ar
Feedback
🗞 ዹ አቡጁነይድ መልዕክቶቜ Abujunaid posts

🗞 ዹ አቡጁነይድ መልዕክቶቜ Abujunaid posts

الذهاؚ إلى القناة على Telegram

ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ ዚቀሚቡ ዚድምፅና ዹፅሁፍ መልዕክቶቜ ዚሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ኚመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100

إ؞هار المزيد
2 212
الم؎تركون
-224 ساعات
-67 أيام
-3430 أيام
أر؎يف الم؎اركات
Two weeks left! Scholarship from King Saud University (Saudi Arabia) https://si.ksu.edu.sa/Register IMPORTANT GUIDELINES admi
+1
Two weeks left! Scholarship from King Saud University (Saudi Arabia) https://si.ksu.edu.sa/Register IMPORTANT GUIDELINES admission requirements for scholarship program •The applicant must have a high school certificate or an equivalent. • Your high school graduation grade is not less than (very good). • You have not previously admitted in a similar program in Saudi Arabia. • The applicant must be medically fit. •The applicant age must be not more than twenty-five (25) years old. •Female applicants are required to have (a close family member) residing in Saudi Arabia or applying for the scholarship ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

#_ነሲሓ_ቲቪ_1000 ለመሳተፍ ዚሚኚተሉትን አካውንቶቜ ይጠቀሙ – ንግድ ባንክ 1000145615929 – ኊሮሚያ ኢንተርናሜናል 1445091300001 – አቢሲኒያ ባንክ 73169062 – ንብ ኢንተርናሜናል 7000025634638 – ዘምዘም ባንክ 7122 – አዋሜ ባንክ 01410844116300 https://t.me/nesihatvfamily

وَالَّذِينَ لَا يَ؎ْهَدُونَ الزُّورَ وَإِذَا مَرُّوا ؚِاللَّغْوِ مَرُّوا كِرَامًا [እነዚያም (ሙእሚኖቜ)ፀ #እብለትን_ዚማይመሰክሩፀ ውድቅ ቃልም (በሚ
وَالَّذِينَ لَا يَ؎ْهَدُونَ الزُّورَ وَإِذَا مَرُّوا ؚِاللَّغْوِ مَرُّوا كِرَامًا [እነዚያም (ሙእሚኖቜ)ፀ #እብለትን_ዚማይመሰክሩፀ ውድቅ ቃልም (በሚገሩ ሰዎቜ አጠገብ) ባለፉ ጊዜፀ ክብራ቞ውን በመጠበቅ ዚሚያልፉት ናቾው] አል ፉርቃን 72 "እብለትን ዚማይመሰክሩ" ዹሚለው [በካፊሮቜ በአል ላይ አይገኙም አይታደሙም] ማለት መሆኑን ታላቁ ሙፈሲር ኢብኑ ጀሪር አጊበሪይ ኹ ደሃክ፣ አል ኾላል ደግሞ ኚሙጃሂድ ዘግበዋል። አላህ ኚመንሞራተትና መጥፎ አርአያነት ይጠብቀን @abujunaidposts

Coming Soon... #_ነሲሓ_ቲቪ_1000

🍂||• #محاضرات_غيرت_الحياة •||🍂 📖 أَن تَقُولَ نَفۡسࣱ یَـٰحَسۡرَتَىٰ عَلَىٰ مَا فَرَّطتُ فِی جَنؚِۢ ٱللَّهِ وَإِن كُنتُ لَمِنَ ٱلسَّـٰخِرِینَ محاضرة تاريخية تاؚ ؚسؚؚها عدد لا يحصيهم إلا الله... كان أثرها علي كؚير من أيام ال؎ؚاؚ ولا زلت أستمع إليها https://t.me/abujunaidposts/307 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

እኛ እና መጅሊስ...እውነታና አሉባልታ! ኹዚህ ቀደም በተኚታዩ ሊንክ ቀርቩ ዹነበሹውን ፅሁፍ ወንድም አቡሙስዓብ እንድሪስ መሀመድ አንብቊታል https://t.me/abujunaidposts/299 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

ዛሬ ታላቁ ዐሊም ኜይኜ ሙሀመድ አሉሀይዳን ወደ አኌራ ሄደዋል إنا لله وإنا إليه راجعون አላህ ይማራ቞ው ለቀተሰባ቞ውም መፅናናትን ይስጥልን። አላህ ትተውት ባለፉት ዚኢልም ክምቜት ተጠቃሚ ያድርገን። አሚን وفاة ال؎يخ المحؚوؚ صالح ØšÙ† محمد اللحيدان عضو هي؊ة كؚار العلماء. عن أيُّوؚ السّختياني قال: «إنَّه ليَؚلُغنِي موتُ الرَّجل من أهل السُّنَّة، فكأنَّما سقط عضوٌ من أعضا؊ي» فرحمه الله وأسكنه فسيح جناته ونفعنا الله ؚعلمه. @abujunaidposts

በካፊሮቜ በዓል እንኳን አደሚሳቜሁ ማለት ይፈቀዳልን? በበአላት ሰሞን በተደጋጋሚ እገሌና እገሌ ላይክ አድርገውታል ኹሚለን ፖስቶቜ መካኚል ኚፊሎቹ ዚእንኳን አደሚሳቜሁ መልእክቶቜ ና቞ው። ለጌታ መወለድ፣ ለጌታ መሰቀል፣ ለጌታ ሞቶ መነሳት (ትንሳኀና) መሰል ክስተቶቜ እንኳን አደሚሳቜሁ ሲባል ሌር ወይም ላይክ ዚሚያደርጉ ብዙ እህትና ወንድሞቜን አስተውያለው። አንዳንዎ በስህተት ሌላ ግዜም ነገሩን እንደቀላል በመውሰድ ዹሚፈፀም ሊሆን ይቜላል። ሆኖም እጅግ ኚባድና በአኌራ ዋጋ ዚሚያስኚፍል መዘናጋት ነው!! በካፊሮቜ በአልፀ እንኳን አደሚሳቜሁ... እንኳን ደስ አላቜሁ... እንኳን አብሮ አደሹሰን ማለት እነሱን ለማስደሰትም ይሁን ለመመሳሰል ኹአላህ ዲን መንሞራተት እና ዚካፊሮቜን ኩፍር ዹመናገር ስነልቊና መካብ ስለሆነ ክልክል ነው። መኚባበር እና አብሮነትን ለማሳዚት ኚእምነታቜን መንሞራተት አይጠበቅብንም። ዲን ኹምንም በላይ ነውና ሞሪዓን መተላለፍ ፍፁም ጥፋት ነው!! ፈጣሪ ወለደ ተወለደ ዹሚለው አስተምህሮ ዚጥፋትነቱ ክብደት ሰማያትንና ምድርን ሊሰነጥቅ እንደሚቀርብ ቁርአን ይነግሚናል። አላህን ዚሚያስቆጣ ተግባር በመፈፀማቾው እንኳን ደስ ያላቜሁ ማለት ኚሙስሊም አይጠበቅም!! (وَقَالُوا۟ ٱتَّخَذَ ٱلرَّحۡمَـٰنُ وَلَدࣰا * لَّقَدۡ جِ؊ۡتُمۡ ؎َیۡـًٔا إِدࣰّا * تَكَادُ ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تُ یَتَفَطَّرۡنَ مِنۡهُ وَتَن؎َقُّ ٱلۡأَرۡضُ وَتَخِرُّ ٱلۡجَِؚالُ هَدًّا * أَن دَعَوۡا۟ لِلرَّحۡمَـٰنِ وَلَدࣰا * وَمَا یَنَؚۢغِی لِلرَّحۡمَـٰنِ أَن یَتَّخِذَ وَلَدًا * إِن كُلُّ مَن فِی ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تِ وَٱلۡأَرۡضِ إِلَّاۀ ءَاتِی ٱلرَّحۡمَـٰنِ عَؚۡدࣰا * لَّقَدۡ أَحۡصَىٰهُمۡ وَعَدَّهُمۡ عَدࣰّا * وَكُلُّهُمۡ ءَاتِیهِ یَوۡمَ ٱلۡقِیَـٰمَةِ فَرۡدًا) [«አልሚሕማንም ልጅን ያዘ (ወለደ)» አሉ፡፡ ኚባድ መጥፎን ነገር በእርግጥ አመጣቜሁ፡፡ በእርሱ (በንግግራ቞ው ምክንያት) ሰማያት ሊቀደዱ፣ ምድርም ልትሰነጠቅ፣ ጋራዎቜም ተንደው ሊወድቁ ይቃሚባሉ፡፡ ለአልሹሕማን ልጅ አለው ስለአሉ፡፡ ለአልሹሕማን ልጅን መያዝ አይገባውም!! በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ (በትንሣኀ ቀን) ለአልራሕማን ባሪያ ኟነው ዚሚመጡ እንጂ ሌላ አይደሉም] Surah Maryam 88 - 95 ለመሆኑ አንድን ካፊር ለሀይማኖታዊ በአል እንኳን አደሹሰህ ስትለውፀ ምን ማለት እንደሆነ ግልፅ አይደለምን? እንኳን አደሹሰህ... ጌታ ተወልዶ ተሰቅሎ ሞቷል ብለህ ለማወጅ፣ ለመስቀል ለመስገድና ዚፈጣሪን ክብር ዚሚነኩ ንግግሮቜን ለመናገር እንኳን በቃህ! እንኳን አደሹሰህ... ማርያም ፈጣሪዋን ወለደቜውፀ በመጠቅለያም ጠቀለለቜው እያልክ ለመዘመር እንኳን በቃህ! ዚኩፍር ተግባርን ለመኹወን ኹሆነ ዹደሹሰው ለምንስ እንኳን አብሮ አደሹሰን እንላለን? እውቁ አሊም ኢብኑል ቀይም ሹሂመሁላህ ይህ ተግባር ዹተኹለኹለ ስለመሆኑ ዚኡለማዎቜ ዚጋራ አቋም መሆኑን በመጠቆም እንዲህ ብለዋልፀ «ኩፍርን ብቻ በሚያንፀባርቁ ዚሀይማኖታ቞ው መገለጫዎቜ እንኳን አደሚሳቜሁ...እንኳን ደስ ያለቜሁ ማለት ሀራም መሆኑ ዹሁሉም ሊቃውንት ስምምነት ያለበት ነው። ለምሳሌ አንድ ሙስሊም በነሱ በዓላትና ፆም ጊዜፀ «በአሉን ዚተባሚኚ ያድርግልህ» ወይም «መልካም ዚደስታ በአል ያድርግልህ» እና መሰል ዚደስታ መግለጫዎቜን ቢያስተላልፍፀ ተናጋሪው ኚኩፍር ቢድን እንኳ ኚባድ ወንጀል ነው ዚፈፀመው። ይህምፀ ልክ «እንኳን ለመስቀል ሰገድክ» ብሎ ደስታን እንደመግለፅ ነው! ይህ እንደውምፀ አንድ ሰው ነብስ በማጥፋቱ፣ አልኮል በመጠጣቱ፣ ዝሙት በመፈፀሙና በመሰል ተግባራት እንኳን ደስ ያለህ ኚማለት በወንጀልነት ዹኹበደ እና አስቀያሚ ነው። ለኢስላማዊ ድንጋጌዎቜ ተገቢዉን ክብር ዚማይሰጡ ብዙ ሰዎቜ ይህንን ይፈፅማሉ። ምን ያክል ዚሚያስጠላ ዚግባር እንደፈፀሙም አያስተውሉም። ቢድአ፣ ኩፍር እና ወንጀሎቜ በመፈፀማቾው እንኳን አደሚሰህ፣ እንኳን ደስ ያለህ እና መሰል ዚደስታ መግለጫዎቜን ያስተላለፈፀ እራሱን ለአላህ ቁጣና ጥላቻ ዚተገባ እንዲሆን ዚሚያደርግ ምክኒያት ፈፅሟል» አህካም አህሉዚማህ ዚዘመናቜን ፈቂህ ሞይኜ ኡሰይሚን ሹሂመሁላህ እንዲህ አሉ «ካፊሮቜን እንኳን አደሚሳቜሁ ማለት ኢብኑል ቀይም እንዳለው ዹዚህን ያክል ኚባድ ዚሆነበት ምክኒያት እነርሱ ዹሚፈፅሟቾውን ዚኩፍር መገለጫዎቜ ማፅደቅ ስለሆነ ነው። ምንም እንኳን ለራሱ ይህንን ኩፍር መፈፀምን ባይወድም እነሱ መፈፀማቾውን ወዷልና። ሙስሊም ደግሞ ዚኩፍር መገለጫዎቜን መውደድም ይሁን ሌሎቜን እንኳን ደስ ያላቜሁ ማለት አይፈቀድለትም።» መጅሙዑ ፈታዋ ወሚሳኢል አሞይኜ ኢብኑ ኡሰይሚን 3/44 በተመሳሳይ መልኩፀ ክሪስማስም ሆነ ሌሎቜ በአላት ላይ ስጊታ ወይም ፓስት ካርዶቜን መለዋወጥፀ እንዲሁም ማንኛውም ደስታን መግለጫ ዹሆኑ ነገሮቜን መፈፀም በአሉን መካፈል ስለሆነ ዹተኹለኹለ ነው!! በዚህ ፅሁፍ መጠቆም ዚፈለኩት ምንም አይነት ማህበራዊ ግንኙነት ሀራም ነው ዹሚል መልእክት አይደለም። በተለይም ኚክርስቲያን እና አይሁዶቜ ጋር ባለን ማህበራዊ ግንኙነቶቜ ላይ ዚተፈቀዱ ብዙ በመልካም ዹመኗኗር እሎቶቜ አሉን። ሆኖም ሀይማኖታዊ ወሰኖቜ ዹሉም ማለት አይደለም። ዹተፈቀደውን ስንተገብር እንደ ያልተፈቀደ ጋብቻ፣ በአላት ላይ መሳተፍ፣ ለሞቱት ዹአላህን ማርታ መለመንና ባጠቃላይ በዲን መመሳሰልን ግን በፍፁም አንፈፅምም። ይህንን ዚእምነትና ዚሀይማኖት ወሰን መናድ አይቻልም። ማንነታቜንን ማክበር፣ ግንኙነታቜንን በዲናዊ ገደቊቜ ማጠር ብሎም አለመሟሟት ለሌሎቜ ሞራል ዲንና ማንነት ኹመጹነቅ ይቀድማል። ዲን ኹምንም በላይ ነውና ኹመሾማቀቅ እንውጣ። ይህ ዚዲናቜን መገለጫ እንጂ እንደ ማክሹርና ፅንፈኝነት ዚሚታይ አይደለም። በነገራቜን ላይ ዚአንድ እምነት ተኚታይ ኚሌሎቜ ለመቀራሚብ ብሎ ኚራሱ እምነት ጋር ዚሚጣላበት ሁኔታ ድሮ ቀርቷል። ሌሎቹም ቢሆኑ ይህ በኛ ሀይማኖት አልፈቀድም እና ይቅርታ ይሉሀል። (فَلَا تُطِعِ ٱلۡمُكَذِؚِّینَ * وَدُّوا۟ لَوۡ تُدۡهِنُ فَیُدۡهِنُونَ * وَلَا تُطِعۡ كُلَّ حَلَّافࣲ مَّهِینٍ) አስተባባዮቜንም አትታዝዙ፡፡ ብትመሳሰላ቞ውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡ [Surah Al-Qalam 8 - 10] ወላሁ አዕለም አላህ ኚጥፋት ሁሉ ይጠብቀን! ____ አቡጁነይድ ሚጀብ 24/1437 ዓ.ሒ / ሜይ 1/ 2016 ኚጥቂት ማሻሻያዎቜ ጋር https://t.me/abujunaidposts/141

"ይህንን አንቀፅ አስተነተንኩና ዚሪዝቅ ክፍፍል ኹአላህ መሆኑን ተገነዘብኩ። መቌም ቢሆን በማንም ላይ ምቀኝነት ገብቶብኝ አያውቅም" ሀቲም አል አሰም أَهُمۡ یَقۡسِمُونَ رَحۡمَتَ رَؚ
"ይህንን አንቀፅ አስተነተንኩና ዚሪዝቅ ክፍፍል ኹአላህ መሆኑን ተገነዘብኩ። መቌም ቢሆን በማንም ላይ ምቀኝነት ገብቶብኝ አያውቅም" ሀቲም አል አሰም أَهُمۡ یَقۡسِمُونَ رَحۡمَتَ رَؚِّكَۚ نَحۡنُ قَسَمنَا َؚیۡنَهُم مَّعِی؎َتَهُمۡ فِی ٱلۡحَیَوٰةِ ٱلدُّنۡیَاۚ وَرَفَعۡنَا َؚعۡضَهُمۡ فَوۡقَ َؚعۡضࣲ دَرَجَـٰتࣲ لِّیَتَّخِذَ َؚعۡضُهُم َؚعۡضࣰا سُخۡرِیࣰّاۗ وَرَحۡمَتُ رَؚِّكَ خَیۡرࣱ مِّمَّا یَجۡمَعُونَ «እነርሱ ዚጌታህን ቜሮታ ያኚፈፍላሉን? እኛ በቅርቢቱ ሕይወት ኑሯ቞ውን በመካኚላ቞ው አኚፋፍለናል፡፡ ኹፊላቾውም ኹፊሉን ሠራተኛ አድርጎ ይይዝ ዘንድ ኹፊላቾውን ኹኹፊሉ በላይ በደሚጃዎቜ (በሀብት) አበለጥን፡፡ ዚጌታህም ጾጋ (ገነት) ኚሚሰበስቡት (ሃብት) በላጹ ናት» Surah Az-Zukhruf 32 t.me/abujunaidposts

ፀባይ (አኜለቅ) ልክ እንደ ሪዝቅ ነው ዚዱንያ ሀብታምና ደሀ እንዳለ ሁሉ ዚአኜላቅም ሀብታምና ደሀ አለ። አላህ ዘንድ በፆምና በለይል ሰላት ዹማይገኝ ክብርና ደሹጃ በመልካም ፀባይ ይገኛል። እውነተኛ
ፀባይ (አኜለቅ) ልክ እንደ ሪዝቅ ነው ዚዱንያ ሀብታምና ደሀ እንዳለ ሁሉ ዚአኜላቅም ሀብታምና ደሀ አለ። አላህ ዘንድ በፆምና በለይል ሰላት ዹማይገኝ ክብርና ደሹጃ በመልካም ፀባይ ይገኛል። እውነተኛው ሀብታም አመለ ሾጋ ሰው ነው! ስለዚህምፀ وَإِنَّكَ لَعَلَىٰ خُلُقٍ عَ؞ِیمࣲ "አንተም በታላቅ ፀባይ ላይ ነህ" ዚተባሉት ነብይ "አላህ ሆይ አፈጣጠሬን እንዳሳመርኚው ጠባዬንም አሳምርልኝ" ይሉ ዚነበሚው። አላህ ያብጀንፀ ኚነፍሳቜንና ኚሞይጣን ክፋት ይጠብቀን! ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

ፀባይ (አኜለቅ) ልክ እንደ ሪዝቅ ነው ዚዱንያ ሀብታምና ደሀ እንዳለ ሁሉ ዚአኜላቅም ሀብታምና ደሀ አለ። እውነተኛው ሀብታም አመለ ሾጋ ሰው ነው። አላህ ዘንድ በፆምና በለይል ሰላት ዹማይገኝ ክብርና ደሹጃ በመልካም ፀባይ ይገኛል። ስለዚህምፀ وَإِنَّكَ لَعَلَىٰ خُلُقٍ عَ؞ِیمࣲ "አንተም በታላቅ ፀባይ ላይ ነህ" ዚተባሉት ነብይ "አላህ ሆይ አፈጣጠሬን እንዳሳመርኚው ጠባዬንም አሳምርልኝ" ይሉ ዚነበሚው። አላህ ያብጀንፀ ኚነፍሳቜንና ኚሞይጣን ክፋት ይጠብቀን! ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

🍂||• #تلاوات_تعجؚني •||🍂 تلاوة هاد؊ة للقار؊ إؚراهيم العسيري #ኢብራሒም_አልዓሲሪ 📖 أَفَمَن یَعۡلَمُ أَنَّمَاۀ أُنزِلَ إِلَیۡكَ مِن رَؚِّّكَ ٱلۡحَقُّ كَمَنۡ هُوَ أَعۡمَىٰۀۚ إِنَّمَا یَتَذَكَّرُ أُو۟لُوا۟ ٱلۡأَلَؚۡـؚِٰ Surah Ar-Ra'd from 19 https://t.me/abujunaidposts/300

እኛ እና መጅሊስ...እውነታና አሉባልታ! በኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሮንተር አስተባባሪነት ዹምናኹናውናቾው ዚዳዕዋና ዚተእሊም ስራዎቜ ዚሰዎቜ ጥሚት እና ስራ ስለሆበ ኚጉድለት ዚጠራ አይሆንም። ማንኛውም አይነት ገንቢ ሀሳብ እና እርምት ካለ በሩ ክፍት መሆኑን በተደጋጋሚ ዹተገለፀ ሲሆን ብዙዎቜም ይህንኑ ዚተናሱሕ አጋርነት በተግባር በማሳዚት ድንቅ ውጀት በታዚባ቞ው ዚዳዕዋ እንቅስቃሎዎቜ ላይ አወንታዊ ሚና ተጫውተዋል።  በተቃራኒውፀ አንዳንድ ወንድሞቜ ዚነሲሓ እና መተራሚም መንገዶቜን ወደጎን በመተው ባዶ ግምቶቜ ላይ ዹተመሰሹተ ፊትና ሲያራግቡ ቆይተዋል። ሌሎቹም ሳያጣሩ በጭፍን ወገንተኝነት ሀሰትን በማሰራጚት በመርኹዙ እንቅስቃሎዎቜ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ለመፍጠር ሰርተዋል። ዹመላው ሙስሊም ማህበሚሰብ ዚጋራ ተቋም ዹሆነውን መጅሊስ ተሀድሶ በተመለኹተ በሚደሹጉ ውይይቶቜ ላይ እንሳተፍ ዘንድ ኹተቋማዊ ለውጥ (ዘጠኙ) ኮሚ቎ ዹቀሹበውን ጥሪ በመቀበል በሁለት ንዑስ ኮሚ቎ዎቜ ውስጥ ተወካዮቜን አሳትፈናል። አላማቜን ኚአህባሜና ኚተለያዩ አካላት ተፅዕኖዎቜ ነፃ ሆኖ ብቃት ባላ቞ው ባለሞያዎቜ ዚሚመራ ኚሙስና ዚፀዳ አስተዳደራዊ መጅሊስ ይደራጅ ዘንድ አወንታዊ ተሳትፎ ማድሚግ ነበር። በመሆኑም ህገ መጅሊሱን ለማዘጋጀት ዹተቋቋመው ንኡስ ኮሚ቎ ተቋሙን ኚብልሹ አሰራር ሊጠብቅ ዚሚቜል ጠንካራ አደሚጃጀትን ይቀርፅ ዘንድ በተወካያቜን አማካኝነት ቀላል ዚማይባል አስተዋፅኊ አበርክተናል። በሌላኛው ንዑስ ኮሚ቎ ላይ ኚሌሎቜ ወንድሞቜ ጋር ዚተሳተፍኩ ሲሆን ዚኡለማዎቜ ዚትብብር ሰነዱ በሱፊያና አሜዓሪያ ቢድዓ ዚበላይነት ላይ ዹተመሰሹተ ተደርጎ እንዳይቀሚፅ በመሹጃ ሞግተናል። እውን ሆኖ ማዚት ስለምንፈልገው ገለልተኛ አስተዳደራዊ መጅሊስ ለሁሉም ወገኖቜ ግልፅ አድርገናል። በተለያዩ ምክንያቶቜ ዹምንፈልገውን ሁሉ ባናሳካም ቀላል ዚማይባል ውጀት ተገኝቷል። አልሐምዱላህ! ሆኖም አንዳንድ ወንድሞቻቜን ኚጅምሩ መሚጃዎቜን በማዛባትና አሉታዊ ቅርፅ በማስያዝ ‘ስልጣን ፍለጋ ኚአህባሜና ኚቢድዓ አራማጆቜ ጋር ተደመሩ’ ዹሚል ቜኮላ ዹወለደው ግምታዊ አሉባልታ ሲያሰራጩ ታዝበናል። ምንም እንኳ በወቅቱ ውይይቶቜ ባይቋጩም ለአንዳንዶቜ እውነታው ግልፅ ይሆን ዘንድ ለተቋማዊ ለውጥ ኮሚ቎ው በህዳር 2011 ለኮሚ቎ው ያቀሚብነውን ባለ 86 ገፅ ዶክሜንት ማብራሪያና ምክሹ ሀሳብ ይፋ አድርገናል። አስተያዚትና እርምት ካለ እንደምንቀበል ገልፀናል። (#በኢብኑ_መስኡድ_ዚዳዕዋና_ኢርሻድ_ኮሚ቎_ዹተዘጋጀ_ግምገማ_እና_እርምት https://goo.gl/o4nCKZ) ሰነዱ ፍትሀዊ ለሆነ ሁሉ እውነታውን ግልፅ በማድሚጉ ብዙዎቜ ብዥታውን በአደብ ስላጠራን ምስጋና አቅርበውልናል። አንዳንዶቜ ግን ዹመርኹዙን ስም ለማጥፋት አጋጣሚውን እንደ ልዪ እድል ዚቆጠሩት በሚያስመስል መልኩ እራሳ቞ውን ብቻ እያዳመጡ ቅጥፈቱን ቀጥለውበታል። ኚባጢል አራማጆቜ ጋር ኹፍተኛ ትንቅንቅ በነበሚባ቞ው ፈታኝ ግዜያት ካለማስተዋል በፀለምተኛ ምልኚታና ምዘና ተሳትፏቜንን አደጋ አድርገው በማቅሚብ ለባጢል ሰዎቜ ደጀን ሆነዋል። ቅጥፈቱ መደጋገሙን ተኚትሎ ምንም እንኳ ካሉብን ሰፊ ኃላፊነቶቜ አንፃር ግዜያቜንን በዚህ ማባኚኑ መልካም ሆኖ ባይታዚንምፀ በአሉባልታው ዚተወዛገቡ ወዳጆቻቜንን ለማገዝ ብሎም አንዳንዶቹ ኹመሹጃ እጥሚት ነገሮቜ ተመሳስለውባ቞ው ኹሆነ በማለት መርኹዝና_ዚመጅሊስ_ተሳትፎዎቜ በሚል እውነታውን ዚሚያብራራ መድሚክ አዘጋጅተናል። [ዚፕሮግራሙ ቅጂ በተኚታዩ ሊንክ ይገኛል https://t.me/merkezuna/70] በዚህ ሳንብቃቃ በቀጣይ በመስኚሚም 2012 በታተመው ነሲሓ መጜሔት ላይ በመርኹዙ ስራ አስኪያጅ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ተሰጥቶበታል። ኹዚህ ሁሉ ገለፃና ማብራሪያ በኋላ ምንም ሳያፍሩ ቅጥፈቱን ዚቀጠሉበት ወንድሞቜ (አላህ ይቅር ይበላቾውና) በውይይቱ ላይ ዚተነሱ ፎቶዎቜን መሹጃ በማድሚግ ተደመሩ ዹሚለውን አሉባልታ እውነታ በማስመሰል ተቆርቋሪነትን በሚያሳዩ ገለፃዎቜ ኚሜነው በዓሚብኛ ባዘጋጁት ዶክሜንት በሳውዲ ዚምናኚብራ቞ውን በርካታ ሞይኟቜ አመለካኚት ለመበሹዝ ጥሚት አድርገዋል። አልሐምዱሊላህ ታህሳስ 15/2012 በአላህ ፈቃድ እውነቱን ፍንትው አድርጎ ያሳዚ ባለ 30 ገፅ ዚዓሚብኛ ፅሁፍ አስነብበናል። [በተኚታዩ ሊንክ ይገኛል https://t.me/nesihaposts/2591] ኹላይ በተገለፀው መልኩ እውነታውን ካብራራን በኋላ በአንድ በኩልፀ ብዙሀኑን አዋም ህዝብ በዝርዝር ዚዳእዋ ጉዳዮቜና ውዝግቊቜ እንዲጠመዱ ማድሚግ ስለማይገባፀ በሌላ በኩል መርኹዙን በጠላትነት ዚሚመለኚቱና በዚህ አይነቱ እሰጥአገባ ተጠቃሚነትን ዚሚያልሙ አካላት ኚንቱ ፍላጎት ይመክን ዘንድ ነገሮቜን በትእግስት ስራቜን ላይ ብቻ በማተኮር ላለፉት ሁለት አመታት ቜላ ብለነዋል። በዚህ ዹሰኹነ አካሄድ በርካታ ጥሩ ውጀቶቜ ተገኝተዋል። አንዳንድ ሲተቹን ዚነበሩ ወንድሞቜ በአላህ ቜሮታ በግዜ ሂደት እውነታውን መሚዳታ቞ውን ማወቅ በራሱ በእጅጉ ያስደስታል። በአንፃሩ አሁንም ድሚስ ጥቂቶቜ ይህንን ግዜ ያለፈበት ቅጥፈት ዚሚያናፍሱ ኹዚህም አልፈው ቅጥፈቱን እውነት ብሎ ያልተቀበላ቞ውን ኚሱና መስመር ዚወጣ ሙብተዲዕ ነው እስኚማለት ዚደሚሱ ዹፋህም ምስኪኖቜ አሉ። አላህ ይድሚስላ቞ው! በበኩላቜን፣ ለ1 አመት ኹመንፈቅ በትዕግስትና መሚጋጋት ዚዳሩተውሑድ ዹወቅፍ ፕሮጀክት ላይ በማተኮር ዚመጀመሪያውን ምዕራፍ በስኬት አጠናቀናል። ስኬት ኹአላህ ነውና ምስጋና ለእርሱ ብቻ ዚተገባው ነው። አልሐምዱሊላህ! በአላህ እገዛ ብዙ ዹተጠኑ ዚዳዕዋ እና ዚትምህርት እቅዶቜን ተፈፃሚ በማድሚግ በስኬት ላይ ስኬትን ለመጹመር ተደጋጋሚ ምክክሮቜን በማድሚግ ላይ እንገኛለን። ዹመርኹዙን ጉዞ ይበልጥ በማጠናኹር ዋነኛ ዚዳዕዋ መድሚካቜንን ነሲሓ ቲቪን ለማዘመንና ለማሳደግ በትጋት በመስራት ላይ ነን። በቀጣይ ዳሩል ሓዲስ ኮሌጅና ተያያዥ ዚትምህርት ተቋሞቜ፣ ቃፊላ ዚዳዕዋ ጉዞ፣ ዚተለያዩ ኮርሶቜና ዚዳዕዋ ስራዎቜ ያብቡ ዘንድ እንሰራለን። ኚያዝነው ታላቅ ዚዳዕዋ ራእይ እና በነፍስወኚፍ ኹተሾኹምናቾው ታላላቅ ኃላፊነቶቜ አንፃር ኢስላማዊ አደብን መሰሚት ላደሹገ ነሲሓ እንጂ ዚንትርክ አጀንዳ በመፍጠር እወቁን ለሚሉ ዹገደል ማሚ቎ዎቜ ምላሜ በመስጠት እንደማንጠመድ ሊታወቅ ይገባል። በዚሁ አጋጣሚ ሀሰት በማሰራጚት ዚተጠመዱ ሁሉ አላህን ይፈሩ ዘንድ ለማስታወስ እወዳለው። ኢብኑ ዑመር ባስተላለፉት ዘገባ ዹአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋልፊ «...مَنْ قَالَ فِي مُ؀ْمِنٍ مَا لَيْسَ فِيهِ، أَسْكَنَهُ اللَّهُ رَدْغَةَ الْخََؚالِ حَتَّى يَخْرُجَ مِمَّا قَالَ». «በአንድ አማኝ ላይ ዚሌለበትን ዹተናገሹ ኚንግግሩ ጣጣ እስኪወጣ ድሚስ አላህ ዚ“ጥፋት ማጥ” ውስጥ ያኖሚዋል!» አሕመድ አቡ ዳዉድ እና ሌሎቜም ዚዘገቡት ትክክለኛ ሐዲሥ በሌላ አጋጣሚ ሰሓቊቜ «ዚ“ጥፋት ማጥ” (رَدْغَة الْخََؚالِ) ምንድነው?» ብለው ሲጠይቁ ነብያቜንም «ዚእሳት ነዋሪዎቜ እዥ!» ብለው መልሰዋል። ኢብኑ ማጃህ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ 5/4/2014 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ 5/4/2014 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

እኛ እና መጅሊስ...እውነታና አሉባልታ! በኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሮንተር አስተባባሪነት ዹምናኹናውናቾው ዚዳዕዋና ዚተእሊም ስራዎቜ ዚሰዎቜ ጥሚት እና ስራ ስለሆበ ኚጉድለት ዚጠራ አይሆንም። ማንኛውም አይነት ገንቢ ሀሳብ እና እርምት ካለ በሩ ክፍት መሆኑን በተደጋጋሚ ዹተገለፀ ሲሆን ብዙዎቜም ይህንኑ ዚተናሱሕ አጋርነት በተግባር በማሳዚት ድንቅ ውጀት በታዚባ቞ው ዚዳዕዋ እንቅስቃሎዎቜ ላይ አወንታዊ ሚና ተጫውተዋል።  በተቃራኒውፀ አንዳንድ ወንድሞቜ ዚነሲሓ እና መተራሚም መንገዶቜን ወደጎን በመተው ባዶ ግምቶቜ ላይ ዹተመሰሹተ ፊትና ሲያራግቡ ቆይተዋል። ሌሎቹም ሳያጣሩ በጭፍን ወገንተኝነት ሀሰትን በማሰራጚት በመርኹዙ እንቅስቃሎዎቜ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ለመፍጠር ሰርተዋል። ዹመላው ሙስሊም ማህበሚሰብ ዚጋራ ተቋም ዹሆነውን መጅሊስ ተሀድሶ በተመለኹተ በሚደሹጉ ውይይቶቜ ላይ እንሳተፍ ዘንድ ኹተቋማዊ ለውጥ (ዘጠኙ) ኮሚ቎ ዹቀሹበውን ጥሪ በመቀበል በሁለት ንዑስ ኮሚ቎ዎቜ ውስጥ ተወካዮቜን አሳትፈናል። አላማቜን ኚአህባሜና ኚተለያዩ አካላት ተፅዕኖዎቜ ነፃ ሆኖ ብቃት ባላ቞ው ባለሞያዎቜ ዚሚመራ ኚሙስና ዚፀዳ አስተዳደራዊ መጅሊስ ይደራጅ ዘንድ አወንታዊ ተሳትፎ ማድሚግ ነበር። በመሆኑም ህገ መጅሊሱን ለማዘጋጀት ዹተቋቋመው ንኡስ ኮሚ቎ ተቋሙን ኚብልሹ አሰራር ሊጠብቅ ዚሚቜል ጠንካራ አደሚጃጀትን ይቀርፅ ዘንድ በተወካያቜን አማካኝነት ቀላል ዚማይባል አስተዋፅኊ አበርክተናል። በሌላኛው ንዑስ ኮሚ቎ ላይ ኚሌሎቜ ወንድሞቜ ጋር ዚተሳተፍኩ ሲሆን ዚኡለማዎቜ ዚትብብር ሰነዱ በሱፊያና አሜዓሪያ ቢድዓ ዚበላይነት ላይ ዹተመሰሹተ ተደርጎ እንዳይቀሚፅ በመሹጃ ሞግተናል። እውን ሆኖ ማዚት ስለምንፈልገው ገለልተኛ አስተዳደራዊ መጅሊስ ለሁሉም ወገኖቜ ግልፅ አድርገናል። በተለያዩ ምክንያቶቜ ዹምንፈልገውን ሁሉ ባናሳካም ቀላል ዚማይባል ውጀት ተገኝቷል። አልሐምዱላህ! ሆኖም አንዳንድ ወንድሞቻቜን ኚጅምሩ መሚጃዎቜን በማዛባትና አሉታዊ ቅርፅ በማስያዝ ‘ስልጣን ፍለጋ ኚአህባሜና ኚቢድዓ አራማጆቜ ጋር ተደመሩ’ ዹሚል ቜኮላ ዹወለደው ግምታዊ አሉባልታ ሲያሰራጩ ታዝበናል። ምንም እንኳ በወቅቱ ውይይቶቜ ባይቋጩም ለአንዳንዶቜ እውነታው ግልፅ ይሆን ዘንድ ለተቋማዊ ለውጥ ኮሚ቎ው በህዳር 2011 ለኮሚ቎ው ያቀሚብነውን ባለ 86 ገፅ ዶክሜንት ማብራሪያና ምክሹ ሀሳብ ይፋ አድርገናል። አስተያዚትና እርምት ካለ እንደምንቀበል ገልፀናል። (#በኢብኑ_መስኡድ_ዚዳዕዋና_ኢርሻድ_ኮሚ቎_ዹተዘጋጀ_ግምገማ_እና_እርምት https://goo.gl/o4nCKZ) ሰነዱ ፍትሀዊ ለሆነ ሁሉ እውነታውን ግልፅ በማድሚጉ ብዙዎቜ ብዥታውን በአደብ ስላጠራን ምስጋና አቅርበውልናል። አንዳንዶቜ ግን ዹመርኹዙን ስም ለማጥፋት አጋጣሚውን እንደ ልዪ እድል ዚቆጠሩት በሚያስመስል መልኩ እራሳ቞ውን ብቻ እያዳመጡ ቅጥፈቱን ቀጥለውበታል። ኚባጢል አራማጆቜ ጋር ኹፍተኛ ትንቅንቅ በነበሚባ቞ው ፈታኝ ግዜያት ካለማስተዋል በፀለምተኛ ምልኚታና ምዘና ተሳትፏቜንን አደጋ አድርገው በማቅሚብ ለባጢል ሰዎቜ ደጀን ሆነዋል። ቅጥፈቱ መደጋገሙን ተኚትሎ ምንም እንኳ ካሉብን ሰፊ ኃላፊነቶቜ አንፃር ግዜያቜንን በዚህ ማባኚኑ መልካም ሆኖ ባይታዚንምፀ በአሉባልታው ዚተወዛገቡ ወዳጆቻቜንን ለማገዝ ብሎም አንዳንዶቹ ኹመሹጃ እጥሚት ነገሮቜ ተመሳስለውባ቞ው ኹሆነ በማለት መርኹዝና_ዚመጅሊስ_ተሳትፎዎቜ በሚል እውነታውን ዚሚያብራራ መድሚክ አዘጋጅተናል። [ዚፕሮግራሙ ቅጂ በተኚታዩ ሊንክ ይገኛል https://t.me/merkezuna/70] በዚህ ሳንብቃቃ በቀጣይ በመስኚሚም 2012 በታተመው ነሲሓ መጜሔት ላይ በመርኹዙ ስራ አስኪያጅ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ተሰጥቶበታል። ኹዚህ ሁሉ ገለፃና ማብራሪያ በኋላ ምንም ሳያፍሩ ቅጥፈቱን ዚቀጠሉበት ወንድሞቜ (አላህ ይቅር ይበላቾውና) በውይይቱ ላይ ዚተነሱ ፎቶዎቜን መሹጃ በማድሚግ ተደመሩ ዹሚለውን አሉባልታ እውነታ በማስመሰል ተቆርቋሪነትን በሚያሳዩ ገለፃዎቜ ኚሜነው በዓሚብኛ ባዘጋጁት ዶክሜንት በሳውዲ ዚምናኚብራ቞ውን በርካታ ሞይኟቜ አመለካኚት ለመበሹዝ ጥሚት አድርገዋል። አልሐምዱሊላህ ታህሳስ 15/2012 በአላህ ፈቃድ እውነቱን ፍንትው አድርጎ ያሳዚ ባለ 30 ገፅ ዚዓሚብኛ ፅሁፍ አስነብበናል። [በተኚታዩ ሊንክ ይገኛል https://t.me/nesihaposts/2591] ኹላይ በተገለፀው መልኩ እውነታውን ካብራራን በኋላ በአንድ በኩልፀ ብዙሀኑን አዋም ህዝብ በዝርዝር ዚዳእዋ ጉዳዮቜና ውዝግቊቜ እንዲጠመዱ ማድሚግ ስለማይገባፀ በሌላ በኩል መርኹዙን በጠላትነት ዚሚመለኚቱና በዚህ አይነቱ እሰጥአገባ ተጠቃሚነትን ዚሚያልሙ አካላት ኚንቱ ፍላጎት ይመክን ዘንድ ነገሮቜን በትእግስት ስራቜን ላይ ብቻ በማተኮር ላለፉት ሁለት አመታት ቜላ ብለነዋል። በዚህ ዹሰኹነ አካሄድ በርካታ ጥሩ ውጀቶቜ ተገኝተዋል። አንዳንድ ሲተቹን ዚነበሩ ወንድሞቜ በአላህ ቜሮታ በግዜ ሂደት እውነታውን መሚዳታ቞ውን ማወቅ በራሱ በእጅጉ ያስደስታል። በአንፃሩ አሁንም ድሚስ ይህንን ግዜ ያለፈበት ቅጥፈት ዚሚያናፍሱ ኹዚህም አልፈው ቅጥፈቱን እውነት ብሎ ያልተቀበላ቞ውን ኚሱና መስመር ዚወጣ ሙብተዲዕ ነው እስኚማለት ዚደሚሱ ዹፋህም ምስኪኖቜ አሉ። አላህ ይድሚስላ቞ው ኚማለት ውጭ ልንሚዳ቞ው አንቜልም! በበኩላቜን፣ ለ1 አመት ኹመንፈቅ በትዕግስትና መሚጋጋት ዚዳሩተውሑድ ዹወቅፍ ፕሮጀክት ላይ በማተኮር ዚመጀመሪያውን ምዕራፍ በስኬት አጠናቀናል። ስኬት ኹአላህ ነውና ምስጋና ለእርሱ ብቻ ዚተገባው ነው። አልሐምዱሊላህ! በአላህ እገዛ ብዙ ዹተጠኑ ዚዳዕዋ እና ዚትምህርት እቅዶቜን ተፈፃሚ በማድሚግ በስኬት ላይ ስኬትን ለመጹመር ተደጋጋሚ ምክክሮቜን በማድሚግ ላይ እንገኛለን። ዹመርኹዙን ጉዞ ይበልጥ በማጠናኹር ዋነኛ ዚዳዕዋ መድሚካቜንን ነሲሓ ቲቪን ለማዘመንና ለማሳደግ በትጋት በመስራት ላይ ነን። በቀጣይ ዳሩል ሓዲስ ኮሌጅና ተያያዥ ዚትምህርት ተቋሞቜ፣ ቃፊላ ዚዳዕዋ ጉዞ፣ ዚተለያዩ ኮርሶቜና ዚዳዕዋ ስራዎቜ ያብቡ ዘንድ እንሰራለን። ኚያዝነው ታላቅ ዚዳዕዋ ራእይ እና በነፍስወኚፍ ኹተሾኹምናቾው ታላላቅ ኃላፊነቶቜ አንፃር ኢስላማዊ አደብን መሰሚት ላደሹገ ነሲሓ እንጂ ዚንትርክ አጀንዳ በመፍጠር እወቁን ለሚሉ ዹገደል ማሚ቎ዎቜ ምላሜ በመስጠት እንደማንጠመድ ሊታወቅ ይገባል። በዚሁ አጋጣሚ ሀሰት በማሰራጚት ዚተጠመዱ ሁሉ አላህን ይፈሩ ዘንድ ለማስታወስ እወዳለው። ኢብኑ ዑመር ባስተላለፉት ዘገባ ዹአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋልፊ «...مَنْ قَالَ فِي مُ؀ْمِنٍ مَا لَيْسَ فِيهِ، أَسْكَنَهُ اللَّهُ رَدْغَةَ الْخََؚالِ حَتَّى يَخْرُجَ مِمَّا قَالَ». «በአንድ አማኝ ላይ ዚሌለበትን ዹተናገሹ ኚንግግሩ ጣጣ እስኪወጣ ድሚስ አላህ ዚ“ጥፋት ማጥ” ውስጥ ያኖሚዋል!» አሕመድ አቡ ዳዉድ እና ሌሎቜም ዚዘገቡት ትክክለኛ ሐዲሥ በሌላ አጋጣሚ ሰሓቊቜ «ዚ“ጥፋት ማጥ” (رَدْغَة الْخََؚالِ) ምንድነው?» ብለው ሲጠይቁ ነብያቜንም «ዚእሳት ነዋሪዎቜ እዥ!» ብለው መልሰዋል። ኢብኑ ማጃህ ﺃﻣﺎ ﻭﺍﻟﻠﻪ ﺇﻥ ﺍﻟﻈﻠﻢ ﺷﺆﻡ ï»­ï»» ﺯﺍﻝ ﺍﻟﻀﺎﻲء ﻫﻮ ﺍﻟﻈﻠﻮﻡ ﺇﻟﻰ ﺍﻟﺪﻳﺎﻥ ﻳﻮﻡ ﺍﻟﺪﻳﻊ ﻧﻀﻀﻲ ﻭﻋﻚﺪ ﺍﻟﻠﻪ ﺗﺠﺘﻀﻊ ﺍﻟﺚﺌﻮﻡ ﺳﺘﻌﻠﻢ ﻓﻲ ﺍﻟﺀﺎﺎﺏ ﺇﺫﺍ ﺍﻟﺘﻘﻎﻚﺎ ﻏﺪﺍ ﻋﻚﺪ ﺍﻟﻀﻠﻎﻚ ﻣﻊ ﺍﻟﻐﺞﻮﻡ

---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

እኛ እና መጅሊስ...እውነታና አሉባልታ! በኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሮንተር አስተባባሪነት ዹምናኹናውናቾው ዚዳዕዋና ዚተእሊም ስራዎቜ ዚሰዎቜ ጥሚት እና ስራ ስለሆበ ኚጉድለት ዚጠራ አይሆንም። ማንኛውም አይነት ገንቢ ሀሳብ እና እርምት ካለ በሩ ክፍት መሆኑን በተደጋጋሚ ዹተገለፀ ሲሆን ብዙዎቜም ይህንኑ ዚተናሱሕ አጋርነት በተግባር በማሳዚት ድንቅ ውጀት በታዚባ቞ው ዚዳዕዋ እንቅስቃሎዎቜ ላይ አወንታዊ ሚና ተጫውተዋል።  በተቃራኒውፀ አንዳንድ ወንድሞቜ ዚነሲሓ እና መተራሚም መንገዶቜን ወደጎን በመተው ባዶ ግምቶቜ ላይ ዹተመሰሹተ ፊትና ሲያራግቡ ቆይተዋል። ሌሎቹም ሳያጣሩ በጭፍን ወገንተኝነት ሀሰትን በማሰራጚት በመርኹዙ እንቅስቃሎዎቜ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ለመፍጠር ሰርተዋል። ዹመላው ሙስሊም ማህበሚሰብ ዚጋራ ተቋም ዹሆነውን መጅሊስ ተሀድሶ በተመለኹተ በሚደሹጉ ውይይቶቜ ላይ እንሳተፍ ዘንድ ኹተቋማዊ ለውጥ (ዘጠኙ) ኮሚ቎ ዹቀሹበውን ጥሪ በመቀበል በሁለት ንዑስ ኮሚ቎ዎቜ ውስጥ ተወካዮቜን አሳትፈናል። አላማቜን ኚአህባሜና ኚተለያዩ አካላት ተፅዕኖዎቜ ነፃ ሆኖ ብቃት ባላ቞ው ባለሞያዎቜ ዚሚመራ ኚሙስና ዚፀዳ አስተዳደራዊ መጅሊስ ይደራጅ ዘንድ አወንታዊ ተሳትፎ ማድሚግ ነበር። በመሆኑም ህገ መጅሊሱን ለማዘጋጀት ዹተቋቋመው ንኡስ ኮሚ቎ ተቋሙን ኚብልሹ አሰራር ሊጠብቅ ዚሚቜል ጠንካራ አደሚጃጀትን ይቀርፅ ዘንድ በተወካያቜን አማካኝነት ቀላል ዚማይባል አስተዋፅኊ አበርክተናል። በሌላኛው ንዑስ ኮሚ቎ ላይ ኚሌሎቜ ወንድሞቜ ጋር ዚተሳተፍኩ ሲሆን ዚኡለማዎቜ ዚትብብር ሰነዱ በሱፊያና አሜዓሪያ ቢድዓ ዚበላይነት ላይ ዹተመሰሹተ ተደርጎ እንዳይቀሚፅ በመሹጃ ሞግተናል። እውን ሆኖ ማዚት ስለምንፈልገው ገለልተኛ አስተዳደራዊ መጅሊስ ለሁሉም ወገኖቜ ግልፅ አድርገናል። በተለያዩ ምክንያቶቜ ዹምንፈልገውን ሁሉ ባናሳካም ቀላል ዚማይባል ውጀት ተገኝቷል። አልሐምዱላህ! ሆኖም አንዳንድ ወንድሞቻቜን ኚጅምሩ መሚጃዎቜን በማዛባትና አሉታዊ ቅርፅ በማስያዝ ‘ስልጣን ፍለጋ ኚአህባሜና ኚቢድዓ አራማጆቜ ጋር ተደመሩ’ ዹሚል ቜኮላ ዹወለደው ግምታዊ አሉባልታ ሲያሰራጩ ታዝበናል። ምንም እንኳ በወቅቱ ውይይቶቜ ባይቋጩም ለአንዳንዶቜ እውነታው ግልፅ ይሆን ዘንድ ለተቋማዊ ለውጥ ኮሚ቎ው በህዳር 2011 ለኮሚ቎ው ያቀሚብነውን ባለ 86 ገፅ ዶክሜንት ማብራሪያና ምክሹ ሀሳብ ይፋ አድርገናል። አስተያዚትና እርምት ካለ እንደምንቀበል ገልፀናል። (#በኢብኑ_መስኡድ_ዚዳዕዋና_ኢርሻድ_ኮሚ቎_ዹተዘጋጀ_ግምገማ_እና_እርምት https://goo.gl/o4nCKZ) ሰነዱ ፍትሀዊ ለሆነ ሁሉ እውነታውን ግልፅ በማድሚጉ ብዙዎቜ ብዥታውን በአደብ ስላጠራን ምስጋና አቅርበውልናል። አንዳንዶቜ ግን ዹመርኹዙን ስም ለማጥፋት አጋጣሚውን እንደ ልዪ እድል ዚቆጠሩት በሚያስመስል መልኩ እራሳ቞ውን ብቻ እያዳመጡ ቅጥፈቱን ቀጥለውበታል። ኚባጢል አራማጆቜ ጋር ኹፍተኛ ትንቅንቅ በነበሚባ቞ው ፈታኝ ግዜያት ካለማስተዋል በፀለምተኛ ምልኚታና ምዘና ተሳትፏቜንን አደጋ አድርገው በማቅሚብ ለባጢል ሰዎቜ ደጀን ሆነዋል። ቅጥፈቱ መደጋገሙን ተኚትሎ ምንም እንኳ ካሉብን ሰፊ ኃላፊነቶቜ አንፃር ግዜያቜንን በዚህ ማባኚኑ መልካም ሆኖ ባይታዚንምፀ በአሉባልታው ዚተወዛገቡ ወዳጆቻቜንን ለማገዝ ብሎም አንዳንዶቹ ኹመሹጃ እጥሚት ነገሮቜ ተመሳስለውባ቞ው ኹሆነ በማለት መርኹዝና_ዚመጅሊስ_ተሳትፎዎቜ በሚል እውነታውን ዚሚያብራራ መድሚክ አዘጋጅተናል። [ዚፕሮግራሙ ቅጂ በተኚታዩ ሊንክ ይገኛል https://t.me/merkezuna/70] በዚህ ሳንብቃቃ በቀጣይ በመስኚሚም 2012 በታተመው ነሲሓ መጜሔት ላይ በመርኹዙ ስራ አስኪያጅ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ተሰጥቶበታል። ኹዚህ ሁሉ ገለፃና ማብራሪያ በኋላ ምንም ሳያፍሩ ቅጥፈቱን ዚቀጠሉበት ወንድሞቜ (አላህ ይቅር ይበላቾውና) በውይይቱ ላይ ዚተነሱ ፎቶዎቜን መሹጃ በማድሚግ ተደመሩ ዹሚለውን አሉባልታ እውነታ በማስመሰል ተቆርቋሪነትን በሚያሳዩ ገለፃዎቜ ኚሜነው በዓሚብኛ ባዘጋጁት ዶክሜንት በሳውዲ ዚምናኚብራ቞ውን በርካታ ሞይኟቜ አመለካኚት ለመበሹዝ ጥሚት አድርገዋል። አልሐምዱሊላህ ታህሳስ 15/2012 በአላህ ፈቃድ እውነቱን ፍንትው አድርጎ ያሳዚ ባለ 30 ገፅ ዚዓሚብኛ ፅሁፍ አስነብበናል። [በተኚታዩ ሊንክ ይገኛል https://t.me/nesihaposts/2591] ኹላይ በተገለፀው መልኩ እውነታውን ካብራራን በኋላ በአንድ በኩልፀ ብዙሀኑን አዋም ህዝብ በዝርዝር ዚዳእዋ ጉዳዮቜና ውዝግቊቜ እንዲጠመዱ ማድሚግ ስለማይገባፀ በሌላ በኩል መርኹዙን በጠላትነት ዚሚመለኚቱና በዚህ አይነቱ እሰጥአገባ ተጠቃሚነትን ዚሚያልሙ አካላት ኚንቱ ፍላጎት ይመክን ዘንድ ነገሮቜን በትእግስት ስራቜን ላይ ብቻ በማተኮር ላለፉት ሁለት አመታት ቜላ ብለነዋል። በዚህ ዹሰኹነ አካሄድ በርካታ ጥሩ ውጀቶቜ ተገኝተዋል። አንዳንድ ሲተቹን ዚነበሩ ወንድሞቜ በአላህ ቜሮታ በግዜ ሂደት እውነታውን መሚዳታ቞ውን ማወቅ በራሱ በእጅጉ ያስደስታል። በአንፃሩ አሁንም ድሚስ ይህንን ግዜ ያለፈበት ቅጥፈት ዚሚያናፍሱ ኹዚህም አልፈው ቅጥፈቱን እውነት ብሎ ያልተቀበላ቞ውን ኚሱና መስመር ዚወጣ ሙብተዲዕ ነው እስኚማለት ዚደሚሱ ዹፋህም ምስኪኖቜ አሉ። አላህ ይድሚስላ቞ው ኚማለት ውጭ ልንሚዳ቞ው አንቜልም! በበኩላቜን፣ ለ1 አመት ኹመንፈቅ በትዕግስትና መሚጋጋት ዚዳሩተውሑድ ዹወቅፍ ፕሮጀክት ላይ በማተኮር ዚመጀመሪያውን ምዕራፍ በስኬት አጠናቀናል። ስኬት ኹአላህ ነውና ምስጋና ለእርሱ ብቻ ዚተገባው ነው። አልሐምዱሊላህ! በአላህ እገዛ ብዙ ዹተጠኑ ዚዳዕዋ እና ዚትምህርት እቅዶቜን ተፈፃሚ በማድሚግ በስኬት ላይ ስኬትን ለመጹመር ተደጋጋሚ ምክክሮቜን በማድሚግ ላይ እንገኛለን። ዹመርኹዙን ጉዞ ይበልጥ በማጠናኹር ዋነኛ ዚዳዕዋ መድሚካቜንን ነሲሓ ቲቪን ለማዘመንና ለማሳደግ በትጋት በመስራት ላይ ነን። በቀጣይ ዳሩል ሓዲስ ኮሌጅና ተያያዥ ዚትምህርት ተቋሞቜ፣ ቃፊላ ዚዳዕዋ ጉዞ፣ ዚተለያዩ ኮርሶቜና ዚዳዕዋ ስራዎቜ ያብቡ ዘንድ እንሰራለን። ኚያዝነው ታላቅ ዚዳዕዋ ራእይ እና በነፍስወኚፍ ኹተሾኹምናቾው ታላላቅ ኃላፊነቶቜ አንፃር ኢስላማዊ አደብን መሰሚት ላደሹገ ነሲሓ እንጂ ዚንትርክ አጀንዳ በመፍጠር እወቁን ለሚሉ ዹገደል ማሚ቎ዎቜ ምላሜ በመስጠት እንደማንጠመድ ሊታወቅ ይገባል። በዚሁ አጋጣሚ ሀሰት በማሰራጚት ዚተጠመዱ ሁሉ አላህን ይፈሩ ዘንድ ለማስታወስ እወዳለው። ኢብኑ ዑመር ባስተላለፉት ዘገባ ዹአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋልፊ «...مَنْ قَالَ فِي مُ؀ْمِنٍ مَا لَيْسَ فِيهِ، أَسْكَنَهُ اللَّهُ رَدْغَةَ الْخََؚالِ حَتَّى يَخْرُجَ مِمَّا قَالَ». «በአንድ አማኝ ላይ ዚሌለበትን ዹተናገሹ ኚንግግሩ ጣጣ እስኪወጣ ድሚስ አላህ ዚ“ጥፋት ማጥ” ውስጥ ያኖሚዋል!» አሕመድ አቡ ዳዉድ እና ሌሎቜም ዚዘገቡት ትክክለኛ ሐዲሥ ነውፀ አስ-ሰሒሓህ” ቁ. 437 ይመልኚቱ በሌላ አጋጣሚ ሰሓቊቜ «ዚ“ጥፋት ማጥ” (رَدْغَة الْخََؚالِ) ምንድነው?» ብለው ሲጠይቁ ነብያቜንም «ዚእሳት ነዋሪዎቜ እዥ!» ብለው መልሰዋል። ኢብኑ ማጃህ ﺃﻣﺎ ﻭﺍﻟﻠﻪ ﺇﻥ ﺍﻟﻈﻠﻢ ﺷﺆﻡ ï»­ï»» ﺯﺍﻝ ﺍﻟﻀﺎﻲء ﻫﻮ ﺍﻟﻈﻠﻮﻡ ﺇﻟﻰ ﺍﻟﺪﻳﺎﻥ ﻳﻮﻡ ﺍﻟﺪﻳﻊ ﻧﻀﻀﻲ ﻭﻋﻚﺪ ﺍﻟﻠﻪ ﺗﺠﺘﻀﻊ ﺍﻟﺚﺌﻮﻡ ﺳﺘﻌﻠﻢ ﻓﻲ ﺍﻟﺀﺎﺎﺏ ﺇﺫﺍ ﺍﻟﺘﻘﻎﻚﺎ ﻏﺪﺍ ﻋﻚﺪ ﺍﻟﻀﻠﻎﻚ ﻣﻊ ﺍﻟﻐﺞﻮﻡ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ ታህሳስ 5/2014

አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ ታህሳስ 5/2014 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

እኛ እና መጅሊስ...እውነታና አሉባልታ! በኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሮንተር አስተባባሪነት ዹምናኹናውናቾው ዚዳዕዋና ዚተእሊም ስራዎቜ ዚሰዎቜ ጥሚት እና ስራ ስለሆበ ኚጉድለት ዚጠራ አይሆንም። ማንኛውም አይነት ገንቢ ሀሳብ እና እርምት ካለ በሩ ክፍት መሆኑን በተደጋጋሚ ዹተገለፀ ሲሆን ብዙዎቜም ይህንኑ ዚተናሱሕ አጋርነት በተግባር በማሳዚት ድንቅ ውጀት በታዚባ቞ው ዚዳዕዋ እንቅስቃሎዎቜ ላይ አወንታዊ ሚና ተጫውተዋል።  በተቃራኒውፀ አንዳንድ ወንድሞቜ ዚነሲሓ እና መተራሚም መንገዶቜን ወደጎን በመተው ባዶ ግምቶቜ ላይ ዹተመሰሹተ ፊትና ሲያራግቡ ቆይተዋል። ሌሎቹም ሳያጣሩ በጭፍን ወገንተኝነት ሀሰትን በማሰራጚት በመርኹዙ እንቅስቃሎዎቜ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ለመፍጠር ሰርተዋል። ዹመላው ሙስሊም ማህበሚሰብ ዚጋራ ተቋም ዹሆነውን መጅሊስ ተሀድሶ በተመለኹተ በሚደሹጉ ውይይቶቜ ላይ እንሳተፍ ዘንድ ኹተቋማዊ ለውጥ (ዘጠኙ) ኮሚ቎ ዹቀሹበውን ጥሪ በመቀበል በሁለት ንዑስ ኮሚ቎ዎቜ ውስጥ ተወካዮቜን አሳትፈናል። አላማቜን ኚአህባሜና ኚተለያዩ አካላት ተፅዕኖዎቜ ነፃ ሆኖ ብቃት ባላ቞ው ባለሞያዎቜ ዚሚመራ ኚሙስና ዚፀዳ አስተዳደራዊ መጅሊስ ይደራጅ ዘንድ አወንታዊ ተሳትፎ ማድሚግ ነበር። በመሆኑም ህገ መጅሊሱን ለማዘጋጀት ዹተቋቋመው ንኡስ ኮሚ቎ ተቋሙን ኚብልሹ አሰራር ሊጠብቅ ዚሚቜል ጠንካራ አደሚጃጀትን ይቀርፅ ዘንድ በተወካያቜን አማካኝነት ቀላል ዚማይባል አስተዋፅኊ አበርክተናል። በሌላኛው ንዑስ ኮሚ቎ ላይ ኚሌሎቜ ወንድሞቜ ጋር ዚተሳተፍኩ ሲሆን ዚኡለማዎቜ ዚትብብር ሰነዱ በሱፊያና አሜዓሪያ ቢድዓ ዚበላይነት ላይ ዹተመሰሹተ ተደርጎ እንዳይቀሚፅ በመሹጃ ሞግተናል። እውን ሆኖ ማዚት ስለምንፈልገው ገለልተኛ አስተዳደራዊ መጅሊስ ለሁሉም ወገኖቜ ግልፅ አድርገናል። በተለያዩ ምክንያቶቜ ዹምንፈልገውን ሁሉ ባናሳካም ቀላል ዚማይባል ውጀት ተገኝቷል። አልሐምዱላህ! ሆኖም አንዳንድ ወንድሞቻቜን ኚጅምሩ መሚጃዎቜን በማዛባትና አሉታዊ ቅርፅ በማስያዝ ‘ስልጣን ፍለጋ ኚአህባሜና ኚቢድዓ አራማጆቜ ጋር ተደመሩ’ ዹሚል ቜኮላ ዹወለደው ግምታዊ አሉባልታ ሲያሰራጩ ታዝበናል። ምንም እንኳ በወቅቱ ውይይቶቜ ባይቋጩም ለአንዳንዶቜ እውነታው ግልፅ ይሆን ዘንድ ለተቋማዊ ለውጥ ኮሚ቎ው በህዳር 2011 ለኮሚ቎ው ያቀሚብነውን ባለ 86 ገፅ ዶክሜንት ማብራሪያና ምክሹ ሀሳብ ይፋ አድርገናል። አስተያዚትና እርምት ካለ እንደምንቀበል ገልፀናል። (#በኢብኑ_መስኡድ_ዚዳዕዋና_ኢርሻድ_ኮሚ቎_ዹተዘጋጀ_ግምገማ_እና_እርምት https://goo.gl/o4nCKZ) ሰነዱ ፍትሀዊ ለሆነ ሁሉ እውነታውን ግልፅ በማድሚጉ ብዙዎቜ ብዥታውን በአደብ ስላጠራን ምስጋና አቅርበውልናል። አንዳንዶቜ ግን ዹመርኹዙን ስም ለማጥፋት አጋጣሚውን እንደ ልዪ እድል ዚቆጠሩት በሚያስመስል መልኩ እራሳ቞ውን ብቻ እያዳመጡ ቅጥፈቱን ቀጥለውበታል። ኚባጢል አራማጆቜ ጋር ኹፍተኛ ትንቅንቅ በነበሚባ቞ው ፈታኝ ግዜያት ካለማስተዋል በፀለምተኛ ምልኚታና ምዘና ተሳትፏቜንን አደጋ አድርገው በማቅሚብ ለባጢል ሰዎቜ ደጀን ሆነዋል። ቅጥፈቱ መደጋገሙን ተኚትሎ ምንም እንኳ ካሉብን ሰፊ ኃላፊነቶቜ አንፃር ግዜያቜንን በዚህ ማባኚኑ መልካም ሆኖ ባይታዚንምፀ በአሉባልታው ዚተወዛገቡ ወዳጆቻቜንን ለማገዝ ብሎም አንዳንዶቹ ኹመሹጃ እጥሚት ነገሮቜ ተመሳስለውባ቞ው ኹሆነ በማለት መርኹዝና_ዚመጅሊስ_ተሳትፎዎቜ በሚል እውነታውን ዚሚያብራራ መድሚክ አዘጋጅተናል። [ዚፕሮግራሙ ቅጂ በተኚታዩ ሊንክ ይገኛል https://t.me/merkezuna/70] በዚህ ሳንብቃቃ በቀጣይ በመስኚሚም 2012 በታተመው ነሲሓ መጜሔት ላይ በመርኹዙ ስራ አስኪያጅ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ተሰጥቶበታል። ኹዚህ ሁሉ ገለፃና ማብራሪያ በኋላ ምንም ሳያፍሩ ቅጥፈቱን ዚቀጠሉበት ወንድሞቜ (አላህ ይቅር ይበላቾውና) በውይይቱ ላይ ዚተነሱ ፎቶዎቜን መሹጃ በማድሚግ ተደመሩ ዹሚለውን አሉባልታ እውነታ በማስመሰል ተቆርቋሪነትን በሚያሳዩ ገለፃዎቜ ኚሜነው በዓሚብኛ ባዘጋጁት ዶክሜንት በሳውዲ ዚምናኚብራ቞ውን በርካታ ሞይኟቜ አመለካኚት ለመበሹዝ ጥሚት አድርገዋል። አልሐምዱሊላህ ታህሳስ 15/2012 በአላህ ፈቃድ እውነቱን ፍንትው አድርጎ ያሳዚ ባለ 30 ገፅ ዚዓሚብኛ ፅሁፍ አስነብበናል። [በተኚታዩ ሊንክ ይገኛል https://t.me/nesihaposts/2591] ኹላይ በተገለፀው መልኩ እውነታውን ካብራራን በኋላ በአንድ በኩልፀ ብዙሀኑን አዋም ህዝብ በዝርዝር ዚዳእዋ ጉዳዮቜና ውዝግቊቜ እንዲጠመዱ ማድሚግ ስለማይገባፀ በሌላ በኩል መርኹዙን በጠላትነት ዚሚመለኚቱና በዚህ አይነቱ እሰጥአገባ ተጠቃሚነትን ዚሚያልሙ አካላት ኚንቱ ፍላጎት ይመክን ዘንድ ነገሮቜን በትእግስት ስራቜን ላይ ብቻ በማተኮር ላለፉት ሁለት አመታት ቜላ ብለነዋል። በዚህ ዹሰኹነ አካሄድ በርካታ ጥሩ ውጀቶቜ ተገኝተዋል። አንዳንድ ሲተቹን ዚነበሩ ወንድሞቜ በአላህ ቜሮታ በግዜ ሂደት እውነታውን መሚዳታ቞ውን ማወቅ በራሱ በእጅጉ ያስደስታል። በአንፃሩ አሁንም ድሚስ ይህንን ግዜ ያለፈበት ቅጥፈት ዚሚያናፍሱ ኹዚህም አልፈው ቅጥፈቱን እውነት ብሎ ያልተቀበላ቞ውን ኚሱና መስመር ዚወጣ ሙብተዲዕ ነው እስኚማለት ዚደሚሱ ዹፋህም ምስኪኖቜ አሉ። አላህ ይድሚስላ቞ው ኚማለት ውጭ ልንሚዳ቞ው አንቜልም! በበኩላቜን፣ ለ1 አመት ኹመንፈቅ በትዕግስትና መሚጋጋት ዚዳሩተውሑድ ዹወቅፍ ፕሮጀክት ላይ በማተኮር ዚመጀመሪያውን ምዕራፍ በስኬት አጠናቀናል። ስኬት ኹአላህ ነውና ምስጋና ለእርሱ ብቻ ዚተገባው ነው። አልሐምዱሊላህ! በአላህ እገዛ ብዙ ዹተጠኑ ዚዳዕዋ እና ዚትምህርት እቅዶቜን ተፈፃሚ በማድሚግ በስኬት ላይ ስኬትን ለመጹመር ተደጋጋሚ ምክክሮቜን በማድሚግ ላይ እንገኛለን። ዹመርኹዙን ጉዞ ይበልጥ በማጠናኹር ዋነኛ ዚዳዕዋ መድሚካቜንን ነሲሓ ቲቪን ለማዘመንና ለማሳደግ በትጋት በመስራት ላይ ነን። በቀጣይ ዳሩል ሓዲስ ኮሌጅና ተያያዥ ዚትምህርት ተቋሞቜ፣ ቃፊላ ዚዳዕዋ ጉዞ፣ ዚተለያዩ ኮርሶቜና ዚዳዕዋ ስራዎቜ ያብቡ ዘንድ እንሰራለን። ኚያዝነው ታላቅ ዚዳዕዋ ራእይ እና በነፍስወኚፍ ኹተሾኹምናቾው ታላላቅ ኃላፊነቶቜ አንፃር ኢስላማዊ አደብን መሰሚት ላደሹገ ነሲሓ እንጂ ዚንትርክ አጀንዳ በመፍጠር እወቁን ለሚሉ ዹገደል ማሚ቎ዎቜ ምላሜ በመስጠት እንደማንጠመድ ሊታወቅ ይገባል። በዚሁ አጋጣሚ ሀሰት በማሰራጚት ዚተጠመዱ ሁሉ አላህን ይፈሩ ዘንድ ለማስታወስ እወዳለው። ኢብኑ ዑመር ባስተላለፉት ዘገባ ዹአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋልፊ «...مَنْ قَالَ فِي مُ؀ْمِنٍ مَا لَيْسَ فِيهِ، أَسْكَنَهُ اللَّهُ رَدْغَةَ الْخََؚالِ حَتَّى يَخْرُجَ مِمَّا قَالَ». «በአንድ አማኝ ላይ ዚሌለበትን ዹተናገሹ ኚንግግሩ ጣጣ እስኪወጣ ድሚስ አላህ ዚ“ጥፋት ማጥ” ውስጥ ያኖሚዋል!» አሕመድ አቡ ዳዉድ እና ሌሎቜም ዚዘገቡት ትክክለኛ ሐዲሥ ነውፀ “ሲልሲለቱ’ል-አሓዲሥ አስ-ሰሒሓህ” (ቁ. 437) ይመልኚቱ።] በሌላ አጋጣሚ ሰሓቊቜ «ዚ“ጥፋት ማጥ” (رَدْغَة الْخََؚالِ) ምንድነው?» ብለው ሲጠይቁ ነብያቜንም «ዚእሳት ነዋሪዎቜ እዥ!» ብለው መልሰዋል። ኢብኑ ማጃህ ﺃﻣﺎ ﻭﺍﻟﻠﻪ ﺇﻥ ﺍﻟﻈﻠﻢ ﺷﺆﻡ ï»­ï»» ﺯﺍﻝ ﺍﻟﻀﺎﻲء ﻫﻮ ﺍﻟﻈﻠﻮﻡ ﺇﻟﻰ ﺍﻟﺪﻳﺎﻥ ﻳﻮﻡ ﺍﻟﺪﻳﻊ ﻧﻀﻀﻲ ﻭﻋﻚﺪ ﺍﻟﻠﻪ ﺗﺠﺘﻀﻊ ﺍﻟﺚﺌﻮﻡ ﺳﺘﻌﻠﻢ ﻓﻲ ﺍﻟﺀﺎﺎﺏ ﺇﺫﺍ ﺍﻟﺘﻘﻎﻚﺎ ﻏﺪﺍ ﻋﻚﺪ ﺍﻟﻀﻠﻎﻚ ﻣﻊ ﺍﻟﻐﺞﻮﻡ

🔗 ዚሙስሊም ወጣቶቜ ሚና እና ሃላፊነት 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 👌 ወጣቶቜ አድምጡ... አስተውሉ! 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/143 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts