድረግ ፕሮጀክቱ ያለበትን ሁኔታ በመገምገም ያሉትን ማነቆዎች በማውጣት ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ናቸው ያሏቸውን በዝርዝር ለይተው አስቅምጠዋል:: በተሰጠውም ግብረመልስ በፕሮጀክቱ አፈፃፀምና አጠቃላይ እንቅስቃሴ ልዑካን ቡድኑ በእጅጉ መደሰቱበመግለፅ ለኮሌጁ ምስጋናቸውን ይቀረቡ ሲሆን በቀጣይም የኢትዮጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በሶላር ዘርፍ በምስራቁ ክፍል center of exellence ሊሆን የሚችልበትን ሁኔታ ና አቅም ለመፍጠር ዝግጁ መሆናቸውንም ገልፀዋል:: ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 14/2016 ዓ.ም

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞች የፀረ-ሙስና ቀንን በፖናል ውይይት አከበሩ:: ዘንድሮ ‹‹ሙስና የጋራ ጠላታችን ነው፤በህብረት እንታገል ›› በሚል መሪ ቃል በአለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ ጊዜ እንዲሁም በሀገራችን ለ19ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ- ሙስና ቀንን እስመልክቶ የኮሌጁ ሰራተኞች እና አመራሮች በተገኙበት በፓናል ውይይት በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ውሏል፡፡ በእለቱ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ እንዲሁም የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸው ሙስናን ምንም ስሙን ማሰማመር እንደማያስፈልግና በትክክለኛ መገለጫው #ሌብነት ብለን ልንጠራው ይገባል ያሉ ሲሆን በተጨማሪም ሙስና የጋራ ጠላታችን በመሆኑ በህብረት ሆነን የማንታገለው ከሆነ ሀገራችንን ወደ ምንመኝላት የእድገት ጎዳና እንዳትደርስ አስሮ ወደኋላ የሚይዝ ማነቆ በመሆኑና ነገ ለልጆቻችን የተሻለች ኢትዮጵያን ማስረከብ የምናልም ከሆነ ይህን ሀገር ገዳይ የሆነ ካንሰር ለመግታት የሁላችንንም ቁርጠኝነትና ሀላፊነት የሚጠይቅ መሆኑን አፅዕኖት ሰጥተው ተናግረዋል:: በመቀጠል ሙስና እንደ ሀገር በምን ያህል ደረጃ እየፈተነን እንደሚገኝ የሚያሳይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነድ በአሰልጣኝ መምህር ፋሲል ማዘንጊያ ሰፋ ባለና ግልፅ በሆነ መልኩ ለኮሌጁ ማህበረሰብ የቀረበ ሲሆን ከተሳታፊዎችም የተለያዩ ሀሳቦችና ግልጽ ያልሆኑ ጉዳዮች ተነስተው ውይይት ከተደረገባቸው በኋላ የኮሌጁ ማህበረሰብ ሙስናን ለመከላከል ቁርጠኛ መሆን እንደሚገባው በመተማመን መድረኩ ፍጻሜ አግኝቷል፡፡ ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 13/2016 ዓ.ም

Repost from N/a

Repost from N/a