ar
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

الذهاب إلى القناة على Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

تُعد قناة ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 13 365 مشتركاً، محتلاً المرتبة 1 754 في فئة النقل والمرتبة 2 531 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 13 365 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 19 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 119، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 19، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 40.59‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.42‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 423 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 060 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 11.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 20 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة النقل.

13 361
المشتركون
+1924 ساعات
+677 أيام
+11930 أيام
أرشيف المشاركات
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እያስገነባቸው ያሉ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀቶችን በቅርበት ለመከታተል የሚያስችለውን አዲስ አደረጃጀት በመፍጠር ወደ ስራ እንደገባ ይታወሳል፡፡ አስተዳደር መስሪያቤቱ በግንባታ ሂደት ላይ ያሉ ፕሮጀክቶችን በቅርበት ለመከታተል የሚያስችል አዲስ አደረጃጀት በመፍጠር 29 የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶችን በመክፈት ነው አገልግሎት መስጠት የጀመረው፡፡ ጽ/ቤቶቹ እንዲቋቋሙ ያስፈለገበት ዋና ምክንያት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመሄዱ ምክንያት የግንባታ ሂደታቸውን በቅርበት መከታተል አስፈላጊ መሆኑ ስለታመነበት ነው፡፡ አዲሱ የአደረጃጀት ለውጥ በግንባታ ፕሮጀክቶቹ ላይ የሚስተዋለዉን የጊዜ ፣ የገንዘብ እና የጥራት ችግር የሚቀርፍ ከመሆኑም ባሻገር እነዚህ ጽ/ቤቶች ፕሮጀክቶቹ በሚገኙባቸው አካባቢዎች የተቋቋሙ በመሆናቸው ፤ የእያንዳንዱ አካባቢ ነዋሪዎች ከዚህ ቀደም ከዘርፉ ጋር በተያያዘ ጥያቄአቸውን ለማቅረብ ወደ ዋና መስሪያ ቤቱ ያደርጉት የነበረውን ምልልስ በመቅረፍ እፎይታን ይፈጥራል ተብሎ ታምኖበታል፡፡ አደረጃጀቱ በእያንዳንዱ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ጽ/ቤት በአማካይ ከ6-13 የሚጠጉ ፕሮጀክቶችን መቆጣጠር የሚያስችል ነው፡፡ በዚህም ረገድ በተቋማችን ስር በተዋቀሩት በእያንዳንዱ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች የተካተቱ ፕሮጀክቶችን ለህብረተሰቡ በቅደም ተከተል እያሳወቅን የምንገኝ ሲሆን ፣ በማዕከላዊ ሪጅን በአዳማ አካባቢ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት ስር የሚተዳደሩ ፕሮጀክቶች የሚከተሉት ናቸው፡፡ በዚህ ጽ/ቤት 8 ፕሮጀክቶች የሚገኙ ሲሆን ፣ የጽ/ቤቱ መቋቋም እነዚህን ፕሮጀክቶች በቅርበት በመከታተል ስኬታማ እንዲሆኑ ለማስቻል ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሎ ይታመናል፡፡ ከታች የተጠቀሱትን ፕሮጀክቶች አስመልክቶ የአካባቢው ህብረተሰብ እና የመስተዳድር አካላት እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት አስተያየትና ጥያቄዎችን ለማቅረብ በአዳማ ከተማ ወደ ተቋቋመው የአዳማ አካባቢ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት ማምራት እንደምትችሉ እየገለጽን ፣ እነዚህ ጽ/ቤቶች የታለመላቸውን ግብ እንዲመቱ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል ሲል የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ያሳስባል፡፡ የአዳማ አካባቢ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት መገኛ አድራሻ ፡-አዳማ ከተማ ሥላሴ ቤተክርስቲያን አጠገብ መኮቢሊ ት/ቤት ሕንጻ 1ኛ ፎቅ ስልክ ቁጥር፡-0911530280 ለማንኛውም ተጨማሪ መረጃ የዋናው መ/ቤት ነጻ የስልክ መስመር 8561 ይጠቀሙ፡፡

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እያስገነባቸው ያሉ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀቶችን በቅርበት ለመከታተል የሚያስችለውን አዲስ አደረጃጀት በመፍጠር ወደ ስራ ገባ፡፡ አዲስ አበባ ህዳር 07 ቀን 2015 ዓ.ም (ኢመአ) የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በግንባታ ሂደት ላይ ያሉ ፕሮጀክቶችን በቅርበት ለመከታተል የሚያስችለውን አዲስ አደረጃጀት በመፍጠር 29 የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶችን በመክፈት አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡ ጽ/ቤቶቹ እንዲቋቋሙ ያስፈለገበት ዋና ምክንያት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመሄዱ ምክንያት የግንባታ ሂደታቸውን በቅርበት መከታተል አስፈላጊ መሆኑ ስለታመነበት ነው፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በ2015 በጀት ዓመት በቁጥር 212 የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን እያስተዳደረ ይገኛል፡፡ ይህም ወደ ገንዘብ ሲቀየር ወደ ግማሽ ትሪሊዮን ብር የሚጠጋ ነዉ፡፡ ከፍተኛ መዋለ ነዋይ የሚፈስባቸውን የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች በቅርበት በመከታተል በተገቢው የጥራት ደረጃ እና ፍጥነት እንዲጠናቀቁ ለማስቻል 29 የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች ተቋቁመው ወደ ስራ ተገብቷል፡፡ አዲሱ መዋቅራዊ ለውጥ በግንባታ ፕሮጀክቶቹ ላይ የሚስተዋለዉን የጊዜ ፣ የገንዘብ እና የጥራት ችግር ለመቅረፍ ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያበረክት ከመሆኑም ባሻገር እነዚህ ጽ/ቤቶች ፕሮጀክቶቹ በሚገኙባቸው አካባቢዎች የተቋቋሙ በመሆናቸው ፤ የእያንዳንዱ አካባቢ ነዋሪዎች ከዚህ ቀደም ከዘርፉ ጋር በተያያዘ ጥያቄአቸውን ለማቅረብ ወደ ዋና መስሪያ ቤቱ ያደርጉት የነበረውን ምልልስ በመቅረፍ እፎይታን ይፈጥራል ተብሎ ታምኖበታል፡፡ መስሪያ ቤቱ በአሁኑ ወቅት በምህንድስና ዘርፍ ተሰማርተው የሚገኙ 216 መሐንዲሶችን የግንባታ ፕሮጀክቶች ወደሚገኙበት ስፍራ በማዘዋወር የክትትልና ቁጥጥር ስራዉን በቅርበት እንዲከናዉኑ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ እነዚህ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶችም የአገሪቱን አስተዳደራዊ መዋቅር ሳይሆን የፕሮጀክቶችን መገኛ አካባቢ ታሳቢ በማድረግ የተደራጁና ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የጽ/ቤቶቹ አድራሻ ሊቀየር እንደሚችል ታሳቢ ተደርጎ የተደራጁ ሲሆን የሚከተሉት ናቸው፡፡ በደቡብ ሪጅን ፡- የሶዶ አካባቢ፣ የሻሸመኔ አካባቢ፣ የጅንካ አካባቢ እና የነጌሌ ቦረና አካባቢ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች በምሥራቅ ሪጅን ፡- የድሬዳዋ አካባቢ፣ የጎዴ አካባቢ፣ የጅግጅጋ አካባቢእና የሰመራ አካባቢ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች በሰሜን ሪጅን ፡- የባሕር ዳር አካባቢ፣ የቡሬ አካባቢ፣ የጎንደር አካባቢ፣ የኮምቦልቻ አካባቢ፣ የመቀሌ አካባቢ እና የሽሬ አካባቢ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች በምዕራብ ሪጅን ፡- የአሶሳ አካባቢ፣ የጋምቤላ አካባቢ፣ የጅማ አካባቢ፣ የሚዛን አካባቢእና የነቀምት አካባቢ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች በማዕከላዊ ሪጅን ፡- የአዳማ አካባቢ፣ የአምቦ አካባቢ፣ የደብረ ብርሃን አካባቢ፣ የባሌ ሮቤ አካባቢእና የቡታጅራ አካባቢ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች የፍጥነት መንገዶችንና ልዩ ፕሮጀክቶችን በተመለከተ ደግሞ ፡- የአዳማ አዋሽ ፣ የሞጆ-ሐዋሳ እና የኮይሻ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች ናቸው፡፡ መዋቅሩ በእያንዳንዱ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ጽ/ቤት በአማካይ ከ10 እስከ 15 ቢሊየን ብር ዋጋ ያላቸው ከ6-13 የሚጠጉ ፕሮጀክቶችን መቆጣጠር የሚያስችል ነው፡፡ በዚህም ረገድ በተቋማችን ስር በተዋቀሩት በእያንዳንዱ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች የተካተቱ ፕሮጀክቶችን ለህብረተሰቡ በቅደም ተከተል የምናሳውቅ ሲሆን ፣ ለመነሻም በደቡብ ሪጅን በጅንካ እና አካባቢው ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት ስር የሚተዳደሩ ፕሮጀክቶችን በሚከተለው መልኩ ይዘን ቀርበናል፡፡ በዚህ ጽ/ቤት አካባቢ 7 ፕሮጀክቶች የሚገኙ ሲሆን ፣ የጽ/ቤቱ መቋቋም እነዚህን ፕሮጀክቶች በቅርበት በመከታተል ስኬታማ እንዲሆኑ ለማስቻል ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሎ ይታመናል፡፡ በመሆኑም ከላይ የተጠቀሱትን ፕሮጀክቶች አስመልከቶ የአካባቢው ህብረተሰብ እና የመስተዳድር አካላት እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት አስተያየትና ጥያቄዎችን ለማቅረብ በጅንካ ከተማ ወደ ተቋቋመው "የጅንካ አካባቢ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት" ማምራት እንደምትችሉ እየገለጽን ፣ እነዚህ ጽ/ቤቶች የታለመላቸውን ግብ እንዲመቱ ሁሉም የሚመለከተው አካል የድርሻውን ሊወጣ ይገባል ሲል የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ያሳስባል፡፡ "የጅንካ አካባቢ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት መገኛ አድራሻ፡- ጅንካ ከተማ አርኪሻ አካባቢ ስልክ ቁጥር ፡+251911953401 ለማንኛውም ተጨማሪ መረጃ የዋናው መ/ቤት ነፃ የስልክ መስመር 8561 ይጠቀሙ፡፡

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እያስገነባቸው ያሉ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀቶችን በቅርበት ለመከታተል የሚያስችለውን አዲስ አደረጃጀት በመፍጠር ወደ ስራ ገባ፡፡ አዲስ አበባ ህዳር 07 ቀን 2015 ዓ.ም (ኢመአ) የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በግንባታ ሂደት ላይ ያሉ ፕሮጀክቶችን በቅርበት ለመከታተል የሚያስችለውን አዲስ አደረጃጀት በመፍጠር 29 የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶችን በመክፈት አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡ ጽ/ቤቶቹ እንዲቋቋሙ ያስፈለገበት ዋና ምክንያት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመሄዱ ምክንያት የግንባታ ሂደታቸውን በቅርበት መከታተል አስፈላጊ መሆኑ ስለታመነበት ነው፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በ2015 በጀት ዓመት በቁጥር 212 የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን እያስተዳደረ ይገኛል፡፡ ይህም ወደ ገንዘብ ሲቀየር ወደ ግማሽ ትሪሊዮን ብር የሚጠጋ ነዉ፡፡ ከፍተኛ መዋለ ነዋይ የሚፈስባቸውን የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች በቅርበት በመከታተል በተገቢው የጥራት ደረጃ እና ፍጥነት እንዲጠናቀቁ ለማስቻል 29 የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች ተቋቁመው ወደ ስራ ተገብቷል፡፡ አዲሱ መዋቅራዊ ለውጥ በግንባታ ፕሮጀክቶቹ ላይ የሚስተዋለዉን የጊዜ ፣ የገንዘብ እና የጥራት ችግር ለመቅረፍ ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያበረክት ከመሆኑም ባሻገር እነዚህ ጽ/ቤቶች ፕሮጀክቶቹ በሚገኙባቸው አካባቢዎች የተቋቋሙ በመሆናቸው ፤ የእያንዳንዱ አካባቢ ነዋሪዎች ከዚህ ቀደም ከዘርፉ ጋር በተያያዘ ጥያቄአቸውን ለማቅረብ ወደ ዋና መስሪያ ቤቱ ያደርጉት የነበረውን ምልልስ በመቅረፍ እፎይታን ይፈጥራል ተብሎ ታምኖበታል፡፡ መስሪያ ቤቱ በአሁኑ ወቅት በምህንድስና ዘርፍ ተሰማርተው የሚገኙ 216 መሐንዲሶችን የግንባታ ፕሮጀክቶች ወደሚገኙበት ስፍራ በማዘዋወር የክትትልና ቁጥጥር ስራዉን በቅርበት እንዲከናዉኑ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ እነዚህ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶችም የአገሪቱን አስተዳደራዊ መዋቅር ሳይሆን የፕሮጀክቶችን መገኛ አካባቢ ታሳቢ በማድረግ የተደራጁና ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የጽ/ቤቶቹ አድራሻ ሊቀየር እንደሚችል ታሳቢ ተደርጎ የተደራጁ ሲሆን የሚከተሉት ናቸው፡፡ በደቡብ ሪጅን ፡- የሶዶ አካባቢ፣ የሻሸመኔ አካባቢ፣ የጅንካ አካባቢ እና የነጌሌ ቦረና አካባቢ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች በምሥራቅ ሪጅን ፡- የድሬዳዋ አካባቢ፣ የጎዴ አካባቢ፣ የጅግጅጋ አካባቢእና የሰመራ አካባቢ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች በሰሜን ሪጅን ፡- የባሕር ዳር አካባቢ፣ የቡሬ አካባቢ፣ የጎንደር አካባቢ፣ የኮምቦልቻ አካባቢ፣ የመቀሌ አካባቢ እና የሽሬ አካባቢ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች በምዕራብ ሪጅን ፡- የአሶሳ አካባቢ፣ የጋምቤላ አካባቢ፣ የጅማ አካባቢ፣ የሚዛን አካባቢእና የነቀምት አካባቢ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች በማዕከላዊ ሪጅን ፡- የአዳማ አካባቢ፣ የአምቦ አካባቢ፣ የደብረ ብርሃን አካባቢ፣ የባሌ ሮቤ አካባቢእና የቡታጅራ አካባቢ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች የፍጥነት መንገዶችንና ልዩ ፕሮጀክቶችን በተመለከተ ደግሞ ፡- የአዳማ አዋሽ ፣ የሞጆ-ሐዋሳ እና የኮይሻ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች ናቸው፡፡ መዋቅሩ በእያንዳንዱ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ጽ/ቤት በአማካይ ከ10 እስከ 15 ቢሊየን ብር ዋጋ ያላቸው ከ6-13 የሚጠጉ ፕሮጀክቶችን መቆጣጠር የሚያስችል ነው፡፡ በዚህም ረገድ በተቋማችን ስር በተዋቀሩት በእያንዳንዱ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች የተካተቱ ፕሮጀክቶችን ለህብረተሰቡ በቅደም ተከተል የምናሳውቅ ሲሆን ፣ ለመነሻም በደቡብ ሪጅን በጅንካ እና አካባቢው ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት ስር የሚተዳደሩ ፕሮጀክቶችን በሚከተለው መልኩ ይዘን ቀርበናል፡፡ በዚህ ጽ/ቤት አካባቢ 7 ፕሮጀክቶች የሚገኙ ሲሆን ፣ የጽ/ቤቱ መቋቋም እነዚህን ፕሮጀክቶች በቅርበት በመከታተል ስኬታማ እንዲሆኑ ለማስቻል ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሎ ይታመናል፡፡ በመሆኑም ከላይ የተጠቀሱትን ፕሮጀክቶች አስመልከቶ የአካባቢው ህብረተሰብ እና የመስተዳድር አካላት እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት አስተያየትና ጥያቄዎችን ለማቅረብ በጅንካ ከተማ ወደ ተቋቋመው "የጅንካ አካባቢ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት" ማምራት እንደምትችሉ እየገለጽን ፣ እነዚህ ጽ/ቤቶች የታለመላቸውን ግብ እንዲመቱ ሁሉም የሚመለከተው አካል የድርሻውን ሊወጣ ይገባል ሲል የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ያሳስባል፡፡ "የጅንካ አካባቢ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት መገኛ አድራሻ፡- ጅንካ ከተማ አርኪሻ አካባቢ ስልክ ቁጥር ፡+251911953401 ለማንኛውም ተጨማሪ መረጃ የዋናው መ/ቤት ነፃ የስልክ መስመር 8561 ይጠቀሙ፡፡

የዓሊ ከተማ-ዋቤ ድልድይ ኮንክሪት አስፋልት መንገድ
+7
የዓሊ ከተማ-ዋቤ ድልድይ ኮንክሪት አስፋልት መንገድ

የዓሊ ከተማ-ዋቤ ድልድይ ኮንክሪት አስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ ተጠናቀቀ። 56.5 ኪ.ሜ የሚረዝምው አስፋልት መንገዱ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ተከትሎ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። ግንባታውን በ2,153, 060, 671 (ሁለት ቢሊዮን አንድ መቶ ሃምሳ ሦስት ሚሊዮን ስልሳ ሺህ ስድስት መቶ ሰባ አንድ) ብር ወጪ ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ አከናውኖታል። የግንባታው ወጪ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት ነው የተሸፈነው። ፕሮጀክቱን በማማከርና በመቆጣጠር በኩል ሆንግ አይኬ ከልደት ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ጋር በጥምረት ተሳትፈዋል። የባሌ ሮቤ አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ ከድር ረዲ(ኢንጅ)፥ ፕሮጀክቱ የአራት ድልድዮች ግንባታና ከባባድ የቆረጣ ሥራ እንደነበረው አስታውሰው፥ ከፈታኝ ሂደት በኋላ በታለመት ጊዜ ተጠናቅቋል ብለዋል። ለዚህም የኅብረተሰቡ ሚና የላቀ እንደነበር አንስተዋል። የፕሮጀክቱ ዕውን መሆን ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው የገለጹት ሥራ አስኪያጁ፥ በተለይም በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን የስንዴ፣ ገብስ እና የፍራፍሬ ምርቶችን ጨምሮ ሌሎች የግብርና ምርቶችን በስፋት እና በጥራት ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማድረስ ኢኮኖሚያዊ ፍይዳው የጎላ ነው ብለዋል። በተጫማሪም መንገዱ በዋናነት ሮቤ፣ ዓሊ እና ዋቤ ከተሞችን በቅርበት በማገናኘት፥ የቱሪዝም መዳረሻ የሆኑትን የሶፍ ዑመር ዋሻ፣ የሳነቴ አምባ እና የዲንሾ ብሔራዊ ፓርክ ለጎብኝዎች ምቹ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ኢንጅ. ከድር ገልጸዋል። በባሌ ዞን የአጋርፋ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው አበበ በበኩላቸው፥ ከዚህ ቀደም የመንገድ መሠረተ ልማት ባለመኖሩ ኅብረተሰቡ ለተለያዩ እንግልቶች ይዳረግ እንደነበር አስታውሰው፥ መንገዱ ተጠናቅቆ በማየታቸው ደስታቸውን ገልጸዋል። የመንገዱ ተጠቃሚዎች በበኩላቸው መንገዱ በማለቁ ከአላስፈላጊ ወጪና እንግልት እንደታደጋቸው ተናግረዋል። በዚህ አጋጣሚ መንገዱ ከፍተኛ ሙዋለ ንዋይ የሀገር ሀብት በመሆኑ ኅብረተሰቡ ተገቢውን ጥበቃና እንክብካቤ እንዲያደርግ ኢ መ አ ያሳስባል። የዚሁ ፕሮጀክት ቀጣይ ምዕራፍ የሆነው የዋቤ ወንዝ-አርሲ ሮቤ ክፍል-2 አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት በግንባታ ላይ ይገኛል፡፡ በጠቅላላው ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ፥ ከአዲስ አበባ ባሌ ሮቤ ለመጓዝ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ርቀት በ 100 ኪ.ሜ ያሳጥረዋል።

ፍቼ - ጎሐፅዮን መልሶ ግንባታ (ከባድ ጥገና)
+8
ፍቼ - ጎሐፅዮን መልሶ ግንባታ (ከባድ ጥገና)

ፍቼ - ጎሐፅዮን መልሶ ግንባታ (ከባድ ጥገና) የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ የግንባታ ሂደት ላይ ይገኛል። ፍቼ - ጎሐፅዮን የመንገድ ፕሮጀክት በአገልግሎት ብዛት ሳቢያ ምክኒያት ለብልሽት ተዳርጎ የነበረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት መንገዱን ወደተሻለ ደረጃ ለመመለስ ከባድ ጥገና እየተደረገለት ነው። መንገዱ የአዲስ አበባ-ጎጃም-ጎንደር ዋናው አውራ ጎዳና (Trunk Road) በመሆኑ በርካታ ከባድ እና ቀላል ተሽከርካሪዎችን ሲያስተናግድ ቆይቷል። በአጠቃላይ መንገዱ ላለፉት 20 ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል። ይህ መንገድ የተለያዩ የመንገድ ብልሽት ዓይነቶችን ማለትም ከአነስተኛ እስከ ከፍተኛ መጠን ባለቸው ጉድጓጎች(Deep hole) እና ሌሎችም እንደ መሰንጠቅ ፣ መስመጥ እና የአስፓልት ድራቡ መላላጥ ያሉ የጉዳት ዓይቶች የተጎዳ ሲሆን በአሁኑ ወቅት የመንገዱ ጥገና በተያዘለት ጊዜ እና ጥራት ደረጃ እየተሰራ ይገኛል። በእስካሁን የግንባታ ሂደት የተሰሩ ዝርዝር ስራዎች፣ የመንገድ ዳር ውሀ ማፋሰሻ ዲች ስራ ፤የእግረኛ መንገድ ስራ ፤የአዲስ አስፋልት ንጣፍ ስራ የመንገድ መልሶ ግንባታ ስራ፤ የፉካ ስራ እና የመንገድ ሀብት ክብካቤ እና ማስተዳደር ስራዎች ተሰርተዋል። የፕሮጀክቱ አሁናዊ አፈፃፀም በመቶኛ 66.15% እና በኪ.ሜ ደግሞ 48.78 ላይ ደርሷል። 75 ኪ.ሜ የሚረዝመው ይህው መንገድ ከመንግሥት በተበጀት 812,182,483.01 ብር ነው ጥገናው እየተካሄደ የሚገኘው። ግንባታውን የሚሰራው የስራ ተቋራጭ አማራ መንገድ ስራዎች ድርጅት ሲሆን የማማካር እና ቁጥጥር ስራውን ደግሞ ጎንድዋና ኢንጂነሪንግ ኃላ.የተ.የግ.ኩባንያ ያዊት ኢንጂነሪነግ ኃላ.የተ.የግ.ኩባንያ ጋር በጣምራ ነው። የመንገድ የጎን ስፋት በገጠር 10 ሜትር፣በወረዳና በከተማ 19 ሚትር ተጨማሪ የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው እየተገነባ የሚገኘው። መንገዱ የሚያገናቸው/አቆራርጦ የሚያልፍባቸው ከተሞች በኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ሸዋ ዞን ግራር ጃርሶ ወረዳ፣ ደገም ወረዳ፣ ኩዩ ወረዳ እና ወረጃርሶ ከተማ አስተዳደር ናቸዉ። አካባቢው ከፍተኛ የሆነ የሰብል ምርት ማለትም የጤፍ ፣ የገብስ እና የስንዴ ምርት የሚመረትበት በመሆኑ አርሶ አደሩን ያመረተውን ምርት በቀላሉ ወደ መሃል ገቢያ እንዲያደርሱ ይረዳቸዋል። የመንገዱ መገንባት ከአባይ ሸለቆ የሚገኘውን የሲሚንቶና የጅብሰም ግብአት ለፋብሪካዎች በተሳለጠ መንገድ ለማዳረስም ሁነኛ መፍትሔ ነው። በተጨማሪም ከሀገሪቱ ዋና ከተማ ወደ ታላቁ የህዳሴ ግድብ እና ወደ ጎረቤት ሀገር ሱዳን የሚያገናኘው የመንገድ አካል በመሆኑ የመንገዱ ጥገና ፋይዳው የጎላ ነው ።

የፊቅ-ሰገግ-ገርቦ-ደናን ምዕራፍ አንድ ፊቅ-ሰገግ የአስፋልት መንገድ ግንባታ
+6
የፊቅ-ሰገግ-ገርቦ-ደናን ምዕራፍ አንድ ፊቅ-ሰገግ የአስፋልት መንገድ ግንባታ

በሶማሌ ክልል እየተገነባ የሚገኘው የፊቅ-ሰገግ-ገርቦ-ደናን ምዕራፍ አንድ ፊቅ-ሰገግ የአስፋልት መንገድ ግንባታ በትኩረት እየተሠራ ነው። የኢትዮጵያ መንገዶች አሰተዳደር በክልሉ እያስገነባቸው ከሚገኙ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ሲሆን፥ ሀገራዊ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ፋይዳው እጅግ የጎላ ነው። 90 ኪ.ሜ የሚረዝመው ፕሮጀክቱ፥ በእስካሁኑ የስራ አፈጻጸም የአፈር ጠረጋ፣ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ማምረት፣ የአፈር ቆረጣና ሙሌት፣ የሮድ ቤድ እንዲሁም የስትራክቸር ግንባታ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። አጠቃላይ የግንባታ ሥራው የትራፊክ እንቅስቃሴውን እንዳያስተጓጉል ተለዋጭ መንገድ ተገንብቶ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል። ግንባታውን ሀገር በቀሉ ድሪባ ደፈርሻ ጠቅላላ ሥራ - ተቋራጭ ድርጅት እያከናወነው ነው፡፡ ፕሮጀክቱን የማማከርና የቁጥጥር ሥራ ቫልዩ ኢንጂነሪንግ አማካሪ ኃ/የተ/የግ/ማ. እየሰራ ይገኛል። ለግንባታው የሚውለው አንድ ቢሊየን አራት መቶ ሃያ ሁለት ሚሊየን ዘጠኝ መቶ ስልሳ ስምንት ሺህ ብር /1,422,968,463.00 / ወጪ በፌደራል መንግስት በጀት የሚሸፈን ነው። በክልሉ ተከስቶ የነበረውን ድርቅ ተከትሎ የተፈጠረው የውኃ እጥረት በፕሮጀከቱ ላይ እክል ፈጥሮ ቆይቷል እንዲሁም ከወሰን ማስከበር ጋር የሚነሱ ጉዳዮች በወቅቱ አለመፈታት አግባብነት የጎደላቸውን ተደጋጋሚ ጥያቄዎች በግንባታው ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አሳድረዋል፡፡ ችግሮቹን ለመቅረፍ የኢትዮጵያ መንገዶች አሰተዳደር፣ ከሥራ ተቋራጩ እንዲሁም ከዞንና ወረዳ መስተዳድር አካላት ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን እያደረገ ይገኛል፡፡ ለፕሮጀክቱ መሳካት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ በመሆኑ የአካባቢው ማኅበረሰብ ይበልጥ ተገቢውን ድጋፍና ትብብር እንዲያደርግ ኢ.መ.አ ያሳስባል፡፡ ፕሮጀክቱ ከአዲስ አበባ 675 ኪ.ሜ ርቀት ፊቅ ወረዳ ላይ ጀምሮ ሰገግ ወረዳ ላይ ያበቃል፡፡ ግናባታው ሲጠናቀቅ ኤረር ዞን እንዲሁም ሰገግ እና ዮሆብ ወረዳዎችን በቅርበት ያገናኛል፡፡ ከጎዴ-ጅጅጋ-ሀረር ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜና የትራፊክ መጨናነቅ ይቀንሰዋል፡፡ በአካባቢው ለሚገኙ አርብቶ አደሮችና በቁም እንስሳት ንግድ ላይ ለተሰማሩ ግለሰቦችም የመንገዱ መገንባት ፋይዳው የጎላ ነው፡፡ የዚሁ መንገድ ፕሮጀክት ትስስር ቀጣይ ክፍል የሆነው ምዕራፍ 2 ሰገግ-ገርቦ-ዮአለ አስፋልት መንገድ በትኩረት እየተሠራ ነው።

80 ኪ.ሜ የሚረዝመው የቱሉ ቦሎ ኬላ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 60 በመቶ የሚሆነው ተገባደደ:: በፕሮጀክቱ ግንባታ ላይ የአስፍልት ማንጠፍ ስራ የተጀመረ ሲሆን አሁን ላይ 39
+2
80  ኪ.ሜ የሚረዝመው የቱሉ ቦሎ ኬላ የአስፋልት ኮንክሪት  የመንገድ ግንባታ  ፕሮጀክት 60 በመቶ የሚሆነው ተገባደደ:: በፕሮጀክቱ ግንባታ ላይ የአስፍልት ማንጠፍ ስራ የተጀመረ ሲሆን አሁን ላይ 39 ኪ.ሜ የአስፈልት ንጣፍ ተከናውኗል:: በተያያዘም የአፈር ቆረጣና ሙሌት ፣የውሀ ማፋሰሻ ቱቦዎች ቀበራ፣የሰብቤዝ፣ቤዝኮርስ እና የድልድይ ስራ ጨምሮ እየተሰራ ይገኛል:: ቀሪ የግንባታ  ለማጠናቀቅ የሚያስችሉ በርካታ የስራ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ናቸው:: ይህ የመንገድ ፕሮጀክት በዋናነት  መነሻዉን  ቱሉ ቦሎ ከተማ ላይ  አድርጎ ኬላ ከተማ ላይ የሚያበቃ ይሆናል:: የዚህን መንገድ ግንባታ የሚያካሄደው ሁናን ሁንዳ ሮድ ኤንድ  ብሪጅ ኮርፖሬሽን የተባለ የስራ ተቋራጭ  ሲሆን የተባበሩት የምህንድስና አማካሪዎች ኃ.የተ.የግ. ኩባንያ የማማከርና የቁጥጥሩን ስራ እየተከታተለው ነው:: የመንገድ ፕሮጀክቱ በወረዳ 19 ሜትር እንዲሁም በገጠር 7 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ነው:: ለመንገዱ ግንባታ  የሚውለውን 1,317,686,548.71( አንድ ቢሊዮን ሶስት መቶ አስራ ሰባት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሰማንያ ስድስት ሺህ አምስት መቶ አርባ ስምንት ብር) በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው:: የቱሉ ቦሎ መንገድ ግንባታ ሲጠናቀቅ በአከባቢው የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ደረጃውን የጠበቀ የመንገድ መሰረተ ልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስችላል:: በተጨማሪም በአካባቢው በስፍት የሚመረቱ ጤፍ  የሰብል ምርቶችን እንዲሁም  የእንሰት ውጤቶችን ወደ መሀል ከተማ ለማጓጓዝ ኢኮኖሚያዊ ፍይዳው የጎላ ነው። መንገዱን ለሚጠቀሙ አሽከርካሪዎችም  ጊዜንና ጉልበት በመቆጠብ ማህበራዊ ትስስሩን ያሳልጣል።

Invitation for Bid Design, Supply, Installation, Operations and Maintenance Electronic Toll Collection (ETC) Systems for Addi
+2
Invitation for Bid Design, Supply, Installation, Operations and Maintenance Electronic Toll Collection (ETC) Systems for Addis Ababa - Adama Expressway

የተቀናጀ ሀገር አቀፍ መሰረተ ልማት ጎባኤ እየተካሄደ ነው አዳማ፣ ጥቅምት 3፣ 2015 ዓም (ኢመአ)፡ በኢፌዴሪ ከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴርና በሴክተሩ ተቋማት በጋራ የተዘጋጀ ሀገር አቀፍ የመሰረ
+5
የተቀናጀ ሀገር አቀፍ መሰረተ ልማት ጎባኤ እየተካሄደ ነው አዳማ፣ ጥቅምት 3፣ 2015 ዓም (ኢመአ)፡ በኢፌዴሪ ከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴርና በሴክተሩ ተቋማት በጋራ የተዘጋጀ ሀገር አቀፍ የመሰረተ ልማት ጉባኤ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡ ጉባኤው በዋናነት መሰረተ ልማቶችን አቀናጅቶ በመምራትና በማስተዳደር ዙሪያ ያሉ መልካም ጅምሮችን ማዳበርና ማጠናከር እንዲሁም የሚታዩ ችግሮችን መፍታትን ዓላማ ያደረገ ሲሆን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒን ጨምሮ የፌራል እና የክልል የዘርፉ ተቋማት ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡ በመድረኩ የፌዴራልና ክልል ተቋማት የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸሞችና የ2015 በጀት ዓመት ዕቅዶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል፡፡

የተቀናጀ ሀገር አቀፍ መሰረተ ልማት ጎባኤ እየተካሄደ ነው አዳማ፣ ጥቅምት 3፣ 2015 ዓም (ኢመአ)፡ በኢፌዴሪ ከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴርና በሴክተሩ ተቋማት በጋራ የተዘጋጀ ሀገር አቀፍ የመሰረ
+5
የተቀናጀ ሀገር አቀፍ መሰረተ ልማት ጎባኤ እየተካሄደ ነው አዳማ፣ ጥቅምት 3፣ 2015 ዓም (ኢመአ)፡ በኢፌዴሪ ከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴርና በሴክተሩ ተቋማት በጋራ የተዘጋጀ ሀገር አቀፍ የመሰረተ ልማት ጉባኤ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡ ጉባኤው በዋናነት መሰረተ ልማቶችን አቀናጅቶ በመምራትና በማስተዳደር ዙሪያ ያሉ መልካም ጅምሮችን ማዳበርና ማጠናከር እንዲሁም የሚታዩ ችግሮችን መፍታትን ዓላማ ያደረገ ሲሆን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒን ጨምሮ የፌራል እና የክልል የዘርፉ ተቋማት ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡ በመድረኩ የፌዴራልና ክልል ተቋማት የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸሞችና የ2015 በጀት ዓመት ዕቅዶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል፡፡