ru
Feedback
🗞 ዹ አቡጁነይድ መልዕክቶቜ Abujunaid posts

🗞 ዹ አቡጁነይድ መልዕክቶቜ Abujunaid posts

Открыть в Telegram

ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ ዚቀሚቡ ዚድምፅና ዹፅሁፍ መልዕክቶቜ ዚሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ኚመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100

БПльше
2 212
ППЎпОсчОкО
-124 часа
-67 ЎМей
-3230 ЎеМь
АрхОв пПстПв
🍂 ቁርአን ዚልብ ብርሃን! ⌚ ዹ 60 ደቂቃ ሙሀደራ 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/97 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

إر؎اد طالؚ العلم إلى طريق فتح ؚاؚ العلم والفهم ن؞م ال؎يخ محمد آدم الإتيوؚي الولوي @nesihastudio

‌‎#وفاة_ال؎يخ_محمد_علي_آدم انتقل الى رحمة الله ال؎يخ العالم المحدث صاحؚ الم؀لفات الغفيرة محمد ØšÙ† علي ØšÙ† آدم الإثيوؚي المدرس ؚدار الحديث الخيرية والمسجد الحرام إنا لله وإنا إليه راجعون احسن الله عزاءكم يا طلاؚ العلم

انقضى الليلُ وآنَ الفرَجُ! @abujunaidposts

"ሱና ዹኑሕ መርኚብ ናትፀ ዚተሳፈሚባት ይድናልፀ ወደኃላ ዹቀሹ ይሰጥማል" ኢማሙ ማሊክ @abujunaidposts
"ሱና ዹኑሕ መርኚብ ናትፀ ዚተሳፈሚባት ይድናልፀ ወደኃላ ዹቀሹ ይሰጥማል" ኢማሙ ማሊክ @abujunaidposts

🔖 ዚእምነት ፈተና እና ዚኢማሙ አሕመድ ፅናት 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⌚ 38:12 ደቂቃ 🍂 ዚአህሉሱና ኢማም አህመድ ኢብኑ ሀንበል በንጉሶቜ በታገዙ ጀህሚያዎቜ ዚደሚሰባ቞ውን ኚባድ ግፍና ፈተና ካለፉበት ፅናት ዚሚወሰዱ ትምህርቶቜ https://t.me/abujunaidposts/92 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

🍂||• #تلاوات_تعجؚني •||🍂 📖 [ أَفَمَن یَعۡلَمُ أَنَّمَاۀ أُنزِلَ إِلَیۡكَ مِن رَؚِّّكَ ٱلۡحَقُّ كَمَنۡ هُوَ أَعۡمَىٰۀۚ إِنَّمَا یَتَذَكَّرُ أُو۟لُوا۟ ٱلۡأَلَؚۡـؚِٰ] الرعد ١٩ تلاوة متميزة جدا لل؎يخ محمد عاؚد من قيام ١ـ١٠هے في المسجد النؚوي #ሞይኜ_ሙሐመድ_ዓቢድ https://t.me/abujunaidposts/91

ብቀላ ወይስ ምህሚት (ዓፍው ማለት)? ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ ኢስላም ስንሰጥም ሆነ ስንነሳ ለአላህ ብቻ እንዲሆን ይፈልግብናል። ይህ ስሜትን ማስደሰትን መሰሚት ያደሚገ ሳይሆን አላህን መታዘዝን ብቻ አላማ ያደሚገ ነው። መልካም ለዋለልን መልካምን መዋል ልንመጻደቅበት ዚሚገባን ነገር ሳይሆን እርሱ በኛ ላይ ያለው ሀቅ ነዉና ተገቢ ነው። መልካም ለማይዉል ሰው መልካም መዋል ግን ኚባድ ጀግንነት ይጠይቃል። እራሱን አሾንፎ ለበደለው ይቅር ዹሚል ሰው በዱንያም ይሁን በአኌራ አላህ ደሹጃውን ኹፍ ያደርገዋልፀ ስሜቱንና ቁጭቱን አሾንፏል እና ድልን ያቀዳጀዋል። ሙስሊም ኚአቡ ሁሚይራ በዘገቡት ሀዲስ ዹአላህ መልዕክተኛፀ [አንድ ባሪያ ይቅር በማለቱ አላህ አሞናፊነትን እንጂ አይጚምርለትም] ብለዋል። ዹዚህ ፅሁፍ አላማ ይቅርታ ማድሚግን ማበሚታራት ሲሆን ተያያዥ ጉዳዮቜንም እንቃኝ ዘንዳ ተኚታዮቹን አምስት ነጥቊቜ አቀርባለው። አላህ ሰውን ኹመበደልም ይሁን በደለኛን ለማገዝ ይጠብቀን ዘንዳ እማለነዋለው። 1ኛ) ሞሪዓዊ መሚጃዎቜን ስናጀን በብዛኛው ይቅር ባይነትን ዚሚያበሚታቱ ሆነው እናገኛ቞ዋለን። ስለዚህም ኡለማዎቜ በቀልን ኚማይወደዱ ባህሪያት ይመድቡታል። ሆኖም ፍትህ በሞሪዓ ልዩ ቊታ ስላለው ተበዳይ ሀቁን ማስመለሱ ብሎም ዚደሚሰበትን በደል መበቀሉ እንደ መብት ኚብዙ ገደቊቜ ጋር ዹተፈቀደ ሆኖ እናገኘዋለን። ነገር ግን በቁርዓን ዉስጥ ባብዘኛው በደል ሲነሳ ኚትዕግስት እና ይቅር ባይነት ጋር ተቆራኝቶ ነው። አላህ እንዲህ ይላልፀ وَجَزَاء سَيِّ؊َةٍ سَيِّ؊َةٌ مِّثْلُهَا فَمَنْ عَفَا وَأَصْلَحَ فَأَجْرُهُ عَلَى اللَّهِ إِنَّهُ لا يُحُِؚّ ال؞َّالِمِينَ (ዚመጥፎም ነገር ዋጋ ዚእርሷ ብጀ መጥፎ ናትፀ ይቅርም ያለና ያሳመሚ ሰው ‘ይቅር ዚማለቱ’ ምንዳው አላህ ዘንድ ነው። እርሱ በደለኞቜን አይወድም) ሹራ 40 ወሰን ሳያልፉ መበቀል እጅግ አስ቞ጋሪና ጠንቃቃነትን ዚሚሻ በመሆኑ ብዙዉን ጊዜ አይሳካም። ብዙ ግዜ ተበዳይ መልሶ በዳይ ይሆናል። አላህ በዚህ አንቀፅ መታገስን ካበሚታታ በኋላ ‘እርሱ በደለኞቜን አይወድም’ በሚል ደምድሞታል። በቀልን ዹተመለኹተው ፍቃድፀ በግለሰቊቜ መካኚል ዚሚኚሰቱ ጠቊቜ፣ መጎዳዳቶቜ እና ድንበር ማለፎቜን ብቻ ዚሚመለኚት ነው። አንዳንዱ ጉዳይ ግን ለፍትህ መቅሚብ አለበት እንጂ በግለሰብ ደሹጃ ቢፈፀም ወንጀል ነው!! 2ኛ) በደልን በኹፋ በደል መመለስ ፍጹም ዹተኹለኹለ ነው። አላህ ይህንን ገደብ ኹጠቆመን በኋላ ትዕግስት ተላብሰን ኹበቀል ብንቆጠብ ዚተሻለ መሆኑን አብራርቷል። وَإِنْ عَاقَؚْتُمْ فَعَاقُِؚواْ ؚِمِثْلِ مَا عُوقِؚْتُم ؚِهِ وَلَ؊ِن صََؚرْتُمْ لَهُوَ خَيْرٌ لِّلصَّاؚِرينَ (ብትበቀሉም፣ በርሱ በተቀጣቜሁበት ብጀ ተበቀሉፀ ብትታገሡም፣ እርሱ ለታጋሟቜ በእርግጥ በላጭ ነው) አል–ነህል 126 በተመሳሳይ አንቀፅ በደልን በኹፋ በደል ኚመመለስ እንድንቆጠብ ይመክሚናል። ዙልም ኹመፈፀም እርሱን ልንፈራ እንደሚገባ ያስጠነቅቀናል። 3ኛ) ዹተበደለ ሰው በተገደበ ሁኔታ እንዲበቀል መፈቃዱ ወንጀልን በወንጀል መበቀልን አያካትትም። فَمَنِ اعْتَدَى عَلَيْكُمْ فَاعْتَدُوْا عَلَيْهِ ؚِمِثْلِ مَا اعْتَدَى عَلَيْكُمْ وَاتَّقُوا اللهَ وَاعْلَمُوْا أن الله مع المتقين (በእናንተም ላይ ወሰን ያለፈባቜሁን ሰው በናንተ ላይ ወሰን ባለፈው ብጀ (ልክ) በርሱ ላይ ወሰን እለፉበት፡፡ አላህንም ፍሩ አላህ ኚሚፈሩት ጋር መኟኑንም ዕወቁ) አል በቀራህ 194 ‘ወሰን ባለፈው ብጀ (ልክ) በርሱ ላይ ወሰን እለፉበት’ ዹሚለው መልእክትፀ በቀል ቀጥተኛ ወንጀል መፈፀምን እንደማይመለኚት ግልፅ ነው። ለምሳሌፀ ኚቀተሰባቜን ዹሰሹቀውን ኚቀተሰቡ በመስሚቅፀ ዚእኛን ዚቀተሰብ አባል ወንጀል ያሰራን ቀተሰቡን ወንጀል በማሰራት መበቀል ፍፁም ክልክል ነው። ስለዚህም በአንቀፁ መቋጫ ላይ (ይቅርም ያለና ያሳመሚ ሰው "ይቅር ዚማለቱ" ምንዳው አላህ ዘንድ ነው) በዳይን ሰው ይቅር ማለት ኹመበቀል ዚተሻለ መሆኑን ተናግሮአል። ጠንካራነት እና ጀግንነት ዚሚለካዉም መጉዳት እዚቻሉ ለአላህ ሲሉ በመተውና ይቅርታ ማድሚግ ላይ ነዉና አላህ እጅግ ኚባድ ምንዳን አዘጋጅቶለታል። 4ኛ) ኹበቀል ምህሚት ዹሚቀደመው መልካም ሆኖ ሲገኝ ብቻ ነው። ድንበር ማለፉ ዹተኹሰተው በአላህ ሀቅ ላይ ኹሆነ ወንጀል እንዲፈጞም መፍቀድን ይቅር ባይነት አድርጎ መቁጠር አላዋቂነት ነው። ለምሳሌፀ ጟታዊ ጥቃቶቜ ዚሚደርስባት ሎት ይቀርታ ይሻላል በማለት ጥፋትን ኚሞፈነቜና እንዲደጋም መንገድ ኚኚፈተቜ ዹወንጀሉ ተካፋይ ትሆናለቜ እንጂ ይቅርታዋ ትክክል አይሆንም። ነገር ግን ዹአላህ ክልኹላ መጣስ ሳይሆን ግላዊ በደል ኹሆነ ይቅር ማለት ተገቢና ዚተሻለ ነው። ቡኻሪና ሙስሊም በዘገቡት ሀዲስ እናታቜን አዒሻ እንዲህ ብለዋልፀ (ዹአላህ መልዕክተኛ ለራሳ቞ው ሲሉ መቌም ቢሆን ተበቅለው አያውቁም...) 5ኛ) አላህ በደል እና ብቀላን አስመልክቶ በሱሚቱል ሹራ ኹ39–42 ድሚስ ያብራራበትን ሂደት ስንመለኚትፀ ዚብቀላን ገደቊቜ ኹመግለፁ በፊት 39ኛው አንቀጜ ላይ አፀፋ ዚመመለስን መብት መግለጹ በቀልን ዚሚያበሚታታ አይደለም። ምክኒያቱምፀ በቀጣዩ አንቀጜ ዚሚተገብሩትን መንገድ በልክ እንዲሆን ያዘዘ ሲሆን ዚተሻለዉና በላጩ ምህሚት ማድሚግ መሆኑንም አፅንቷል። አል ኢማም አልቁርጡቢ ሲያብራሩፀ እንዲህ ብለዋልፀ አላህ ምዕመናንን ሁለት አይነት አድርጓ቞ዋልፊ ኚፊሎቹ በደልን ይቅር ዹሚሉ ሲሆኑ ኚአንቀጹ ቀደም ብሎ 37ኛው አንቀጜ ላይ (በተቆጡም ጊዜ እነሱ ዚሚምሩ ለሆኑት) በማለት እነሱን አውስቶ ጉዳዩን ጀምሮታል። ኚፊሎቹ ደግሞ በደልን ዹሚበቀሉ ናቾውና አስኚትሎ ዹበቀልን ገደብ ገለጞ። ወሰን ማለፍ እንደማይገባም ተናገሹ” አልጃሚዕ ሊአህካሚል ቁርዓን ኢብኑ ሚጀብ እንዲህ ብለዋልፀ “አላህ (ለነዚያም በደል በደሚሰባ቞ው ጊዜ እነሱ በሲሚቱ ሹራ 39 ላይ "ተመሳሳይ አፀፋን" ዚሚመልሱ ለሆኑት) ዹሚለው አንቀፅ ይቅርታ ኚማድሚግ ጋር ዹሚጋጭ አይደለም። በቅድሚያ መበቀል እንደሚቜሉ አሳይተው ይቅርታ ማድሚግን ማስኚተላ቞ው ዹተሟላና ዚተሻለ ያደርገዋል” ጃሚዑል ዑሉም ወልሂኹም 1/450 ብዙዎቜ ዘንድ ትዕግስት እና ይቅር ባይነት እንደ ድክመትፀ ብቀላ ደግሞ እንደ ጀግንነት ይታያል። ይህ ስህተት ነው። ይቅር ባይነት ኹአላህ ኹፍተኛ ምንዳን ዚሚያስገኝ መልካም ባህሪ ነው። በብቀላ ቁጭትን ለመወጣት ሲባል ድንበርን በማለፍ ጞጞት ዉስጥ ኹመዉደቅ ኹአላህ ዹሚገኘውን ምንዳ በማሰብ በቀልን መራቅ ብልህነት ነው። ቁጭቱን በመዋጥ ይቅርታ ለሚያደርግ ሰው አላህ ታላላቅ ሜልማቶቜን ቃል በመግባት እንዲህ ብሏልፀ وَالْكَا؞ِمِينَ الْغَيْ؞َ وَالْعَافِينَ عَنِ النَّاسِ وَاللَّهُ يُحُِؚّ الْمُحْسِنِينَ [ለነዚያፀ በድሎትም ኟነ በቜግር ለሚለግሱት፥ ቁጭትንም ገቺዎቜ፥ ኚሰዎቜም ይቅርታ አድራጊዎቜ ለሆኑት (ጀነት ተደግሳለቜ)ፀ አላህም በጐ ሠሪዎቜን ይወዳል] አል ዒምራን 134 አላህ ሆይ! ኹበደል አርቀን። ኚነብሳቜን እና ኚሞይጣን ክፋት አንተው ጠብቀን! አቡጁነይድ መስኚሚም 18/2006 ኚጥቂት ማሻሻያዎቜ ጋር t.me/abujunaidposts

🔖 ዓቂዳ እና መንሐጅ... ዘጠኝ ወሳኝ ነጥቊቜ 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ 📌 ትኩሚት ዚሚሹ 9 ዚአቂዳና ዹመንሐጅ ጉዳዮቜን ይዳስሳል https://t.me/abujunaidposts/88

🍂||• ጣፋጭ ቲላዋ •||🍂 ቃሪእ ኢብራሂም ዓሲሪ 📖 [ዹአደም ልጆቜ ሆይ! ሰይጣንን አትገዙፀ እርሱ ለእናንተ ግልጜ ጠላት ነውና በማለት ወደእናንተ አላዘዝኩምን? ] ያሲን 60 #تلاوات_لا_أنساها @abujunaidposts

🔖 ዚሰለፎቜ ልገሳና አርአያነቱ 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🍂 ዹሰደቃ ታላቅነትና ዚሰለፎቜ ገድል ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

🔖 ዹኑህ መርኚብ 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ ዚቢድዓን አደጋዎቜ በመግለፅ ለቢድአ አራማጆቜ ማደናገሪያዎቜ ምላሜ ዚሚሰጥ ትምህርት http://nesiha.com/wp-content/uploads/2018/05/ዹኑህ-መርኚብ.mp3 @abujunaidposts

ኚሶስቱ መስጂዶቜ ውጭ መንፈሳዊ ጉዞዎቜን ማድሚግ በሞሪዓ ይፈቀዳልን? ክፍል 2/2 (ማደናገሪያዎቜ እና ምላሟቻ቞ው) ባለፈው ክፍል ኚሶስቱ መስጂዶቜ ውጭ ዹሚደሹጉ (መንፈሳዊ) ጉዞዎቜን ክልክልነት ዹሚገልፀውን ሀዲስ እና ተያያዠ መሚጃዎቜን ቃኝተናል። በዚህ ክፍል ደግሞ በተቃራኒ ወገኖቜ ለሚቀርቡ ማደናገሪያዎቜ ምላሜ አቀርባለው። 1) áŠ¥áŠá‹šáˆ…áŠ• ጉዞዎቜ በቀብር ዚያራ በማስታኚክ ህጋዊነትን ለማላበስፀ ‹‹ቀብርን መጐብኘት ኚልክያቜሁ ነበር አሁን ግን ጐብኙ›› ዹሚለውን ዚነብያቜን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሐዲስ ይጠቅሳሉ።  áˆáˆ‹áˆœ:–  ነብያቜን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ቀብር ዘይሚዋል፣ ዘይሩ ብለውም አዘዋል። ዚዚያራው ዋነኛ አላማ አኌራን ማስታወስ እንደሆነም ተናግሚዋል። እሳ቞ውም ሆኑ ሶሐቊቻ቞ው ቀብር ለመዘዹር ብለው ጉዞ አልወጡም ሌሎቜ እንዲጓዙም አልፈቀዱም። በመመርመር ላይ ያለነው ግን በአካባቢያቜን ዹሚገኙ ቀብሮቜን ስለመዘዚር ሳይሆን በቀብር ዚያራ አላማ ኚሚኖሩበት ኹተማ ወይም ሀገር ወደ ሌላ ቊታ ጉዞ ማድሚግን ነው። ቀብር ዚያራ ለማድሚግ ዹሚፈልግ በአካባቢው ወደሚገኝ መቃብር መሄድ እንጂ ጉዞ በሚያስወጣ ርቀት ዹሚገኝ ቀብርን ለመዘዹር ጓዝ አስሮ መነሳት ክልክል መሆኑ ያሳለፍነው ሐዲስ ግልፅ መሹጃ ነው። 2) ነቢዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ዚኡሁድ ሞሂዶቜን ቀብር ለመዘዹር መውጣታ቞ውን እንደማስሚጃ በመጥቀስ ጉዞ ወጥቶ ቀብር ዚያራ እንደሚቻል ዚሚሞግቱም አሉ።   ምላሜፊ ኡሁድ ባሁኑ ዹኹተማው ሁኔታ በመዲና ኹተማ ለነብዩ መስጂድ ቅርብ ኚሚባሉ ቊታዎቜ አንዱ ሲሆን ቀድሞ በነበሹው ዹኹተማዋ ሁኔታም ቢሆን እንደ ሌላ ኹተማ ዚሚታይና ጉዞ ዚሚባል ርቀት ላይ ዹሚገኝ አለመሆኑ ግልፅ ነው። 3)  áŠá‰¢á‹© (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ዚእናታ቞ውን ቀብር መዘዚራ቞ውን በመጥቀስ ለቀብር ዚያራ ሲባል ርቀት ጉዞ መሄድ እንደሚቻል ይሞግታሉ።  ምላሜፊ ነቢዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ዚእናታ቞ውን ቀብር ዚዘዚሩት መካን ለመክፈት በተጓዙት ዘመቻ ላይ እግሚ መንገዳ቞ውን እንጂ በዚያራ አላማ ስንቅ ሰንቀውና ጓዝ ሾክፈው ተጉዘው አልነበሚም። 4)  áŠ áŠ•á‹³áŠ•á‹¶á‰œ አቡ ሑሚይራ ኚልካይ ሀዲሶቜን ኹማወቃቾው ጋር ጡር ወደተባለው ተራራ መሄዳ቞ው እንደሚፈቀድ ያሳይል ይላሉ። ምላሜፊ ሀቅን ለመደበቅ ሆን ብለው ካልሞኚሩ በቀርፀ አል ኢማም ማሊክ እና አስሀቡሱነን በዘገቡት እና ይህ ክስተት በተወሳበት ሀዲስ ላይ አቡሁሚይራ ኹጉዞ ሲመለሱ ያገኛ቞ው አቡ በስራ አልጊፋሪይ ኚሶስቱ መስጂዶቜ ውጭ ወደ ሌላ ስፍራ ለኢባዳ ጉዞ ማድሚግ እንደማይፈቀድ መሹጃ በመጥቀስፀ "ኚመሄድህ በፊት ባገኝህ ኖሮ (ጉዞ) አትወጣም ነበር] á‰¥áˆˆá‹ ስራ቞ው ተገቢ እንዳልነበሚ አስታውሰዋ቞ዋል። አቡሁሚይራም ተቀበሉ እንጂ አልሞገቱም!! 5)  á‹šáˆ€á‹²áˆ± ክልኹላ ዹሚመለኹተው ወደ መስጂዶቜ ዹሚደሹግን ጉዞ እንጂ ቀብሮቜ እና ዚዚያራ ቊታዎቜን አይመለኚትም ይላሉ። ምላሜፊ ዚሀዲሱ ክልኹላ መስጂዶቜ ቢልም ኹላይ ዹተጠቀሰው ሀዲስፀ ዚነብያት እና ሷሊሆቜ ቀብር እንዲሁም ታዋቂ እና ታሪካዊ ቊታዎቜንም ክልኹላው እንደሚመለኚት ዚአቡ በስራ ግንዛቀ እና ዚአቡሁሚይራ መስማማት ግልፅ መሹጃ ነው።  ኢብኑ ተይሚያህ ሹሂመሁላህ እንዲህ ብለዋልፀ “ይህ ክልኹላ ወደ መስጂዶቜም ሆነ ወደ አላህ ለመቃሚብ በሚፈፀም ማንኛውም ጉዞ ግብ ዹሚደሹጉ ቊታዎቜን ይመለኚታል።” ካሉ በኃላ  በአቡ በስራ እና በአቡ ሁሚይራ መካኚል ዹተኹሰተውን ክስተት ጠቅሰው እንዲህ አሉ። “ጡር እና መሰል አንቢያዎቜን ያስተናገዱ ቊታዎቜ በዚህ ሀዲስ ክልኹላ ውስጥ እንደሚገቡ ሀዲሱን ያስተላለፈው ይህ ሰሐቢይ ተገንዝቧል
 ይህ ታሪካዊ ቊታዎቜን ኹተመለኹተ ዚአምልኮ ቀቶቜም በዋናነት ክልኹላው ይመለኚታ቞ዋል።” ኢቅቲዷኡ ሲራጥ ቅፅ 2 ገፅ 645 6)  á‰ áˆ€á‹²áˆ± ላይ በተፈቀደው መሰሚት ዚነብዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) መስጂድ ስንሄድ ኹጎን ዹሚገኘው ቀብራ቞ው ጋር ሄደን እንዘይራለን። ይህ ቀብሮቜን ለመዘዹር በማሰብ መጓዝ እንደሚቻል መሹጃ ነው በማለትም ይሞግታሉ።  ምላሜፊ ዚነብዩን መስጂድ ለመዘዹር ዹሄደ ሰው በዛው ወደ ነቢዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ቀብር ሄዶ መዘዹር ይቜላል። ሆኖም ዚሳ቞ው ንግግር እንደሚያመለክተው ጉዞ ማድሚግ ያለብን ወደ ሶስቱ መስጆዶቜ ብቻ ነው። በጉዞዬ ቀብራ቞ውን መዘዹር እንጂ መስጂዳ቞ውን  መዘዹርን አላማ አላደሚኩም በማለት መጓዝ  ዚሳ቞ውን ክልኹላ መጣስ ነው። በዚሁ አጋጣሚ ልብ ልንል ዚሚገባውፀ ቀብርን መዘዹር ሙስተሐብ ሲሆን ዚሳ቞ውን ቀብር መዘዹር ደግሞ ታላቅ መልካም ነገር ነው።  ዚርሳ቞ውም ቀብር ኹዚህ እንደሚካተት ግልጜ ነው፡፡ ሆኖም ኚእርሳ቞ው ቀብር ጋር ተያይዘው ዚሚነገሩት ሐዲሶቜ ዶኢፍ ወይም ጭራሹኑ ዹተቀጠፉ መውዱእ ና቞ው። በመጚሚሻምፀ ይህ ድንጋጌ አላማው ተውሒድን ኹሰርጎ ገብ አመለካኚት መጠበቅ ነው። ጉዞ ዚሚደሚግባ቞ውን ብዙ ቀብሮቜ ብንመለኚት ኚጉብኝት እና ጉዞ ጋር በተያያዘ ብዙ ዚአቂዳ ግድፈቶቜን እናስተውላለን። ለዚህም ውቅሮ ኹሚገኘው ዚነጃሺ ቀብር በምሳሌነት መመልኚት ይቻላል። በቀብሮቜ ላይ መስጊድን መገንባት ፍፁም ዹተኹለኹለ መሆኑ ግልፅ ነው። ምንም እንኳ ታላቁን ነጃሺ ቢን አስሀማ (ሹሂመሁላህ) ዚምናኚብርና ዚምንወድ ብንሆንም ኚሱ ፍቃድና ፍላጎት ውጪ እነዚህ ነቢያዊ ትእዛዛትን በመጣስ በቀብሩ ላይ ዚሚደሚጉት ክልክል ተግባራት ሁሉ እናወግዛለን። ነጃሺን በምሳሌነት ጠቀስን እንጂ በዚአካባቢው ይህ አይነቱ ፈተና ይገኛል። በብዙ መሰል ቊታዎቜ አላዋቂዎቜ ወደ ቀብር ሄደው ስለት በማስገባት ኹጭንቅ እንዲያወጣ቞ው እና ሀጃቾውን እንዲያወጣላ቞ው ይለምናሉ። ወደ አላህ ብቻ ሊዘሚጉት ዚሚገባውን እጃ቞ውን በማንሳት ዚሚፈልጉት ሁሉ እንዲሰጧ቞ው ሙታንን ይማፀናሉ። ይህ ግልፅ ዚጃሂሊያ ተግባር ወደሚፈፀምበት ቊታ ዹጉዞ ጥሪ ማስተጋባት ፍፁም ስህተት ነው። ቅርስን ለመንኚባኚብም ይሁን ለሌላ ምክንያት ወደ ቀብሮቜ ዹሚደሹግ ጉዞ መጀ ተግባር ላይ መሳተፍ ኹመሆኑም በላይፀ ዚነብዩን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ግልፅ ክልኹላ መጣስ ነው። ኚኚባድ ወንጀል አንስቶ እስኚ ቢድዓ እና ሺርክ ዚሚያደርሱ ጥፋቶቜን ሊያስኚትል እንደሚቜል አውቀናልና መልእክቱን ሁሉም ሊያስተጋባውና ሙስሊሙን ሊያነቃ ይገባል። አላህ ኹጅህልና ይጠብቀን! አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ t.me/abujunaidposts

ኚሶስቱ መስጂዶቜ ውጭ መንፈሳዊ ጉዞዎቜን ማድሚግ በሞሪዓ ይፈቀዳልን? ክፍል 1/2 በሀገራቜን እና በብዙ ሀገራት በሚኖሩ ዹሌላ እምነት ተኚታዮቜ ዘንድ ኚተለመዱ ተግባራት አንዱ መንፈሳዊ ጉዞ áŠá‹á¢  ይህ አይነቱ ጉዞ ሰዎቜ  ቅዱስነቱን ወደሚያምኑበት ስፍራ ወይም ቅዱሳን መሆናቾው ዚሚታመንባ቞ው ሰዎቜ ወደተቀበሩበት ቊታ ዹሚደሹግ ሲሆንፀ  ኚዚሄዱበት ስፍራ በሚኚትንና ፈውስን ዚመሳሰሉ ጥቅሞቜን ይኚጅላሉ። መነሻው በጥቂት አስተባባሪዎቜ እና ተሳታፊዎቜ ቅንጅት ይኹወን ዹነበሹ ቢሆንም ቀስ በቀስ ነጋዎዎቜ ስርአት እያስያዙትና ዹጉዞ ማህበራት በማቋቋም እያደራጁት ሄደዋል። ይህንን ተሞክሮ ወደ ሙስሊሙ በማምጣት ዚታላላቅ ሰዎቜን ቅዱስነት እና ወልይነት አጉልቶ መስበክ፣ ወደቀብራ቞ውም ጉዞ ማድሚግ፣ ዚተለያዪ ፕሮግራሞቜን በቀብራ቞ው ዙርያ ማዘጋጀት በተደራጀ መልኩ ቀጥሏል።  ኹዚህ ቀደም ባልተደራጀ መልኩ ጉዞዎቜን ዚሚያስተናግዱ እንደ ነጃሺ፣ አናጂና፣ አብሬት፣ ቃጥባሬ እና መሰል ቊታዎቜ አሁን አሁን ሌሎቜ ጋር ዹተለመደውን ዹጉዞ አደሚጃጀት በመኹተል መጠናኹሹቾውን ዚሚያሳዩ ማስታወቂያዎቜና እና እንቅስቃሎዎቜ በመስጂዶቻቜን ላይ በስፋት እዚታዩ ነው። ባእድ አምልኮ ዚሚፈፀምባ቞ውን ዚቀብር ስፍራዎቜፀ ቅርስን በመንኚባኚብ እና ባህላዊ እሎቶቜ በመጠበቅ ስም ለማነፅ በኹፍተኛ በጀት ዚሚበጅቱት ዚአንዳንድ ሀገራት ኀምባሲዎቜ አላማ ኹህዝበ ሙስሊሙ ዹተደበቀ አይደለም። በሌሎቜ እምነቶቜ ተፅእኖ ስር ዚወደቁትን ዚሱፊያ አስተሳሰብ መስመሮቜ ለሙስሊሙ ህብሚተሰቡ በማስተዋወቅ ዚኢትዮጵያ ሙስሊሞቜ መገለጫ አድርገው በማቅሚብ ሙስሊሙን እኛ እናውቅልሀለን ዚሚሉት ወገኖቜ አላማም አጠያያቂ ነው። ይህ አይነቱ ጉዞ በሞሪአ እንዎት ይታያል ዹሚለውን ለመቃኘት እንሞክራለንፀ 1)  áŠá‰¢á‹«á‰œáŠ• (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) {ወደ ሶስት ቊታዎቜ ካልሆነ ጓዝን ጠቅልሎ ጉዞ አይወጣምፀ መስጅድ አልሐሹም (መካ) መስጂድ አነበዊ (መዲና) እና መስጂድ አልዓቅሷ} áˆ›áˆˆá‰³á‰žá‹ በሰሒሕ ቡኻሪ እና ሌሎቜም ድርሳናት ተዘግቧል ይህ ሐዲስ እንደሚጠቁመው አምልኮትን ፍለጋ አንድን ቊታ በማላቅ ዹሚደሹግ ጉዞ ወደ ሶስቱ መስጅዶቜ ካልሆነ ወደ ሌላ ቊታ መሄድን ይኚለክላል። ይኾውም ሰዎቜ አንድን ቊታ በተለዹ ቀድሰው በቊታው ዹሚገኝን ቀብር ወይም ሌላ ነገር በማላቅ ወደ ማምለክ(ሜርክ) እንዳይገቡና ኚዲና቞ው እንዳይወጡ ለመጠበቅ ሲባል ነው። ኹዚህም በመነሳትፀ  አንድን ቊታ በማላቅ ወይም ኚሌሎቜ ቊታዎቜ ይልቅ አምልኮት ተቀባይነት ያገኙበታል በሚል ግምትፀ ኚሶስቱ መስጅዶቜ ውጭ መንፈሳዊ ጉዞ ማድሚግ ሀራም ነው። ይህ አላህን በሰላት ዱአ እና መሰል ኢባዳዎቜ ለማምለክ ኹሆነ ነው። ስለት በማስገባት፣ ድሚሱልን ወይም አማልዱኝ በማለት  ቅዱሳንን መማፀን ኹሆነ ግን ባእድ አምልኮ ነውና  በእጅጉ ኹዚህ ዹኹበደ ዚሜርክ ተግባር ነው።  2) በአምልኮት ተግባራ቞ው እና ሌሎቜ  በሚለዩባ቞ው ባህልና ልማዶቜ አርአያ አድርጎ መመሳሰል ብሎም መኹተል ዚማይፈቀድ ክልክል ተግባር ነው። ነብያቜን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) በአንድ ሐዲስ ... [ኹናንተ በፊት ዚነበሩትን ፈለግ ስንዝር በስንዝር፣ ክንድ በክንድ ትኚተላላቜሁፀ ዹአርጃኖ ጉድጓድ ቢገቡ እንኳ ትኚተሏ቞ዋላቜሁ] áŠ áˆ‰á€ ይህን ዚሚሰሙት ሶሐቊቜም "ዹአላህ መልእክተኛ ሆይ ዚዚሁዳና ነሳራዎቜን (ፈለግ ማለት ነው) ?] á‰¥áˆˆá‹ ሲጠይቋ቞ው እሳ቞ውም ]ታዲያስ?] á‰¥áˆˆá‹ መለሱላ቞ው። ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል፡፡  á‹šáŠ áˆ‹áˆ… መልእክተኛ እንዲህ ብለዋልፀ [ኚህዝቊቜ ዚተመሳሰለ እርሱ ኚነርሱ ነው] áŠ á‰¡ ዳውድ ዘግበውታል   ቅዱሳንን በማላቅ አላማ ዚሚካሄዱ ጉዞዎቜ ዚሌሎቜን  ዚአምልኮ ተግባራት በመኮሚጅ ኢስላማዊ ቅብ መቀባት በመሆኑ መመሳሰል (ተሞቡህ) ነውና አይፈቀድም። በዲናቜን አንድን ቊታ በማላቅ ወይም ኹፍ በማድሚግ ወደዛ ስፍራ ሄዶ አምልኮትን መፈፀም ዹሚፈቀደው ወደ ሶስቱ መስጅዶቜ ብቻ ነው። 3) áˆžáˆªá‹“ቜን ኚተደነገጉት ሶስቱ መስጂዶቜ ውጭ አንድን ቊታ በማላቅ ወይም አንዳቜ ጥቅም በመፈለግ ዹሚደሹግ ዹጀመዓ ጉዞ ነብያቜንም ሆኑ ሶሐቊቻ቞ው በኖሩበት ጊዜ ዚማይታወቅ ዚቢድአ ተግባር ነው።  ወደ ተለያዩ ዶሪሆቜ እና መሳጂዶቜ ዹሚደሹገው ጉዞ በእስልምናቜን ዚማይታወቅ ነብያቜን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ያላዘዙት መጀ ዚቢድአ ተግባር ነው። ነብያቜንም (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሞሪዓቜንን በሚገባ አስተምሚው እሳ቞ው ያላዘዙትን ኹመፈፀም በብርቱ አስጠንቅቀው አልፈዋል። እናታቜን አዒሻ ባስተላለፉት ሐዲስ ነብያቜን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል [ዹኛ ትእዛዝ ዚሌለበትን (ዚአምልኮ) ስራ ዚሰራፀ (ስራው) ተመላሜ ነው] áˆ™áˆµáˆŠáˆ ዘግበውታል፡፡ ስለሆነም ይህ በሞሪዓ እንዲጎበኝ ወዳልታዘዘ ቊታ በመጓዝ አጅር አገኛለሁ ብሎ መሳተፍ አላህም ሆነ መልእክተኛው ያላዘዙትን መስራት በመሆኑ አደገኛ ዚቢድዓ ወንጀል ነው! 4)  áŠ áˆ‹áˆ… ዲናቜንን ዹተሟላ እና ምንም አይነት ጭማሪም ሆነ ማሻሻያ ዚማይሻ ዹማይፈልግ ለሁሉም ዘመንና ቊታ ዹሚሆን ሐይማኖት አድርጎታል። መንፈሳዊ ጉዞ ታላላቅ ዚዲን መሪዎቜ በኖሩባ቞ው ዚኢስላም ቀዳሚ ዘመናት ሙስሊሞቜ ዚማያውቁት ኚሌሎቜ ዚተኮሚጀ እንግዳ ስራ ነው። اليَومَ أَكمَلتُ لَكُم دينَكُم وَأَتمَمتُ عَلَيكُم نِعمَتي وَرَضيتُ لَكُمُ الإِسلامَ دينًا «ዛሬ ሃይማኖታቜሁን ለናንተ ሞላሁላቜሁ፡፡ ጞጋዬንም በናንተ ላይ ፈጞምኩ፡፡ ለእናንተም ኢስላምን ኚሃይማኖት በኩል ወደድኩ» ሱሚቱ'ል-ማኢዳህ 3 በመሆኑምፀ መንፈሳዊ ጉዞ በሚል በተለያዩ መስጅዶቜ እዚተዋወቀ ያለው ጥሪ ትኩሚት አድርገን ካልተኚላኚልነው ለብዙ ጥፋቶቜ ዚሚያጋልጥ ነው። በሞሪአቜን በግልፅ ዹተኹለኹለ በመሆኑ  ሙስሊሙ እንዲጠነቀቅ፣ ራሱንና ቀተሰቡን በዲን ስም ኹሚፈፀም ጥፋት እንዲጠብቅ እናሳስባለን።  5) በብዙ አካባቢዎቜፀ መቃብሮቜ ኚአንድ ስንዝር በላይ ኹፍ እንዳይሉ፣ እንዳይገነቡና እንዳይቀቡ እንዲሁም መቃብሮቜ መስጂድ ተደርገው እንዳይያዙ ዹሚኹለክሉ ነብያዊ ትእዛዛትን ዹተቃሹነ ተግባር በስፋት ይፈፀማል። ጁንዱብ ኢብኑ አብደላህ ባስተላለፉት ሐዲስ  ዹአላህ መልዕክተኛ (ሰለላሁ ዓለይሁ ወሰለም) ኚመሞታ቞ው ኚአምስት ቀናት በፊት እንዲህ ሲሉ ሰምቻለው ብለዋል ‹‹ኚእናንተ በፊት ዚነበሩ ህዝቊቜ ዚነቢያ቞ውንና ዹደጋግ ባሮቜን ቀብር መስገጃ ስፍራ አደሚጉ፡፡ አደራ! ቀብሮቜን መስገጃ እንዳታደርጉ ኚልክያቜኃለው››  ሙስሊም ዘግበውታል በሌላ ዘገባም ጃቢር እንዲህ ብለዋልፀ ‹‹ዚአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ቀብርን በጄሶ መመሚግ፣ ላዩ ላይ መቀመጥ፣ ኚላዩ መገንባት፣ ኚአፈሩ ውጭ መጹመርና ቀብር ላይ መፃፍ ኚልክለዋል››  ኹላይ ዚተዘሚዘሩት መሚጃዎቜ በግልፅ እንደሚያሳዩት ኚሶስቱ መስጂዶቜ ውጭ ወደ ወልዮቜ ሷሊሆቜና ነብያት መቃብሮቜም ይሁን መናገሻ ኚተማዎቜ ዹሚደሹጉ ጉዞዎቜ በሞሪዓ ዹተወገዙ ለሜርክ እና ባእድ አምልኮ ዚሚያጋልጡ መሆናቾው ግልፅ ነው። በአላህ ፈቃድ በቀጣይ ክፍል ሙስሊሙን ማህበሚሰብ ለማደናገርና ወደ ቀብር አምልኮ ለመምራት በዚህ ሀዲስ ዙርያ ለሚቀርቡ ማደናገሪያዎቜ ምላሜ እንሰጣለን። አምልኮ ሁሉ ዚሚገባው ለአላህ ብቻ ነው። ስላሳወቀን ዚተውሂድ ብርሀን እናመሰግነዋለን። መንገድ ኚመሳት በርሱ እንጠበቃለን። ወልሐምዱ ሊላሂ ሚቢል ዓለሚን! T.me/abujunaidposts

📝 ለምን ወቅፍ እናደርጋለን? ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ T.me/abujunaidposts

🔖 ዹመንሐጅ ቅብብሎሜ... ኚኞዋሪጅ እስኚ ሀዳዲያ 🎙 አቡ ጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🍂 ኹ 10 አመታት በፊት በጃሊያ አዳራሜ ዹቀሹበ አጭር መልዕክት ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts