ar
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

الذهاب إلى القناة على Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

تُعد قناة ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 13 342 مشتركاً، محتلاً المرتبة 1 756 في فئة النقل والمرتبة 2 537 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 13 342 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 17 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 95، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 18، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 41.14‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.24‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 485 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 032 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 16.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 18 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة النقل.

13 342
المشتركون
+1824 ساعات
+417 أيام
+9530 أيام
أرشيف المشاركات
የሀይቅ - ቢስቲማ - ጭፍራ የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታ በመካሄድ ላይ ይገኛል አዲስ አበባ፣ መጋቢት 26፣ 2016 (ኢ መ አ):- 74 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የሀይቅ - ቢስቲማ - ጭፍራ የዲዛይንና ግንባታ መንገድ ስራ ፕሮጀክት በመካሄድ ላይ ነው ፡፡ በአሁኑ ወቅት የመንገድ ፕሮጀክቱ አጠቃላይ የግንባታ አፈፃፀም 29.72 በመቶ የደረሰ ሲሆን ይህንንም ስራ አጠናክሮ ለማሰቀጠል እየተሰራ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት የጠረጋ፣ የአፈር ቁፋሮ ፣ የአፈር ሙሌት፣ የካፒንግ ስራ፣ የውሀ ማፋሰሻ ቱቦ ስራ አንዲሁም የድልድይ ስራ ከኪ.ሜ. 3+000 እስከ ኪ.ሜ. 74+000 ድረስ እየተከናወነ ይገኛል። ተደጋጋሚ የጸጥታ እና ያለመረጋጋት ችግሮች፣ የወሰን ማስከበር እና በአካባቢው ወቅቱን ያልጠበቀ ከፍተኛ ዝናብ መኖር እንዲሁም የግንባታ ግብአት እጥረቶች ፕሮጀክቱ በሚፈለገው ፍጥነት እንዳይሄድ አድርጎት ቆይቷል፡፡ ይህንንም ለመቅረፍ ብሎም የግንባታውን ሂደት ለማሻሻል በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በኩል የቅርብ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ ነው፡፡ የመንገድ ግንባታውን እያከናወኑ የሚገኙት ፓወርኮን ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር እና አሰር ኮንስትራክሽን በጋራ በመሆን ነው። የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን እየሰራ የሚገኘው ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ነው። መንገዱ 19 ሜትር በወረዳ ፣ 15 ሜትር በቀበሌ፣ 10 ሜትር በገጠር ትከሻን ጨምሮ አጠቃላይ የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ነው፡፡ የሀይቅ ቢስቲማ ጭፍራ የመንገድ ፕሮጀክትን ለመገንባት የሚውለው 2,233,149,775.29 ብር የተሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው፡፡ በመስመሩ ከዚህ በፊት ደረጃውን የጠበቀ የመንገድ አውታር ያልተዘረጋበትና ለትራንስፖርት እንቅስቃሴ አስቸጋሪ የነበረ ሲሆን ለአካባቢው ሕብረተሰብ ሆነ ለሀገራችን ያለው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ከግምት ውስጥ በማስገባት በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል፡፡ መንገዱ በዋናነት የአፋርና የአማራ ክልሎችን በቅርበት በማገናኘት ማህበራዊ እድገት በማፋጠን ጥራት ያለዉ ፣ ምቹ እና ፈጣን የሆነ የትራፊክ ፍሰት እንዲኖር ከማስቻሉ ባሻገር በአካባቢው በስፋት የሚገኙትን ማሽላ፣ ጫት እና የተለያዩ የፍራፍሬ ምርቶችን በማጓጓዝ የንግድ እንቅስቃሴን ለማቀላጠፍ ያስችላል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የደሎ - ሰብሮ - ጃራ-ሼይኽ ሑሴን መንገድ ግንባታ በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው አዲስ አበባ፣ መጋቢት 20፣ 2016 (ኢ መ አ):- በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ባሌ ዞን የታሪካዊው ድሪ ሼይኽ ሑሴን መካነ - ቅርስ መዳረሻ የሆነው የደሎ - ሰብሮ - ጃራ - ሼይኽ ሑሴን መንገድ ግንባታ በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው የመንገድ ፕሮጀክቱ 77 ነጥብ 48 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፣ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል። ከአነስተኛ እስከ ከፍተኛ ያሉ ድልድዮች፣ የፍሳሽ ማስተላለፊያ ቱቦዎች እና ከልቨርቶችም የግንባታው አካል ናቸው። አሁን ላይ የአፈር ቆረጣ፣ የአፈር ድልዳሎ እና ሙሌት፣ የሰብቤዝ፣ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ማምረት እንዲሁም የወሰን ማስከበር ሥራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ። የቻይናው ዓለም አቀፍ የሥራ ተቋራጭ ዠይጂያንግ ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ቡድን ግንባታውን በማከናወን ላይ ይገኛል። ለግንባታው ማስፈጸሚያ ብር 1,592,270,000.00 (1 ነጥብ 5 ቢሊዮን) በፌደራሉ መንግስት ተመድቧል። አይዲኮን ኢንፍራስትራክቸር ዴቬሎፕመንት ኮንሰልታንት ኃላ.የተ.የግ ማኅበር የግንባታውን ጥራት በማማከር እና በመቆጣጠር በኩል ይሳተፋል። የግንባታ ግብዓት እጥረት እና ዋጋ መናር፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ የሥራ ተቋራጩ የአቅም ውስንነት፣ በመንገድ ወሰን ውስጥ በወቅቱ ያልተነሱ በርካታ ንብረቶች በግንባታው እንቅስቃሴ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አሳርፋል። ችግሮቹን ለመቅረፍ፣ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የባሌ አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በየደረጃው ከሚገኙ የመስተዳድር አካላት እና ከኅብረተሰቡ ጋር በመጣመር የተለያዩ ጥረቶች በመደረግ ላይ ናቸው። አንጻራዊ ለውጦችም ተመዝግበዋል። ፕሮጀክቱ ተጠቅቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ቀድሞ ለመጓዝ ይወስድ የነበረውን የ3 ሰዓታት የጉዞ ጊዜ ወደ 1ሰዓት ተኩል ያሳጥረዋል። የጊኒር እና ጎሎልቻ ወረዳዎችን ጨምሮ በርካታ አጓራባች ቀበሌዎችን ደረጃውን በጠበቀ መንገድ በማስተሳሰር የሕዝብ ለሕዝብ መስተጋብሩን ይበልጥ ያጠናክራል። የመንገድ ፕሮጀክቱ በተለይም በየዓመቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች እንደሚጎበኙት የሚነገርለት የታሪካዊው የድሪ ሼይኽ ሑሴን ባሌ መዳረሻ እንደመኾኑ፣ መንገዱን ለቱሪስቶች ምቹ በማድረግ ረገድ የጎላ ሚና ይኖረዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

THE 7th ANNUAL ROAD RESEARCH CONFERENCE ETHIOPIAN ROADS ADMINISTRATION ROAD RESEARCH CENTER Call for Paper

በአዴሌ - ግራዋ   የመንገድ   ግንባታ  ፕሮጀክት  የአስፋልት ንጣፍ ስራ ተጀመረ   አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢመአ) ፡-  53   ኪሎ ሜትር   በሚረዝመው  የአዴሌ - ግራዋ  የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታ  አስፋልት የማንጠፍ ስራ ተጀምሯል፡፡ ከአስፋልት  ንጣፍ   ስራው  ጎን  ለጎን  የአፈር ስራ ፣ የሰብ ቤዝ ፣ የቤዝ ኮርስ  እንዲሁም  የውሃ መፋሰሻ ቱቦ ቀበራ ስራዎች  በመካሄድ  ላይ ይገኛሉ፡፡ የፕሮጀክቱ   አሁናዊ   የግንባታ  እንቅስቃሴ  60.84  በመቶ የደረሰ ሲሆን ይህንንም  በማጠናከር በተያዘው እቅድ መሰረት ለማስኬድ በትኩረት እየተሰራ ነው። ፕሮጀክቱን  በሚፈለገው  ፍጥነት  ለማስኬድ  ይቻል  ዘንድ  በግንባታ  ሂደቱ  ላይ የተስተዋሉ የወሰን ማስከበር ፣ የካሳ ክፍያ እንዲሁም የግብዓት  እጥረቶችን  ለመፍታት የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር  ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ እየሰራ ይገኛል፡፡ የመንገድ  ግንባታውን  እያከናወነ የሚገኘው  ሂቤ  ኮንስትራክሽን ግሩፕ  የተባለ የስራ ተቋራጭ ሲሆን ጎጎት ኮንሰልቲንግ  ኢንጅነሪንግ  የማማከር  እና የቁጥጥር ስራውን እያካሄደ ይገኛል፡፡ መንገዱ   በገጠር  7 ሜትር ፣ በቀበሌ 12  ሜትር ፣ በወረዳ 19  ሜትር  እንዲሁም  በከተማ  20 ሜትር  አጠቃላይ  የጎን ስፋት ያለው ነው  ። ግንባታውን ለማከናወን የሚያስችለውን አንድ ቢሊዮን አራት መቶ ሰላሳ ስድስት ሚሊዮን ሦስት መቶ ሺህ ብር በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው። ፕሮጀክቱ  በዋናነት  በምስራቅ ሀረርጌ ዞን የሚገኙትን  ሀሮማያ ፣ ቀርሳ ፣ ቁርፋ ጨሌ እና የግራዋ ከተማዎችን  በቅርበት ለማስተሳሰር የሚያስችል ነው፡፡ ግንባታው  ሲጠናቀቅም በአካባቢው በስፋት የሚገኙትን የቁም  እንስሳት ውጤቶች ፣ ፍራፍሬና  ሌሎችንም ምርቶች  ወደ ገበያ  አውጥቶ  በመሸጥ  ነዋሪዎች  ከምርታቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከማድረግ አንጻር  ጠቀሜታው የላቀ ነው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የኮምቦልቻ የመንገድ ጥገና ዲስትሪክት የተለያዩ የጥገና ስራዎችን በማካሄድ ላይ ነው አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢመአ) ፡-  የኮምቦልቻ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ከፊል ሰሜን ሸዋን ጨምሮ ከወሎ እስከ አፋር ላሉት መንገዶች አስፈላጊውን ጥገና እና እንክብካቤ እያደረገ ይገኛል። የጥገና ዲስትሪክቱ በ2016 በጀት ዓመት ስምንት ወራት በርካታ የጥገና ስራዎችን ያካሄደ ሲሆን ፣ ከእነዚህ የመንገድ ጥገና ስራዎች መካከልም የወልዲያ ከተማን ወደ አስፓልት ደረጃ የማሳደግ ፕሮጀክት አንዱ ነው። ከዚህም ባሻገር የአምቤዶም ድልድይ ግንባታንም በማካሄድ ላይ ይገኛል። ይኸው ድልድይ በመጎዳቱ ምክንያት የአፋር አርብቶ አደሮች ለረጅም ጊዜያት ከዲችኦቶ ወደ ኤሊዳር ለመሄድ በጋላፊ በኩል ተጨማሪ 30 ኪሎ ሜትር ለመጓዝ ተገደዋል። ይሁንና የዚህ ድልድይ ግንባታ አብዛኛው ስራ የተጠናቀቀ በመሆኑ በሚቀጥለው ወር ለትራፊክ ክፍት ሆኖ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል፡፡ በተጨማሪም ከደሴ ወደ ወልዲያ የሚወስደው መንገድ ከደሴ 17 ኪሎ ሜትር  እና 58 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በደዶ እና ውጫሌ መግቢያ ውልቄ በሚባል ቦታ ላይ በነበረው ብልሽት የትራፊክ  ፍሰቱ ተስተጓጉሎ የነበረ መሆኑ ይታወቃል። ሆኖም ግን በበጀት አመት ውስጥ በተሰራው ስራ የበደዶ ጥገና ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት የሆነ ሲሆን ፣ የውልቄ ጥገና ስራንም በማጠናቀቅ ለትራፊክ ክፍት ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው። የግንባታ ሂደታቸው ተቋርጦ የነበረው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ለምሳሌ የጉጉፍቱ-ወርኢሉ እና ጃማ-ደጎሎ ፕሮጀክቶች አፋጣኝ  ጥገና ተደርጎላቸው ለትራፊክ ክፍት ሆነዋል። እነዚህ ስራዎች በበጀት ዓመቱ ስምንት ወራት የተሰሩ ሲሆኑ እስከ በጀት አመቱ መጨረሻ ድረስ በርካታ የጥገና ስራዎች የሚከናወኑ ይሆናል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የቁንዲ-ጎሮዳሞሌ-ጂብሪል ክፍል-3 መንገድ ግንባታ በጥሩ አፈጻጸም ላይ ይገኛል፡፡ አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2016 (ኢ መ አ) ፡- የሶማሌ እና ኦሮሚያ ክልሎችን በቅርበት የሚያስተሳስረው የቁንዲ-ጎሮዳሞሌ-ጂብሪል ክፍል-3 መንገድ ግንባታ በጥሩ አፈጻጸም ላይ ይገኛል፡፡ የመንገድ ግንባታው ጠቅላላ 82 ነጥብ 8 ኪሎሜትር ርዝመት ኖሮት በአስፋልት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል፡፡ ግንባታው የጨረቲ-ጎሮቦክሳ-ጎሮዳሞሌ ፕሮጀክት ክፍል-3 ሲኾን፣ ከጨረቲ- ዶሎአዶ ከሚያቀናው አውራ መንገድ ተገንጥሎ ወደ ጎሮዳሞሌ የሚወስደው መንገድ አካል ነው፡፡ አሁን ላይ የተለዋጭ መንገድ፣ የመሬት ጠረጋ፣ የአፈር ጠረጋ እና ሙሌት፣ የካምፕ ግንባታ አንዲሁም የዲዛይን ክለሳ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው፡፡ የ9 ድልድዮች ግንባታን ጨምሮ አነስተኛ፣ ከፍተኛ ፍሳሽ ማስተላለፊያ ቱቦዎች እና ከልቨርቶች ግንባታ ሥራም በፕሮጀክቱ ተካትቷል፡፡ መንገዱ፣ የመንገድ ትከሻን ጨምሮ በገጠር 8 ሜትር፣ በወረዳ እና በከተማ የእግረኛ መንገድን ጨምሮ 19 ሜትር እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ይገኛል። በዚህ ዓመት መጨረሻም የግንባታውን አፈጻጸም ደረጃ 20 በመቶ ለማድረስ ዕቅድ ተቀምጦ ነው እየተሠራ የሚገኘው፡፡ ሀገር በቀሉ ኤም ሲ ጂ ኮንስትራክሽን ኃላ/የተ/ የግ/ ማኅበር ግንባታውን በማከናወን ላይ የሚገኘ ሲኾን፣ ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ፕሮጀክቱን የማማከር እና የመቆጣጠር ሥራ በመሥራት ላይ ይገኛል፡፡ ለግንባታው ማስፈጸሚያ የሚውለው 3,811,899,916.93 (3 ነጥብ 8 ቢሊዮን) ብር ወጪ በፌደራል መንግስት በጀት ይሸፈናል፡፡ ፕሮጀክቱ የሶማሌ እና ኦሮሚያ ክልሎችን በቅርበት ከማገናኘቱም ባሻገር ከጨረቲ እስከ ጅብሪል ማለትም በ216 ኪሎሜትር ርቀት ውስጥ የሚገኙትን ቁንዲ እና ጎሮዳሞሌ ወረዳዎችን ጨምሮ በርከት ያሉ ከተሞችን ደረጃውን በጠበቀ መንገድ የሚያገናኘ ነው፡፡ በተለይም ሥፍራው ከዚህ ቀደም ምንም ዓይነት የመንገድ መሠረተ-ልማት ያልነበረ በመኾኑ፣ የመንገዱ መገንባት የሕዝብ ለሕዝብ ትስስሩን በእጅጉ ያጠናክራል፡፡ የዚህ ግዙፍ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አካል የኾኑት ክፍል አንድ ጨረቲ-ሀገረመቆር እና ክፍል ኹለት ሀገረመቆር-ቁንዲ ፕሮጀክቶች ከዚህ ቀደም ግንባታቸው ተጠናቅቆ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የላሊበላ - ኩልመስክ - ሙጃ መንገድ ፕሮጀክት በጥሩ የአፈጻጸም ደረጃ ላይ ይገኛል አዲስ አበባ፣ መጋቢት 03፣ 2016 (ኢ መ አ) ፡- የላሊበላ ውቅር አብያተ-ክርስቲያናት መዳረሻ የሆነው የላሊበላ - ኩልመስክ - ሙጃ መንገድ ፕሮጀክት አሁን ላይ በጥሩ የአፈጻጸም ደረጃ ላይ ይገኛል። ፕሮጀክቱ 48 ነጥብ 78 ኪሎሜትር የሚሸፍን ኾኖ፣ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ በመንገድ ግንባታው እስከ አሁን የካምፕ ግንባታ፣ የዲዛይን፣ የአፈር ጠረጋ፣ ቆረጣ እና ሙሌት፣ የውኃ ተፋሰስ እንዲሁም የቅድመ-ምርት ሥራዎች ተሠርተዋል፡፡ የግንባታው አጠቃላይ አፈጻጸም በአሁን ወቅት 10 ነጥብ 51 በመቶ ደርሷል፡፡ በተጨማሪም የአነስተኛ እና ከፍተኛ ከልቨርቶች፣ የአስፋልት ንጣፍ እንዲሁም የስድስት ድልድዮች ግንባታ ሥራም በፕሮጀክቱ ተካትቷል፡፡  ዓለም አቀፉ ቻይና ሲቪል ኢንጂነሪነግ ኮንስትራክሽን ኮራፖሬሽን ግንባታውን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ቤዛ ኢንጅነሪንግ ኬኒያ ሊሚትድ የግንባታውን ጥራት የመቆጣጠር እና የማማከር ሥራ ይሠራል፡፡ ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ 1,888,292,297 (1 ነጥብ 8 በሊዮን) ብር በፌደራል መንግስት ተመድቧል፡፡ በአካባቢው አልፎ አልፎ የሚስተዋለው የጸጥታ ስጋት፣ በመንገድ ክልል ውስጥ የሚገኙ ንብረቶች በወቅቱ አለመነሳት እንዲሁም የግንባታ ግብዓት አቅርቦት እጥረት እና ዋጋ መናር በግንባታው ሂደት ውስጥ የገጠሙ ተግዳሮቶች ናቸው፡፡ ችግሮቹን ለመፍታት የአትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከየአካባቢው ማኅበረሰብ እና የመስተዳድር አካላት ጋር በመቀናጀት ጥረት በመደረጉ አሁን ላይ ግንባታው በመልካም ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ የመንገዱ ነባር ገጽታ በጠጠር መንገድ ደረጃ ሲኾን፥ በአገልግሎት ብዛት በእጅጉ የተጎዳ ነው፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅ በተለይም የላሊበላ ፍልፍል አብያተ-ክርስቲያናት አማራጭ መዳረሻ በመኾን ለቱሪስቶች ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡ በሥፍራው የሚመረቱትን የዘንጋዳ፣ ገብስ፣ ባቄላ እና መሰል የግብርና ምርት ውጤቶች ወደ ማዕከላዊ ገበያ በቀላሉ ለማድረስ ያስችላል፡፡ የላሊበላ፣ ኩልመስክ እና ሙጃ ከተሞችን ደረጃውን በጠበቀ መንገድ ያስተሳስራል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

https://youtu.be/8ivQ3u-C_aI የባሌ - ሮቤ ጎሮ ሶፍ ዑመር ጊኒር መገንጠያ መንገድ ግንባታ

ዳዬ - ጭሪ - ናንሴቦ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ የአፈፃፀም  ሂደት ላይ ይገኛል አዲስ አበባ ፣ የካቲት 28 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢ መ አ) የሲዳማ እና ኦሮሚያ ክልሎችን በቅርበት የሚያስተሳስረው የዳዬ-ጭሪ-ናንሴቦ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ የአፈፃፀም ሂደት ላይ ይገኛል፡፡ የፕሮጀክቱ አሁናዊ የግንባታ አፈጻጸም 84 በመቶ ላይ የደረሰ ሲሆን ቀሪ ስራዎችን በቅርቡ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡ የመንገድ ግንባታዉ አጠቃላይ 71.4 ኪ.ሜትር ርዛማኔ ያለዉ ሲሆን ከዚህም ውስጥ 47 ኪ.ሜትር የአስፋልት ንጣፍ ስራው ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል፡፡ አብዛኛዉ የቅድመ አስፋልት ንጣፍ ስራው እየተገባደደ ነው። ቀሪ የአስፋልት ንጣፍ ስራውም በቅርቡ የሚጠናቀቅ ይሆናል፡፡ ለግንባታው የሚውለው  1,723,608,313 ብር  ሲሆን ይህ ወጪ የሚሸፍነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ  ከአዲስ አበባ 404 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከምትገኘው ዳዬ ከተማ መነሻውን በማድረግ በኦሮሚያ ክልል እየተገነባ ከሚገኘው የኤዶ-ሴሮፍታ-ወርቃ መንገድ ፕሮጀክት ጋር ይገናኛል። የመንገድ ፕሮጀክቱ የሚካሄድበት አካባቢ የተራዘመ ዝናብ የሚዘንብበት በመሆኑ የግንባታ ሂደቱ በታሰበለት ፍጥነት እንዳይሄድ እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል፡፡ በተጨማሪም የወሰን ማስከበር እና ተያያዥ ችግሮች ፣ የዋጋ ንረትና የግንባታ ግብዓት አቅርቦት ችግሮች በግንባታ ሂደቱ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖዎችን አሳድረዋል፡፡ ከዚህ ባለፈም ግንባታዉ በሚካሄድበት አካባቢ ሲስተዋል የቆየው የመሬት መንሽራተት ለግንባታዉ መዘግየት ሌላኛዉ ፈተና ነበር፡፡ ሆኖም ግን አሁን ላይ በአካባቢው የሚስተዋለው የዝናብ ሁኔታ በመቀነሱ እና በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሻሸመኔ እና አካባቢው ፕሮጀክቶች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት እና በኢመአ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ በመሆኑ ችግሮቹ ከሞላ ጎደል ተቀርፈዉ አሁን ላይ አፈፃፀሙ እየተፋጠነ ይገኛል፡፡ መንገዱ  ትከሻን ጨምሮ በገጠር 10 ሜትር እና በከተማ 19 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረዉ ተደርጎ ነዉ እየተገነባ የሚገኘዉ፡፡    ግንባታውን በማካሄድ ላይ የሚገኘው ቻይና ዉ ይ ኮርፖሬሽን ሊሚትድ  ሲሆን ፣ ክላሲክ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን በማከናወን ላይ ይገኛል ፡፡ የቀድሞ የመንገዱ ይዘት በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን ለትራንስፖርት አስቸጋሪ ነበር። ይህ ፕሮጀክት ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ሲዳማ ክልልን ከኦሮሚያ ክልል ጋር በመንገድ መሰረት ልማት በቅርበት ያስተሳስራል። በተጨማሪ አካባቢው  ቡናን ጨምሮ ሌሎች የአዝርዕት ምርቶች የሚመረቱበት በመሆኑ አርሶ አደሮች ያመረቱትን ምርት በቀላሉ ወደ ገቢያ እንዲያደርሱ ይረዳቸዋል። በተጨማሪም ፕሮጀክቱ በንሳ፣ዳኤላ፣ጭሪ እና ነንሰቦ የሚባሉ ወረዳዎችን እና በርካታ ትናንሽ ከተሞችን  በቅርበት የሚያስተሳስር በመሆኑ የከተሞች እድገት እንዲፋጠን ያደርጋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

ዳዬ - ጭሪ - ናንሴቦ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ የአፈፃፀም  ሂደት ላይ ይገኛል አዲስ አበባ ፣ የካቲት 28 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢ መ አ) የሲዳማ እና ኦሮሚያ ክልሎችን በቅርበት የሚያስተሳስረው የዳዬ-ጭሪ-ናንሴቦ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ የአፈፃፀም ሂደት ላይ ይገኛል፡፡ የፕሮጀክቱ አሁናዊ የግንባታ አፈጻጸም 84 በመቶ ላይ የደረሰ ሲሆን ቀሪ ስራዎችን በቅርቡ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡ የመንገድ ግንባታዉ አጠቃላይ 71.4 ኪ.ሜትር ርዛማኔ ያለዉ ሲሆን ከዚህም ውስጥ 47 ኪ.ሜትር የአስፋልት ንጣፍ ስራው ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል፡፡ አብዛኛዉ የቅድመ አስፋልት ንጣፍ ስራው እየተገባደደ ነው። ቀሪ የአስፋልት ንጣፍ ስራውም በቅርቡ የሚጠናቀቅ ይሆናል፡፡ ለግንባታው የሚውለው  1,723,608,313 ብር  ሲሆን ይህ ወጪ የሚሸፍነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ  ከአዲስ አበባ 404 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከምትገኘው ዳዬ ከተማ መነሻውን በማድረግ በኦሮሚያ ክልል እየተገነባ ከሚገኘው የኤዶ-ሴሮፍታ-ወርቃ መንገድ ፕሮጀክት ጋር ይገናኛል። የመንገድ ፕሮጀክቱ የሚካሄድበት አካባቢ የተራዘመ ዝናብ የሚዘንብበት በመሆኑ የግንባታ ሂደቱ በታሰበለት ፍጥነት እንዳይሄድ እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል፡፡ በተጨማሪም የወሰን ማስከበር እና ተያያዥ ችግሮች ፣ የዋጋ ንረትና የግንባታ ግብዓት አቅርቦት ችግሮች በግንባታ ሂደቱ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖዎችን አሳድረዋል፡፡ ከዚህ ባለፈም ግንባታዉ በሚካሄድበት አካባቢ ሲስተዋል የቆየው የመሬት መንሽራተት ለግንባታዉ መዘግየት ሌላኛዉ ፈተና ነበር፡፡ ሆኖም ግን አሁን ላይ በአካባቢው የሚስተዋለው የዝናብ ሁኔታ በመቀነሱ እና በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሻሸመኔ እና አካባቢው ፕሮጀክቶች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት እና በኢመአ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ በመሆኑ ችግሮቹ ከሞላ ጎደል ተቀርፈዉ አሁን ላይ አፈፃፀሙ እየተፋጠነ ይገኛል፡፡ መንገዱ  ትከሻን ጨምሮ በገጠር 10 ሜትር እና በከተማ 19 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረዉ ተደርጎ ነዉ እየተገነባ የሚገኘዉ፡፡    ግንባታውን በማካሄድ ላይ የሚገኘው ቻይና ዉ ይ ኮርፖሬሽን ሊሚትድ  ሲሆን ፣ ክላሲክ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን በማከናወን ላይ ይገኛል ፡፡ የቀድሞ የመንገዱ ይዘት በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን ለትራንስፖርት አስቸጋሪ ነበር። ይህ ፕሮጀክት ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ሲዳማ ክልልን ከኦሮሚያ ክልል ጋር በመንገድ መሰረት ልማት በቅርበት ያስተሳስራል። በተጨማሪ አካባቢው  ቡናን ጨምሮ ሌሎች የአዝርዕት ምርቶች የሚመረቱበት በመሆኑ አርሶ አደሮች ያመረቱትን ምርት በቀላሉ ወደ ገቢያ እንዲያደርሱ ይረዳቸዋል። በተጨማሪም ፕሮጀክቱ በንሳ፣ዳኤላ፣ጭሪ እና ነንሰቦ የሚባሉ ወረዳዎችን እና በርካታ ትናንሽ ከተሞችን  በቅርበት የሚያስተሳስር በመሆኑ የከተሞች እድገት እንዲፋጠን ያደርጋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et