ar
Feedback
🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

الذهاب إلى القناة على Telegram

ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ የቀረቡ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክቶች የሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ከመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100

إظهار المزيد
2 212
المشتركون
-124 ساعات
-67 أيام
-3230 أيام
أرشيف المشاركات
🍂 ቁርአን የልብ ብርሃን! ⌚️ የ 60 ደቂቃ ሙሀደራ 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/97 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

إرشاد طالب العلم إلى طريق فتح باب العلم والفهم نظم الشيخ محمد آدم الإتيوبي الولوي @nesihastudio

‌‎#وفاة_الشيخ_محمد_علي_آدم انتقل الى رحمة الله الشيخ العالم المحدث صاحب المؤلفات الغفيرة محمد بن علي بن آدم الإثيوبي المدرس بدار الحديث الخيرية والمسجد الحرام إنا لله وإنا إليه راجعون احسن الله عزاءكم يا طلاب العلم

انقضى الليلُ وآنَ الفرَجُ! @abujunaidposts

"ሱና የኑሕ መርከብ ናት፤ የተሳፈረባት ይድናል፤ ወደኃላ የቀረ ይሰጥማል" ኢማሙ ማሊክ @abujunaidposts
"ሱና የኑሕ መርከብ ናት፤ የተሳፈረባት ይድናል፤ ወደኃላ የቀረ ይሰጥማል" ኢማሙ ማሊክ @abujunaidposts

🔖 የእምነት ፈተና እና የኢማሙ አሕመድ ፅናት 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⌚️ 38:12 ደቂቃ 🍂 የአህሉሱና ኢማም አህመድ ኢብኑ ሀንበል በንጉሶች በታገዙ ጀህሚያዎች የደረሰባቸውን ከባድ ግፍና ፈተና ካለፉበት ፅናት የሚወሰዱ ትምህርቶች https://t.me/abujunaidposts/92 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🍂||• #تلاوات_تعجبني •||🍂 📖 [ أَفَمَن یَعۡلَمُ أَنَّمَاۤ أُنزِلَ إِلَیۡكَ مِن رَّبِّكَ ٱلۡحَقُّ كَمَنۡ هُوَ أَعۡمَىٰۤۚ إِنَّمَا یَتَذَكَّرُ أُو۟لُوا۟ ٱلۡأَلۡبَـٰبِ] الرعد ١٩ تلاوة متميزة جدا للشيخ محمد عابد من قيام ١٤١٠هے في المسجد النبوي #ሸይኽ_ሙሐመድ_ዓቢድ https://t.me/abujunaidposts/91

ብቀላ ወይስ ምህረት (ዓፍው ማለት)? ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ ኢስላም ስንሰጥም ሆነ ስንነሳ ለአላህ ብቻ እንዲሆን ይፈልግብናል። ይህ ስሜትን ማስደሰትን መሰረት ያደረገ ሳይሆን አላህን መታዘዝን ብቻ አላማ ያደረገ ነው። መልካም ለዋለልን መልካምን መዋል ልንመጻደቅበት የሚገባን ነገር ሳይሆን እርሱ በኛ ላይ ያለው ሀቅ ነዉና ተገቢ ነው። መልካም ለማይዉል ሰው መልካም መዋል ግን ከባድ ጀግንነት ይጠይቃል። እራሱን አሸንፎ ለበደለው ይቅር የሚል ሰው በዱንያም ይሁን በአኼራ አላህ ደረጃውን ከፍ ያደርገዋል፤ ስሜቱንና ቁጭቱን አሸንፏል እና ድልን ያቀዳጀዋል። ሙስሊም ከአቡ ሁረይራ በዘገቡት ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ፤ [አንድ ባሪያ ይቅር በማለቱ አላህ አሸናፊነትን እንጂ አይጨምርለትም] ብለዋል። የዚህ ፅሁፍ አላማ ይቅርታ ማድረግን ማበረታራት ሲሆን ተያያዥ ጉዳዮችንም እንቃኝ ዘንዳ ተከታዮቹን አምስት ነጥቦች አቀርባለው። አላህ ሰውን ከመበደልም ይሁን በደለኛን ለማገዝ ይጠብቀን ዘንዳ እማለነዋለው። 1ኛ) ሸሪዓዊ መረጃዎችን ስናጤን በብዛኛው ይቅር ባይነትን የሚያበረታቱ ሆነው እናገኛቸዋለን። ስለዚህም ኡለማዎች በቀልን ከማይወደዱ ባህሪያት ይመድቡታል። ሆኖም ፍትህ በሸሪዓ ልዩ ቦታ ስላለው ተበዳይ ሀቁን ማስመለሱ ብሎም የደረሰበትን በደል መበቀሉ እንደ መብት ከብዙ ገደቦች ጋር የተፈቀደ ሆኖ እናገኘዋለን። ነገር ግን በቁርዓን ዉስጥ ባብዘኛው በደል ሲነሳ ከትዕግስት እና ይቅር ባይነት ጋር ተቆራኝቶ ነው። አላህ እንዲህ ይላል፤ وَجَزَاء سَيِّئَةٍ سَيِّئَةٌ مِّثْلُهَا فَمَنْ عَفَا وَأَصْلَحَ فَأَجْرُهُ عَلَى اللَّهِ إِنَّهُ لا يُحِبُّ الظَّالِمِينَ (የመጥፎም ነገር ዋጋ የእርሷ ብጤ መጥፎ ናት፤ ይቅርም ያለና ያሳመረ ሰው ‘ይቅር የማለቱ’ ምንዳው አላህ ዘንድ ነው። እርሱ በደለኞችን አይወድም) ሹራ 40 ወሰን ሳያልፉ መበቀል እጅግ አስቸጋሪና ጠንቃቃነትን የሚሻ በመሆኑ ብዙዉን ጊዜ አይሳካም። ብዙ ግዜ ተበዳይ መልሶ በዳይ ይሆናል። አላህ በዚህ አንቀፅ መታገስን ካበረታታ በኋላ ‘እርሱ በደለኞችን አይወድም’ በሚል ደምድሞታል። በቀልን የተመለከተው ፍቃድ፤ በግለሰቦች መካከል የሚከሰቱ ጠቦች፣ መጎዳዳቶች እና ድንበር ማለፎችን ብቻ የሚመለከት ነው። አንዳንዱ ጉዳይ ግን ለፍትህ መቅረብ አለበት እንጂ በግለሰብ ደረጃ ቢፈፀም ወንጀል ነው!! 2ኛ) በደልን በከፋ በደል መመለስ ፍጹም የተከለከለ ነው። አላህ ይህንን ገደብ ከጠቆመን በኋላ ትዕግስት ተላብሰን ከበቀል ብንቆጠብ የተሻለ መሆኑን አብራርቷል። وَإِنْ عَاقَبْتُمْ فَعَاقِبُواْ بِمِثْلِ مَا عُوقِبْتُم بِهِ وَلَئِن صَبَرْتُمْ لَهُوَ خَيْرٌ لِّلصَّابِرينَ (ብትበቀሉም፣ በርሱ በተቀጣችሁበት ብጤ ተበቀሉ፤ ብትታገሡም፣ እርሱ ለታጋሾች በእርግጥ በላጭ ነው) አል–ነህል 126 በተመሳሳይ አንቀፅ በደልን በከፋ በደል ከመመለስ እንድንቆጠብ ይመክረናል። ዙልም ከመፈፀም እርሱን ልንፈራ እንደሚገባ ያስጠነቅቀናል። 3ኛ) የተበደለ ሰው በተገደበ ሁኔታ እንዲበቀል መፈቃዱ ወንጀልን በወንጀል መበቀልን አያካትትም። فَمَنِ اعْتَدَى عَلَيْكُمْ فَاعْتَدُوْا عَلَيْهِ بِمِثْلِ مَا اعْتَدَى عَلَيْكُمْ وَاتَّقُوا اللهَ وَاعْلَمُوْا أن الله مع المتقين (በእናንተም ላይ ወሰን ያለፈባችሁን ሰው በናንተ ላይ ወሰን ባለፈው ብጤ (ልክ) በርሱ ላይ ወሰን እለፉበት፡፡ አላህንም ፍሩ አላህ ከሚፈሩት ጋር መኾኑንም ዕወቁ) አል በቀራህ 194 ‘ወሰን ባለፈው ብጤ (ልክ) በርሱ ላይ ወሰን እለፉበት’ የሚለው መልእክት፤ በቀል ቀጥተኛ ወንጀል መፈፀምን እንደማይመለከት ግልፅ ነው። ለምሳሌ፤ ከቤተሰባችን የሰረቀውን ከቤተሰቡ በመስረቅ፤ የእኛን የቤተሰብ አባል ወንጀል ያሰራን ቤተሰቡን ወንጀል በማሰራት መበቀል ፍፁም ክልክል ነው። ስለዚህም በአንቀፁ መቋጫ ላይ (ይቅርም ያለና ያሳመረ ሰው "ይቅር የማለቱ" ምንዳው አላህ ዘንድ ነው) በዳይን ሰው ይቅር ማለት ከመበቀል የተሻለ መሆኑን ተናግሮአል። ጠንካራነት እና ጀግንነት የሚለካዉም መጉዳት እየቻሉ ለአላህ ሲሉ በመተውና ይቅርታ ማድረግ ላይ ነዉና አላህ እጅግ ከባድ ምንዳን አዘጋጅቶለታል። 4ኛ) ከበቀል ምህረት የሚቀደመው መልካም ሆኖ ሲገኝ ብቻ ነው። ድንበር ማለፉ የተከሰተው በአላህ ሀቅ ላይ ከሆነ ወንጀል እንዲፈጸም መፍቀድን ይቅር ባይነት አድርጎ መቁጠር አላዋቂነት ነው። ለምሳሌ፤ ጾታዊ ጥቃቶች የሚደርስባት ሴት ይቀርታ ይሻላል በማለት ጥፋትን ከሸፈነችና እንዲደጋም መንገድ ከከፈተች የወንጀሉ ተካፋይ ትሆናለች እንጂ ይቅርታዋ ትክክል አይሆንም። ነገር ግን የአላህ ክልከላ መጣስ ሳይሆን ግላዊ በደል ከሆነ ይቅር ማለት ተገቢና የተሻለ ነው። ቡኻሪና ሙስሊም በዘገቡት ሀዲስ እናታችን አዒሻ እንዲህ ብለዋል፤ (የአላህ መልዕክተኛ ለራሳቸው ሲሉ መቼም ቢሆን ተበቅለው አያውቁም...) 5ኛ) አላህ በደል እና ብቀላን አስመልክቶ በሱረቱል ሹራ ከ39–42 ድረስ ያብራራበትን ሂደት ስንመለከት፤ የብቀላን ገደቦች ከመግለፁ በፊት 39ኛው አንቀጽ ላይ አፀፋ የመመለስን መብት መግለጹ በቀልን የሚያበረታታ አይደለም። ምክኒያቱም፤ በቀጣዩ አንቀጽ የሚተገብሩትን መንገድ በልክ እንዲሆን ያዘዘ ሲሆን የተሻለዉና በላጩ ምህረት ማድረግ መሆኑንም አፅንቷል። አል ኢማም አልቁርጡቢ ሲያብራሩ፤ እንዲህ ብለዋል፤ አላህ ምዕመናንን ሁለት አይነት አድርጓቸዋል፦ ከፊሎቹ በደልን ይቅር የሚሉ ሲሆኑ ከአንቀጹ ቀደም ብሎ 37ኛው አንቀጽ ላይ (በተቆጡም ጊዜ እነሱ የሚምሩ ለሆኑት) በማለት እነሱን አውስቶ ጉዳዩን ጀምሮታል። ከፊሎቹ ደግሞ በደልን የሚበቀሉ ናቸውና አስከትሎ የበቀልን ገደብ ገለጸ። ወሰን ማለፍ እንደማይገባም ተናገረ” አልጃሚዕ ሊአህካሚል ቁርዓን ኢብኑ ረጀብ እንዲህ ብለዋል፤ “አላህ (ለነዚያም በደል በደረሰባቸው ጊዜ እነሱ በሲረቱ ሹራ 39 ላይ "ተመሳሳይ አፀፋን" የሚመልሱ ለሆኑት) የሚለው አንቀፅ ይቅርታ ከማድረግ ጋር የሚጋጭ አይደለም። በቅድሚያ መበቀል እንደሚችሉ አሳይተው ይቅርታ ማድረግን ማስከተላቸው የተሟላና የተሻለ ያደርገዋል” ጃሚዑል ዑሉም ወልሂከም 1/450 ብዙዎች ዘንድ ትዕግስት እና ይቅር ባይነት እንደ ድክመት፤ ብቀላ ደግሞ እንደ ጀግንነት ይታያል። ይህ ስህተት ነው። ይቅር ባይነት ከአላህ ከፍተኛ ምንዳን የሚያስገኝ መልካም ባህሪ ነው። በብቀላ ቁጭትን ለመወጣት ሲባል ድንበርን በማለፍ ጸጸት ዉስጥ ከመዉደቅ ከአላህ የሚገኘውን ምንዳ በማሰብ በቀልን መራቅ ብልህነት ነው። ቁጭቱን በመዋጥ ይቅርታ ለሚያደርግ ሰው አላህ ታላላቅ ሽልማቶችን ቃል በመግባት እንዲህ ብሏል፤ وَالْكَاظِمِينَ الْغَيْظَ وَالْعَافِينَ عَنِ النَّاسِ وَاللَّهُ يُحِبُّ الْمُحْسِنِينَ [ለነዚያ፤ በድሎትም ኾነ በችግር ለሚለግሱት፥ ቁጭትንም ገቺዎች፥ ከሰዎችም ይቅርታ አድራጊዎች ለሆኑት (ጀነት ተደግሳለች)፤ አላህም በጐ ሠሪዎችን ይወዳል] አል ዒምራን 134 አላህ ሆይ! ከበደል አርቀን። ከነብሳችን እና ከሸይጣን ክፋት አንተው ጠብቀን! አቡጁነይድ መስከረም 18/2006 ከጥቂት ማሻሻያዎች ጋር t.me/abujunaidposts

🔖 ዓቂዳ እና መንሐጅ... ዘጠኝ ወሳኝ ነጥቦች 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ 📌 ትኩረት የሚሹ 9 የአቂዳና የመንሐጅ ጉዳዮችን ይዳስሳል https://t.me/abujunaidposts/88

🍂||• ጣፋጭ ቲላዋ •||🍂 ቃሪእ ኢብራሂም ዓሲሪ 📖 [የአደም ልጆች ሆይ! ሰይጣንን አትገዙ፤ እርሱ ለእናንተ ግልጽ ጠላት ነውና በማለት ወደእናንተ አላዘዝኩምን? ] ያሲን 60 #تلاوات_لا_أنساها @abujunaidposts

🔖 የሰለፎች ልገሳና አርአያነቱ 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🍂 የሰደቃ ታላቅነትና የሰለፎች ገድል ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🔖 የኑህ መርከብ 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ የቢድዓን አደጋዎች በመግለፅ ለቢድአ አራማጆች ማደናገሪያዎች ምላሽ የሚሰጥ ትምህርት http://nesiha.com/wp-content/uploads/2018/05/የኑህ-መርከብ.mp3 @abujunaidposts

ከሶስቱ መስጂዶች ውጭ መንፈሳዊ ጉዞዎችን ማድረግ በሸሪዓ ይፈቀዳልን? ክፍል 2/2 (ማደናገሪያዎች እና ምላሾቻቸው) ባለፈው ክፍል ከሶስቱ መስጂዶች ውጭ የሚደረጉ (መንፈሳዊ) ጉዞዎችን ክልክልነት የሚገልፀውን ሀዲስ እና ተያያዠ መረጃዎችን ቃኝተናል። በዚህ ክፍል ደግሞ በተቃራኒ ወገኖች ለሚቀርቡ ማደናገሪያዎች ምላሽ አቀርባለው። 1) እነዚህን ጉዞዎች በቀብር ዚያራ በማስታከክ ህጋዊነትን ለማላበስ፤ ‹‹ቀብርን መጐብኘት ከልክያችሁ ነበር አሁን ግን ጐብኙ›› የሚለውን የነብያችን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሐዲስ ይጠቅሳሉ።  ምላሽ:–  ነብያችን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ቀብር ዘይረዋል፣ ዘይሩ ብለውም አዘዋል። የዚያራው ዋነኛ አላማ አኼራን ማስታወስ እንደሆነም ተናግረዋል። እሳቸውም ሆኑ ሶሐቦቻቸው ቀብር ለመዘየር ብለው ጉዞ አልወጡም ሌሎች እንዲጓዙም አልፈቀዱም። በመመርመር ላይ ያለነው ግን በአካባቢያችን የሚገኙ ቀብሮችን ስለመዘየር ሳይሆን በቀብር ዚያራ አላማ ከሚኖሩበት ከተማ ወይም ሀገር ወደ ሌላ ቦታ ጉዞ ማድረግን ነው። ቀብር ዚያራ ለማድረግ የሚፈልግ በአካባቢው ወደሚገኝ መቃብር መሄድ እንጂ ጉዞ በሚያስወጣ ርቀት የሚገኝ ቀብርን ለመዘየር ጓዝ አስሮ መነሳት ክልክል መሆኑ ያሳለፍነው ሐዲስ ግልፅ መረጃ ነው። 2) ነቢዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) የኡሁድ ሸሂዶችን ቀብር ለመዘየር መውጣታቸውን እንደማስረጃ በመጥቀስ ጉዞ ወጥቶ ቀብር ዚያራ እንደሚቻል የሚሞግቱም አሉ።   ምላሽ፦ ኡሁድ ባሁኑ የከተማው ሁኔታ በመዲና ከተማ ለነብዩ መስጂድ ቅርብ ከሚባሉ ቦታዎች አንዱ ሲሆን ቀድሞ በነበረው የከተማዋ ሁኔታም ቢሆን እንደ ሌላ ከተማ የሚታይና ጉዞ የሚባል ርቀት ላይ የሚገኝ አለመሆኑ ግልፅ ነው። 3)  ነቢዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) የእናታቸውን ቀብር መዘየራቸውን በመጥቀስ ለቀብር ዚያራ ሲባል ርቀት ጉዞ መሄድ እንደሚቻል ይሞግታሉ።  ምላሽ፦ ነቢዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) የእናታቸውን ቀብር የዘየሩት መካን ለመክፈት በተጓዙት ዘመቻ ላይ እግረ መንገዳቸውን እንጂ በዚያራ አላማ ስንቅ ሰንቀውና ጓዝ ሸክፈው ተጉዘው አልነበረም። 4)  አንዳንዶች አቡ ሑረይራ ከልካይ ሀዲሶችን ከማወቃቸው ጋር ጡር ወደተባለው ተራራ መሄዳቸው እንደሚፈቀድ ያሳይል ይላሉ። ምላሽ፦ ሀቅን ለመደበቅ ሆን ብለው ካልሞከሩ በቀር፤ አል ኢማም ማሊክ እና አስሀቡሱነን በዘገቡት እና ይህ ክስተት በተወሳበት ሀዲስ ላይ አቡሁረይራ ከጉዞ ሲመለሱ ያገኛቸው አቡ በስራ አልጊፋሪይ ከሶስቱ መስጂዶች ውጭ ወደ ሌላ ስፍራ ለኢባዳ ጉዞ ማድረግ እንደማይፈቀድ መረጃ በመጥቀስ፤ "ከመሄድህ በፊት ባገኝህ ኖሮ (ጉዞ) አትወጣም ነበር] ብለው ስራቸው ተገቢ እንዳልነበረ አስታውሰዋቸዋል። አቡሁረይራም ተቀበሉ እንጂ አልሞገቱም!! 5)  የሀዲሱ ክልከላ የሚመለከተው ወደ መስጂዶች የሚደረግን ጉዞ እንጂ ቀብሮች እና የዚያራ ቦታዎችን አይመለከትም ይላሉ። ምላሽ፦ የሀዲሱ ክልከላ መስጂዶች ቢልም ከላይ የተጠቀሰው ሀዲስ፤ የነብያት እና ሷሊሆች ቀብር እንዲሁም ታዋቂ እና ታሪካዊ ቦታዎችንም ክልከላው እንደሚመለከት የአቡ በስራ ግንዛቤ እና የአቡሁረይራ መስማማት ግልፅ መረጃ ነው።  ኢብኑ ተይሚያህ ረሂመሁላህ እንዲህ ብለዋል፤ “ይህ ክልከላ ወደ መስጂዶችም ሆነ ወደ አላህ ለመቃረብ በሚፈፀም ማንኛውም ጉዞ ግብ የሚደረጉ ቦታዎችን ይመለከታል።” ካሉ በኃላ  በአቡ በስራ እና በአቡ ሁረይራ መካከል የተከሰተውን ክስተት ጠቅሰው እንዲህ አሉ። “ጡር እና መሰል አንቢያዎችን ያስተናገዱ ቦታዎች በዚህ ሀዲስ ክልከላ ውስጥ እንደሚገቡ ሀዲሱን ያስተላለፈው ይህ ሰሐቢይ ተገንዝቧል… ይህ ታሪካዊ ቦታዎችን ከተመለከተ የአምልኮ ቤቶችም በዋናነት ክልከላው ይመለከታቸዋል።” ኢቅቲዷኡ ሲራጥ ቅፅ 2 ገፅ 645 6)  በሀዲሱ ላይ በተፈቀደው መሰረት የነብዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) መስጂድ ስንሄድ ከጎን የሚገኘው ቀብራቸው ጋር ሄደን እንዘይራለን። ይህ ቀብሮችን ለመዘየር በማሰብ መጓዝ እንደሚቻል መረጃ ነው በማለትም ይሞግታሉ።  ምላሽ፦ የነብዩን መስጂድ ለመዘየር የሄደ ሰው በዛው ወደ ነቢዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ቀብር ሄዶ መዘየር ይችላል። ሆኖም የሳቸው ንግግር እንደሚያመለክተው ጉዞ ማድረግ ያለብን ወደ ሶስቱ መስጆዶች ብቻ ነው። በጉዞዬ ቀብራቸውን መዘየር እንጂ መስጂዳቸውን  መዘየርን አላማ አላደረኩም በማለት መጓዝ  የሳቸውን ክልከላ መጣስ ነው። በዚሁ አጋጣሚ ልብ ልንል የሚገባው፤ ቀብርን መዘየር ሙስተሐብ ሲሆን የሳቸውን ቀብር መዘየር ደግሞ ታላቅ መልካም ነገር ነው።  የርሳቸውም ቀብር ከዚህ እንደሚካተት ግልጽ ነው፡፡ ሆኖም ከእርሳቸው ቀብር ጋር ተያይዘው የሚነገሩት ሐዲሶች ዶኢፍ ወይም ጭራሹኑ የተቀጠፉ መውዱእ ናቸው። በመጨረሻም፤ ይህ ድንጋጌ አላማው ተውሒድን ከሰርጎ ገብ አመለካከት መጠበቅ ነው። ጉዞ የሚደረግባቸውን ብዙ ቀብሮች ብንመለከት ከጉብኝት እና ጉዞ ጋር በተያያዘ ብዙ የአቂዳ ግድፈቶችን እናስተውላለን። ለዚህም ውቅሮ ከሚገኘው የነጃሺ ቀብር በምሳሌነት መመልከት ይቻላል። በቀብሮች ላይ መስጊድን መገንባት ፍፁም የተከለከለ መሆኑ ግልፅ ነው። ምንም እንኳ ታላቁን ነጃሺ ቢን አስሀማ (ረሂመሁላህ) የምናከብርና የምንወድ ብንሆንም ከሱ ፍቃድና ፍላጎት ውጪ እነዚህ ነቢያዊ ትእዛዛትን በመጣስ በቀብሩ ላይ የሚደረጉት ክልክል ተግባራት ሁሉ እናወግዛለን። ነጃሺን በምሳሌነት ጠቀስን እንጂ በየአካባቢው ይህ አይነቱ ፈተና ይገኛል። በብዙ መሰል ቦታዎች አላዋቂዎች ወደ ቀብር ሄደው ስለት በማስገባት ከጭንቅ እንዲያወጣቸው እና ሀጃቸውን እንዲያወጣላቸው ይለምናሉ። ወደ አላህ ብቻ ሊዘረጉት የሚገባውን እጃቸውን በማንሳት የሚፈልጉት ሁሉ እንዲሰጧቸው ሙታንን ይማፀናሉ። ይህ ግልፅ የጃሂሊያ ተግባር ወደሚፈፀምበት ቦታ የጉዞ ጥሪ ማስተጋባት ፍፁም ስህተት ነው። ቅርስን ለመንከባከብም ይሁን ለሌላ ምክንያት ወደ ቀብሮች የሚደረግ ጉዞ መጤ ተግባር ላይ መሳተፍ ከመሆኑም በላይ፤ የነብዩን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ግልፅ ክልከላ መጣስ ነው። ከከባድ ወንጀል አንስቶ እስከ ቢድዓ እና ሺርክ የሚያደርሱ ጥፋቶችን ሊያስከትል እንደሚችል አውቀናልና መልእክቱን ሁሉም ሊያስተጋባውና ሙስሊሙን ሊያነቃ ይገባል። አላህ ከጅህልና ይጠብቀን! አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ t.me/abujunaidposts

ከሶስቱ መስጂዶች ውጭ መንፈሳዊ ጉዞዎችን ማድረግ በሸሪዓ ይፈቀዳልን? ክፍል 1/2 በሀገራችን እና በብዙ ሀገራት በሚኖሩ የሌላ እምነት ተከታዮች ዘንድ ከተለመዱ ተግባራት አንዱ መንፈሳዊ ጉዞ ነው።  ይህ አይነቱ ጉዞ ሰዎች  ቅዱስነቱን ወደሚያምኑበት ስፍራ ወይም ቅዱሳን መሆናቸው የሚታመንባቸው ሰዎች ወደተቀበሩበት ቦታ የሚደረግ ሲሆን፤  ከየሄዱበት ስፍራ በረከትንና ፈውስን የመሳሰሉ ጥቅሞችን ይከጅላሉ። መነሻው በጥቂት አስተባባሪዎች እና ተሳታፊዎች ቅንጅት ይከወን የነበረ ቢሆንም ቀስ በቀስ ነጋዴዎች ስርአት እያስያዙትና የጉዞ ማህበራት በማቋቋም እያደራጁት ሄደዋል። ይህንን ተሞክሮ ወደ ሙስሊሙ በማምጣት የታላላቅ ሰዎችን ቅዱስነት እና ወልይነት አጉልቶ መስበክ፣ ወደቀብራቸውም ጉዞ ማድረግ፣ የተለያዪ ፕሮግራሞችን በቀብራቸው ዙርያ ማዘጋጀት በተደራጀ መልኩ ቀጥሏል።  ከዚህ ቀደም ባልተደራጀ መልኩ ጉዞዎችን የሚያስተናግዱ እንደ ነጃሺ፣ አናጂና፣ አብሬት፣ ቃጥባሬ እና መሰል ቦታዎች አሁን አሁን ሌሎች ጋር የተለመደውን የጉዞ አደረጃጀት በመከተል መጠናከረቸውን የሚያሳዩ ማስታወቂያዎችና እና እንቅስቃሴዎች በመስጂዶቻችን ላይ በስፋት እየታዩ ነው። ባእድ አምልኮ የሚፈፀምባቸውን የቀብር ስፍራዎች፤ ቅርስን በመንከባከብ እና ባህላዊ እሴቶች በመጠበቅ ስም ለማነፅ በከፍተኛ በጀት የሚበጅቱት የአንዳንድ ሀገራት ኤምባሲዎች አላማ ከህዝበ ሙስሊሙ የተደበቀ አይደለም። በሌሎች እምነቶች ተፅእኖ ስር የወደቁትን የሱፊያ አስተሳሰብ መስመሮች ለሙስሊሙ ህብረተሰቡ በማስተዋወቅ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች መገለጫ አድርገው በማቅረብ ሙስሊሙን እኛ እናውቅልሀለን የሚሉት ወገኖች አላማም አጠያያቂ ነው። ይህ አይነቱ ጉዞ በሸሪአ እንዴት ይታያል የሚለውን ለመቃኘት እንሞክራለን፤ 1)  ነቢያችን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) {ወደ ሶስት ቦታዎች ካልሆነ ጓዝን ጠቅልሎ ጉዞ አይወጣም፤ መስጅድ አልሐረም (መካ) መስጂድ አነበዊ (መዲና) እና መስጂድ አልዓቅሷ} ማለታቸው በሰሒሕ ቡኻሪ እና ሌሎችም ድርሳናት ተዘግቧል ይህ ሐዲስ እንደሚጠቁመው አምልኮትን ፍለጋ አንድን ቦታ በማላቅ የሚደረግ ጉዞ ወደ ሶስቱ መስጅዶች ካልሆነ ወደ ሌላ ቦታ መሄድን ይከለክላል። ይኸውም ሰዎች አንድን ቦታ በተለየ ቀድሰው በቦታው የሚገኝን ቀብር ወይም ሌላ ነገር በማላቅ ወደ ማምለክ(ሽርክ) እንዳይገቡና ከዲናቸው እንዳይወጡ ለመጠበቅ ሲባል ነው። ከዚህም በመነሳት፤  አንድን ቦታ በማላቅ ወይም ከሌሎች ቦታዎች ይልቅ አምልኮት ተቀባይነት ያገኙበታል በሚል ግምት፤ ከሶስቱ መስጅዶች ውጭ መንፈሳዊ ጉዞ ማድረግ ሀራም ነው። ይህ አላህን በሰላት ዱአ እና መሰል ኢባዳዎች ለማምለክ ከሆነ ነው። ስለት በማስገባት፣ ድረሱልን ወይም አማልዱኝ በማለት  ቅዱሳንን መማፀን ከሆነ ግን ባእድ አምልኮ ነውና  በእጅጉ ከዚህ የከበደ የሽርክ ተግባር ነው።  2) በአምልኮት ተግባራቸው እና ሌሎች  በሚለዩባቸው ባህልና ልማዶች አርአያ አድርጎ መመሳሰል ብሎም መከተል የማይፈቀድ ክልክል ተግባር ነው። ነብያችን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) በአንድ ሐዲስ ... [ከናንተ በፊት የነበሩትን ፈለግ ስንዝር በስንዝር፣ ክንድ በክንድ ትከተላላችሁ፤ የአርጃኖ ጉድጓድ ቢገቡ እንኳ ትከተሏቸዋላችሁ] አሉ፤ ይህን የሚሰሙት ሶሐቦችም "የአላህ መልእክተኛ ሆይ የየሁዳና ነሳራዎችን (ፈለግ ማለት ነው) ?] ብለው ሲጠይቋቸው እሳቸውም ]ታዲያስ?] ብለው መለሱላቸው። ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል፡፡  የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል፤ [ከህዝቦች የተመሳሰለ እርሱ ከነርሱ ነው] አቡ ዳውድ ዘግበውታል   ቅዱሳንን በማላቅ አላማ የሚካሄዱ ጉዞዎች የሌሎችን  የአምልኮ ተግባራት በመኮረጅ ኢስላማዊ ቅብ መቀባት በመሆኑ መመሳሰል (ተሸቡህ) ነውና አይፈቀድም። በዲናችን አንድን ቦታ በማላቅ ወይም ከፍ በማድረግ ወደዛ ስፍራ ሄዶ አምልኮትን መፈፀም የሚፈቀደው ወደ ሶስቱ መስጅዶች ብቻ ነው። 3) ሸሪዓችን ከተደነገጉት ሶስቱ መስጂዶች ውጭ አንድን ቦታ በማላቅ ወይም አንዳች ጥቅም በመፈለግ የሚደረግ የጀመዓ ጉዞ ነብያችንም ሆኑ ሶሐቦቻቸው በኖሩበት ጊዜ የማይታወቅ የቢድአ ተግባር ነው።  ወደ ተለያዩ ዶሪሆች እና መሳጂዶች የሚደረገው ጉዞ በእስልምናችን የማይታወቅ ነብያችን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ያላዘዙት መጤ የቢድአ ተግባር ነው። ነብያችንም (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሸሪዓችንን በሚገባ አስተምረው እሳቸው ያላዘዙትን ከመፈፀም በብርቱ አስጠንቅቀው አልፈዋል። እናታችን አዒሻ ባስተላለፉት ሐዲስ ነብያችን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል [የኛ ትእዛዝ የሌለበትን (የአምልኮ) ስራ የሰራ፤ (ስራው) ተመላሽ ነው] ሙስሊም ዘግበውታል፡፡ ስለሆነም ይህ በሸሪዓ እንዲጎበኝ ወዳልታዘዘ ቦታ በመጓዝ አጅር አገኛለሁ ብሎ መሳተፍ አላህም ሆነ መልእክተኛው ያላዘዙትን መስራት በመሆኑ አደገኛ የቢድዓ ወንጀል ነው! 4)  አላህ ዲናችንን የተሟላ እና ምንም አይነት ጭማሪም ሆነ ማሻሻያ የማይሻ የማይፈልግ ለሁሉም ዘመንና ቦታ የሚሆን ሐይማኖት አድርጎታል። መንፈሳዊ ጉዞ ታላላቅ የዲን መሪዎች በኖሩባቸው የኢስላም ቀዳሚ ዘመናት ሙስሊሞች የማያውቁት ከሌሎች የተኮረጀ እንግዳ ስራ ነው። اليَومَ أَكمَلتُ لَكُم دينَكُم وَأَتمَمتُ عَلَيكُم نِعمَتي وَرَضيتُ لَكُمُ الإِسلامَ دينًا «ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ፡፡ ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ፡፡ ለእናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ» ሱረቱ'ል-ማኢዳህ 3 በመሆኑም፤ መንፈሳዊ ጉዞ በሚል በተለያዩ መስጅዶች እየተዋወቀ ያለው ጥሪ ትኩረት አድርገን ካልተከላከልነው ለብዙ ጥፋቶች የሚያጋልጥ ነው። በሸሪአችን በግልፅ የተከለከለ በመሆኑ  ሙስሊሙ እንዲጠነቀቅ፣ ራሱንና ቤተሰቡን በዲን ስም ከሚፈፀም ጥፋት እንዲጠብቅ እናሳስባለን።  5) በብዙ አካባቢዎች፤ መቃብሮች ከአንድ ስንዝር በላይ ከፍ እንዳይሉ፣ እንዳይገነቡና እንዳይቀቡ እንዲሁም መቃብሮች መስጂድ ተደርገው እንዳይያዙ የሚከለክሉ ነብያዊ ትእዛዛትን የተቃረነ ተግባር በስፋት ይፈፀማል። ጁንዱብ ኢብኑ አብደላህ ባስተላለፉት ሐዲስ  የአላህ መልዕክተኛ (ሰለላሁ ዓለይሁ ወሰለም) ከመሞታቸው ከአምስት ቀናት በፊት እንዲህ ሲሉ ሰምቻለው ብለዋል ‹‹ከእናንተ በፊት የነበሩ ህዝቦች የነቢያቸውንና የደጋግ ባሮችን ቀብር መስገጃ ስፍራ አደረጉ፡፡ አደራ! ቀብሮችን መስገጃ እንዳታደርጉ ከልክያችኃለው››  ሙስሊም ዘግበውታል በሌላ ዘገባም ጃቢር እንዲህ ብለዋል፤ ‹‹የአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ቀብርን በጄሶ መመረግ፣ ላዩ ላይ መቀመጥ፣ ከላዩ መገንባት፣ ከአፈሩ ውጭ መጨመርና ቀብር ላይ መፃፍ ከልክለዋል››  ከላይ የተዘረዘሩት መረጃዎች በግልፅ እንደሚያሳዩት ከሶስቱ መስጂዶች ውጭ ወደ ወልዮች ሷሊሆችና ነብያት መቃብሮችም ይሁን መናገሻ ከተማዎች የሚደረጉ ጉዞዎች በሸሪዓ የተወገዙ ለሽርክ እና ባእድ አምልኮ የሚያጋልጡ መሆናቸው ግልፅ ነው። በአላህ ፈቃድ በቀጣይ ክፍል ሙስሊሙን ማህበረሰብ ለማደናገርና ወደ ቀብር አምልኮ ለመምራት በዚህ ሀዲስ ዙርያ ለሚቀርቡ ማደናገሪያዎች ምላሽ እንሰጣለን። አምልኮ ሁሉ የሚገባው ለአላህ ብቻ ነው። ስላሳወቀን የተውሂድ ብርሀን እናመሰግነዋለን። መንገድ ከመሳት በርሱ እንጠበቃለን። ወልሐምዱ ሊላሂ ረቢል ዓለሚን! T.me/abujunaidposts

📝 ለምን ወቅፍ እናደርጋለን? ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ T.me/abujunaidposts

🔖 የመንሐጅ ቅብብሎሽ... ከኸዋሪጅ እስከ ሀዳዲያ 🎙 አቡ ጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🍂 ከ 10 አመታት በፊት በጃሊያ አዳራሽ የቀረበ አጭር መልዕክት ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts