ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 692 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 014 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 155 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 692 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 30 أغسطس, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 145، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 2، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 31.28‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.96‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 909 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 661 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 31 أغسطس, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 692
المشتركون
+224 ساعات
+187 أيام
+14530 أيام
أرشيف المشاركات
⚡️ ኢትዮጵያ - የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ማማ (Power Hub)! 🇪🇹 ሀገራችን ኢትዮጵያ በተፈጥሮ የታደለችው የታዳሽ ኃይል ጸጋ እጅግ ግዙፍ መሆኑን ያውቃሉ? እውነታው ምን ይላል? 📊 ኢትዮጵ
⚡️ ኢትዮጵያ - የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ማማ (Power Hub)! 🇪🇹 ሀገራችን ኢትዮጵያ በተፈጥሮ የታደለችው የታዳሽ ኃይል ጸጋ እጅግ ግዙፍ መሆኑን ያውቃሉ? እውነታው ምን ይላል? 📊 ኢትዮጵያ ያላት እምቅ አቅም፦ ከውሃ፣ ከፀሐይ፣ ከነፋስና ከከርሰ ምድር እንፋሎት (Geothermal) ምንጮች እስከ 150 ጊጋ ዋት (GW) ኃይል የማመንጨት አቅም አላት። 🏗 እስካሁን የለማው፦ ካለን አጠቃላይ አቅም ውስጥ እስካሁን ማልማት የቻልነው 9.5 ጊጋ ዋት (GW) ብቻ ነው። ይህ ማለት ካለን ጸጋ ጥቅም ላይ የዋለው 6.33% ብቻ ሲሆን፣ ቀሪው 93.67% ገና ያልተነካና ለልማት የሚጠበቅ መሆኑን ያሳያል። ይህ አቅም ለሀገራችን ምን ትርጉም አለው? 1. 🏭 የኢንዱስትሪ ሽግግርን ይደግፋል፤  ለአምራች ፋብሪካዎቻችንና ለኢንዱስትሪ ፓርኮች አስተማማኝና ርካሽ ኃይል ለማቅረብ ያስችላል። 2. 💰 የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ያሰፋል፤  ለጎረቤት ሀገራት ኃይል በመሸጥ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማግኘት የመሰረተ ልማት ተደራሽነት ለማረጋገጥ ተጨማሪ አቅም ይፈጥርላታል። 3. 🌿 የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታን ያግዛል፤  ከብክለት ነጻ የሆነና የአካባቢ ጥበቃን ያገናዘበ ታዳሽ የኃይል ምንጭ ለመገንባት የተጀመረውን ሀገራዊ እንቅስቃሴ እውን ለመሆን ያግዛል። 4. 💡 ለትውልድ ብርሃን ይሆናል፤  የኤሌክትሪክ አገልግሎት ያልደረሳቸውን የገጠር አካባቢዎች ተጠቃሚ ማድረግ ያስችላል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይህንን እምቅ አቅም በስፋት በማልማት፣ ኢትዮጵያን የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለማድረግ በቁርጠኝነት ይሰራል! ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ትበራለች! ምስል በአርቴፊሻል ኢንተሌጀንስ የበለፀገ

ተቋሙ የትራንስፖርትና የነዳጅ አስተዳደሩን በማዘመን ውጤት እያመጣ ነው ………///….…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሽከርካሪና የነዳጅ አስተዳደርን ለማዘመንና ብክነትን ለመቀነስ የዘረጋቸው አዳዲ
+1
ተቋሙ የትራንስፖርትና የነዳጅ አስተዳደሩን በማዘመን ውጤት እያመጣ ነው ………///….…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሽከርካሪና የነዳጅ አስተዳደርን ለማዘመንና ብክነትን ለመቀነስ የዘረጋቸው አዳዲስ አሠራሮች ውጤት እያመጡ መሆኑን በተቋሙ የተሽከርካሪ አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደገለፁት ተቋሙ በአሁኑ ወቅት በ27 ዋና ዋና መስመሮች ላይ የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 26ቱ በራሱ ተሽርካሪዎች የሚሸፈኑ ናቸው፡፡ ከእነዚህ መስመሮች መካከል 16ቱ ሙሉ በሙሉ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መሆናቸውን ጠቅሰው ይህም በተቋሙ የትራንስፖርትና የነዳጅ አጠቃቀም ሥርዓት ላይ አዲስ ምዕራፍ ከመክፈቱም ባሻገር በዓመት ለነዳጅ ይወጣ የነበረውን ከ18 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ለማዳን አስችሏል ብለዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-የትራንስፖርትና-የነዳጅ-አስተዳደ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም

የምስራቅ ሪጂን አንድ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን (ማርች 8) አከበረ .......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ ሪጂን አንድ "የሴቶች ድምፅ ለእኩልነትና ለበለፀገች ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን (ማርች 8) በልዩ ሁኔታ አክብሯል። በበዓሉ አከባበር ላይ የሪጂኑ ዳይሬክተር አቶ ወርዲ መሀመድን ጨምሮ ሌሎች አመራሮችና ሠራተኞች ተገኝተዋል። አቶ ወርዲ በመርሃ-ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት በሪጂኑ የሚገኙ ሴት አመራሮችና ሠራተኞች ለድርጅቱ ውጤታማነት እያበረከቱት ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው በቀጣይም የሴቶችን ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ ተቋሙ በትኩረት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል። የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ ጊዜ፣ በሀገራችን ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ተከብሮ ውሏል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

photo content
+9

በስርቆት ምክንያት የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ወድቋል ……..///……. በአማራ ክልል ማዕከላዊ ጎንደር ዞን እንፍራንዝ ከተማ ልዩ ስሙ ሰብሀ ገብርኤል አካባቢ በስርቆት ምክንያት በከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ ጉዳት መድረሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ። በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ በላይነህ ልጅዓለም እንዳስታወቁት በተፈፀመው ስርቆት ምክንያት ከባህርዳር- አዘዞ ቁጥር ሁለት በተዘረጋ አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡ በዚህም ምክንያት የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶው መውደቁን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ከባህርዳር - አዘዞ ቁጥር ሁለት የተዘረጋው መስመር ኃይል ማስተላለፍ ማቋረጡን ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል። ይሁን እንጂ በባህርዳር - አዘዞ ቁጥር አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመርን እንደ አማራጭ በመጠቀም በማዕከላዊ እና ሰሜን ጎንደር ዞኖች ስር ለሚገኙ ከተሞች ኤሌክትሪክ እየቀረበ ይገኛል ብለዋል። እንደ አቶ በላይነህ የወደቀውን የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ በአፋጣኝ መልሶ በመትከል በአጭር ጊዜ ውስጥ የኃይል አቅርቦቱን ወደነበረበት ለመመለስ  የተቀናጀ ጥረት ይደረጋል፡፡ በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶው ላይ የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ አካላትን ተከታትሎ ለህግ ለማቅረብ እየተሰራ እንደሆነ ነው ያብራሩት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

በዳወሮ እና ኮንታ ዞኖች የኤሌክትሪክ ኃይል እቅርቦት ተቋርጧል ......///....... የጅማ- አባ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ለጊዜው ምክንያቱ ባልታወቀ ምክንያት ከመጋቢት
+1
በዳወሮ እና ኮንታ ዞኖች የኤሌክትሪክ ኃይል  እቅርቦት ተቋርጧል ......///....... የጅማ- አባ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ለጊዜው ምክንያቱ ባልታወቀ ምክንያት ከመጋቢት 22 ቀን 2018 ሌሊት 9፡15 ጀምሮ ኃይል ማስተላለፍ ማቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንዳስታወቁት የማስተላለፊያ መስመሩ ኃይል ማስተላለፍ ማቋረጡን ተከትሎ በዳውሮና በኮንታ ዞኖች ከትላንት ሌሊት ጀምሮ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ተቋርጧል፡፡ መስመሩ የተቋረጠበትን ምክንያት በመለየት ለችግሩ መፍትሔ ለመስጠት የሪጅኑ የጥገና ባለሙያዎች በመስመሩ ላይ የፍተሻ ሥራዎችን  እያከናወኑ እንደሚገኙም ጠቅሰዋል፡፡ የማስተላለፊያ መስመሩ ዳግም ኃይል ማስተላለፍ እስኪጀምር ድረስ ኃይል በተቋረጠባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠብቁ አቶ ጌታሁን ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

photo content

በተሽከርካሪ አስተዳደር ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን የማረም ሥራ እየተሰራ ነው …….///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተሽከርካሪ አስተዳደር ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ለማረም ጥብቅ የማስተካከያ እርምጃዎች እየወሰደ መሆኑን በተቋሙ የተሽከርካሪ አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደገለፁት ከተሽከርካሪ አስተዳደር ጋር በተያያዘ ተሽከርካሪዎችን ላልተፈቀደላቸው አካላት አሳልፎ መስጠትን ጨምሮ መመሪያን ያለማክበር እና የተቋሙን ተሸከርካሪ እንደ ግል ንብረት ያለመጠበቅ የአያያዝ ጉድለቶች እየተበራከቱ መጥተዋል፡፡ ችግሮቹን ለማረም የአያያዝ ችግር በሚፈጥሩ አሽከርካሪዎች ላይ ከሥራ ማገድን ጨምሮ ሌሎች አስተዳደራዊ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን ነው የገለፁት። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የተሸከርካሪዎችን ደህንነት ይበልጥ ለማረጋገጥ የሰርቪስ ጊዜያቸው ሳያልፍ በወቅቱ እንዲጠገኑ የማስቻል ሥራ የሁሉም ሥራ ኃላፊዎች እና አሽከርካሪዎች ኃላፊነት ሊሆን ይገባል፡፡ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት አዳዲስ አሰራሮችን ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩን የጠቆሙት አቶ ዋለ አዲስ ተሽከርካሪዎች ሲገዙም ሆነ ከፕሮጀክት ሲመለሱ ጥብቅ በሆነ የፍተሻ እና የርክክብ ሂደት ውስጥ እንደሚያልፉ ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም

የቴክኒክ ችግር የገጠመውን የበለስ ትራንስፎርመር በሌላ ቀይሮ አገልግሎት ለማስጀመር በርብርብ እየተሰራ ነው …....///….... በበለስ 400/132/33 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ የቴ
+9
የቴክኒክ ችግር የገጠመውን የበለስ ትራንስፎርመር በሌላ ቀይሮ አገልግሎት ለማስጀመር በርብርብ እየተሰራ ነው …....///….... በበለስ 400/132/33 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ የቴክኒክ ችግር ምክንያት ለረጅም ጊዜ ተቋርጦ የቆየውን የኃይል አቅርቦት ለመመለስ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የበለስ ኃይል ማንጫ ጣቢያ አስታወቀ፡፡ የጣቢያው ኃላፊ አቶ የወጉ ጌትዬ እንዳስታወቁት በጣቢያው ላይ 400 ኪሎ ቮልትን ወደ 132 ኪሎ ቮልት የሚቀይር 125 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ባለው ትራንስፎርመር ላይ በተፈጠረ የቴክኒክ ችግር ምክንያት በመቃጠሉ ለኢንዱስትሪዎችና ለአካባቢው ነዋሪዎች የሚደርሰውን አስተማማኝ ኃይል ለዓመታት አስተጓጉሏል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የቴክኒክ-ችግር-የገጠመውን-የበለስ-ትራን&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል የማከፋፈያ ጣቢያው አገልግሎት መስጠት ጀመረ …....///…….. የአርባምንጭ ቁጥር 2 ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ ሥራ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ተጠናቆ አገልግሎት
+3
የኃይል የማከፋፈያ ጣቢያው አገልግሎት መስጠት ጀመረ …....///…….. የአርባምንጭ ቁጥር 2 ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ ሥራ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት አስታወቀ። የፕሮጀክቱ ተወካይ ሥራ አስኪያጅ አቶ አንዱዓለም መላኩ እንደገለፁት የአርባ ምንጭ 2 ማከፋፈያ ጣቢያ ከወላይታ ሶዶ ቁጥር 2 ባለ 400/230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ግንባታ ቀጥሎ አገልግሎት መስጠት የጀመረ የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አንዱ አካል ነው፡፡ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው በአርባ ምንጭ ከተማ ሊገነባ ለታሰበው የተቀናጀ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ እና በ120 ኪሎ ሜትር ወሰን ውስጥ ለሚገኙ አካባቢዎች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ታስቦ መገንባቱን ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-የማከፋፈያ-ጣቢያው-አገልግሎት-መ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም

በአካባቢያዊና ማህበረሰባዊ እንዲሁም በሥራ ላይ ጤናና ደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ በተከናወነ ዳሰሳ ጥናት ላይ አውደ ጥናት ተካሄደ …....///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአካባቢያዊና ማህበረሰ
+9
በአካባቢያዊና ማህበረሰባዊ እንዲሁም በሥራ ላይ ጤናና ደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ በተከናወነ ዳሰሳ ጥናት ላይ አውደ ጥናት ተካሄደ …....///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአካባቢያዊና ማህበረሰባዊ እንዲሁም በሥራ ላይ ጤናና ደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ በተከናወነ የዳሰሳ ጥናት ላይ አውደ ጥናት ተካሂዷል። በአዲስ አበባ ቤስት ዌስተርን ፕላስ ሆቴል በዛሬው ዕለት በተዘጋጀው አውደጥናት ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢትዮ ፓወር አካዳሚ ዳይሬክተር ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር) እንደገለፁት ተቋሙ የሀገርን ልማት የሚያረጋግጡ በርካታ የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን እያከናወነ ይገኛል። ፕሮጀክቶቹን ሲያከናውን ለማህበረሰባዊ እና አካባቢያዊ ጉዳዮች ትኩረት እንደሚሰጥ የተናገሩት ዳይሬክተሩ ጥናቱ በፕሮጀክቶች ላይ ለሚነሱ ችግሮች ቀድሞ መፍትሔ ለመስጠት በሚሰራው ሥራ ላይ የተቋሙን አቅም ለማጠናከር እንደሚያግዝ ገልፀዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በአካባቢያዊና-ማህበረሰባዊ-እንዲሁም-በ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም

የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታው የሲቪል ሥራ ከ85 በመቶ በላይ ደርሷል ……..///…….. የገንደአርባ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታን በተያዘለት የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ እየተሰራ
+7
የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታው የሲቪል ሥራ ከ85 በመቶ በላይ ደርሷል ……..///…….. የገንደአርባ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታን በተያዘለት የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራዎች አስተባባሪ አስታወቁ፡፡ አስተባባሪው አቶ ገረመው ወልደ ማርያም እንደገለፁት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት ለቡልቡላ የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ አስተማማኝ ኤሌክትሪክ ለማቅረብ ያስችላል። ለኢንዱስትሪ ፓርኩ ኃይል ለማቅረብ ከአራት ዓመት በፊት ሥምምነት ቢፈረምም በወቅቱ ከውጭ ምንዛሪ እጥረት ጋር በተያያዘ ግንባታው መዘግየቱን አስታውሰዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የማከፋፈያ-ጣቢያ-ግንባታው-የሲቪል-ሥራ-ከ85&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋማዊ ለውጡን በብቃት መምራት የሚችል አመራር ለመፍጠር እየተሰራ ነው …….///…… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተጀመረውን ተቋማዊ ለውጥ በአግባቡ መምራት የሚችል የሥራ መሪ ለመፍጠር እየተሰራ መ
+3
ተቋማዊ ለውጡን በብቃት መምራት የሚችል አመራር ለመፍጠር እየተሰራ ነው …….///…… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተጀመረውን ተቋማዊ ለውጥ በአግባቡ መምራት የሚችል የሥራ መሪ ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን የኢትዮ ፓወር አካዳሚ የአመራር ልማት ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ተናኘ መኮንን ገለጹ። ሥራ አስኪያጇ እንደተናገሩት ተቋማዊ ለውጡን በአግባቡ ተረድቶ መምራት የሚችል አመራር ለመፍጠር የለውጥ ምንነትንና ተያያዥ ጉዳዮችን ማዕከል ያደረጉ ተከታታይ ስልጠናዎች እየተሰጡ ይገኛሉ። ቀደም ሲል በ14 ዙሮች በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ስልጠና መሰጠቱን ያስታወሱት ወ/ሮ ተናኘ ዛሬን ጨምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ተመሳሳይ የአቅም ግንባታ ሥልጠና መጀመሩን አስታውቀዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋማዊ-ለውጡን-በብቃት-መምራት-የሚችል-አ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 21 ቀን 2018 ዓ.ም

ፕሮጀክቱን ወደ ኦፕሬሽን በማስገባት ሀገራዊ የኃይል ስብጥርን ማስፋት እንደሚገባ ተገለፀ ……..///…….. የአሉቶ ላንጋኖ የእንፋሎት ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን በማጠናቀቅ ለኦፕሬሽን ማብቃት እንደሚገ
+5
ፕሮጀክቱን ወደ ኦፕሬሽን በማስገባት ሀገራዊ የኃይል ስብጥርን ማስፋት እንደሚገባ ተገለፀ ……..///…….. የአሉቶ ላንጋኖ የእንፋሎት ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን በማጠናቀቅ ለኦፕሬሽን ማብቃት እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወልደኪዳን የተመራ የሥራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ቡድን በአሉቶ ላንጋኖ የእንፋሎት ጉድጓድ (Wellhead) ፕሮጀክት እና በነባሩ የአሉቶ ጂኦተርማል የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የመስክ ምልከታ አድርጓል። የመስክ ምልከታው የ5 የእንፋሎት ጉድጓድ ቁፋሮና የነባሩን ጣቢያ የመልሶ ጥገና ሂደት በመገምገም ቀጣይ የሥራ መመሪያዎችን ለማስተላለፍ ያለመ ነው። ጉብኝቱ ነባር የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ውጤታማነት እና ደህንነት ለማሳደግ ዘርፉ የጀመረው ተሃድሶ አካል መሆኑም ተገልጿል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ፕሮጀክቱን-ወደ-ኦፕሬሽን-በማስገባት-ሀገ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 21 ቀን 2018 ዓ.ም

የጉዞ አበል የአሰራር ሂደትን ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለመቀየር እየተሰራ ነው .........///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በወረቀት እየተሰራ ያለውን የጉዞ አበል የአሰራር ሂደት ወደ ዲጂ
+6
የጉዞ አበል የአሰራር ሂደትን ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለመቀየር እየተሰራ ነው .........///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በወረቀት እየተሰራ ያለውን የጉዞ አበል የአሰራር ሂደት ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለመቀየር እየተሰራ መሆኑን በተቋሙ የፋይናንስ ሥራ አስፈጻሚ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስፈጻሚው አቶ አለማየሁ መንግስቱ እንዳስታወቁት ተቋሙ የጉዞ አበልን ጨምሮ  የተለያዩ የአሰራር ሂደቶችን ዲጂታላይዝድ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል፡፡ በተቋሙ እየተተገበረ ያለውን የጉዞ አበል አሰራር ወደ ዲጂታል ሥርዓት የመቀየሩ ሥራ በሦስት ምዕራፎች ተከፋፍሎ የሚተገበር ሲሆን በመጀመሪያው ምዕራፍ በኮርፖሬት ዘርፎችና በዋና ሥራ አስፈጻሚ ስር ባሉ የሥራ ክፍሎች፣ በሁለተኛው ምዕራፍ በቢዝነስ ዘርፎች እንዲሁም በሦስተኛው ምዕራፍ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችና በሪጂኖች ላይ ተግባራዊ እንደሚደረግ አስረድተዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የጉዞ-አበል-የአሰራር-ሂደትን-ወደ-ዲጂታል&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠግኖ ከሁለት ዓመታት በኋላ ለአገልግሎት ዝግጁ ተደረገ ........///........ የበለስ-ጃዊ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ከሁለት ዓመታት በ
+4
የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠግኖ ከሁለት ዓመታት በኋላ ለአገልግሎት ዝግጁ ተደረገ ........///........ የበለስ-ጃዊ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ከሁለት ዓመታት በኋላ ተጠግኖ ዳግም ኤሌክትሪክ ለመስጠት ዝግጁ መደረጉን የሰሜን ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ። በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ በላይነህ ልጅዓለም እንዳስታወቁት ከሁለት ዓመት በፊት በበለስ ባለ 400/132/ 33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ የትራንስፎርመር ችግር ምክንያት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ከአገልግሎት ውጪ ሆኖ ቆይቷል፡፡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ለረጅም ጊዜ ከአገልግሎት ውጪ ሆኖ በመቆየቱ ምክንያትም በአማራ ክልል አዊ ብሔረሰብ ዞን ጃዊ ከተማ አካባቢ ለከፍተኛ ስርቆትና ውድመት ተዳርጎ እንደነበርም አስረድተዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-ማስተላለፊያ-መስመሩ-ተጠግኖ-ከሁ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 16 ቀን 2018 ዓ.ም

በማከፋፈያ ጣቢያው ተጨማሪ የኃይል ትራንስፎርመር ለመትከል ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል …….///…… ለድሬዳዋ ቁጥር 3 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አንድ ተጨማሪ የኃይል ትራንስፎርመር ለመትከል የቅድመ ዝግጅት
+5
በማከፋፈያ ጣቢያው ተጨማሪ የኃይል ትራንስፎርመር ለመትከል ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል …….///…… ለድሬዳዋ ቁጥር 3 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አንድ ተጨማሪ የኃይል ትራንስፎርመር ለመትከል የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጠናቀቃቸውን የምስራቅ አንድ ሪጅን ገለፀ። የሪጅኑ ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ቴዎድሮስ በየነ እንዳስታወቁት በምስራቅ ኢትዮጵያ ያለውን ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ለማርካት ተጨማሪ የኃይል ትራንስፎርመር ለመትከል የሚያስችሉ ሥራዎች ተከናውነዋል። 125 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለውን የኃይል ትራንስፎርመር የማጓጓዝ ሥራ በቅርቡ እንደሚጀመር የገለፁት አቶ ቴዎድሮስ የተከላ ሥራው በሪጅኑ ባለሙያዎች በራስ አቅም እንደሚከናወን ተናግረዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በማከፋፈያ-ጣቢያው-ተጨማሪ-የኃይል-ትራን&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 15 ቀን 2018 ዓ.ም