ar
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

الذهاب إلى القناة على Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

تُعد قناة ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 13 365 مشتركاً، محتلاً المرتبة 1 754 في فئة النقل والمرتبة 2 531 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 13 365 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 19 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 119، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 19، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 40.59‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.42‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 423 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 060 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 11.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 20 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة النقل.

13 361
المشتركون
+1924 ساعات
+677 أيام
+11930 أيام
أرشيف المشاركات
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን በቅርበት ለመከታተል የሚያስችል አዲስ አደረጃጀት በመፍጠር 27 የፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶችን ከፍቶ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወቃል። በመሆኑም የጽ/ቤቶቹን አድራሻ እና በስራቸው የሚያስተዳድሯቸውን የግንባታ ፕሮጀክቶች በተከታታይ እያስተዋወቅን እንገኛለን። በአደረጃጀቱ መሠረት በምስራቅ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ፕሮግራም ዳይሮክቶሬት ስር የጅግጅጋ አካባቢ፣ የድሬዳዋ አካባቢ፣ የሰመራ አካባቢ እና የጎዴ አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች ይገኛሉ። ለዛሬ የጅግጅጋ አካባቢ እና የድሬዳዋ አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶችን እንመለከታለን። በጅግጅጋ አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶ ማኔጅመንት ጽ/ቤት 10 (በዲዛይን እና በጨረታ ሂደት ላይ የሚገኙትን ሳያካትት) ፕሮጀክቶች የሚገኙ ሲሆን ፣ የድሬዳዋ አካባቢ የግንባታ ፕሮጀክቶች ጽ/ቤት 4 (በዲዛይን እና በጨረታ ሂደት ላይ የሚገኙትን ሳያካትት) እያስተዳደረ ይገኛል። የጽ/ቤቶቹ መቋቋም እነዚህን ፕሮጀክቶች በቅርበት በመከታተል ስኬታማ እንዲሆኑ ለማስቻል ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሎ ይታመናል፡፡ እነዚህ የግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች የአገሪቱን አስተዳደራዊ መዋቅር ሳይሆን የፕሮጀክቶችን መገኛ አካባቢ ታሳቢ በማድረግ የተደራጁና ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የጽ/ቤቶቹ አድራሻ ሊቀየር እንደሚችል ታሳቢ ተደርጎ የተደራጁ ናቸው፡፡ በመሆኑም ፕሮጀክቶቹን አስመልከቶ የአካባቢው ህብረተሰብ እና የመስተዳድር አካላት እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት አስተያየትና ጥያቄዎችን ለማቅረብ በቅርቡ ወደ ተከፈቱት ጽ/ቤቶች ማምራት እንደምትችሉ እየገለጽን ፣ እነዚህ ጽ/ቤቶች የታለመላቸውን ግብ እንዲመቱ ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት የድርሻቸውን ሊወጡ ይገባል ሲል የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ያሳስባል፡፡ የጅግጅጋ አካባቢ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት አድራሻ፡- ጅግጅጋ ከተማ ቀበሌ 07 አዲሱ ታይዋን ከጎማጣ አደባባይ ወደ ግራ 500 ሜትር ገባ ብሎ የድሬዳዋ አካባቢ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት አድራሻ:- ድሬዳዋ ከተማ ከዚራ ዳሽን ባንክ ህንጻ 2ኛ ፎቅ ለተጨማሪ መረጃ የዋናው መ/ቤት ነፃ የስልክ መስመር 8561 ይጠቀሙ፡፡ ፖ.ሳ.ቁ. 1770 ድረ ገጽ www.era.gov.et ፌስ ቡክ www.facebook.com/ethiopianroadsauthority ቴሌግራም@ethioroads

በ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ወጪ የሚገነባው የሮቤ-ጎሮ-ሶፍ ዑመር-ጊኒር መገንጠያ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ሥራ በይፋ ተጀመረ በታሪካዊው የሶፍ ዑመር ዋሻ አካባቢ በተከናወነው የግንባታ ማስጀመሪያ መርኀ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ሃብታሙ ተገኘን (ኢንጅ.) ጨምሮ በርካታ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ታድመዋል። መንገዱ 120 ነጥብ 6 ኪ.ሜ ርዝማኔ ያለው ሲሆን፥ በፌደራል መንግስት ወጪ ነው የሚገነባው። ርዕሰ-መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በሥነ-ስርዓቱ ላይ እንዳሉት፤ ፕሮጀክቱ የቱሪዝም እና የግብርናውን ዘርፍ በማነቃቃት ረገድ ጉልህ ሚና አለው። ዞኑ ባለፉት ዓመታት ተገቢው ትኩረት እንዳልተሰጠው አንስተው፥ አሁን ግን በርካታ መንገዶች እየተገነቡ መሆኑን ተናግረዋል። የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ፣ የዛሬው መንገድ ጅማሮ የኅብረተሰቡን የዘመናት የልማት ጥያቄ ምላሽ የሰጠ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይ እንደ መንግስት የተያዘውን ስንዴን ወደ ውጭ የመላክ እቅድ በእጅጉ የሚያሳልጥ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጽያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ሃብታሙ ተገኘ (ኢንጅ) በበኩላቸው፣ የባሌ ዞን በበርካታ የተፈጥሮ ጸጋዎችና የቱሪዝም መዳረሻዎች የታደለ በመሆኑ፥ በቂ የመንገድ መሠረተ-ልማት ያስፈልገዋል ብለዋል። በመሆኑም ዛሬ ግንባታው የተበሰረው መንገድ በርካታ ሀገራዊ ጠቀሜታ እንዳለው አንስተው፥ በተለይም ከባድ ተሽከርካሪዎችና ኮምባይነሮች የሚመላለሱበት በመሆኑ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ይገነባል ብለዋል። የግንባታ ሥራው በሦስት ዓመት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ የጠቆሙት ኢንጅነር ሃብታሙ፥ ለፕሮጀክቱ ዕውን መሆን የ ሁለቱ ዞኖች የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ኅብረተሰቡ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ አደራ ብለዋል። ግንባታውን የሚያከናውነው ዓለም-አቀፉ ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ድርጅት በኢትዮጽያ ካንትሪ ዳይሬክተር ታኦ ሆንግ ድርጅታቸው በሀገሪቱ በተለያየ የመንገድ ግንባታ ሥራ እየተሳተፈ መሆኑን ገልጸው፣ ይህን የላቀ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው ፕሮጀክት በሦስት ዓመት ውስጥ እንደሚያጠናቅቁ አረጋግጠዋል። ፕሮጀክቱ፥ መነሻውን ከአዲስ አበባ 437 ኪ.ሜ ርቀት ሮቤ ከተማ ላይ አድርጎ ጊኒር- ራይቱ-ኢሚ መንገድ መገንጠያ ድረስ የሚዘልቅ ነው፡፡ በምሥራቅ ባሌ ዞን የሲናና፣ ጎሮ፣ ጊኒር እና ዳዌ ቃቻን ወረዳዎችንም ደረጃውን በጠበቀ መንገድ በቅርበት ያስተሳስራል። መንገዱ፣ በገጠር የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 8-10 ሜትር ስፋት ሲኖረው፣ በቀበሌ የመንገድ ትከሻና የመንገድ አካፋይን ጨምሮ 13 ሜትር ስፋት ይኖረዋል፣ በወረዳ የመንገድ አካፋይና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ 21 ሜትር ስፋት በዞን የመንገድ አካፋይ፣ የእግረኛ መንገድና የመኪና ማረፊያ ጨምሮ 28.5 ሜትር ስፋት ይኖረዋል::

የሳውላ-ቃቆ ኮንትራት 2 የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመፋጠን ላይ ይገኛል፡፡ ታህሳስ 7 ቀን 2015 (ኢመአ) በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ውስጥ የሚገኘው የሳውላ-ቃቆ ኮንትራት 2 የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሶዶ ዲስትሪክት አማካኝነት ነው ግንባታው በመካሄድ ላይ የሚገኘው፡፡ የአካባቢው ተፈጥሮአዊ አቀማመጥ እጅግ አስቸጋሪ መሆን በግንባታ ሂደቱ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ቢፈጥርም የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስፈላጊውን የግንባታ ግብዓት እና የሰው ሃይል በቦታው በመመደብ መንገዱን ገንብቶ ለማጠናቀቅ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል፡፡ አጠቃላይ የፕሮጀክቱ ርዝመት 30 ኪሎ ሜትሮችን ይሸፍናል፡፡ የግንባታውን ማማከርና የቁጥጥር ሥራ በማካሄድ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዲዛይን እና ሱፐርቪዥን ስራዎች ኮርፖሬሽን (Ethiopian construction design & super vision works corporation transport design & supervision works sector) ነው፡፡ 433,614,697.8 (አራት መቶ ሰላሳ ሶስት ሚሊዮን ስድስት መቶ አስራ አራት ሺህ ስድስት መቶ ዘጠና ሰባት ብር ከስምንት ሳንቲም) የግንባታ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው። ግንቦት 17 ቀን 2014 ዓ.ም የተጀመረውን ይኸው መንገድ እስከ ቀጣዩ 2016 በጀት ዓመት መጨረሻ ተገንብቶ እንዲጠናቀቅ ለማስቻል የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እያደረገ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት በመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ ለግንባታ ግብዓትነት የሚውል ምርት የማምረት ፣ የአፈር ቆረጣና ሙሌት እንዲሁም በርካታ የስትራክቸር ስራዎች በመካሔድ ላይ ይገኛሉ፡፡ መንገዱ በገጠር 7 ሜትር እና በከተማ 14 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ የዚህ መንገድ የመጀመሪያው ኮንትራት 93 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን ፣ በአስፋልት ደረጃ ተገንብቶ አገልግሎት በመስጠት ላይ ነው፡፡ ከኪሎ ሜትር 93+000 እስከ 122+768 (ቃቆ ከተማ) ድረስ የሚዘልቀውን ኮንትራት ሁለት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል፡፡ ፕሮጀክቱ እየተካሄደ በሚገኝበት አካባቢ ፍየል እና ሌሎች የቀንድ ከብቶች ፣ ቦለቄ ፣ ለውዝ ፣ በቆሎ ፣ ማሽላ ፣ ማር ፣ ቡና እና ሌሎች አትክልት እና ፍራፍሬዎች በከፍተኛ ሁኔታ የሚገኙ በመሆናቸው መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ አርሶ እና አርብቶ አደሮች ምርቶቻቸውን እና የቁም እንስሶቻቸውን ካለምንም ውጣ ውረድ በአፋጣኝ ወደ ገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል፡፡ በተጨማሪም የጤና ፣ የትምህርትና ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ተደራሽነትን ያሰፋል። በተጨማሪም በመስመሩ የሚገኙ የማሌ እና ከባናይ ህዝቦችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መስተጋብር ይበልጥ የሚያስተሳስር ከመሆኑም ባሻገር ከሶዶ ወደ ጂንካ ለመሄድ በኮንሶ መስመር ይደረግ ለነበረውን ዙሪያ ጥምጥም ጉዞ አማራጭ በመሆን የደቡብ ኦሞ ፣ ወላይታ ፣ ጋሞ እና ጎፋ ዞን ህዝቦችን በአቋራጭ ለማገናኘት ያስችላል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን በቅርበት ለመከታተል የሚያስችል አዲስ አደረጃጀት በመፍጠር 27 የፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶችን ከፍቶ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወቃል። በመሆኑም ጽ/ቤቶቹን እና በስራቸው የሚያስተዳድሯቸው የግንባታ ፕሮጀክቶችን በተከታታይ እያስተዋወቅን እንገኛለን። በአደረጃጀቱ መሠረት በማዕከላዊ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ፕሮግራም ዳይሮክቶሬት ስር የአዳማ አካባቢ፣ የአምቦ አካባቢ፣ የደብረ ብርሃን አካባቢ፣ የባሌ አካባቢ እና የቡታጅራ አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች ይገኛሉ። በዚህኛው ዘር የቡታጀራ አካባቢ እና የአምቦ አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶችን እንመለከታለን። በቡታጀራ አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶ ማኔጅመንት ጽ/ቤት 5 (በዲዛይንና ጨረታ ሂደት ላይ ያሉትን ሳይጨምር) የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች የሚገኙ እንዲሁም የአምቦ አካባቢ የግንባታ ፕሮጀክቶች ጽ/ቤት ደግሞ 8(በዲዛይንና ጨረታ ሂደት ላይ ያሉትን ሳይጨምር) የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን እያስተዳደረ ይገኛል። የጽ/ቤቶቹ መቋቋም እነዚህን ፕሮጀክቶች በቅርበት በመከታተል ስኬታማ እንዲሆኑ ለማስቻል ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሎ ይታመናል፡፡ እነዚህ የግንባታ ፕሮጀክት ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች የአገሪቱን አስተዳደራዊ መዋቅር ሳይሆን የፕሮጀክቶችን መገኛ አካባቢ ታሳቢ በማድረግ የተደራጁና ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የጽ/ቤቶቹ አድራሻ ሊቀየር እንደሚችል ታሳቢ ተደርጎ የተደራጁ ናቸው፡፡ በመሆኑም ፕሮጀክቶቹን አስመልከቶ የአካባቢው ህብረተሰብ እና የመስተዳድር አካላት እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት አስተያየትና ጥያቄዎችን ለማቅረብ በቅርቡ ወደ ተከፈቱት ጽ/ቤቶች ማምራት እንደምትችሉ እየገለጸ ፣ እነዚህ ጽ/ቤቶች የታለመላቸውን ግብ እንዲመቱ ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት የድርሻቸውን ሊወጡ ይገባል ሲል የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ያሳስባል፡፡ የቡታጀራ አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶ ማኔጅመንት ጽ/ቤት አድራሻ:- ቡታጀራ ከተማ ዲያስፖራ መንደር የአምቦ አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት አድራሻ:- አምቦ ከተማ ዩኒዮን ሕንጻ 4ኛ ፎቅ ላይ ይገኛሉ ማሳሰቢያ፡ ለማንኛውም ተጨማሪ መረጃ እና አስተያየት የዋናው መ/ቤት ነጻ የስልክ መስመር 8561 ይደውሉ።

በሰሜን ወሎ ዞን ከወልድያ ወደ ቆቦ በሚወስደው መንገድ ላይ የሚገኘው የአለውሃ ወንዝ የብረት ድልድይ ስራ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ። በኮንክሪት ደረጃ በጣልያኖች ተገንብቶ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው ነባሩ የአለውሃ ድልድይ 102 ሜትር ርዝመት ነበረው፡፡ ጉዳቱ ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ ትንንሽ እና መለስተኛ ተሽከርካሪዎት በኮምቦልቻ ዲስትሪክት የተሰራውን ተለዋጭ መንገድ በመጠቀም እና ወንዙን በማቋረጥ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ቆይተዋል። ሆኖም ግን ለከባድ ተሽከርካሪዎች ወንዙን አቋርጦ ወደ ተቃራኒ አቅጣጫ መሻገር አስቸጋሪ የነበረ በመሆኑ የድልድይ ጥገናው እስከሚጠናቀቅ ድረስ ለሁለት ወራት ከዚህ ቀደም የተለመደው የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ተስተጓጉሎ ቆይቷል። ይህ ድልድይ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ለሁለተኛ ጊዜ በተካሄደው ጦርነት ወቅትም ጉዳት ደርሶበት የነበረ ሲሆን ፣ በወቅቱ 54 ነጥብ 86 ሜትር ርዝመት ያለው የብረት ድልድይ ተሰርቶለት አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ነገር ግን ፣ ነሐሴ 09 ምሽት ላይ የተፈጠረው ድንገተኛ ጎርፍ የድልድዩን ተሸካሚ ምሶሶዎች በማፍረሱ ፣ በጊዜያዊነት የተሠራው የብረት ድልድይ ላይ የመውደቅ ስጋት አስከትሎ ቆይቷል፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የብሪጅ ስትራክቸር ዳይሬክቶሬት እና ኮምቦልቻ ዲስትሪክት ባለፉት ሁለት ወራት አስፈላጊውን የጥገና ቁሳቁስ ወደ ቦታው በማንቀሳቀስ ድልድዩን ሲገነቡ ቆይተዋል። አዲሱ የብረት ድልድይ 109.73 ሜትር ርዝመት ያለው ነው። የብረት ድልድይ ግንባታውን ለማጠናቀቅ ላለፉት ሁለት ወራት ሌት ከቀን እንቅስቃሴ ሲደረግ ቆይቷል። ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበት የነበረውን ድልድይ በአሁኑ ወቅት በብረት ድልድይ በመተካት በአዲስ መልኩ ተገንብቶ ከዛሬ ታህሳስ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ለትራንስፖርት አገልግሎት ክፍት ሆኗል። የብረት ድልድዩ እስከ 400 ኩንታል ወይም 40 ቶን ድረስ መሸከም የሚችል አቅም እንዲኖረው ተደርጎ የተገነባ ነው። በሌላ በኩል ግን በዘላቂነት ሊሠራ ዲዛይኑ የተጠናቀቀው 120 ሜትር ርዝመት ያለው የኮንክሪት ድልድይ ግንባታ ለማስጀመር÷ የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡

የዳባት-አጅሬ-ቀራቅር-ከተማ ንጉስ አስፋልት መንገድ ግንባታ በመካሄድ ላይ ይገኛል ጎንደር፤ ኅዳር 30/2014(ኢመአ) የማዕከላዊና ሰሜን ጎንደር ዞን ወረዳዎችን የሚያገናኝው የዳባት-አጅሬ-ቀራቅር-ከተማ ንጉስ 100 ነጥብ 46 ኪ.ሜ አስፋልት መንገድ ግንባታ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ፕሮጀክቱ በ 2 ኮንትራቶች ተከፍሎ እየተገነባ የሚገኝ ሲሆን፥ የዳባት-አጅሬ 43 ነጥብ 2 ኪ.ሜ ኮንትራት-1 መንገድ ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው 85 በመቶ ተከናውኗል። ቀሪ ሥራዎች በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ መሆኑ በተካሄደው የመስክ ሥምሪት ተመላክቷል። ከአጠቃላይ የመንገዱ ክፍል 16 ኪ.ሜትሩን አስፋልት ማልበስ ተችሏል። በተጨማሪም የአፈር ቆረጣና ሙሌት፣ የስትራክቸርና የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ቀበራ እንዲሁም የሰብቤዝና ቤዝኮርስ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። ግንባታውን ከፌደራል መንግስት በተመደበ 931,304,149 (ዘጠኝ መቶ ሰላሳ አንድ ሚሊዮን ሦስት መቶ አራት ሺህ አንድ መቶ አርባ ዘጠኝ) ብር ወጪ ፓወርኮን ኃ/የ/የ/ማኅበር እያከናወነ ይገኛል። የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ቤስት ኮንሰልት እና ኢንስራድ ሲቪል ሲስተም በጣምራ ይሠራሉ። የፕሮጀክቱ ቀጣይ ክፍል የሆነው የአጅሬ-ቀራቅር-ከተማ ንጉስ 57 ነጥብ 26 ኪ.ሜ አስፋልት መንገድ ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው 59.71 በመቶ ተከናውኗል። በቀጣዮቹ ሦስት ወራት ውስጥ አስፋልት የማንጠፍ ሥራ ይጀምራል። በተጨማሪም የአፈር ቆረጣና ሙሌት፣ የስትራክቸር እና የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ቀበራ እንዲሁም የሰብቤዝ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። ግንባታውን 1,158,659, 797(አንድ ቢሊዮን አንድ መቶ ሃምሳ ስምንት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሃምሳ ዘጠኝ ሺህ ሰባት መቶ ዘጠና ሰባት) ብር በሆነ ወጪ ፓወርኮን ከተስፋዪ ለገሰ ኮንስትራክሽን ጋር በጣምራ በመሆን ያከናውናሉ። ወጪው ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት ይሸፈናል። የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ጂ እና ዋይ ኢንጅነሪግ እየሠራ ነው። ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ እንዲሁም ተደጋጋሚ የጸጥታ ችግሮች የመንገዱ የሥራ እንቅስቃሴ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አሳድረዋል። ሆኖም ችግሩን ለመፍታት ከወረዳ የጸጥታ መዋቅር አካላት ጋር በመነጋገር የጸጥታ ኃይል እንዲመደብ ተደርጓል። በቀጣይም ፕሮጀክቶቹ እውን እንዲሆኑ የአካባቢው ነዋሪና የወረዳ መስተዳድር አካላት አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር ኢንዲያደርጉ ኢ.መ.አ ያሳስባል። ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ በዋናነት የጎንደር-ዳንሻ-ሁመራ እና የጎንደር-ዳባት-ደባርቅ-ሽሬ አውራ ጎዳና ያገናኛል። የዳባትና ጠገዴ ወረዳዎችን በማገናኘት የሕዝብ ለሕዝብ ትስስሩን ያሳልጣል። በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን ማሽላ፣ ዳጉሳ፣ ሰሊጥ፣ ጤፍና መሰል የግብርና ምርቶችን ወደ ገበያ ማዕከላት በተሻለ ጥራትና ፍጥነት በማድረስ የአርሶ-አደሩን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ያሰፋል።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን በቅርበት ለመከታተል የሚያስችል አዲስ አደረጃጀት በመፍጠር 27 የፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶችን ከፍቶ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወቃል። አዲሱ መዋቅራዊ ለውጥ በግንባታ ፕሮጀክቶቹ ላይ የሚስተዋለዉን የጊዜ ፣ የገንዘብ እና የጥራት ችግር ለመቅረፍ ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያበረክት ከመሆኑም ባሻገር እነዚህ ጽ/ቤቶች፥ ፕሮጀክቶቹ በሚገኙባቸው አካባቢዎች የተቋቋሙ በመሆናቸው ፤ የእያንዳንዱ አካባቢ ነዋሪዎች ከዚህ ቀደም ከዘርፉ ጋር በተያያዘ ጥያቄአቸውን ለማቅረብ ወደ ዋና መስሪያ ቤቱ ያደርጉት የነበረውን ምልልስ ያስቀራል። በመሆኑም ጽ/ቤቶቹን እና በስራቸው የሚያስተዳድሯቸው የግንባታ ፕሮጀክቶችን በተከታታይ እያስተዋወቅን እንገኛለን። በአደረጃጀቱ መሠረት በማዕከላዊ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ፕሮግራም ዳይሮክቶሬት ስር የአዳማ አካባቢ፣ የአምቦ አካባቢ፣ የደብረ ብርሃን አካባቢ፣ የባሌ አካባቢ እና የቡታጅራ አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች ይገኛሉ። በዚህ ጽሑፍ የደብረ ብርሃን አካባቢ እና የባሌ አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶችን እንመለከታለን። በደብረ ብርሃን አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶ ማኔጅመንት ጽ/ቤት 13 ፕሮጀክቶች የሚገኙ ሲሆን ፣ የባሌ አካባቢ የግንባታ ፕሮጀክቶች ጽ/ቤት 6 ፕሮጀክቶችን እያስተዳደረ ይገኛል። የጽ/ቤቶቹ መቋቋም እነዚህን ፕሮጀክቶች በቅርበት በመከታተል ስኬታማ እንዲሆኑ ለማስቻል ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሎ ይታመናል፡፡ እነዚህ የግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች የአገሪቱን አስተዳደራዊ መዋቅር ሳይሆን የፕሮጀክቶችን መገኛ አካባቢ ታሳቢ በማድረግ የተደራጁና ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የጽ/ቤቶቹ አድራሻ ሊቀየር እንደሚችል ታሳቢ ተደርጎ የተደራጁ ናቸው፡፡ በመሆኑም ፕሮጀክቶቹን አስመልከቶ የአካባቢው ህብረተሰብ እና የመስተዳድር አካላት እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት አስተያየትና ጥያቄዎችን ለማቅረብ በቅርቡ ወደ ተከፈቱት ጽ/ቤቶች ማምራት እንደምትችሉ እየገለጽን ፣ እነዚህ ጽ/ቤቶች የታለመላቸውን ግብ እንዲመቱ ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት የድርሻቸውን ሊወጡ ይገባል ሲል የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ያሳስባል፡፡ የደብረ ብርሃን አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶ ማኔጅመንት ጽ/ቤት አድራሻ:- ደብረብርሃን ከተማ ጠባሴ (ድልድዩ) አካባቢ ፃድቃኔ ህንፃ ላይ 5ኛ ፎቅ የባሌ አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት አድራሻ:- ባሌ ሮቤ ከተማ ሲኮሜንዶ ሕንጻ 2ኛ ፎቅ ለተጨማሪ መረጃ የዋናው መ/ቤት ነፃ የስልክ መስመር 8561 ይጠቀሙ፡፡ ፖ.ሳ.ቁ. 1770 ድረ ገጽ www.era.gov.et ፌስ ቡክ www.facebook.com/ethiopianroadsauthority ቴሌግራም@ethioroads

የኢትዮ-ጅቡቲ የትራንስፖርት ኮሪደር አካል የሆነው አዋሽ-መኢሶ መንገድ ከባድ ጥገና እየተደረገለት ነው አዲስ አበባ፣ ኅዳር 27/2015(ኢመአ) የኢትዮ-ጅቡቲ ዋና መንገድ አካል የሆነው አዋሽ-መኢሶ 70 ነጥብ 5 ኪ.ሜ መንገድ የመስመሩን ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት በበቂ ሁኔታ ለማስተናገድ በሚያስችል መልኩ ከባድ ጥገና እየተደረገለት ነው። ጥገናውን ሀገር-በቀሉ 'ዮንአብ ኮንስትራክሽን' በ 478,385,156(አራት መቶ ሰባ ስምንት ሚሊዮን ሦስት መቶ ሰማኒያ አምስት ሺህ አንድ መቶ ሃምሳ ስድስት) ብር በሆነ ወጪ በማከናወን ላይ ነው። ወጪው ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት ነው የሚሸፈነው። ሀይዌይ ኢንጅነርስ ኤንድ ኮንሰልታንት ኃላ/የተ/የግ/ማ ግንባታውን በማማከር እና በመቆጣጠር እየተሳተፈ ይገኛል። መንገዱ የሀገሪቱ የገቢ እና ወጪ ንግድ ዋና መስመር እና ከከባድ እስከ ቀላል ተሽክከርካሪዎች የሚተላለፉበት እንደመሆኑ፥ የመንገዱ መሠረት እና ትከሻ ላይ ብልሽት በመስተዋሉ መንገዱ ለከፋ ብልሽት ከመዳረጉ በፊት ነው ከባድ ጥገናው ያስፈለገው። በተጨማሪም መንገዱ ከአነስተኛ እስከ ከባድ መጠን ባላቸው ጉድጎዶች(deep holes) እና ሌሎች እንደ መሰንጠቅ እና የአስፋልት ድራቡ ያሉ የጉዳት ዓይነቶች በመጎዳቱ የጥገና ሥራ እየተከናወነለት ይገኛል። በእስከ አሁኑ የግንባታ እንቅስቃሴ የ3 ነጥብ 6 ኪ.ሜ የኦቨርሌይ አስፋልት ንጣፍ፣ የተለዋጭ መንገድ እና የመኖሪያ ካምፕ ግንባታ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። በዚህም ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው 18 በመቶ መከናወኑ ተመላክቷል። ከዚህም ሌላ የድልድይ እና ተጨማሪ የውኃ መፋሰሻ እንዲሁም የመንገድ ደኅንነት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። መንገዱ፥ በአፋር ክልል ገቢረሱ ዞን አሚባራ ወረዳ፣ በሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን መኢሶ ወረዳ እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል መኢሶ ዞን ጉምቢ ቦርደዴ ወረዳዎችን የሚያገናኝ ሁነኛ መስመር ነው። በሥፍራው የሚመረቱትን ከፍተኛ የሰብል ምርት ውጤቶች በቀላሉ ወደ መሀል ገበያ በማድረስ የአርሶ-አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ይጨምራል። የጉዞ ጊዜን በማሳጠር አሽከርካሪዎችንና የተሽከርካሪ ባለንብረቶችን ከአላስፈላጊ ወጪ እና እንግልት ይታደጋል። የዚህ መንገድ ትስስር አካል የሆነው ከአዳማ-ኪ.ሜ 60-አዋሽ ከባድ ጥገና ፕሮጀክት በግንባታ ላይ የሚገኘ ሲሆን፣ ከመኢሶ-ቁልቢ-ሀረር ያሉት መንገዶች በጨረታ ሂደት ላይ ናቸው። ይህ በእንዲህ እንዳለ፥ የኢትዮ-ጅቡቲ የትራንስፖርት መስመር የሀገሪቱ 90 ከመቶ በላይ የገቢ እና ወጪ ንግድ የሚተላለፍበት እንደመሆኑ ያለውን የትራፊክ ፍሰት ይበልጥ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ሊያስተናግድ የሚያስችል የፍጥነት መንገድ አዳማ-አዋሽ 60 ኪ.ሜ ምዕራፍ አንድ ግንባታ መጀመሩ ይታወቃል፡፡

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገድ ፕሮጀክቶችን በቅርበት ለመከታተል የሚያስችል አደረጃጀት በመፍጠር 27 የፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ\ቤቶችን ከፍቶ ወደ ሥራ መገባቱ ይታወቃል፡፡ የጽ/ቤቶቹ መከፈ
+1
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገድ ፕሮጀክቶችን በቅርበት ለመከታተል የሚያስችል አደረጃጀት በመፍጠር 27 የፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ\ቤቶችን ከፍቶ ወደ ሥራ መገባቱ ይታወቃል፡፡ የጽ/ቤቶቹ መከፈት የመንገድ ፕሮጀክት ሥራዎችን በቅርበት ለመከታተልና ከአካባቢው ህብረተሰብ ጋር ተቀራርቦ በመነጋገርና የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ ካለው ፋይዳ አንጻር ለተቋሙ የድጋፍና ክትትል ሥራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው። በምዕራብ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ማነጅመንት ፕሮግራም ዳይሬክቶሬት ስር ያሉ የፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ\ቤቶች የአሶሳ አካባቢ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት፣ የጋምቤላ አካባቢ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት ፣ የጅማ አካባቢ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት፣ የሚዛን አካባቢ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት እና የነቀምት አካባቢ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት ናቸው፡፡ ከዚህ አኳያ ለዛሬው የጅማ እና የሚዛን አካባቢ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ፅ/ቤቶችና የሚያስተዳድሯቸው ፕሮጀክቶች መረጃ እናቀርባለን፡፡ የመጀመሪያው የጅማ አካባቢ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ፅ/ቤት ስድስት (6) የመንገድ ፕሮጀክቶችን የሚያስተዳድር ሲሆን የሚገኘው በጅማ ከተማ ውሃ ልማት አካባቢ ነው፡፡ ሁለተኛው የሚዛን አካባቢ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ፅ/ቤት ደግሞ ሰባት (7) የመንገድ ፕሮጀክቶችን የሚያስተዳድር ሲሆን የሚገኘውም በሚዛን አማን ከተማ፣ በተለምዶ “አሮጌው አየር ማረፊያ” በሚባል አካባቢ ነው፡፡ ማሳሰቢያ፡ ለማንኛውም ተጨማሪ መረጃ እና አስተያየት የዋናው መ/ቤት ነጻ የስልክ መስመር 8561 ይደውሉ።

ስለ መንገድ ፕሮጀክት ጽ/ቤቶች ክፍል ሁለት፡ የሚዛንና የጅማ አካባቢ የመንገድ ፕሮጀክቶች ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች መረጃ :- የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ የመንገድ ፕሮጀ
+3
ስለ መንገድ ፕሮጀክት ጽ/ቤቶች ክፍል ሁለት፡ የሚዛንና የጅማ አካባቢ የመንገድ ፕሮጀክቶች ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች መረጃ :- የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ የመንገድ ፕሮጀክቶችን በቅርበት ለመከታተል እንዲቻል በቅርቡ ስራ ካስጀመራቸው የፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች አንዱ የሚዛን እና አካባቢው ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት ነው። በሚዛን እና አካባቢው ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ፅ/ቤት የሚዛን እና አካባቢው ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት የሚገኝበት አድራሻ:- የፅ/ቤቱ አድራሻ፦ ሚዛን አማን ከተማ፣ በተለምዶ “አሮጌው አየር ማረፊያ” የሚባል አካባቢ። ስልክ ቁጥር 0913884917 የጅማ እና አካባቢው ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት የሚገኝበት አድራሻ፦ የፅ/ቤቱ መገኛ:- ጅማ ከተማ ውሃ ልማት አካባቢ። ስልክ ጥቁር፦0910800730 የፕሮጀክት ፅ/ቤቶቹ መከፈት ከአካባቢው ህብረተሰብ፣ ከአማካሪ መሃንዲሶች እና ከኮንትራክተሮቹ ጋራ በቅርበት በመናበብ የመንገድ ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ እና የጥራት ደረጃ ተገንብተው እንዲጠናቀቁ ይረዳል። በመሆኑም ከላይ የተጠቀሱትን ፕሮጀክቶች አስመልከቶ የአካባቢው ህብረተሰብ እና የመስተዳድር አካላት እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት አስተያየትና ጥያቄዎችን ለማቅረብ በሚዛን ከተማ እና ጅማ ከተማ ወደ ተቋቋመው "የሚዛን እና አካባቢው ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት" እና “የጅማ እና አካባቢው ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት “ ማምራት ይችላሉ፡፡ ማሳሰቢያ፡ ለማንኛውም ተጨማሪ መረጃ እና አስተያየት የዋናው መ/ቤት ነጻ የስልክ መስመር 8561 ይደውሉ። ይቀጥላል…

የመንገድ ዜናዎች - Copy.docx0.20 KB