የፍትህ መድረክ/justice forum
الذهاب إلى القناة على Telegram
በዚህ ቻናል ህግ ነክ ዜናዎች፣ ከህግ ጋር የተያያዙ የተመራረጡ ህግ ነክ ጽሁፎች ይቀርባሉ። "የተሻለች አለም እንድትኖረን ሁላችንም ለፍትህ እንቁም"!
إظهار المزيد2 676
المشتركون
+1824 ساعات
+217 أيام
+2630 أيام
أرشيف المشاركات
የአዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር በአዲሱ የትግራይ ክልል አዋጅ ተጠርጥረው ፍርድ ቤት ቀረቡ
የአዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሜዲሲን እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዲን የሆኑት ዶ/ር የማነ ገብረማርያም፤ በቅርቡ በትግራይ ክልል በወጣው አዋጅ ላይ የሚገኝን እና ከ15 ዓመት እስከ ሞት የሚያስቀጣ አንቀጽን በመጣስ ተጠርጥረው ፍርድ ቤት መቅረባቸውን ጠበቃቸው ለቢቢሲ ተናገሩ።
መርማሪ ፖሊስ፤ ዶ/ር የማነ "ከፌደራል መንግሥት እና ከሀራ መሬት ታጣቂዎች" ጋር ግንኙነት እንዳላቸው በመግለጽ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድለት መጠየቁንም ጠበቃው አስረድተዋል።
የአዲግራት ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር እና የሕጻናት ስፔሻሊስት የሆኑት ዶ/ር የማነ በቁጥጥር ስር የዋሉት ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ ሰኔ 27/2018 ዓ.ም. እንደሆነ የሥራ ባልደረቦቻቸው ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ዶ/ር የማነ በዕለቱ ወደ አዲስ አበባ ለመድረስ ከአዲግራት ከተማ ተነስተው ወደ መቀለ እየተጓዙ እንደነበረም ገልጸዋል።
የሕክምና ባለሙያው ጠበቃ ብርሃነ ገብረማርያም እንደሚገልጹት፤ ዶ/ር የማነ ወደ አዲስ አበባ ጉዞ የጀመሩት የአፍሪካ የሕክምና ትምህርት አህጉራዊ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ነበር። ሰኞ ዕለት በተጀመረው እና ዛሬ ረቡዕ ሐምሌ 1 በሚጠናቀቀው አህጉራዊ ጉባኤ መክፈቻ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ተገኝተዋል።
የትግራይ የሕክምና ማኅበርም እሁድ ሰኔ 28 ቀን የጤና ባለሙያውን እስር በተመለከተ ባወጣው መግለጫ፤ ዶ/ር የማነ ጉባኤው ላይ ለመሳተፍ እየተጓዙ እንደነበር ጠቅሷል። ሐኪሙ "በትግራይ የሕክምና እና አካዳሚክ ማኅበረሰብ ዘንድ እጅግ የታወቁ" እንደሆኑ የጠቀሰው ማኅበሩ፤ ለእስራቸው "ምንም ሕጋዊ ማብራሪያ አልቀረበም" ሲል ተችቷል።
ጠበቃው ብርሃነም በበኩላቸው፤ "ከአዲግራት ወጣ ብሎ ዕዳጋ ሐሙስ በሚባል ከተማ ነው የተያዙት። በመጀመሪያ ሲያዙ ምንም የተገለጸ ነገር የለም። ከላይ በተሰጠን ትዕዛዝ የሚል ምክንያት ብቻ ነው የተሰጣቸው" ሲሉ ዶ/ር የማነ የተያዙበትን ሁኔታ ገልጸዋል።
ጠበቃው እንደሚናገሩት፤ በትራፊክ ፖሊስ እና "በአንድ የፀጥታ ሰው" የተያዙት የሕጻናት ስፔሻሊስቱ፤ "ወደ አዲግራት የፖሊስ ጣቢያ ጽህፈት ቤት ጊዜያዊ ማቆያ ተወስደው" ታስረዋል። አብረዋቸው ተሽከርካሪው ውስጥ የነበሩ ሁለት ሰዎች መለቀቃቸውን አስረድተዋል።
ከተያዙ በኋላ ፍርድ ቤት አለመቅረባቸውን የሚናገሩት ጠበቃው፤ ፖሊስ "ከላይ የመጣ ትዕዛዝ ስለሆነ የእኔ እስረኛ አይደሉም፤ እዚያ ይቆዩ በሚል ነው የያዝኳቸው" የሚል ምላሽ መስጠቱን ገልጸዋል። ይህንን ተከትሎም "አካልን ነፃ የማውጣት ማመልከቻ" ለፍርድ ቤት መቅረቡን ተናግረዋል።
የአዲግራት ከተማ አንደኛ ደረጃ ፍርድ ቤት ሰኞ በዋለው ችሎት ጉዳዩን መመልከቱን ጠበቃው ገልጸዋል። በችሎቱ መርማሪ ፖሊስ የጤና ባለሙያው በቁጥጥር ስር የዋሉት "ከጠላት ጋር በመተባበር ወንጀል ስለጠረጠራቸው" እንደሆነ ማስረዳቱን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ጠበቃው ብርሃነ እንደሚገልጹት፤ ዶ/ር የማነ የተጠረጠሩበት ወንጀል በህወሓት ውሳኔ ወደ ሥራ የተመለሰው የትግራይ ክልል ምክር ቤት ግንቦት ላይ ያጸደቀውን "የትግራይ ሕዝብ ኅልውና እና ደኅንነትን ለማረጋገጥ የወጣ አዋጅ" በመጣስ ነው።
መርማሪ ፖሊስ "ከፌደራል መንግሥት እና እዚያ ሀራ መሬት ተብለው ከሚታወቁ፤ ራሳቸውን የትግራይ የሰላም ሠራዊት ብለው ከሚገልጹ ታጣቂዎች ጋር ግንኙነት አላቸው" ሲል ለፍርድ ቤት መናገሩን ጠበቃው ገልጸዋል። ወደ ታጣቂዎቹ "የሚሄዱ ሰዎችን እየመለመሉ ፈንድ እያደረጉ ይልካሉ" ማለቱንም አክለዋል።
ጠበቃው እንደሚያስረዱት መርማሪ ፖሊስ ተጥሷል ያለው የአዋጁን አንቀጽ 44 ላይ የሰፈረውን ድንጋጌ ነው። ይህ አንቀጽ "የጠላት ዓላማ እንዲሳካ በማሰብ፣ በማማከር፣ በመምራት፣ በማሰማራት፣ በመመልመል ወይም በተግባር ጠላት በመደገፍ" የሚፈጸሙ ወንጀሎችን የሚደነግግ ነው።
በዚህ አንቀጽ ጥፋተኛ ሆነው የሚገኙ ተከሳሾች ከ15 እስከ 25 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት እንደሚቀጡ፤ "አፈጻጸሙ ከባድ" ከሆነ ደግሞ በዕድሜ ልክ እስራት ወይም በሞት እንደሚቀጡ ደንግጓል።
በተጨማሪም አዋጁ ከ15 ዓመት በላይ በሚያስቀጡ ወንጀሎች ለተከሰሱ ሰዎች የዋስትና መብት እንደሚከለክል ጠበቃው አስረድተዋል።
በትናንቱ የችሎት ውሎ፤ መርማሪ ፖሊስ ተጨማሪ ምርመራ ለማድረግ የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ እንዲፈቀድለት ጠይቋል።
የዶ/ር የማነ ጠበቃ ይህ አዋጅ በራሱ "የግል ነፃነትን እና ሕገ መንግሥታዊ መብቶችን እንደሚጋፋ" እንዲሁም የወጣበት አግባብ "ሕገ መንግሥታዊ እንዳልሆነ" በመጥቀስ በፍርድ ቤት መከራከራቸውን ገልጸዋል። "እንዲሁም የድርጊቱ እና የተከሰሱበት አዋጅም ሁለቱም የማይገናኙ ስለሆነ በቂ የሆነ መጠርጠሪያ ምክንያት የላቸውም" የሚል መከራከሪያ አቅርበዋል።
በዚህም የተነሳ ፍርድ ቤት በዋስ ሊለቃቸው እና "አካልን ነፃ የማውጣት መብታቸው መከበር እንዳለበት" በማንሳት በችሎቱ መጠየቃቸውን ገልጸዋል።
የሁለቱን አካላት ክርክር የተመለከተው የአዲግራት ከተማ አንደኛ ደረጃ ፍርድ ቤት በጉዳዩ ላይ ብይን ለመስጠት ለዛሬ ረቡዕ ሐምሌ 1 ረፋድ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም፤ ችሎቱ ወደ ሚቀጥለው ሳምንት ሰኞ መዛወሩን ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ ጠበቃው የተሰጠው የቀጠሮ ቀን "ረጅም በመሆኑ ተሰብሮ እንዲታይ" ባስገቡት ማመልከቻ መሠረት፤ ለዛሬ ከሰዓት ሌላ ችሎት መቀጠሩን አስረድተዋል።
ቻናላችንን ለመቀላቀል ይህንንhttps://t.me/j_f125 ሊንክ ያስፈንጥሩ! በቻናላችን ላይ በምናቀርባቸው ህግ ነክ ጉዳዮችና ዜናዎች ላይ ሀሳብ፣ ጥቆማና ማንኛውንም አይነት ህግ ነክ ጥያቄዎችን ማቅረብ ሲፈልጉ ይህንን https://t.me/justice_forum_bot የቴሌግራም ቦት ሊንካችንን በማስፈንጠር ሊያገኙን ይችላሉ.
Chaanalii keenyatti makamuuf liinkii kana https://t.me/j_f125 tuqaa! Chaanalii keenya irratti dhimmoota seeraa fi oduuwwan dhiyeessinu ilaalchisee yaada, eeruu fi gaaffiiwwan seeraa kamiyyuu dhiyeessuu yoo barbaaddan, liinkii bootii Telegraamii keenya kana https://t.me/justice_forum_bot tuquun nu argachuu dandeessu.
የቤት ኪራይ ጭማሪ
" የ11.5% ጭማሪ አነስተኛ ይመስላል፤ በዓለምአቀፍ ደረጃ ሲታይ ግን እጅግ ከፍተኛ ጭማሪ ነው የተደረገው " - የኢትዮጵያ ሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት
👉 " ሞሎች፣ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ሥር ያሉ ሱቆች ቀድመው የገዙ የሚያከራዩበት ዋጋ ለመስማት የሚዘገንን ነው! "
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት አስተዳደር ቢሮ ዛሬ ጠዋት ይፋ ያደረገው የ11.5% የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ " እጅግ ከፍተኛ " ፣ " አብዛኛው ተከራይ ከፍተኛ ጭማሪ ከተደረበትና ከተፈናቀለ በኋላ ይፋ የተደረገ " በመሆኑ የዘገዬ ውሳኔ መሆኑን የኢትዮጵያ ሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት ለቲክቫህ ኢትዮጵያን ገለጸ።
የድርጅቱ መስራችና ዋና ዳይሬክተር አቶ ቁምላቸው አበበ በሰጡን ቃል፣ " 11.5% የሚለው ጭማሪ ከኛ ሀገር የዋጋ ግሽበት አንፃር ተመጣጣኝ ቢሆንም ከሌሎች ሀገራት ጋር ሲታይ ከፍተኛ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" በሌሎች ሀገራት የቤት ኪራይ ጭማሪ የሚደረገው ቤቱን ለማስጠገን የሚያስፈልግ ወጭ ታሳቢ ተደርጎ ከነጠላ አሀዝ ያላለፈ ጭማሪ ነው " ያሉት አቶ ቁምላቸው፣ " የኛ 11.5% ጭማሪ አነስተኛ ይመስላል፤ በዓለምአቀፍ ደረጃ ሲታይ ግን እጅግ ከፍተኛ ጭማሪ ነው የተደረገው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ለዛውም ለቤቶቹ ፦
- ጥገና ለማድረግ፣
- ቀለም ለመቀባት፣
- ቤት ውስጥ ያሉ ነገሮችን ለማስተካከል ጭምር ነው ? ጭማሪ የተደረገው የሚለው ሳይታሰብ ለዋጋ ግሽበት ብቻ የተደረገ ጭማሪ ነው " ብለውታል።
የከተማዋ ቤቶች ልማት አስተዳደር ደግሞ፣ ጭማሪው " በጥናት የተደገፈ ፣ የነዋሪውን የመክፈል አቅም ያገናዘበ ፣ አከራዮች ወቅታዊውን የኢኮኖሚ ሁኔታ ያገናዘበ ፍትሐዊ ገቢ እንዲያገኙ " የሚያስችል ብሎታል።
የሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት በሌላ በኩል፥ " የቢሮው ውሳኔ እንደ መነሻ ይበል የሚያሰኝ ቢሆንም፣ ማስተካከያው ይፋ መደረግ የነበረበት በግንቦትና ሚያዚያ ወር ነበር፤ በጣም የዘገየ ነው " ብሏል።
" አብዛኛው ተከራይ ከኪራይ ከተፈናቀለ፣ ከፍተኛ የኪራይ ጭማሪ ከተደረገበት በኋላ ነው ውሳኔው ይፋ የተደረገው " ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ተከራዮች በበኩላቸው፣ የኪራይ ጭማሪው 11.5% ሆኖ ከመወሰኑ በፊት ፦
• " ቤቴን ላድስ ነው"
• " ቤተሰብ ሊገባበት ነው " በሚል ሰበብ የተጋነነ ጭማሪ እንደተደረገባቸው ቅሬታ እያቀረቡ ሲሆን፣ ቲክቫህ ኢትዮጵያም ለዚህ ምን አይነት መፍትሄ ያስፈልጋል ? ሲል ድርጅቱን ጠይቋል።
የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ቁምላቸው አበበ፣ " የዚህ መመሪያ አንዱ ፈታኝ ነገር አፈጻጸሙ እንዴት ይሆናል ? እግር በእግር ተከታትሎ ማን ያስፈጽመዋል ? " የሚለው መሆኑን ገልጸው፣ ከዚህ በፊት ቤቱ ተከራይቶበት የነበረው ዋጋና አሁን ስንት እንደሚሆን ስለሚታወቅ የጭማሪው አፈጻጸም ስርዓታዊ እንዲሆን አሳስበዋል።
" ዛሬ ይፋ የሆነው ውሳኔ፣ እንዴት ይፈጸማል ? ማስፈጸሚያ ስልቱ ምንድን ነው ? የሚለው ግልጽ አይደለም " ብለው በጥናቱ ድርጅታቸው እንዳልተሳተፈ አመልክተዋል።
" እንዲህ አይነት ጥናቶች ሲደረጉ እንደ እኛ አይነት የሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅቶችን፣ ተከራዩን፣ አከራዩን በግልጽ ማወያየት ይገባል " ብለዋል።
ጉዳዩ በአከራዮችና ተከራዮች መካከል ጭቅጭቅ እንዳያስከትል አፈጻጸሙ ለወረዳ ብቻ ሳይተው የበላይ የመንግስት አካል መከታተል አለበት ባይ ናቸው።
ከ50 እስከ 100% ኪራይ ጭማሪ እንደተደረገ፣ በተለይ በጋራ መኖሪያ ቤቶች ፦
° ባለአንድ መኝታ ቤት ከ9፣ 10 ሺሕ ተነስቶ እስከ 22 ሺሕ ብር እንደደረሰ፤
° 15፣ 16 ሺሕ ብር ሲከራይ የነበረው ባለሁለት መኝታ ቤት 28፣ 30 ሺሕ መከራየትና መጠራት እንደተጀመረ ከዚህ ቀደም ማሳወቃቸውንም አስታውሰዋል።
" አሁን የወጣው ውሳኔ ቀድሞ ባስቸኳይ ይፋ እንዲደረግ፣ እርምጃ እንዲወሰድ አሳስበን ነበር " ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ " ያን ካሳሰብን በኋላ ዛሬ ይፋ የሆነው ውሳኔ የዘገዬ ነው " ሲሉም ተችተዋል።
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ በበኩሉ፣ " ዋጋ ጭማሪው እና የውል እድሳቱ መነሻ የሚሆነው ከዚህ ቀደም በነበረው ውል ላይ የተቀመጠው የኪራይ ዋጋ ብቻ ነው " ሲል አስታውቋል።
የሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት በሌላ በኩል በሰጠን ገለጻ፣ በቤት ኪራይ ብቻ ሳይሆን በሌሎች የመንግስት አገልግሎቶች፣ የንግድ ዘርፎች ላይ እንዲሁ ተመሳሳይ የዋጋ ጣሪያ የትርፍ ህዳግ ሊወሰን ይገባል ሲል በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሳስቧል።
የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ስለአጠቃላይ ችግሩና መፍትሄው አክለው ምን አሉ ?
" ለቤት ኪራይ መወደድ ትልቅ ጫና የፈጠረው በኮሪደር ልማቱ በርካታ ቤቶች ፈርሰው በቂ ተጨማሪ ቤት ባለመገንባቱ በቤት ኪራይ ላይ የመጣው ጫና ነው። ከፍተኛ የመኖሪያ ቤት እጥረት፤ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት፤ የኑሮ ውድነት አለ።
መንግስት በተለይ ለደመወዝተኛው የዋጋ ግሽበቱን ታሳቢ ያደረገ የደመወዝ ጭማሪ ሊያደርግ ይገባል። ላለው የዋጋ ግሽበት አንዱ ምክንያት የመኖሪያ ቤት እጥረት ነው። እጥረቱ በዘላቂነት ሊቀረፍ የሚችለው በተለያዩ አማራጮች መኖሪያ ቤቶችን በመገንባት ነው።
ሌላው ፥ በቤት ኪራይ ከፍተኛ ጭማሪ የሚያደርገው ህገወጥም፣ ህጋዊም ደላላ ነው። ከቤት ባለቤት ደውሎ 'ይህን ያህል ላከራይልህ' በማለት። ዘላቂው መፍትሄ በአከራይና ተከራይ መካከል ያለውን ደላላ በማስወጣት አከራዩ እና ተከራዩ የሚገናኝበትን የቴክኖሎጂ መተግበሪያ መዘርጋት ነው።
በተያያዘ፥ ከፍተኛ የቤት ግንባታ ማድረግ፤ የሊዝ ዋጋ መቀነስ ይገባል።
የኛ ሀገር ሊዝ እነ ኒዮርክ፣ ለንደን ያስከፍሉታል ከሚባለው አያንስም በሚል ነው የሚተቸው። ስለዚህ በካሬ ሜትር የሊዝ ዋጋ መቀነስና የመሬት አቅርቦቱን ሌሎች አማራጮችን ፈልጎ መፍትሄ ማማጣት ያስፈልጋል።
ያለው ችግር የመኖሪያ ቤት ብቻ አይደለም። የንግድ ቤቶችም በከፍተኛ ዋጋ ነው የሚከራዩት። በከፍተኛ ዋጋ የተከራየ ነጋዴ ባለሱቅ ያንን ዋጋ የሚጭነው ሸማቹ ላይ ነው። ሞሎች፣ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ሥር ያሉ ሱቆችን ቀድመው የገዙ ሰዎች የሚያከራዩበት ዋጋ ለመስማት የሚዘገንን ነው፤ ይሄ መስተካከል አለበት።
ለንግድ የኪራይ ቤቶችም ታሪፍና የዋጋ ጣሪያ ሊቀመጥ ይገባል " ብለዋል።
በሌላ በኩል ፥ " በአከራዮች ላይ በጣም ስለተጋነነ እንጅ አንዳንድ አከራዮች ደግሞ ልጆች የሚያስተምሩት ባለአንድ መኝታ ቤት ካላቸው ያን አከራይተው፣ ከከተማ ወጣ ያለ ቤት ተከራይተው ነው። የኑሮ ውድነቱ በአከራዩም በተከራዩም ስለሆነ ይህን ችግር ለመፍታት አስታራቂ መፍትሄ ያሻል " ሲሉ አስገንዝበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ሃምሌ 1 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
ቻናላችንን ለመቀላቀል ይህንንhttps://t.me/j_f125 ሊንክ ያስፈንጥሩ! በቻናላችን ላይ በምናቀርባቸው ህግ ነክ ጉዳዮችና ዜናዎች ላይ ሀሳብ፣ ጥቆማና ማንኛውንም አይነት ህግ ነክ ጥያቄዎችን ማቅረብ ሲፈልጉ ይህንን https://t.me/justice_forum_bot የቴሌግራም ቦት ሊንካችንን በማስፈንጠር ሊያገኙን ይችላሉ.
Chaanalii keenyatti makamuuf liinkii kana https://t.me/j_f125 tuqaa! Chaanalii keenya irratti dhimmoota seeraa fi oduuwwan dhiyeessinu ilaalchisee yaada, eeruu fi gaaffiiwwan seeraa kamiyyuu dhiyeessuu yoo barbaaddan, liinkii bootii Telegraamii keenya kana https://t.me/justice_forum_bot tuquun nu argachuu dandeessu.
በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 542 ሌላ ሰው ራሱን እንዲያጠፋ ማነሳሳትን ወይም መርዳትን ወንጀል ለማድረግ የተዘረጋ ሥርዓታዊ እና የሕግ ንድፈ-ሐሳብን የተከተለ መሣሪያ ነው። ራስን ማጥፋትን ከወንጀል ነፃ በማድረግ፣ ሕጉ በከባድ ጭንቀት ውስጥ ያሉ ግለሰቦችን ከመቅጣት ይቆጠባል። ይልቁንም፣ የመንግሥትን የቅጣት ኃይል ወደ ውጫዊ አጥፊዎች እና ደካማነትን ተጠቅመው ጉዳት ወደሚያደርሱ ኃይሎች ያዞራል።
በተቀረጸው የቅጣት እርከን አማካኝነት፣ ድንጋጌው በውጤት ላይ የተመሠረተ ተጠያቂነትን እና በመንግሥት የሚደረግን የጥበቃ ጣልቃ ገብነት በጥንቃቄ ያመጣጥናል። ከአገር በቀል ባህላዊ እሴቶች እና ከዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ግዴታዎች ጋር የተጣጣመው አንቀጽ 542፣ የሰውን ክብር ለማስከበር እና በማኅበረሰቡ ውስጥ በጣም ተጋላጭ የሆኑትን ወገኖች ለመጠበቅ የሚቆም ጠንካራ የሕግ ማዕቀፍ ነው።
ዋቢዎች
African Charter on Human and Peoples' Rights (adopted 27 June 1981, entered into force 21 October 1986) 1520 UNTS 217 (ACHPR)
Criminal Code of the Federal Democratic Republic of Ethiopia, Proc። No 414/2004
International Covenant on Civil and Political Rights (adopted 16 December 1966, entered into force 23 March 1976) 999 UNTS 171 (ICCPR)
Kenya National Commission on Human Rights & 2 Others v Attorney General, Director of Public Prosecution & 3 Others [2025] KEHC 6 (KLR) (Constitutional Petition E045 of 2022)
Mill JS, On Liberty (first published 1859, Stefan Collini ed, Cambridge University Press 1989)
National Assembly of Kenya, Report of the Departmental Committee on Justice and Legal Affairs on Public Petition No 13 of 2024 Regarding Decriminalization of Attempted Suicide (Parliament of Kenya 2025)
Penal Code of Kenya, Cap 63
Suicide Act 1961 (United Kingdom)
ማሳሰቢያ፦ ይህ ጽሑፍ የተዘጋጀው ለትምህርታዊ፣ ለአካዳሚክ እና ለአጠቃላይ መረጃ አገልግሎት ብቻ ሲሆን፣ ሙያዊ የሕግ ምክርን (legal advice) የሚተካ ወይም የሚወክል አይደለም። በጽሑፉ ውስጥ የቀረቡት ትንተናዎች፣ ድምዳሜዎች እና የሕግ ንጽጽሮች የአዘጋጁን ንባብና ምልከታዎች ብቻ የሚያንጸባርቁ ናቸው። አንባቢዎች ይህንን ጽሑፍ እንደ ቀጥተኛ የሕግ መመሪያ ወይም ዋቢነት ከመጠቀም እንዲቆጠቡ እና ከጉዳያቸው ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ተገቢውን የሕግ መፍትሔ ለማግኘት ፈቃድ ካላቸውና ብቁ ከሆኑ የሕግ ባለሙያዎች (legal professionals) ዘንድ ቀጥተኛ ሙያዊ ምክር እንዲያገኙ እንዲሁም ለምርምር ስራዎች አስተማማኝ ምንጮችን እንዲጎበኙ በጥብቅ ይመከራሉ!!
ይልቁንም የኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ ራስን እንዲያጠፋ ማነሳሳትን ወይም መርዳትን ራሱን የቻለ (sui generis) ወንጀል አድርጎ ይመለከተዋል። በዚህም ምክንያት የረዳቱ ድርጊት ወንጀለኛነት ቀጥተኛ እና መሠረታዊ ሲሆን፣ የሚመነጨውም የሰውን ሕይወት የመጠበቅ እና የመንከባከብን ማኅበራዊ እና ሕጋዊ ግዴታ በመጣሱ ነው።
፬. ባህላዊ እሴቶች እና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች መዋቅሮች
የአንቀጽ 542 መዋቅር የንድፈ-ሐሳብ ውጤት ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያን ማኅበራዊ እና ባህላዊ እሴቶች እንዲሁም ዓለም አቀፍ የሕግ ግዴታዎቿን በጥልቀት የሚያንጸባርቅ ነው ተብሎም ይታመናል።
ሀ. ማኅበራዊ-ባህላዊ እና ሃይማኖታዊ እሴቶች
በኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ውስጥ ልክ እንደ ሌሎች የአፍሪካ ማኅበረሰቦች፣ የሕይወት ቅድስና መሠረታዊ የሞራል መርሕ ነው። ይህ መርሕ የሰውን ሕይወት የማይደፈር ስጦታ አድርገው በሚመለከቱት በክርስትና እና በእስልምና ሃይማኖታዊ አስተምህሮዎች በጥልቀት የተደገፈ መሆኑ ሲገለፅም ይሰማል፤ ይታወቃልም። ራስን ማጥፋት በአገር በቀል እሴት እንደ ትልቅ ሀዘን ብቻ ሳይሆን በማኅበረሰቡ ላይ እንደተፈጸመ የሞራል ጥሰትም ይቆጠራል።
በተጨማሪም የአፍሪካ ሕግ ፍልስፍና በማኅበራዊ ኃላፊነት እና በጋራ መረዳዳት ላይ ያተኩራል። በዚህ መዋቅር ውስጥ ግለሰቦች ሙሉ በሙሉ የተነጠሉ ወኪሎች ሳይሆኑ የጋራ ማኅበረሰብ አባላት ተደርገው ይታያሉ ። ስለዚህ ሕጉ የጋራ እንክብካቤ ግዴታን ያስገድዳል፣ ይህም ኅበራዊ ደህንነትን የሚናጉትንና ሰዎችን ለራስ-ጥፋት የሚያነሳሱትን ይቀጣል።
ለ. ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ስምምነቶች
ከላይ በንዑስ ፊደል ‘ሀ’ ስር በአጭሩ ከተጠቀሱት የወንጀል ሕግ ፍልስፍናዊ መሠረቶች ባሻገር፣ የድንጋጌው ሰብዓዊና ሕጋዊ ዋጋ ይበልጥ ጎልቶ የሚታየው ከዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ስምምነቶች አንጻር ሲመረመር ነው ። ከዚህ አቅጣጫ ሲታይ፣ አንቀጽ 542 የኢትዮጵያ መንግሥት በዓለም አቀፍ ሕግ ያለበትን ግዴታ የሚወጣበት ዋነኛ መሣሪያ ሆኖ ያገለግላል። በተለይም፣ እንደ ዓለም አቀፉ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን (ICCPR) አንቀጽ 6 እና የአፍሪካ የሰዎችና የሕዝቦች መብቶች ቻርተር (ACHPR) አንቀጽ 4 ያሉ መሠረታዊ የሰብዓዊ መብቶች ሰነዶች መንግሥታት የሰውን ሕይወት የመጠበቅ ጥብቅ ግዴታ እንዳለባቸው በግልጽ ይደነግጋሉ።
ይህንን ዓለም አቀፋዊ መርሕ ይበልጥ ትርጉም ባለው መልኩ የሚያብራራው የሰብዓዊ መብቶች ሕግ ሥነ-አመክንዮ ሲሆን፣ የመንግሥት ሕይወትን የመጠበቅ ግዴታ አሉታዊ ብቻ ሳይሆን አወንታዊም ጭምር መሆኑን ያስረዳል። አሉታዊ ግዴታው መንግሥት ራሱ ወይም ወኪሎቹ የአንድን ግለሰብ ሕይወት ያለአግባብ ከመቅጠፍ እንዲቆጠቡ የሚፈልግ ሲሆን፤ አወንታዊ ግዴታው ደግሞ መንግሥት ግለሰቦችን በሶስተኛ ወገኖች ከሚደቀኑባቸው ማናቸውም አደጋዎች ለመጠበቅ የሚያስችሉ ተጨባጭ የሕግና የአስተዳደር ዋስትናዎችን በተግባር እንዲያዘጋጅ ያስገድዳል ። በመሆኑም የኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 542 ተጋላጭ የሆኑ ሰብዓዊ ሕይወቶች ላይ ከውጭ የሚሰነዘሩ አደጋዎችን በወንጀል በመቅጣት፣ ይህንን አወንታዊ የመንግሥት የጥበቃ ኃላፊነት በተግባር የሚተርጉም ዋነኛውና ቀዳሚው የሕግ ዋስትና ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል ነው።
፭. ንጽጽራዊ ገጽታዎች
የኢትዮጵያን የወንጀል ሕግ ድንጋጌዎች ይዘትና ስፋት ይበልጥ ግልጽ በሆነ መልክ ለመገምገም፣ ጉዳዩን ከሌሎች የሕግ ሥርዓቶች ንጽጽራዊ ተሞክሮ አንጻር መመልከት እጅግ ጠቃሚ ነው ። ከዚህ ንጽጽራዊ ትንተና በግንባር ቀደምትነት የምናገኘው የዩናይትድ ኪንግደምን የሕግ ሥርዓት ሲሆን፣ አገሪቱ በ1961 በወጣው የራስ-ማጥፋት ሕግ (Suicide Act 1961) አማካኝነት ድርጊቱን ከወንጀል ሕግ ሙሉ በሙሉ የለየች ቢሆንም፣ በሶስተኛ ወገን የሚደረግን እርዳታ ለመከላከል ግን እስከ 14 ዓመት የሚደርስ ከፍተኛ ጽኑ እስራት አስቀምጣለች። ይህ ዓለም አቀፋዊ አዝማሚያ እንደሚያሳየው አብዛኞቹ ዘመናዊ የሕግ ሥርዓቶች ራስን ማጥፋት የፈጸመውን ግለሰብ ከመቅጣት ይልቅ፣ በድርጊቱ ጀርባ ያለውን የሶስተኛ ወገን ማነሳሳትና መርዳት የሕይወትን ቅድስና ለመጠበቅ ሲሉ በከፍተኛ ሁኔታ መቅጣታቸውን ቀጥለዋል፡፡
ይህንን የግል ነፃነት እና የመንግሥት የጥበቃ ሚና የማመጣጠን ጉዳይ በተመለከተ፣ እንደ ጀርመን እና ካናዳ ያሉ የሕግ ሥርዓቶች ረቂቅና ልዩ የሆኑ አቀራረቦችን ይከተላሉ። ለምሳሌ የጀርመን ሕግ በተደራጀ መልኩ ራስን ማጥፋትን መርዳትን የሚከለክል ቢሆንም፣ የግለሰቡን የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት ከመንግሥት የጥበቃ ግዴታ ጋር ለማመጣጠን ይሞክራል ። በሌላ በኩል ደግሞ፣ የካናዳ ሕግ በሕክምና የታገዘ ሞትን (MAID) ለአዋቂዎች በከፍተኛ ጥንቃቄና በጥብቅ የሙያ ሁኔታዎች ሥር ቢፈቅድም ከዚህ የሕግ ማዕቀፍ ውጭ የሚደረግን ማናቸውንም የራስ-ማጥፋት እርዳታ ግን አሁንም በከባድ የወንጀል ተጠያቂነት ይቀጣል።
በምሥራቅ አፍሪካ ቀጠና የጎረቤታችንን የኬንያን የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ተሞክሮ ስንመለከት ደግሞ ጉዳዩ በቅኝ ግዛት ውርስ እና በቅርብ ጊዜ በተደረጉ አበረታች የሕግ ማሻሻያዎች መካከል ያለውን ታሪካዊ ሽግግር በጥልቀት ያሳያል። ለብዙ አሥርተ ዓመታት የኬንያ የወንጀል ሕግ ራስን የማጥፋት ሙከራን እንደ መለስተኛ ወንጀል (misdemeanor) በመቁጠር እስከ ሁለት
ዓመት የሚደርስ እስራትን ይደነግግ የነበረ ሲሆን፣ ይህም በስነ-አእምሮአዊ ቀውስ ውስጥ ያሉ ዜጎችን ከደህንነት ይልቅ በድጋሚ ለቅጣትና ለማኅበራዊ መገለል የሚዳርግ ጊዜ ያለፈበት አቀራረብ ነበር። ይሁን እንጂ፣ ጥር 9 ቀን 2025 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) የኬንያው ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሕገ-መንግሥታዊ ትርጉም መርሆዎችን መሠረት በማድረግ ይህንን ድንጋጌ ውድቅ ያደረገበትን ታሪካዊ ውሳኔ አስተላልፏል። ፍርድ ቤቱ ራስን የማጥፋት ሙከራን በወንጀል መቅጣት ሰብዓዊ ክብርን፣ እኩልነትን እና ዜጎች በሕገ-መንግሥቱ የተረጋገጠላቸውን ከፍተኛ የጤና ደረጃ የማግኘት መብት የሚጥስ መሆኑን በመወሰን፣ ጉዳዩ ከወንጀል ፍትሕ ይልቅ በሕዝብ ጤና ማዕቀፍ መታየት እንዳለበት ወስኗል። ይህ የፍርድ ቤት ውሳኔ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ፓርላማ ውስጥ እየተካሄደ ላለው የሕግ ማሻሻያ ረቂቅ የጀርባ አጥንት በመሆን፣ ኬንያን ከቅጣት ይልቅ ለሰብዓዊ ክብርና ለጤና እንክብካቤ ቅድሚያ ወደሚሰጥ ተራማጅ የሕግ ሥርዓት በማሸጋገር ላይ የሚገኝ መሆኑ እየተገለፀ ይገኛል።
ከእነዚህ ዓለም አቀፋዊ ተሞክሮዎች ጋር ሲነጻጸር፣ የኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ ድንጋጌ ልዩ መለያ ሆኖ የሚጠቀሰው በተጎጂው ተጋላጭነት ደረጃ ላይ ያደረገው ግልጽ የሕግ ትኩረት ነው። አብዛኞቹ አገሮች እርዳታ ወይም ማነሳሳትን በጠቅላላ የወንጀል ድንጋጌ ብቻ ሲቀጡ፣ የኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ ግን በተለየ ሁኔታ በተጎጂው አቅመ-ቢስነት (እንደ ሕፃናት፣ የአእምሮ በሽተኞች
እና አረጋውያን) ላይ የተመሠረተ ግልጽ የቅጣት እርከን መዘርጋቱ በንጽጽር ሲታይ የላቀ ኅበራዊ ጥበቃን የሚያረጋግጥ ሥርዓታዊ አካሄድ ያሳያል ተብሎ ሊገለፅ የሚችል ነው።
፮. ማጠቃለያ
source #Almaw Wolie(Advocate and Legal Consultants at law) faacebook page.
ራስን ከማጥፋት ሙከራ እስከ ሦስተኛ ወገን ተጠያቂነት፡- የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 542 እና የኬንያ አዲሱ የሕግ ሽግግር
፩. መግቢያ
የወንጀል ሕግ በተለይም የአንድ ግለሰብ ምርጫ ወደ ራስ-ጥፋት በሚያመራበት ጊዜ፣ በግለሰቡ የግል ነፃነት እና በመንግሥት የጥበቃ ጣልቃ ገብነት መካከል ያለውን የሞራል እና የሕግ ገደብ ለመወሰን ረጅም ዘመናትን የታገለ ጉዳይ ነው። በኢትዮጵያ የሕግ ሥርዓት ውስጥ፣ ይህ ውጥረት በ2004 (1997 ዓ.ም) በወጣው የወንጀል ሕግ አንቀጽ 542 ሥር ሌላ ሰው ራሱን እንዲያጠፋ ማነሳሳት ወይም መርዳትን ወንጀል በማድረግ ጥልቅ በሆነ መንገድ ተቀምጧል። በ1949ኙ የወንጀል ህግም በአንቀፅ 525 ስር ተቀምጦ ይገኝ ነበር፡፡
ራስን የማጥፋት ሙከራን በወንጀል ከሚቀጡ የቀድሞ የኮመን ሎው (common law) እና የሲቪል ሎው (continentallaw) ስርዓቶች በተለየ፣ የወቅቱ የኢትዮጵያ ሕግ ራስን ጥፋት የተለመደ የወንጀል ጥፋት ሳይሆን ከፍተኛ የስነ-ልቦና ቀውስ ውጤት መሆኑን ይገነዘባል። በዚህም ምክንያት የቅጣት መሣሪያው ትኩረት የሚያደርገው በጭንቀት ውስጥ ባለው ግለሰብ ላይ ሳይሆን፣ ድርጊቱን ባመቻቹ ወይም ባበረታቱ ሶስተኛ ወገኖች ላይ ነው። ይህ ጽሑፍ አንቀጽ 542ን የሕግ አካላት፣ የፍልስፍና መሠረቶች እና የቅጣት እርከኖችን ከንጽጽራዊ እና ከሰብዓዊ መብቶች አንጻር በአጭር ይፈተሻል፡፡
፪.የአንቀጽ 542 አወቃቀርና ይዘት
የኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 542 የተጠያቂነትን ወሰን በሁለት መሠረታዊ ንዑሳን ድንጋጌዎች በመክፈል፣ የአጥፊውን የቅጣት ደረጃ በተጎጂው የመወሰን አቅም እና በድርጊቱ የመጨረሻ ውጤት ላይ በመመሥረት ይደነግጋል ። በዚህም መሠረት፣ ንዑስ-አንቀጽ አንድ ሙሉ የሕግ ችሎታና አቅም ያላቸውን አዋቂ ተጎጂዎችን የሚመለከት ሲሆን፣ ድንጋጌው ማነሳሳትን እና መርዳትን/ማገዝን እንደ ሁለት የተለያዩ የራስ-ጥፋት ተባባሪነት ዓይነቶች ይለያል። እዚህ ላ፣ ማነሳሳት ተጎጂው ራሱን እንዲያጠፋ ለማድረግ የታለመ ልዩ የወንጀል ሐሳብን (dolus) በመያዝ ሆን ብሎ ማነቃቃትን፣ ማበረታታትን ወይም ማሳመንን የሚጠይቅ ሲሆን፤ መርዳት ወይም ማገዝ ደግሞ ድርጊቱን ለማመቻቸት ቁሳዊ እርዳታን (ለምሳሌ ገዳይ መሣሪያዎችን ማቅረብ) ወይም የሞራል ድጋፍን መስጠትን ያካትታል። በዚህ መደበኛ ተጠያቂነት ሥር የሚወሰነው ቅጣት በውጤት ላይ የተመሠረተ ነው፤ በተጎጂው የተደረገው ራስን የማጥፋት ሙከራ ሳይሳካ ሲቀር አጥፊው በቀላል እስራት የሚቀጣ ሲሆን፣ ድርጊቱ ተፈጽሞ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ግን ቅጣቱ እስከ አምስት ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ይከብዳል።
በሌላ በኩል፣ ንዑስ-አንቀጽ ሁለት በተጎጂው ስነ-አእምሮአዊ እና አካላዊ ተጋላጭነት ላይ በመመሥረት የተደነገገ ልዩ የቅጣት ማክበጃ ነው። ድንጋጌው ጥበቃ ለሚያስፈልጋቸው እንደ ሕፃናት፣ የአእምሮ በሽተኞች እና በዕድሜ መግፋት (እርጅና) ምክንያት የመወሰን አቅማቸውን ላጡ አቅመ-ቢስ ወገኖች የሚተገበር ሲሆን፤ በእነዚህ ግለሰቦች ላይ የተደረገው ራስን የማጥፋት ሙከራ ለአጥፊው እስከ አምስት ዓመት የሚደርስ ጽኑ እስራት የሚያስከትል ሲሆን፣ ድርጊቱ ተፈጽሞ የመጨረሻውን የሞት ውጤት በሚያስከትልበት ጊዜ ግን የአጥፊው ተጠያቂነት እስከ አሥር ዓመት ጽኑ እስራት እንዲደርስ ይደረጋል ። ይህ የተቀናጀ የቅጣት እርከን ሕጉ ለደረሰው የመጨረሻ ጉዳት ክብደት እንዲሁም ለተጎጂው ተጋላጭነት ደረጃ የሚሰጠውን ጥልቅ እና ሚዛናዊ ትኩረት ያሳያል።
ሕግ አውጪው እነዚህን ሁኔታዎች ለይቶ በመደንገግ፣ የአጥፊው የሞራል ጥፋተኝነት ደረጃ ከተጎጂው ተጋላጭነት ስፋት እና ከድርጊቱ የመጨረሻ ውጤት ጋር በቀጥታ የተቆራኘ መሆኑን ያረጋግጣል። ይህንን ዝርዝር የተጠያቂነት እና የቅጣት መዋቅር ተከትሎ የሚነሳው ወሳኝ ጥያቄ፣ ራሱን ያጠፋውን ወይም ለመሞት የሞከረውን ግለሰብ ከቅጣት ነፃ በማድረግ፣ ድርጊቱን ያመቻቸውን ወይም ያነሳሳውን ሶስተኛ ወገን ግን በወንጀል ለመቅጣት የተወሰነበት ሰብአዊና ፍልስፍናዊ መነሻ ምንድን ነው? የሚለው ነው። በዚህ ረገድ የተደነገገውን የሕግ አቅጣጫ በተገቢው መንገድ ለመረዳት፣ ድንጋጌው የተመሠረተባቸውንና የተሟላ ትርጉም የሚሰጡትን በርካታ የወንጀል ሕግ፣ የስነ-ወንጀል ጥናት (criminology) እና የሰብዓዊ መብቶች ንድፈ-ሐሳቦችን በጥልቀት መመርመር አስፈላጊ ይሆናል።
፫. የአንቀጽ 542 ፍልስፍናዊ እና ሰብዓዊ መብቶች መሠረቶች:-ንድፈ-ሐሳቦች
ከእነዚህ መሠረታዊ ንድፈ-ሐሳቦች መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚነሳው የጆን ስቱዋርት ሚል የጉዳት መርሕ (Harm Principle) ነው። ሚል "በነፃነት ላይ" (On Liberty) በተሰኘው ታዋቂ ሥራው ላይ በግልጽ እንደ አስረዳው፣ መንግሥት በማንኛውም የሰለጠነ ማኅበረሰብ አባል ላይ ካለው ፍላጎት ውጭ የመንግሥትን አስገዳጅ ኃይል በሕጋዊ መንገድ ሊጠቀም የሚችለው በሌሎች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመከላከል ብቻ ነው። ራስን ማጥፋት በራስ ላይ ብቻ የሚደርስ ጉዳት እንደመሆኑ፣ በገዛ ፈቃዱ ሕይወቱን ለማጥፋት በሞከረ ግለሰብ ላይ የሕጉ ጣልቃ ገብነት እንደ ሥልጣን ማለፍ የሚቆጠር ቢሆንም፤ አንድ 3ኛ ወገን ድርጊቱን ሲያነሳሳ ወይም ሲረዳ ግን፣ ሂደቱ ከግል ምርጫነት ባለፈ ውጫዊ እና ጎጂ የሆነ አካል መኖሩን የሚያስተዋውቅበት ሁኔታ ይፈጠራል። በመሆኑም፣ በአንቀጽ 542 ሥር የተደነገገው የመንግሥት ጣልቃ ገብነት ሕጋዊ መሠረት ያገኛል፤ ምክንያቱም ሕጉ ራሱን የጎዳውን ግለሰብ ከመቅጣት ይልቅ፣ ሌላውን ሰው ለከፋ ጉዳት ያጋለጠውን 3ኛ ወገን ለመከላከልና ለመገደብ ያለመ ነው።
ይህንን የግል ነፃነት ወሰን ተከትሎ የሚነሳውና ድንጋጌውን ይበልጥ የሚያጠናክረው ሌላው ወሳኝ ጽንሰ-ሐሳብ የወንጀል ጥበቃ (paternalism) እና ተጋላጭ ወገኖችን የመከላከል ግዴታ ነው። ዘመናዊው የወንጀል ሕግ ለግል ነፃነት ክብር ቢሰጥም፣ ይህ ነፃነት ግን ገደብ የለሽ አይደለም ። የሕግ ሥርዓቶች ትክክለኛ፣ ነፃ እና ምክንያታዊ ውሳኔ ለመስጠት የአእምሮ ብስለት፣ የአእምሮ ጤና እና ስሜታዊ መረጋጋት ቀዳሚ መሥፈርቶች መሆናቸውን በጥልቀት ይገነዘባሉ። በመሆኑም፣ እንደ ሕፃናት፣ አረጋውያን ወይም የአእምሮ በሽተኞች ያሉ የግለሰቡ የመወሰን አቅም የሚዳከምባቸው ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ፣ መንግሥት የግለሰቦቹን መብት ለመጠበቅ የጥበቃ (paternalistic) አቋም ይይዛል ። በእነዚህ ሁኔታዎች ውስጥ፣ ሕጉ ተጎጂው ለራስ-ጥፋት የሰጠው "ስምምነት" በሕግ ፊት ፈጽሞ ዋጋ እንደሌለው ይቆጥረዋል፤ በዚህም ምክንያት 3ኛውን ወገን እንደ ተራ ወንጀል ተባባሪ ሳይሆን፣ የሰውን ስነ-ልቦናዊ እና አካላዊ ደካማነት ለራስ ዓላማ የተጠቀመ በዝባዥ አድርጎ ይፈርጀዋል።
በመጨረሻም የድንጋጌው ልዩ የሕግ ባህሪ ይበልጥ ጎልቶ የሚታየው ከተለመደው የተባባሪነት ንድፈ-ሐሳብ የሚለይበትን መንገድ ስንመረምር ነው። በተለመደው የሕግ አስተሳሰብ፣ የተባባሪ ተጠያቂነት ብዙውን ጊዜ ጥገኛ/ተቀጥላ (derivative) ነው፤ ይህም ማለት ረዳቱ ወይም አነሳሺው የሚቀጣው ዋናው አጥፊ የፈጸመው ድርጊት ወንጀል ሆኖ ሲገኝ ብቻ ነው ። አንቀጽ 542 ግን ከዚህ የጥገኝነት ሞዴል ፍጹም ይለያል። ራስን ማጥፋት በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ ሥር ወንጀል ስላልሆነ፣ አነሳሺው ወይም ረዳቱ ጥፋታቸውን ከተጎጂው ድርጊት ሊያገኙት አይችሉም።
ይህ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የተሰጡ አስገዳጅ የወንጀል ሕግ ትርጉም ውሳኔዎችን በየጉዳዩ አደራጅቶ የያዘ ልዩ እትም ነው።
እትሙ በየካቲት 2018 ዓ.ም የታተመ ሲሆን፣ ከአውሮፓ ሕብረት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ በባለሙያዎች ቡድን የተዘጋጀ የመጀመሪያ እትም ነው።
ስለዚህ ልዩ እትም ዝርዝር ማብራሪያና ይዘት እንደሚከተለው ቀርቧል፦
1. የልዩ እትሙ ዋና ዓላማና ጠቀሜታ
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ከበደ በገለጹት መልዕክት መሠረት፣ የሰበር ሰሚ ችሎት አስገዳጅ ውሳኔዎችን አሳትሞ ማሰራጨት የፍርዶችን ይፋዊ ይዘት ለመረዳት፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ለማስፈን ከፍተኛ ፋይዳ አለው። የዚህ ልዩ እትም ዋና ዋና ጠቀሜታዎች የሚከተሉት ናቸው፦
ወጥ የሕግ አተረጓጎም ማረጋገጥ፦ በመላ አገሪቱ በሚገኙ ማናቸውም ደረጃ ላይ ያሉ የፌዴራልም ሆነ የክልል ፍርድ ቤቶች ዘንድ ወጥና ተገማች የሆነ የሕግ አተረጓጎም ሥርዓት እንዲኖር ያደርጋል።
ውጤታማነትና ወጪን መቀነስ፦ የሕግ ክርክሮች በአጭር ጊዜና በአነስተኛ ወጪ እንዲቋጩ ከመረዳቱም በላይ፣ ዐቃቢያነ ሕግ ክስ ከመመስረታቸው በፊት ቀደሞ የተሰጡ ውሳኔዎችን መርምረው ተገቢና ብልህ ውሳኔ ለመወሰን ያስችላቸዋል።
የሥነ-ሕግ ዕውቀትን ማዳበር፦ ለሕግ ትምህርት፣ ለምርምር እንዲሁም ሕጎች በተግባር በሰዎች ዕለት ከዕለት ኑሮ ላይ የሚያስከትሉትን ውጤት ለመፈተሽና ለመመርመር ከፍተኛ ሚና አለው።
የተደራጀና ተደራሽ መሆን (የእትሙ ልዩ እሴት)፦ ከዚህ ቀደም የሰበር ውሳኔዎች በቅጽ መልክ ሲታተሙ የወንጀልና የፍትሐብሔር ጉዳዮች ተደባልቀው ይወጡ ስለነበር ፈልጎ ማግኘት አስቸጋሪ ነበር። ይህ እትም ግን ውሳኔዎችን በወንጀል ዓይነትና በሕጉ ፍሰት መሠረት በማደራጀት፣ ተመሳሳይ ውሳኔዎችን በአንድ ላይ በማሰናዳትና ተዛማጅ ጉዳዮችን በግርጌ ማስታወሻ በማጣቀስ ተጠቃሚዎች በቀላሉ እንዲያገኟቸው የተለየ እሴት ጨምሯል።
2. የመጽሐፉ መዋቅርና ይዘት
መጽሐፉ በባለሰባትና በባለአምስት የሰበር ዳኞች የተሰጡ 86 ማይልስቶን (መሠረታዊ) ውሳኔዎችን ከነሙሉ ይዘታቸው ያካተተ ሲሆን፣ በአራት ዋና ዋና ምዕራፎችና በ45 ክፍሎች የተዋቀረ ነው፦
ምዕራፍ አንድ - የወንጀል ሕግ የጠቅላላ ድንጋጌ ክፍል የሰበር ሕግ ትርጉም ውሳኔዎች፦ ይህ ምዕራፍ በ13 ክፍሎች የተደራጀ ሲሆን፣ የወንጀል ሕግ መርሆዎችን (እንደ አንድ ሰው በአንድ ወንጀል ድጋሚ እንዳይከሰስና እንዳይቀጣ የሚከለክለውን መብትና የሕጋዊነት መርህን)፣ የፍርድ ቤቶችን የስረ-ነገር ሥልጣን፣ የወንጀል አፈጻጸም ደረጃዎችንና ተካፋይነትን፣ የቅጣት አወሳሰን መመሪያዎችን፣ ንብረት መውረስንና ቅጣትን መገደብን (ማገድን) የመሳሰሉ ጠቅላላ መርሆዎችን ያብራራል።
ምዕራፍ ሁለት - የወንጀል ሕግ የልዩ ክፍል የሰበር የሕግ ትርጉም ውሳኔዎች፦ በሕጉ ልዩ ክፍል ሥር የተዘረዘሩ የተወሰኑ ወንጀሎችን የሚመለከት ሲሆን፤ በመንግሥትና በሕዝብ ጥቅም ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን (የከበሩ ማዕድናት በሕገ-ወጥ መንገድ ማዘዋወር፣ የሥራ ኃላፊነትን አለመወጣት፣ ሐሰተኛ ምስክርነትና ፍርድ ቤትን መድፈር)፣ በሰው ሕይወት፣ አካልና ነጻነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን (የሰው ግድያ፣ ከባድና ቀላል አካል ጉዳት፣ ሰዎችን ለሥራ ወደ ውጭ በሕገ-ወጥ መንገድ መላክ)፣ እንዲሁም በንብረትና በሩካቤ ሥጋ ነጻነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን (ስርቆት፣ እምነት ማጉደል፣ ማታለልና በቂ ስንቅ የሌለው ቼክ ማውጣት) ያካትታል።
ምዕራፍ ሶስት - በልዩ ልዩ አዋጆች ላይ የተሰጡ አስገዳጅ የሰበር የሕግ ትርጉም ውሳኔዎች፦ ከዋናው የወንጀል ሕግ ውጭ በልዩ ልዩ አዋጆች ሥር የተደነገጉ ወንጀሎችንና የተሰጡ አስገዳጅ ትርጉሞችን ይዟል። ከነዚህም መካከል የሽብር ወንጀል፣ የሰዎች ዝውውርና ድንበር ማሻገር፣ የሙስና ወንጀል አዋጅ (የተከሳሽን ሐሳብ የማስረዳት ሸክም ወደ ተከሳሹ የሚዞርበትን ሁኔታ)፣ የቴሌኮሙኒኬሽን፣ የታክስ አስተዳደር (ሐሰተኛ የግብር ደረሰኝ) እና የጉምሩክ አዋጆችን፣ የባንክ ሥራ፣ የሊዝ አዋጅ (የከተማ ቦታ ወረራ)፣ የጦር መሣሪያ ቁጥጥር፣ እና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጆችን የተመለከቱ ውሳኔዎች ይገኙበታል።
ምዕራፍ አራት - በወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕግ ላይ የተሰጡ የሰበር የሕግ ትርጉም ውሳኔዎች፦ የወንጀል የፍርድ ሂደትን የሚመሩ ድንጋጌዎች ትርጉም ሲሆን፤ የፖሊስ ምርመራን (ለፖሊስ የተሰጠ የእምነት ቃል፣ የኢግዚቢት አመላለስ፣ የብርበራ ሕጋዊነት)፣ የዋስትና መብት መፈቀድና መከልከልን፣ የክስ አዘገጃጀት፣ ማሻሻልና ወደ ሌላ ስፍራ ማዛወርን፣ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያና የእምነት ክህደት ቃልን፣ የማስረጃ አቀራረብና ምዘናን፣ እንዲሁም ተከሳሽ በሌለበት ክርክር ስለመቀጠልና የይግባኝ/ሰበር አቤቱታ ሥነ-ሥርዓቶችን ያጠቃልላል።
3. የመጽሐፉ ልዩ የአጠቃቀም መመሪያዎች
ጭብጥና የግርጌ ማስታወሻ፦ በእያንዳንዱ የክፍል ወይም ንዑስ ክፍል ርዕስ ስር የውሳኔዎቹ ዋና ጭብጥ ይገኛል። በጭብጡ መጨረሻ ላይ የተቀመጡት የግርጌ ማስታወሻዎች ከዋናው ውሳኔ ጋር ተመሳሳይ ወይም ተያያዥ የሆኑ ሌሎች የሰበር ውሳኔዎችን ዝርዝር ይጠቁማሉ። ይህ አንባቢው በሌሎች ታተሙ ቅጾችና ድረ-ገጾች ያሉ ተመሳሳይ ውሳኔዎችን በቀላሉ አውጥቶ እንዲጠቀም ጥቆማ ይሰጣል።
የተለያዩ የሕግ አቋሞች ማሳያ፦ ምንም እንኳ ያልተለመደ ቢሆንም፣ አልፎ አልፎ በተመሳሳይ ጉዳይ ላይ የተለያየ አቋም የተያዘባቸው የሕግ ትርጉሞች (ለምሳሌ ስለ ተደራራቢ ወንጀሎች ወይም ስለ ቅጣት መገደብ) ሲያጋጥሙ፣ አዘጋጆቹ ለማስተያየት እንዲረዳ በአቋም የተለዩትን ውሳኔዎችም በልዩ ሁኔታ አመልክተዋል።
የመፈለጊያ ቃላት (Index)፦ አንባቢዎች ከዋናው ማውጫ በተጨማሪ በመጽሐፉ መጨረሻ ክፍል ላይ ያለውን የቃላት መፈለጊያ እንደ ጠቋሚ በመጠቀም ስለሚፈልጉት ጉዳይ የተጻፈበትን ቦታ በቀላሉ ማወቅ ይችላሉ።
ይህ ልዩ እትም ለዳኞች፣ ለዐቃቢያነ ሕግ፣ ለጠበቆች፣ ለሕግ ተመራማሪዎችና ፍላጎት ላላቸው ዜጎች የወንጀል ፍትሕ አስተዳደሩን ሥረ-ነገርና ሥነ-ሥርዓታዊ ሕጋዊ አተረጓጎም በጥራት፣ በግልጽነትና በተደራጀ መልኩ ለመረዳት የሚያስችል ወሳኝ የሕግ መጽሐፍ ነው።
ይህንን ልዩ እትም ለማግኘት ቀጥሎ ያለውን ሊንክ ያስፈንጥሩ!
https://t.me/j_f125/9725
በማህበራዊ ፍርድ ቤት የተሰጠ ውሳኔ በመደበኛ ፍርድ ቤት አዲስ ክስ እንዳይቀርብ በ "Res Judicata" (በፍርድ አልቋል) መርህ ሊያግደው አይችልም። ሰበር መ.ቁ 256261
አንድ ጉዳይ በማህበራዊ ፍርድ ቤት ታይቶ ውሳኔ ካገኘ በኋላ፣ ያው ጉዳይ በድጋሚ በመደበኛ ፍርድ ቤት አዲስ ክስ ሆኖ ሲቀርብ "በፍርድ አልቋል" (Res Judicata) ተብሎ ውድቅ ሊደረግ አይገባም። ጉዳዩ በመደበኛው ፍርድ ቤት ታይቶ ውሳኔ ሊሰጥበት ይገባል፤ ለዚህም የሰበር ሰሚ ችሎት ያስቀመጣቸው ዋና ዋና ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው፡
የዳኞች የህግ እውቀት ውስንነት፡በማህበራዊ ፍርድ ቤት የሚሰየሙ ዳኞች መደበኛ የህግ ትምህርትና እውቀት የሌላቸው፣ ይልቁንም በሰፈር ልምድና በባህላዊ የግልግል መንገድ የሚወስኑ በመሆናቸው ውሳኔያቸው ከመደበኛ ፍርድ ቤት የህግ ትንተና ጋር እኩል ሊታይ አይችልም።
የቀድሞው የሰበር ውሳኔ ልዩነት፡"ስልጣን በሌለው ፍርድ ቤት የተሰጠ ውሳኔ በይግባኝ ደረጃውን ጠብቆ ካልተሻረ የፀና ፍርድ ነው" የሚለው የቀድሞው የሰበር ህግ ትርጉም፣ ጉዳዩ በመደበኛ ፍርድ ቤቶች መካከል የተደረገን ክርክር መሰረት አድርጎ የተሰጠ ነው። ስለዚህ ይህ የህግ ትርጉም በቀጥታ ከመደበኛ ፍርድ ቤት ውጭ ለሆኑት ለማህበራዊ ፍርድ ቤቶች ተፈጻሚነት አይኖረውም።
Join👉https://t.me/binimoslawyer
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ ሥነ- ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ የአሰልጣኞች ሥልጠና መስጠት ተጀመረ
************************
የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ-ሥርዓት ሕግን በመተካት መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጸደቀውን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1410/2018 በአግባቡ ለማስፈጸም የሚያስችል የቅድመ-ትግበራ ዝግጅት አካል የሆነና ለአምስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የአሰልጣኞች ሥልጠና ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ተጀምሯል።
በመድረኩ መክፈቻ ላይ ይህ ከብዙ ዓመታት ጥረት በኋላ የጸደቀው የሕግ መድብል በአገሪቱ የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ውስጥ የነበሩ በርካታ መሠረታዊ ክፍተቶችን የሚሞላና የወንጀል ፍትሕ ስርዓቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሰረታዊ የወንጀል ፍትሕ ሪፎርም መሆኑ ተገልጿል።
በዚህ ረገድ ሕጉ የታለመለትን ስትራቴጂካዊ ግብ ይመታ ዘንድ የፍትሕ አካላት ባለሙያዎችን አቅም ማጎልበት፣ ወጥ አረዳድ መፍጠር እና የተቀናጀ አሠራርን መዘርጋት የላቀ ሚና እንዳለው የተጠቆመ ሲሆን፣ ዛሬ የተጀመረው የአሰልጣኞች ሥልጠናም በቀጣይ በፌዴራልና በክልሎች ለሚሰጡ አገር አቀፍ ሥልጠናዎች አሰልጣኞችን ለማዘጋጀት ታሳቢ ያደረገ መሆኑ ተመላክቷል።
በዛሬው የመጀመሪያ ቀን የሥልጠና ውሎ በአዲሱ የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ ውስጥ የተካተቱ መሠረታዊ ፅንሰ-ሐሳቦች፣ ዋና ዋና ለውጦች፣ መርሆዎች ፣ የፍትሕ ተቋማት ስልጣን እና የዳኝነት የስልጣን ድልድል ላይ ያተኮረ ሰፊ ገለጻ ከተደረገ በኋላ የወንጀል ምርመራና የማስረጃ አሰባሰብ ላይ ስልጠና መስጠት ተጀምሯል።
ሥልጠናው በቀጣይ ቀናት በዋስትና እና በምርመራ መዝገብ ላይ በዐቃቤ ሕግ የሚሰጡ ውሳኔዎችን፣ ክስ መስማት፣ ማስረጃ፣ አማራጭ ቅጣት እና ልዩ ሥነ-ስርዓት፣ ፍርድ እና ቅጣት፣ የይግባኝ፣ የሰበር እና ፍርድን በድጋሚ የማየት ስርዓት እንዲሁም በወንጀል ጉዳይ ዓለም ዓቀፍ ትብብር ላይ ሕጉን በማርቀቅ ሂደት በተሳተፉ እና በዘርፉ በማስተማር፣ በምርምር፣ በወንጀል ምርመራ፣ ክርክር እና ውሳኔ በመስጠት የካበተ ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች ስልጠና እንደሚሰጥ ታውቋል።
የስልጠና መድረኩን የፍትሕ ሚኒስቴር ከአውሮፓ ሕብረት ጋር በመተባበር አዘጋቶታል፡፡
የፍትሕ ሚኒስቴርን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆችን እና ድረ-ገፅን ይቀላቀሉ
Website
https://www.justice.gov.et
Facebook
https://www.facebook.com/MOJEthiopia/
(x) Twitter
https://x.com/MOJEthiopia
YouTube channel
https://youtube.com/@fdreministryofjustice...3701...
Telegram
https://t.me/fdreattorneyGeneral_externabo
Qajeelfama_Kenna_Hayyama_Mirkaneessa_Gahumsa_Dandeettii_Daldala.pdf17.78 MB
Akkaataa Labsii Liizii Lafa Magaalaa Lkk 721/2004tti Namni Lafa Magaalaa Liiziin Fudhatee Ijaarsa Eegalee Garuu Akkaataa Waliigalteetti Otuu HinXumurin Hafe Mirga Akkamii Qabaata? Ijaarsi Eegalame 10% ol yoo ta’e Caalbaasiin Nama Biraatti Darbuu Nidanda’aa?
==================================
Labsii Liizii Lkk 721/2004 kwt 23(7(a)) fi 23 (3); Murtii Mana Maree Federeeshiinii glme Lkk 824/16 ta’erratti gaafa 25/10/2016 kenname ilaala.
==================================
Karaalee lafti magaalaa itti argatame keessaa inni duraa fi ijoon liizii ta’uu fi Innis waliigaltee qaama Lafa bulchu waliin taasifamu hordofee tajaajila/misooma barbaadameef akka oolu kan taasifamu akka ta’e Labsii liizii Lkk 721/2004 Seensa isaa fi tumaalee rogummaa qaban biroo irraa nihubatama. Akkaatuma kanaan Lafa liiziin fudhatame irratti ijaarsi yoom eegaluu fi xumuramuu akka qabu, daangaa yeroo jedhame keessatti eegalamuu ykn xumuramuu yoo hafe bu’aa akkamii akka hordofsiisus labsichi bal’inaan diriirsuun tumee jira. Kana keessaa Bu’aan inni tokko yeroo daangaa yeroo ijaarsichi itti eegalamuu ykn xumuramuu qabutti raawwatamuu hafe qaamni bulchiinsaa qabeenya irra jiru irraa kaasisee laficha deebisee fudhachuu akka danda’u labsicha kwt 23 jalatti tumamee argama.
Akkaataa tumaa labsicha keewwattoota olitti caqafamanitti ijaarsi laficha irratti eegalame 10% ol yoo ta’e nama ittifufee xumuruu danda’utti caalbaasii ifaan gurguramuudhaan gatii argame irraa baasiin raawwachiisa caalbaasiif bahe hir’ifamee kaan namnicha waliigalteen liizii isaa adda cite abbaa qabeenyichaaf deebi’uu akka qabu labsicha kwt 23(7(a) fi 23(3) jalatti tumamee jira.
Haata’u malee Manni Maree Federeeshiinii Murtii glme Lkk 824/16 ta’erratti gaafa 25/10/2016 kenneen mirgi abbaa qabeenyummaa lafaa kan ummataa fi mootummaa ta’uu fi namni dhuunfaa mirga qabeenya irratti horachuu fi fayyadamuu qofa akka qabu Heera Mootummaa kwt 40(1) fi (6) jalatti kan tumame irraa kan hubatamu ta’uu bal’inaan xiinxaluudhaan, namni lafa liiziin fudhatee ijaarsa yeroo jedhametti raawwachuu hafe waliigalteen isaa adda citee ijaarsi on qabeenyi laficha irratti horate yoo jiraate qaama walaba ta’een tilmaamamee mootummaan bifa beenyaan kanfalameefii laficha gad-lakkisuu akka qabuu fi;
Kanaan alatti sababa ijaarsa dhibbentaa 10 ol ijaaree jira jedhuun caalbaasiin akka Nama dhuunfaatti lafti darbu tumaan Labsii Liizii Lkk 721/2004 kwt 23(7(a)) fi 23(3) ajaju mirga abbaa qabeenyummaa Saboota, sablammootaa fi Ummattootaa Heeraan eegame kan miidhuu fi faallaa heeraa waan ta’eef raawwatiinsa hinqabu jechuun murteessee jira.
https://t.me/speaklawinabsentia
ባጠቃላይ፣ እነዚህን የተጠቀሱ የላቁ የቴክኒክ ዘዴዎችንና አማራጮችን በመጠቀም በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) መተግበሪያን በተሳካ ሁኔታና በተሻለ ፍጥነት ማስተግበር ይቻላል። የጂሾና የሌሎች ስክሪን አንባቢዎች ተጠቃሚዎች እነዚህን መንገዶች እንዲሞክሯቸው እመክራለሁ። በቀጣይ መተግበሪያው በባንኩ በኩል ቢሻሻል እንኳ፣ ይህ በፍጥነት የመጠቀም ልምድ ለሌሎች ፍጥነትን ለሚሹ መተግበሪያዎች ጠቃሚ ስንቅ ይሆንዎታል። መሠረታዊ መብቶቻችንን ለማስከበር የሚደረገው ሕጋዊ ውትወታና ትግል እንደቀጠለ ሆኖ፣ ከትግሉ ጎን ለጎን ራሳችንን ከቴክኖሎጂው ዕድገት ጋር እያላመድን መሄድ ይኖርብናል።
በቻናላችን ላይ በምናቀርባቸው ሕግ ነክ ጉዳዮችና ዜናዎች ላይ ተጨማሪ ሐሳብ፣ ጥቆማና ማንኛውንም ዓይነት የሕግ ጥያቄዎችን ማቅረብ ሲፈልጉ ከታች ያሉትን ይፋዊ የመገናኛ መስመሮቻችንን መጠቀም ይችላሉ፦
የቴሌግራም ቻናላችንን ለመቀላቀል ይህንን ሊንክ ያስፈንጥሩ፦ https://t.me/j_f125
ማንኛውንም ዓይነት ሕግ ነክ ጥያቄዎችን ለማቅረብ ይህንን የቴሌግራም ቦት ሊንክ ያስፈንጥሩ፦ https://t.me/justice_forum_bot
Chaanalii keenyatti makamuuf liinkii kana https://t.me/j_f125 tuqaa! Chaanalii keenya irratti dhimmoota seeraa fi oduuwwan dhiyeessinu ilaalchisee yaada, eeruu fi gaaffiiwwan seeraa kamiyyuu dhiyeessuu yoo barbaaddan, liinkii bootii Telegraamii keenya kana https://t.me/justice_forum_bot tuquun nu argachuu dandeessu.
በመተግበሪያው ላይ በዋናነት የተስተዋሉ የተደራሽነት ክፍተቶች የሚከተሉት ናቸው፦
ከኪቦርድ የአጻጻፍ ስልት ጋር አለመጣጣምና የጊዜ ገደብ (Timeout) ችግር፦ ደንበኞች የገንዘብ ማንቀሳቀስ ሂደቱን እንደጀመሩ፣ መተግበሪያው ከጥቂት ሰከንዶች ቆይታ በኋላ በድንገት ወደኋላ ተመልሶ ፒን ኮድ (PIN Code) እንድናስገባ ይጠይቃል። ይህ የሰከንዶች መቆራረጥ ሂደቱን ደጋግሞ የሚያስጀምር በመሆኑ የገንዘብ ዝውውር ማድረግን ፈጽሞ የማይቻል አድርጎታል።
ያልተሰየሙ አዝራሮች (Unlabelled Buttons)፦ በመተግበሪያው ውስጥ ያሉ አንዳንድ ወሳኝ ቁልፎች በእስክሪን አንባቢው አይነበቡም። ለምሳሌ ያህል፣ የደህንነት ሚስጥር ቁጥርን ለመቀየር ወደ "Change PIN" ክፍል ውስጥ በሚገባበት ጊዜ፣ አዝራሮቹ ስም ስለሌላቸው (Unlabelled) ዓይነ-ስውራን ደንበኞች ፒናቸውን መቀየር አልቻሉም።
ይህ ችግር ከተከሰተ በኋላ፣ በአንዳንድ ብርቱ ግለሰቦችና በኢትዮጵያ ዓይነ-ስውራን ብሔራዊ ማኅበር (ENAB) ጥረትና ውትወታ፣ መተግበሪያው ከእስክሪን አንባቢ ጋር እንዲጣጣም ተደርጎ ዳግም እንዲሻሻል ለባንኩ ጥያቄ ቀርቧል። በዚህም መሠረት ለ iPhone (iOS) ተጠቃሚዎች ማሻሻያው የተለቀቀ ቢሆንም፣ ለአንድሮይድ (Android) ተጠቃሚዎች ግን መተግበሪያው ለዳግም ግምገማ ወደ ጎግል (Google Play Store) ተልኮ ከ72 ሰዓታት በኋላ እንደሚለቀቅ ከማኅበሩ የቴሌግራም ገጽ ለማወቅ ተችሏል። ይሁን እንጂ እስካሁን ድረስ የአንድሮይድ ማሻሻያ በይፋ አልተለቀቀም፤ ባንኩም በማኅበራዊ ትስስር ገጾቹም ሆነ በየሳምንቱ በሚያቀርባቸው የሚዲያ መግለጫዎች ላይ ስለዚህ ጉዳይ የሰጠው ይፋዊ ማብራሪያ የለም።
፬. መተግበሪያውን በተሻለ ፍጥነት ለመጠቀም የሚያስችሉ ጊዜያዊና አማራጭ መፍትሔዎች
ባንኩ መተግበሪያውን ሙሉ በሙሉ አሻሽሎ እስኪለቅ ድረስ፣ ዓይነ-ስውራን ደንበኞች የዕለት ከዕለት የባንክ ፍላጎቶቻቸውን ለማሟላትና የፒን ኮድ ጊዜ ገደብ (Timeout) ችግርን ለመቋቋም የሚረዱ በርካታ የተሞከሩና ውጤታማ የሆኑ አማራጭ ዘዴዎችን መጠቀም ይችላሉ።
፩. የስክሪን ሪደር ቅንብርን ማስተካከል (One-Touch / Single Tap)
ይህ መፍትሔ በተለይ የጂሾ (Jieshuo) ስክሪን አንባቢ ተጠቃሚዎችን በእጅጉ ይረዳል። አፕሊኬሽኖችን በሁለት ንክኪ (Double Tap) ከመክፈት ይልቅ በአንድ ንክኪ (Single Tap) እንዲሠሩ ማድረግ ትልቅ ጊዜ ይቆጥባል። ይህንን ለማድረግ የሚከተሉትን ቅደም-ተከተሎች ይከተሉ፦
ወደ Operation Settings ይግቡ።
Clicking Settings የሚለውን ይምረጡ።
በመቀጠል Lift up to activate controls የምትለዋን ምርጫ ያብሩ (Check ያድርጉ)።
ይህንን ስናደርግ ፒን ኮድ ስናስገባም ሆነ እንደ ‘CBE Transfer’ ያሉ አገልግሎቶችን ስንመርጥ፣ ጣታችንን ቁጥሩ ወይም ጽሑፉ ላይ አድርገን ልክ ስናነሳው (Lift ስናደርግ) ወዲያውኑ ክሊክ ያደርጋል። እያንዳንዱን ነገር ደብል ታፕ በማድረግ የሚባክነውን ወሳኝ ሰከንድ በማስቀረት ከጊዜ ገደቡ (Timeout) ቀድመን እንድንሠራ ይረዳናል።
፪. የስዋይፕ (Swipe) አጠቃቀምን መቀየር እና የአዝራሮችን ቦታ ማጥናት
በተለምዶ የምንፈልገውን ቁልፍ ለማግኘት ስክሪኑን ደጋግመን ስዋይፕ እናደርጋለን፤ ይህ ደግሞ በርካታ አዝራሮችን እንድናልፍ ስለሚያስገድደን ጊዜ ይወስዳል። በሱ ምትክ፦
አዝራሮቹ በስልኩ ስክሪን ላይ የት አካባቢ እንደሚገኙ (ከላይ፣ ከታች፣ ግራ ወይም ቀኝ) አስቀድሞ በማጥናት በሕሊና መቅረፅ።
በግራና ቀኝ ስዋይፕ ከመዳሰስ ይልቅ፣ ጣትን በስክሪኑ ላይ ቀጥታ በማንሸራተት (Explore by touch) የምንፈልገውን ቁልፍ ወዲያውኑ ማግኘት። ይህ ልምድ ከላይ ከተጠቀሰው 'One-touch' አሠራር ጋር ሲጣመር የሥራ ፍጥነታችንን በእጅጉ ይጨምረዋል።
፫. ለፈጣን አጠቃቀም የሚረዱ ተጨማሪ አማራጭ መፍትሔዎች (Advanced Workarounds)
ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪ፣ ዓይነ-ስውራን ደንበኞች መተግበሪያውን ይበልጥ ፈጣን በሆነ መንገድ ለመጠቀም የሚከተሉትን ተጨማሪ ስልቶች መተግበር ይችላሉ፦
የአጭር ቁጥር (USSD *889#) ኮድን እንደ አማራጭ መጠቀም፦ የሞባይል መተግበሪያው በማሻሻያ ምክንያት ሙሉ በሙሉ ለአጠቃቀም አስቸጋሪ በሚሆንበት ጊዜ፣ የባንኩን የ USSD ኮድ (*889#) መጠቀም እጅግ አስተማማኝ አማራጭ ነው። የ USSD ይዘቶች ቀለል ያሉ የጽሑፍ ዝርዝሮች (Plain Text Menus) በመሆናቸው ስክሪን አንባቢዎች ያለምንም መቆራረጥና ያለምንም የፒን ታይም-አውት ችግር በከፍተኛ ፍጥነት ያነቧቸዋል።
ቁልፎችን መሰየም: (Custom Labeling)፦
በመተግበሪያው ውስጥ ስም የሌላቸው አዝራሮች (Unlabelled Buttons) ሲያጋጥሙ፣ የ Jieshuo ወይም የ TalkBack የላቁ ቅንብሮችን በመጠቀም ለአዝራሮቹ የራስዎን ስም (ለምሳሌ፡ "Confirm" ወይም "Change PIN") ለቁልፉ መስጠት ይችላሉ። ይህንን ለማድረግ አዝራሩ ላይ በመቆም በቶክባክ ሲሆን፣ ጣትዎን ከቀኝ ወደላይ በማሰስ ቶክባክ ሜኑን በመክፈት አድ ሌብል የሚለውን በመጫን ለቁልፉ ስያሜ መስጠት ይቻላል።
በጂሽዎ ሲሆን ደግሞ ኖድ ኤሊያስ ኤዲቲንግ የሚለውን በመጫን ለቁልፉ ስያሜን መስጠት ይቻላል።
የቅንጥብ ሰሌዳ (Clipboard) እና አስቀድሞ የተዘጋጀ ጽሑፍን መጠቀም፦ የሂሳብ ቁጥሮችን (Account Numbers) አንድ በአንድ በእጅ መተየብ ጊዜ ስለሚወስድና ለታይም-አውት ችግር ስለሚያጋልጥ፣ በተደጋጋሚ ገንዘብ የሚልኩላቸውን የሂሳብ ቁጥሮች በስልኮ ማስታወሻ (Notes) ወይም በስክሪን አንባቢው የቅንጥብ ሰሌዳ (Clipboard History) ላይ አስቀድመው ያስቀምጡ። ሂደቱን ሲጀምሩ የሂሳብ ቁጥሩን በቀጥታ ኮፒ-ፔስት (Copy-Paste) በማድረግ የሰከንዶች ዕድሜ ማዳን ይቻላል።
፭. የባንክ ሥርዓቶችን ተደራሽ ለማድረግ ለቀጣይ የሚበጁ ስትራቴጂካዊ የውሳኔ ሐሳቦች
የተደራሽነት ቀውስ በየጊዜው እንዳይከሰትና ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክና ሌሎች የፋይናንስ ተቋማት የሚከተሉትን ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች መውሰድ ይኖርባቸዋል፦
አካታች ዲዛይን (Inclusive Design) መከተል፦ ማንኛውም የሶፍትዌር ማሻሻያ ከመደረጉ በፊት፣ የዕቅድና የዲዛይን ሂደቱ የአካል ጉዳተኞችን ፍላጎት ያማከለ መሆኑን ማረጋገጥ።
ከተጠቃሚዎች ጋር ቅድመ-ፍተሻ (User Testing) ማድረግ፦ አዳዲስ መተግበሪያዎች ለሕዝብ ይፋ ከመደረጋቸው በፊት፣ ዓይነ-ስውራንና ሌሎች አካል ጉዳተኞች በተገኙበት በተግባር ተፈትነው ማረጋገጫ ማግኘት አለባቸው።
የባለሙያዎች ስልጠና፦ የባንኩ የሶፍትዌር መሐንዲሶችና የዲጂታል ምርት አዘጋጆች ስለ WCAG 2.1 መመሪያዎችና ስለ ረዳት ቴክኖሎጂዎች (Assistive Technologies) አሠራር በቂ ሥልጠና ሊኖራቸው ይገባል።
ማጠቃለያ እና ማኅበራዊ ትስስር (Conclusion & Social Links)
የዲጂታል ባንክ አገልግሎቶችን ለዓይነ-ስውራን ተደራሽ የማድረግ ሕጋዊ ግዴታዎች፣ ተግዳሮቶችና አሁን ስራ ላይ ያለውን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መተግበርያን በተሻለ ፍጥነት ለመጠቀም የሚረዱ ጊዜያዊ አማራጭ መብትሔዎች:
ተጻፈ በጊዲሳ ፈዬራ።
ሰላም ጤና ይስጥልኝ የቻናሌ ተከታታዮች...ሰላማችሁ ባላችሁበት እንዲበዛላችሁ እየተመኘሁ፣ ለዛሬ በኛ መድረክ ሰሞኑን መነጋገርያ ስለሆነው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሞባይል ባንኪንግ መተግበርያ ተደራሽነትና መተግበርያው ተሻሽሎ እስኪለቀቅ ድረስ፣ መተግበርያውን በተሻለ ፍጥነት ለመጠቀም ስለሚያስችሉ ጊዜያዊ አማራጭ መብትሄዎችን ከአጠቃላዩ የዲጂታል ባንኪንግ ተደራሽነት ሀሳብ ጋር አያይዤ ላወጋችሁ ፈለግሁና ወደመድረካችሁ ብቅ አልሁኝ።
በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ የዲጂታል ባንክ አገልግሎቶች (የሞባይል ባንኪንግ፣ የኢንተርኔት ባንኪንግ፣ የኤቲኤም እና የተለያዩ የክፍያ ሥርዓቶች) በከፍተኛ ፍጥነትና ስፋት እያደጉ ይገኛሉ። ይህ ሽግግር ለብዙኃኑ ማኅበረሰብ የዕለት ተዕለት ሕይወት መቅለል ትልቅ አስተዋጽዖ እያበረከተ ቢሆንም፣ ለአካል ጉዳተኞች በተለይም ለዓይነ-ስውራን ያለው ተደራሽነት ግን አሁንም ሰፊ ክፍተቶች ያሉበት ነው።
እነዚህን አገልግሎቶች ተደራሽ ማድረግ የቸርነት ወይም የደግነት ጉዳይ ሳይሆን፣ ተቋማት ሊወጡት የሚገባው መሠረታዊ የሕግ ግዴታና የሰብአዊ መብት ጥያቄ ነው።
ይህ ጽሁፍ በቅርቡ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) መተግበሪያ ላይ የተደረገውን ማሻሻያ ተከትሎ የተከሰቱትን የተደራሽነት ተግዳሮቶች በዝርዝር ይተነትናል። ከተከሰቱት ችግሮች ጎን ለጎንም ዓይነ-ስውራን ደንበኞች የስክሪን አንባቢ (Screen Reader) ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም መተግበሪያውን በተሻለ ፍጥነትና ቅልጥፍና ማስተግበር የሚችሉባቸውን ጊዜያዊና ስትራቴጂካዊ አማራጭ መፍትሔዎች በሰፊው ያብራራል።
፩. ዓለም አቀፍና አገራዊ የሕግ ማዕቀፎች (Legal Frameworks)
የዲጂታል ፋይናንስ ሥርዓት ተደራሽነትን በተመለከተ በኢትዮጵያ ውስጥ ቀጥተኛ ተፈጻሚነት ያላቸው በርካታ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችና አገራዊ ሕጎች አሉ። እነዚህ ሕጎች የፋይናንስ ተቋማት አገልግሎቶቻቸውን ያለምንም አድልዎ ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ እንዲያደርጉ ያስገድዳሉ።
ሀ. የተባበሩት መንግሥታት የአካል ጉዳተኞች መብቶች ስምምነት (UN CRPD)
ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የአካል ጉዳተኞች መብቶች ስምምነትን በ2002 ዓ.ም በአዋጅ ቁጥር 676/2002 አጽድቃ የሕጓ አካል አድርጋዋለች። በኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 9(4) መሠረት ኢትዮጵያ ያጸደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች የአገሪቱ ሕግ አካል ናቸው። ስለዚህ በስምምነቱ ላይ የሰፈሩት ድንጋጌዎች በኢትዮጵያ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ የመንግሥትም ሆነ የግል ባንኮች ላይ ቀጥተኛ ተፈጻሚነትና አስገዳጅነት አላቸው።
አንቀጽ 9 – ተደራሽነት (Accessibility)፦ ይህ አንቀጽ አካል ጉዳተኞች ከሌሎች ዜጎች ጋር በእኩልነት በአካባቢያቸው፣ በትራንስፖርት፣ በመረጃና በኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂዎችና ሥርዓቶች (ICT) እንዲሁም በሕዝብ ዘንድ ክፍት የሆኑ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ መንግሥታትና የሚመለከታቸው አካላት ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ ያስገድዳል። የባንክ መተግበሪያዎች፣ ድረ-ገጾች እና የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ሥርዓቶች (እንደ ኤቲኤም እና ፖስ ማሽኖች) ለአካል ጉዳተኞች በተለይም ለዓይነ-ስውራን ምቹና ተደራሽ የመሆን ግዴታ አለባቸው።
አንቀጽ 9(2)(ለ) – የግል ተቋማት ግዴታ፦ ይህ ንዑስ አንቀጽ ለሕዝብ አገልግሎት የሚሰጡ የግል ተቋማት (ባንኮችን ጨምሮ) አገልግሎቶቻቸውን ለአካል ጉዳተኞች ተደራሽ እንዲያደርጉና ሁሉንም የተደራሽነት ገጽታዎች ከግምት ውስጥ እንዲያስገቡ በግልጽ ያዝዛል።
ለ. የአገር ውስጥ ሕጎችና የብሔራዊ ባንክ መመሪያዎች ትስስር
የኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 41(5) መንግሥት ለአካል ጉዳተኞች አስፈላጊውን እንክብካቤ የማድረግና የመደገፍ ግዴታ እንዳለበት ይደነግጋል። የፋይናንስ ሥርዓቱን የሚመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ (NBE) እንዲሁም የቴክኖሎጂ ዘርፉን የሚቆጣጠሩት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር (MInT) እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ባንኮች ቴክኖሎጂዎችን ሲዘረጉ ተደራሽነታቸውን እንዲያረጋግጡ የመቆጣጠር ኃላፊነት አለባቸው።
፪. የድህረ-ገጽና መተግበሪያ ይዘት ተደራሽነት መመሪያ (WCAG) እና የቴክኒክ መስፈርቶች
የሕግ ድንጋጌዎቹ "ተደራሽ መሆን አለበት" ብለው ሲያስገድዱ፣ ይህንን በተግባር ለመተርጎም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያለው መመሪያ የድህረ-ገጽ ይዘት ተደራሽነት መመሪያ (Web Content Accessibility Guidelines - WCAG) ነው። በአሁኑ ወቅት የባንኮች ዲጂታል መድረኮች ቢያንስ የ WCAG 2.1 (ደረጃ AA) መስፈርትን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል። ይህ መመሪያ አራት ዋና ዋና ምሶሶዎችን (POUR Principles) ያስቀምጣል፦
መሠረታዊ መርሆ (POUR)
የቴክኒክ መግለጫ
ተግባራዊ ምሳሌና መስፈርት
፩. ሊገነዘቡት የሚቻል (Perceivable)
በድረ-ገጽ ወይም በመተግበሪያ ላይ ያሉ መረጃዎችና ክፍሎች ተጠቃሚው በስሜት ሕዋሳቱ ሊገነዘባቸው የሚችሉ መሆን አለባቸው።
በመተግበሪያው ላይ ያሉ ምስሎችና ምልክቶች በሙሉ የጽሑፍ ማብራሪያ (Alt-text) ሊኖራቸው ይገባል፤ በዚህም የስክሪን አንባቢው ሊያነበው ይችላል።
፪. ሊያንቀሳቅሱት የሚቻል (Operable)
የተጠቃሚ በይነገጹ (User Interface) እና የዳሰሳ (Navigation) ክፍሎቹ በቀላሉ ሊሠሩ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
ማውዝ ወይም ቀጥተኛ እይታ መጠቀም ለማይችሉ፣ መተግበሪያው በኪቦርድ ወይም በንክኪ ምልክቶች (Gestures) ብቻ ሙሉ በሙሉ መሥራት አለበት።
፫. ሊረዱት የሚቻል (Understandable)
የመረጃው ይዘትና የአሠራር ሂደቱ ግልጽና በቀላሉ ሊረዱት የሚችሉ መሆን አለባቸው።
የገንዘብ ማስተላለፍ ሂደቱ ግራ የሚያጋቡ ቃላት የሌሉበትና ተጠቃሚው ስህተት ሲሠራ እንዴት ማስተካከል እንዳለበት የሚጠቁም መሆን አለበት።
፬. ጠንካራ/የሚጣጣም (Robust)
ይዘቱ ቴክኖሎጂው እያደገ ሲሄድም ከተለያዩ የአካል ጉዳተኞች ረዳት መሣሪያዎች ጋር ተጣጥሞ መሥራት መቻል አለበት።
መተግበሪያው ከተለያዩ ረዳት ቴክኖሎጂዎች (TalkBack, VoiceOver, Jieshuo) ጋር ያለምንም መቆራረጥ መጣጣም ይኖርበታል።
፫. የሰኔ ፪፲፱፻፲፰ (June 2026) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) መተግበሪያ ማሻሻያና የተደራሽነት ቀውስ
በቅርቡ በሰኔ ፫ ቀን ፪፲፱፻፲፰ ዓ.ም (June 3, 2026) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመተግበሪያው ላይ ባደረገው አዲስ ማሻሻያ፣ ከላይ ከተጠቀሱት ዓለም አቀፍ ድንጋጌዎችና የ WCAG መመሪያዎች አንጻር ሲገመገም ከፍ ያለ የተደራሽነት ችግር ታይቶበታል። ይህ ማሻሻያ ዓይነ-ስውራን ደንበኞች የዕለት ተዕለት የገንዘብ እንቅስቃሴዎቻቸውን በተገቢው መንገድ እንዳያከናውኑ እንቅፋት ሆኗል።
የትግራይ ህክምና ማህበር የአዲግራት ሆስፒታል ዋና ስራ አስፈፃሚ የዶ/ር የማነ ገብረማርያምን መታሰር አወገዘ።
የትግራይ ህክምና ማህበር (TMA) የህፃናት ህክምና ስፔሻሊስትና የአዲግራት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ዶ/ር የማነ ገብረማርያም ያለአግባብ መታሰራቸውን በመግለጽ ድርጊቱን ተቃውሞ መግለጫ አወጣ።
ማህበሩ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ፣ ዶ/ር የማነ በትግራይ የህክምና እና የትምህርት ማህበረሰብ ዘንድ በጤና አገልግሎት አመራርና በህክምና መምህርነታቸው የሚታወቁ አንጋፋ ባለሙያ መሆናቸውን ገልጿል።
በተጨማሪም የህክምና ማህበሩ የቀድሞ የስራ አስፈፃሚ ቦርድ አባል እና በአሁኑ ወቅት የአማካሪ ቦርድ አባል ሆነው በማገልገል ላይ የሚገኙ መሆናቸውን አመልክቷል።
እንደ ማህበሩ መረጃ ከሆነ፣ ዶ/ር የማነ በቁጥጥር ስር የዋሉት "MedEd Africa" በተሰኘ የሙያ ትምህርት መርሃ ግብር ላይ ለመሳተፍ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ ሳሉ ነው።
እስካሁንም ለቤተሰቦቻቸው፣ ለስራ ባልደረቦቻቸውም ሆነ ለማህበሩ የታሰሩበት ህጋዊ ምክንያት እንዳልተገለጸ ማህበሩ አሳውቋል።
የህክምና ማህበሩ ይህ እስር የህክምና ባለሙያዎች በነፃነት የመንቀሳቀስ፣ የመደራጀት እና ሙያዊ የሳይንስና የትምህርት ተግባራትን ያለ ምንም ትንኮሳ የማከናወን መብታቸውን የሚጥስ መሆኑን አስታውቋል።
ድርጊቱ በትግራይ ክልል እያገገመ የሚገኘውን የጤና ስርዓት፣ በተለይም ከፍተኛ ቁጥር ያለውን ህዝብ የሚያገለግለውን ሆስፒታልና የቀጣይ የጤና ባለሙያዎችን የሚያሰለጥነውን የትምህርት ማዕከል ስራ የሚያደናቅፍ ነው ብሏል።
ማህበሩ በመግለጫው
• ዶ/ር የማነ ገብረማርያም ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲፈቱ።
• በቁጥጥር ስር የዋሉበት ምክንያት በግልጽ እንዲታወቅና የህግ የበላይነት እንዲከበር እንዲሁም
• የጤና እና የአካዳሚክ ህክምና አመራሮች ደህንነትና ገለልተኝነት እንዲከበር ጥሪ አቅርቧል።
የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እና ዓለም አቀፍ የጤና አጋሮች የዶ/ር የማነን መፈታት እንዲያረጋግጡና የህክምና ባለሙያዎች ያለ ስጋት ስራቸውን እንዲያከናውኑ ግፊት እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርቧል።
መግለጫው ዶ/ር የማነ የታሰሩት መቼ እንደሆነ አልገለጸም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
የፌዴሬሽን ምክርቤት 17 መዝገቦች ላይ የሕገመንግሥት ትርጉም ውሳኔ አጸደቀ።
የፌዴሬሽን ምከርቤት 6ኛ የፓርላማ ዘመን 5ኛ ዓመት 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው።
በጉባኤው የሕገመንግሥት አጣሪ ጉባኤ የሕገመንግሥቱ ትርጉም ያስፈልጋቸዋል እና አያስፈልጋቸውም በሚል የቀረቡ መዝገቦችን በሕገመንግሥት ትርጉም እና የውሳኔ አፈጻጸም ቋሚ ኮሚቴ ለምከርቤቱ ቀርበዋል።
የቋሚ ኮሚቴው ጸሐፊ ፍሬሕይወት ዱባለ የቋሚ ኮሚቴያቸውን አፈጻጸም ያቀረቡ ሲኾን ቋሚ ኮሚቴው የሕገመንግሥቱ ትርጉም የተሰጠባቸውን መዝገቦች በማዘመን ወደ ኤሌክትሮኒክ መዝገብ የመቀየር ሥራ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን አከናውኗል ብለዋል።
ከሕገመንግሥት አጣሪ ጉባኤ ለሚቀርቡ የሕገመንግሥት ትርጉም አቤቱታዎች መቶ በመቶ ምላሽ ተሰጥቷል ነው ያሉት።
ጸሐፊዋ ያቀረቡትን 13 የነጠላ መዝገብ አቤቱታ የውሳኔ ሀሳብ፣ 3 በጋራ እና አንድ በልዩ የቀረቡ ውሳኔዎችን ምክርቤቱ ገምግሟል።
በመኾኑም በ17 መዝገቦች የሕገመንግሥት ትርጉም ያስፈልጋቸዋል በሚል ውሳኔ ሰጥቷል። ሌሎች በርካታ የአቤቱታ መዝገቦች ደግሞ ትርጉም አያስፈልጋቸውም በሚል ምክርቤቱ በሙሉ ድምጽ ውሳኔ አጽድቋል።
@EthioLawAdvice_Bot
🫳https://t.me/ethiopianlawyerspage
