ch
Feedback
የፍትህ መድረክ/justice forum

የፍትህ መድረክ/justice forum

前往频道在 Telegram

በዚህ ቻናል ህግ ነክ ዜናዎች፣ ከህግ ጋር የተያያዙ የተመራረጡ ህግ ነክ ጽሁፎች ይቀርባሉ። "የተሻለች አለም እንድትኖረን ሁላችንም ለፍትህ እንቁም"!

显示更多
2 761
订阅者
-124 小时
+47 天
+3830 天
帖子存档
join us_155616195.mp33.46 MB

#ቅፅ 26 ሰበር በሰዎች የባንክ አካውንት ያስተላለፉትን ገንዘብ እንዲመልስልዎ መጠየቅ ይችላሉ? *** በመርህ ደረጃ ሊከፍል የማይገባዉን ገንዘብ ከከፈሉ፤ ግለሰቡ ገንዘቡን እንዲመልስልዎ መጠየቅ ይችላሉ (የፍትሃብሄር ህግ አንቀፅ 2164)። ይሁን እንጅ ገንዘቡን ያስተላለፉት የግለሰቡን ስም እና አካውንት ቁጥር በመፃፍ በባንክ ከሆነ ገንዘቡን አስበዉት በራስዎ ፍቃድ እንደላኩለት የሚያስቆጥር በመሆኑ ገንዘቡ እንዲመለስልዎ የመጠይቅ መብት አይኖርዎትም (የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሠበር ሠሚ ችሎት በቅፅ 26 የመ/ቁ. 175660)። ነገር ግን ገንዘቡን የግለሰቡን አካውንት እና ስም በመፃፍ በባንክ የላኩት በገንዘብ ተቀባዩ ተጭበርብረው፣ ተገደው እና መሰል ድርጊቶች ተፈፅሞበዎት ከሆነ ገንዘቡ እንዲመለስልዎ የመጠየቅ ሙሉ መብት ይኖርዎታል Join👇 https://t.me/ethiolawtips

🧩 ካርሎስ ወደ ናይጄሪያ ሲጓዝ፣ አጭበርባሪዎቹ ውስብስብ የሆነ የወንጀል ቡድን አካል ይመስሉት እንደነበር ይናገራል። ከአዚዝ ጋር የፈጠረው ግንኙነት ግን ይህንን ግምቱን መልሶ እንዲያጤነው አስገድዶታል። 🔄 📱 "ስልኩን ከያዘ ከዚህ ልጅ ይልቅ፣ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ ኃይለኛ የወንጀል መረብ እየጎዳን ነው ብሎ ማመን ይቀላል" ይላል። 🌍 💸 ካርሎስ፣ እነዚህ ወጣቶች ራሳቸውም ሲጭበረበሩ ተመልክቷል። በማጭበርበር ያገኙትን ገንዘብ ይዘው የሚታዩት እነዚህ ወጣቶች፣ ራሳቸው የሌሎች ኃይለኛ ወንጀለኞች ሰለባ ይሆናሉ። ⛓️ ❓ አሁንም ግን አንድ ጥያቄ ምላሽ አላገኘም፤ ትምህርታቸውን እንኳ ያላጠናቀቁ ታዳጊዎች እንደ ካርሎስ እናት ያሉ አዋቂዎችን እንዴት ማሳመን ቻሉ? 🤯 🫂 አጭበርባሪዎቹ ለሰዎቹ የሚያቀርቡት፣ ብዙዎች ያጡትን 'ጥልቅ ትስስር' እንደሆነ ለካርሎስ ነግረውታል። 🗣️ "'ትኩረት መስጠት ብቻ ነው ያለብህ' ይሉኝ ነበር። ከጎናቸው የመገኘት ጉዳይ ነው። 'እንዴት አደርሽ? የኔ ፍቅር እንዴት ነሽ? ማሬ እንደምን አለሽ? ምሳ ምን በላሽ?' እያሉ መጠየቅ ነው" ሲል ከእነርሱ የሰማውን ያስረዳል። 💬 😔 ይህ ከሰዎች ጋር ትስስር የመፈለግ ጉዳይ ከብቸኝነት የሚመነጭ እንደሆነ ይናገራል። ካነጋገራቸው የተጭበረበሩ ሰዎች ውስጥ ብዙዎቹም ይህንኑ እንዳነሱለት ይጠቅሳል። 💔 አንድ የማጭበርበር ሰለባ፣ "ይህንን በዓለም ላይ እጅግ አሳዛኙ ወንጀል የሚያደርገው የሚወስዱት ገንዘብህን ብቻ አለመሆኑ ነው። ስሜትህን ጭምር አሟጠው ይጨርሱታል። ያ ሰው በድንገት ሲጠፋ የሚሰማህ ባዶነት አለ። ማኅበረሰቡ ደግሞ ሞኝ እንደሆንክ እና ጥፋተኛው አንተው እንደሆንክ ይነግርሃል" ሲል ለካርሎስ ነግሮታል። 😭 📘 ካርሎስ የናይጄሪያ አጋጣሚውን በተመለከተ 'ዘ ያሁ ቦይስ' (The Yahoo Boys) የሚል መጽሐፍ አሳትሟል። ✍️ https://t.me/j_f125

🌐 በኢንተርኔት ግንኙነት እናቱን ያጭበረበረውን ናይጄሪያዊ ፍለጋ አህጉራትን ያቋረጠው ስፔናዊ 🇪🇸 🗣️ "ውስብስብ መንገድ የሚጠቀሙ ሆነው አላገኘኋቸውም። ብልህም አልነበሩም… እጅግ ያስገረመኝም ይኸው ነው" ይላል ካርሎስ ባራጋን። 💔 ካርሎስ አፍቃሪ ሰው መስሎ እናቱን ያጭበረበረውን ግለሰብ ለማግኘት ወደ ናይጄሪያ ሲጓዝ፣ የተካነ አጭበርባሪ እንደሚያገኝ ጠብቆ ነበር። 🇳🇬 🪖 ራሱን በሶሪያ እንደሚገኝ አሜሪካዊ ወታደር አድርጎ የገለጸው ግለሰብ፣ በላካቸው ኢሜይሎች ላይ ያለው የበይነ መረብ (አይፒ) አድራሻ የሚያሳየው ግን ናይጄሪያ ውስጥ መሆኑን ነበር። 💻 ✈️ ካርሎስ ወደ ናይጄሪያ ከሄደ በኋላ ግን ወንጀለኛውን የማጋለጥ ዕቅዱን ትቶታል። ይልቁንም ለአራት ዓመታት ያህል 'ያሁ ቦይስ' (Yahoo Boys) ተብለው የሚታወቁትን የናይጄሪያ ወጣት አጭበርባሪዎች ማጥናት ተያያዘ። 🕵️‍♂️ ከእነዚህ ወጣቶች ውስጥ አብዛኞቹ በትምህርታቸው ያልገፉ፣ ገንዘብ የሌላቸው እና ዕድል ያልተመቻቸላቸው ናቸው። 🌍 ናይጄሪያ ከሄደ በኋላ ያጋጠመው ነገር፣ እናቱን ስላጭበረበረው ሰው የነበረውን አስተሳሰብ ተፈታትኖታል። በዘመናዊው ዓለም ውስጥ ብቸኝነት ስለሚፈጥረው ተጽዕኖም ራሱን እንዲጠይቅ አድርጎታል። 😔 🪖 የአሜሪካው ወታደር 'ብራያን' 👩‍👦 ካርሎስ ከእናቱ ጋር 👩‍⚕️ ካርሎስ እናቱን 'ጠንካራ እና በራሷ የቆመች ሴት' ሲል ይገልጻታል። ሕክምና ያጠናችው እና የጥርስ ክሊኒክ ያላት እናቱ፣ ትጭበረበራለች ተብላ የምትገመት አልነበረችም። ለዚያም ነበር እሱ እና ወንድሞቹ እናታቸው በአጭበርባሪ መታለሏን ሲረዱ እጅግ የደነገጡት። 😲 📧 እንዴት ለዚህ እንደበቃች የሚያስረዳ ፍንጭ ያገኙት፣ ለአዲሱ ፍቅረኛዋ "ብራያን" የላከችውን ኢሜይል ሲመለከቱ ነው። 💌 የኢሜይል መልዕክቱ፤ "መጀመሪያ እናቴን ከዚያም ታናሽ እህቴን ስንከባከብ ነበር፤ ቀጥሎ ደግሞ ባለቤቴን እና ልጆቼን ተንከባከብኩ። ሕይወቴን በሙሉ ሌሎችን ስንከባከብ ኖሬያለሁ፤ አሁን እኔን የሚንከባከበኝ ሰው እፈልጋለሁ" ይላል። ❤️‍🩹 📱 ይህ ከመፈጠሩ ወራት አስቀድሞ፣ ከባለቤቷ በመፋታቷ ምክንያት እናቱ ብቸኝነት እንደተሰማት ያስተዋለው ካርሎስ፣ 'ቲንደር' (Tinder) የተባለውን የፍቅረኞች መገናኛ መተግበሪያ እንድትጠቀም አበረታትቷት ነበር። 🇺🇸 በ50ዎቹ አጋማሽ ላይ ከሚገኝ ሸበላ እና በሶሪያ ከተሰማራ አሜሪካዊ ወታደር ነኝ ከሚለው 'ብራያን' ጋር የተገናኘችውም ብዙም ሳይቆይ ነበር። 🤨 ራሱም ወታደር የነበረው የካርሎስ ታላቅ ወንድም ወዲያውኑ ጥርጣሬውን ለእናቱ ገልጿል። 🤫 እናቱ በልጇ ከተሰጣት ማሳሰቢያ በኋላ ስለግንኙነቱ ከእሱ ጋር ማውራት ብታቆምም፣ አልፎ አልፎ ከብራያን የሚላኩላትን ኢሜይሎች ግን ለካርሎስ ታሳየው ነበር። 📩 💕 የኢሜይል ልውውጦቹ በፍቅር እና በጥልቅ ስሜት የተሞሉ ነበሩ። ብራያን ብዙም ሳይቆይ አብረው ለመኖር ወደ ስፔን እንደሚመጣ መናገር ጀመረ። ✈️ ግንኙነቱ እዚህ የደረሰበት ፍጥነት የካርሎስን እናት ጭምር ያስገረመ ነበር። 🤔 "በተወሰነ መልኩ ትጠራጠር የነበረ ይመስለኛል" ይላል ካርሎስ። 🥇 ቀጥሎ ደግሞ ብራያን ጥፍጥፍ ወርቆችን ወደ ቤታቸው እንደሚልክ ሲናገር በቤተሰቡ ውስጥ አለመግባባት ተፈጠረ። 😠 💍 ካርሎስ ይህንን ጉዳይ ማጣራት የጀመረው፣ እናቱ ሁለት ቀለበቶችን ይዛ ወደ ቤት በመምጣት በቅርቡ አብረው መኖር እንደሚጀምሩ ስትናገር ነው። 📍 ከዚያም የብራያን ኢሜይሎች የተላኩት ከናይጄሪያዋ ሌጎስ ከተማ መሆኑን የሚያረጋግጥ መረጃ ለእናቱ አሳያት። ብዙ ነገር አልተናገረችም፤ ከቀናት በኋላ ግን አብዛኞቹን የኢሜይል መልዕክቶች አጠፋቻቸው። 🗑️ ሐዘንም ገብቷት ነበር። 😢 🧳 ካርሎስ፣ እናቱ ከብቸኝነት ጋር ስትታገል ማየቱ በውስጡ አንዳች ነገር ጫረበት። ወደ ናይጄሪያ ተጉዞም ያንን ድብቅ አጭበርባሪ ለማግኘት ወሰነ። 🕵️‍♂️ 💻 "ያሁ ቦይስ" (Yahoo Boys) 🤝 ካርሎስ አካባቢውን በሚያውቅ ሰው አማካኝነት ናይጄሪያ ውስጥ ቢጊ የተባለ አጭበርባሪን ተዋወቀ። ቢጊ ደግሞ ከጓደኞቹ ጋር ሊያስተዋውቀው፣ እንዲሁም "ሁሉም ሰው ገንዘብ ለማግኘት የሚሯሯጥበት" ኢኮቱን የተባለውን የሌጎስ ሰፈር ሊያሳየው ተስማማ። 🏙️ 🧑🏾‍🦱 በ20ዎቹ መጨረሻ ላይ የሚገኘው ቢጊ፣ ከካርሎስ ጋር እኩያ ነው። ብልህ እና "እጅግ ተጫዋች" ወጣት ነው። ⏳ ካርሎስ አብዛኛውን ጊዜውን ከቢጊ ጋር ባሳለፈ ቁጥር፣ በአስገራሚ ሁኔታ እየተቀራረቡ መጡ። 💭 "እንደ እርሱ ያለ ሰው፣ እንዴት ሌሊቱን ሙሉ በኢንተርኔት ብቸኛ ሰዎችን ሲያወራ የሚያድር አጭበርባሪ ሆነ?" ብሎ ያስብ እንደነበር ይናገራል። 🌙 🕸️ ካርሎስ የአካባቢውን ሰዎች ሲያነጋገር ሰፊ የአጭበርባሪዎች መረብ እንዳለ ተረዳ። 'ያሁ ቦይስ' በመባል የሚታወቁት እነዚህ ወጣቶች በመቶዎች የሚቆጠሩ መሆናቸውንም ተገነዘበ። 🤯 አጭበርባሪዎቹ ይህንን መጠሪያ ያገኙት በፊት ይጠቀሙበት በነበረው 'ያሁ' (Yahoo) የኢሜይል አገልግሎት ምክንያት ነው። 📧 🇳🇬 ካርሎስ፣ ሐሰተኛ ስም እና የኢሜይል አድራሻን ብቻ ይዞ ከ240 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ባላት ናይጄሪያ ውስጥ የእናቱን አጭበርባሪ ማግኘት እንደማይችል በጊዜ ሂደት ተረዳ። 🚫 📖 በምትኩም ስለ 'ያሁ ቦይስ' ዓለም እያጠና ራሱን አገኘው። 🌃 ካርሎስ የኢኮቱንን የምሽት ሕይወት የተዋወቀው በቢጊ አማካኝነት ነበር። 🚶‍♂️ ነጭ አውሮፓዊ የሆነው ካርሎስ፣ በሄደበት ሁሉ ተለይቶ ይታይ ነበር። ብዙ ሰዎችም የኤፍቢአይ (FBI) ወኪል ወይም ቻይናዊ የንግድ ሰው እንደሆነ ያስቡ እንደነበር ይናገራል። 🕵️‍♂️ 🤡 ሰዎች የሚጠሩት "ማጋ" ብለው ነበር፤ ትርጉሙም "በቀላሉ ሊታለል የሚችል ሞኝ ሰው" ማለት ነው። 🎤 እንዲያም ሆኖ ግን በቢጊ አማካኝነት በማጭበርበር ላይ የተሰማሩ 50 ያህል ወጣቶችን ማነጋገር ችሏል። 💶 ከአጭበርባሪዎቹ አንዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ያገኘው 300 ዩሮ ነበር። ይህ የገንዘብ መጠን ለአንድ ዓመት ተኩል ፋብሪካ ውስጥ በሰራበት ጊዜ ከተከፈለው የሚበልጥ ነበር። 🏭 🎣 የሚጭበረበር ሰው ግን በቀላሉ አይገኝም። "በመቶዎች ካልሆነም በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን መሞከር ይኖርብሃል" ይላል ካርሎስ። 👦 ካርሎስ፣ በ14 ዓመቱ ማጭበርበር ከጀመረ አዚዝ ከተባለ ሌላ 'ያሁ ቦይ' ጋር ተቀራረበ። ከገጠር ወደ ሌጎስ የመጣው አዚዝ፣ ከእናቱ እና ከሕፃን እህቱ ጋር በጠባብ የአፓርታማ ክፍል ውስጥ ይኖራል። 🏚️ 👱‍♀️ አዚዝ የአንዲት ቆንጆ ነጭ ሴት ፎቶን በመጠቀም እና ስሙ 'ቫኔሳ' እንደሆነ በመግለጽ ከአሜሪካውያን ወንዶች ጋር ይተዋወቃል። 🇺🇸 📉 መጀመሪያ ላይ ግን አልተሳካለትም ነበር። እንግሊዘኛው እምብዛም ነው፤ ፍቅረኛ ይዞም ሆነ አሜሪካ ሄዶም አያውቅም። 🤷‍♂️ ካርሎስ "እያወራን ያለነው ስለ ምዕራቡ ዓለም ብዙም ዕውቀት ስለሌላቸው ትናንሽ ልጆች ነው" ይላል። 💵 በጊዜ ሂደት አዚዝ የመጀመሪያውን 5 ዶላር አገኘ፤ ምግብ ቤት ሄዶም ዶሮ በላበት። 🍗 👵 ትምህርት ያልቀመሱና የመንገድ ላይ ምግብ ሻጮች የሆኑት የአዚዝ እናት እና አያት ግን፣ ልጁ የሚያደርገው ነገር ስህተት መሆኑን ተረድተው ነበር። አያቱም ማጭበርበሩን የማያቆም ከሆነ ከቤተሰቡ እንደሚባረር የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጡት። 🛑 🛑 ከዚያ ጊዜ አንስቶም አጭበርብሮ አያውቅም።

ሚስት የባለቤቷን ብልት በጥርሷ ነክሳ ከባድ ጉዳት አደረሰች! በዚምባብዌ ሃራሬ ከተማ ከባለቤቷ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት የተናደደችው የ29 ዓመቷ ሻርሊን ሩቴንዶ ሙኔንጋ፣ የ33 ዓመቱን ባለቤቷን ብልት በመንከስ ከባድ ጉዳት ማድረሷን የዚምባብዌው "The Herald" ጋዜጣ ዘገበ። የጋዜጣው መረጃ እንደሚያሳየው፣ ይህ አሰቃቂ ድርጊት የተፈጸመው ባለቤቷ ከጋብቻ ውጭ ግንኙነት አለው በሚል ጥርጣሬ በተነሳ ከፍተኛ ጭቅጭቅና ግብግብ ወቅት ነው። በደረሰበት ከባድ ጉዳት ምክንያት ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል የተወሰደው ባለቤቱ አሁን ላይ በአስጊ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ዘገባው አመልክቷል። ጥፋተኛዋ ባለቤት በሃራሬ ማጂስትሬት ፍርድ ቤት ቀርባ በከባድ የአካል ጉዳት ወንጀል ክስ የተመሰረተባት ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱም ጉዳዩ እስኪጣራ ድረስ  በእስር እንድትቆይ ትዕዛዝ አስተላልፏል። https://t.me/j_f125

💔 ⚖️ ለቀድሞ ፍቅረኛው ያበረከታቸውን ስጦታዎች በገንዘብ አስልቶ እንዲመለሱለት ክስ ያቀረበው ግለሰብ ጥያቄ ውድቅ ሆነ አንድ ሲንጋፖራዊ ለቀድሞ ፍቅረኛው ለስጦታ እና ለተለያዩ ነገሮች ያወጣውን በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ዶላር ከተለያዩ በኋላ ለማስመለስ ያቀረበው ክስ በፍርድ ቤት ውድቅ ተደረገበት። 💸❌ ቻንደር አጋርዋል የተባለው ግለሰብ የቀድሞ ፍቅረኛው ፌሊሺያ ሊ አብረው በነበሩበት ጊዜ ያወጣውን 468,000 የሲንጋፖር ዶላር (በግምት 370 ሺህ የአሜሪካ ዶላር) ለማስመለስ በፍርድ ቤት ክስ መሥርቶ ሲከራከር ቆይቶ ነበር። 🏢✈️ ነገር ግን ጉዳዩን የተመለከተው የሲንጋፖር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከሳሽ ገንዘቡን ለቀድሞ ፍቅረኛው ያወጣው ወዶና ፈቅዶ በመሆኑ እንድትመልስለት ፍቅረኛውን እንደማያስገድድ ወስኗል። ⚖️👩‍⚖️ የፍርድ ቤቱ ዳኛ ሊ ሴዩ ኪን እንደገለጹት፣ አጋርዋል ከሊ ጋር ፍቅር ከመጀመሩ በፊትም ቢሆን ውድ ስጦታዎችን በተደጋጋሚ ይሰጣት ነበር፤ እንዲሁም ገንዘቡን እንድትመልስለት እንደማይጠብቅ ያረጋግጥላት ነበር። 🎁❤️ አጋርዋል የአንድ የትራንስፖርት ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሲሆን፣ የቀድሞ ፍቅረኛው ፌሊሺያ ሊ ደግሞ የአውሮፕላን አስተናጋጅ ነበረች። ሁለቱ በአውሮፓውያኑ 2019 በአንድ በረራ ላይ ተዋውቀው፣ ከአንድ ዓመት በላይ በፍቅር ግንኙነት ውስጥ ነበሩ። ✈️👩‍✈️ አጋርዋል ሊ ከሌላ ወንድ ጋር ግንኙነት እንዳላት ከጠረጠረ በኋላ በመለያየታቸው፣ በፍቅር ግንኙነታቸው ወቅት ያወጣውን ገንዘብ በማስላት እንድትመልስለት ክስ መሥርቷል። እንዲሁም ሊ በግንኙነታቸው ወቅት "ወለድ የሌላቸው ብድሮችን" በተደጋጋሚ ጠይቃው እንደነበር ተከራክሯል። 💔📉 እነዚህም በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የክሬዲት ካርድ ወጪዎችን፣ ለውጭ አገር ጉዞዎች፣ ለቤት ማሻሻያ እና ለሕይወት ኢንሹራንስ ያወጣቸውን ከፍተኛ ክፍያዎች ጨምሮ ሌሎች ወጪዎችን እንድትመልስለት የጠየቀበት ነው። 💳✈️🏡 ሊ በበኩሏ የቀድሞ ፍቅረኛዋ እንዲመለሱለት የዘረዘራቸው ወጪዎች "በፍቅር እና በአክብሮት የተበረከቱ ስጦታዎች ናቸው እንጂ ብድር አይደሉም" ስትል ተከራክራለች። 🎁🤝 ዳኛውም ከሊ ጋር በመስማማት፣ አጋርዋል ያቀረበው ክስ እና ክርክር በሰነድ ማስረጃ ያልተደገፈ እጅግ ደካማ መሆኑን ጠቁመዋል። ለምሳሌ፣ ሊ እነዚያን ብድሮች እንደወሰደች የሚያሳይ ማረጋገጫ ማቅረብ አልቻለም ብለዋል። 📄❌ "ለፍርድ ቤቱ የቀረበው ማስረጃ በሙሉ ከሳሽ በተከሳሽ ተማርኮ በግንኙነታቸው ወቅት ውድ ስጦታዎችን ሲያበረክትላት እንደነበር ብቻ ያሳያል" ብለዋል ዳኛው። 💭💝 "ነገር ግን ግንኙነቱ በመጥፎ ሁኔታ ሲቋጭ፣ አጋርዋል በቂም ተነሳስቶ የቀድሞ ፍቅረኛውን ከፍተኛ ዋጋ ለማስከፈል ክስ መሥርቷል" ሲሉ ዳኛው ክሱን ውድቅ አድርገውታል። ⚖️🔨 ዳኛው በተጨማሪም አጋርዋል "ብዙ ገንዘብ ያለው እና ውድ ነገሮችን የሚወድ ሰው" መሆኑን፣ ሊ ደግሞ "ከዚያ ደረጃ የራቀች" መሆኗን መገንዘባቸውን ገልጸዋል። 💰💼 ሁለቱ የቀድሞ ፍቅረኞች ባደረጓቸው በርካታ የጽሑፍ መልዕክት ልውውጦች ውስጥ ሊ፣ አጋርዋል ውድ ስጦታዎችን ሲያቀርብላት መደነቋን፣ አንዳንድ ጊዜም ለመቀበል ማመንታቷን ገልጻ እንደነበር ዳኛው ጠቅሰዋል። 📱💬 📌 ተመሳሳይ የቀድሞ አጋጣሚዎች እንዲህ ዓይነቱ ክስ በሲንጋፖር ውስጥ የመጀመሪያ አይደለም። ከሦስት ዓመት በፊት ሌላ ግለሰብ የፍቅር ጥያቄውን ውድቅ ያደረገችበት ሴት ከ3 ሚሊዮን የሲንጋፖር ዶላር በላይ የሚገመት ካሳ እንድትከፍለው በመጠየቅ ሁለት ክሶችን አቅርቦ ነበር። 🇸🇬⚖️ ኬ. ካውሺጋን የተባለው ግለሰብ፣ ኖራ ታን ለተባለች ሴት ያቀረበውን የፍቅር ጥያቄ ባለመቀበሏ "የሥነ ልቦና ጉዳት እንደደረሰበት እና መልካም ስሙ እንደተበላሸ" ተከራክሮ ነበር። 💔🤦‍♂️ ጉዳዩን የተመለከተው የአገሪቱ ፍርድ ቤት ግን ክሶቹን ውድቅ አድርጎታል። በኋላም ተከሳሿ ታን በከሳሹ ካውሺጋን ላይ ተቃዋሚ ክስ በማቅረብ፣ ከተከሰሰችበት ክስ ራሷን ለመከላከል ያወጣችውን ወጪ እንዲከፍል ጠይቃለች። ⚖️🛡️

4ኛ. ከመደበኛው ሥነ-ሥርዓት ይልቅ የሕፃናት ወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕግ ልዩ ሙያና ልምድን የሚጠይቅ፣ ልዩ ትኩረት የሚሻ፣ እና የሕግ ባለሙያዎችን (ዳኛ፣ ዓቃቤ ሕግ፣ ጠበቃ) ብቻ ሳይሆን እንደ ሕክምና ባለሙያ፣ ሥነ-ልቦና ባለሙያ፣ የሕፃናት አያያዝና እድገት ባለሙያ፣ ሳይኪያትሪስት ወዘተ ካሉ ሌሎች ልዩ ሙያ ካላቸው ባለሙያዎች ጋር በቅርበት መስራትን የሚጠይቅ መሆኑን ከላይ ከተጠቀሱት የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ-ሥርዓት ሕግ ድንጋጌዎች እና ከወንጀል ሕግ አንቀጽ 157-165 ድንጋጌዎች መረዳት ይቻላል። ይህም ጉዳዩ በአንድ ዳኛ ብቻ በቀላሉ ሊታይ የሚችል ሳይሆን፣ ልዩ ባህሪ ያለውና ውስብስብ በመሆኑ ከአንድ በላይ በሆኑ ዳኞች መታየትን የሚጠይቅ መሆኑን የሚያሳይ ነው። ከዚህም በላይ፣ የጉዳዩ ባህሪ ውስብስብ መሆን እና ሂደቱ ቀላል መሆን አለመሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ሕግ አውጪው አካል በግልጽ በሦስት ዳኞች ችሎት እንዲታይ የደነገገውን ድንጋጌ እንደተደነገገው ሥራ ላይ መተግበር የዳኝነት አካሉ (ፍርድ ቤት) ሀላፊነትና ግዴታ መሆኑ መረሳት የለበትም። https://t.me/speaklawinabsentia

ዕድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናት ከ10 ዓመት በላይ በሚያስቀጣ ከባድ ወንጀል በተከሰሱበት ጉዳይ የወረዳ ፍርድ ቤት በስንት ዳኞች መሰየም/ጉዳዩን መስቻል አለበት? ============================================================================== ከፌደራልና የክልሉ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 36፣ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 157-165፤ የአዋጅ ቁጥር 216/2011 አንቀጽ 33(2)፤ የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ-ሥርዓት ሕግ፤ አዲሱ የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ቁጥር 1410/2018 አንቀጽ 361-373 እና ከፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 29(4(ሀ)) ጋር አብሮ የታየ። ============================================================================== በፍትሐብሔርም ሆነ በወንጀል ጉዳዮች፣ በማናቸውም የፖለቲካ፣ የአስተዳደር እና የሕግ እርምጃዎች አሰጣጥ ውስጥ የሕፃናት መብትና ጥቅም ከፍተኛ ስፍራ እንደሚሰጠው፣ ቅድሚያ ተሰጥቶት ልዩ ትኩረት ሊደረግለት እንደሚገባ የፌደራልና የክልሉ ሕገ-መንግሥት በአንቀጽ 36 ሥር ደንግገው ይገኛሉ። ሀገሪቱ በተቀበለቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶችም በተመሳሳይ ሁኔታ ስምምነት ላይ ተደርሷል። ከዚሁ በመነሳት፣ የወንጀል ተጠያቂነትን በተመለከተ ወንጀል የፈጸሙ ሕፃናት በምን ሁኔታ መያዝ እንዳለባቸው እ.ኤ.አ በ2004 በወጣው የወንጀል ፖሊሲ፣ በ1996 በወጣው የወንጀል ሕግ፣ በ1952 በወጣው የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ-ሥርዓት ሕግ እና በ2018 ጸድቆ ባለው (እስካሁን ሥራ ላይ ባልዋለው) አዲሱ የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ውስጥ በሰፊው ተዘርግቶ ተደንግጎ ይገኛል። በዚሁ መሠረት ዕድሜያቸው ከ9 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናት ከወንጀል ተጠያቂነት ነፃ እንደሆኑ፣ ከ9 እስከ 15 ዓመት መካከል ያሉ ደግሞ በልዩ ሥነ-ሥርዓት እና ልዩ እርምጃ ወይም አያያዝ ተጠያቂ እንደሚሆኑ አሁን በሥራ ላይ ባለው የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ-ሥርዓት ሕግ አንቀጽ 172 እና ተከታዮቹ ፣ አዲሱ የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ደግሞ በአንቀጽ 362-375 ሥር ተዘርግቶ የተደነገገ ሲሆን፣ ክርክሩ እና የማረሚያ እርምጃው ከመደበኛው የክርክር ሂደት በተለየ ልዩ ሥነ-ሥርዓት (special procedures) እንዲታይ ተደንግጎ ይገኛል። በሌላ በኩል፣ ወንጀልን በተመለከተ የወረዳ ፍርድ ቤት እስከ 15 ዓመት እሥራት የሚያስቀጡ የወንጀል ጉዳዮችን በመጀመሪያ ደረጃ ሥልጣን ተቀብሎ ማየት እንደሚችል በአዋጅ ቁጥር 216/2011 አንቀጽ 31(3) ሥር የተደነገገ ሲሆን፤ ወንጀሉ ከ10 ዓመት በላይ የሚያስቀጣ ከሆነ ደግሞ በሦስት ዳኞች ችሎት ታይቶ መወሰን እንዳለበት በዚሁ አዋጅ አንቀጽ 33(2) ሥር ተደንግጎ ይገኛል። እንግዲህ ለዚህ ጽሑፍ ዋና ምክንያት የሆነው ነጥብ፡ የአዋጁ አንቀጽ 33(2) ድንጋጌ፣ የቅጣት ጣሪያው ከ10 ዓመት በላይ የሚያስቀጣ ሆኖ ነገር ግን ዕድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች በሆኑ ሕፃናት በተፈጸመ ወንጀል ላይ ተፈጻሚነት አለው ወይስ የለውም? የሚለው ጥያቄ ነው። በዚህ ላይ ዕድሜያቸው ከ9-15 የሆኑ ሕፃናት የወንጀል ጉዳይ በቀላል እና አጭር በሆነ ልዩ የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ-ሥርዓት ሕግ የሚታይ እና የእሥራት ቅጣት የሌለው በመሆኑ፣ ከ10 ዓመት በላይ የሚያስቀጣ ወንጀል ቢፈጽሙም በሦስት ዳኞች ማየት ግዴታ አይደለም በማለት አንድንድ የወረዳ ፍርድ ቤቶች በአንድ ዳኛ እየሠሩ እንደሆነ ከተጨባጭ ሁኔታው ይታያል። ይህም ጉዳዩ የሚታይበት ልዩ ሂደት አጭርና ቀላል ከመሆኑም በላይ፣ የአካል ነፃነትን የሚገድብ የእሥራት ቅጣትን የሚያስከትል ስላልሆነ የአዋጅ ቁጥር 216/2011 አንቀጽ 33(2) ድንጋጌ ግዴታ ሊከተሉት አይገባም በሚል ምክንያት ነው። ይህ አሠራር የሕግ መሠረት አለው ወይስ የለውም? በእርግጥ ከ10 ዓመት በላይ የሚያስቀጣ ወንጀል ዕድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች በሆኑ ሕፃናት ሲፈጸም በሦስት ዳኞች ችሎት እንዲታይ አዋጁ በአንቀጽ 33(2) ሥር የደነገገው ተፈጻሚነት የለውም ማለት ይቻላል? የሚለው ነጥብ ሊታይ የሚገባው ሆኖ ተገኝቷል። በዚህ ላይ፡ 1ኛ. አሁን በሥራ ላይ ያለውም ሆነ አዲሱ የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ-ሥርዓት ሕግ አዋጅ ቁጥር 1410/2018 ከመደበኛው የሥነ-ሥርዓት ሕግ የተለየ የሕፃናት ወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕግ የደነገጉበት ምክንያት፡ ሕፃናት ከአእምሮ ብስለታቸው፣ ከአካላዊ እድገታቸው፣ ነገሮችን የመረዳት አቅማቸው እንዲሁም ከሥነ-ልቦናቸው አኳያ ልዩ እንክብካቤና አያያዝ ስለሚያስፈልጋቸው እና ባህሪያቸውም በእሥራት ቅጣት ሳይሆን በእንክብካቤ፣ ሕክምና እና ማደግ ላይ ባተኮሩ ልዩ እርምጃዎች የሚቃና በመሆኑ እንደሆነ ከሕግ ጽሑፎችና ከዘርፉ እሳቤዎች (jurisprudence) መረዳት ይቻላል። ይህም የፈጸሙት ወንጀል ከባድ ወይም ቀላል መሆኑን ሳይሆን፣ የሕፃኑን የላቀ ጥቅም እና ፍላጎት መሠረት ያደረገ መሆኑን ያሳያል። 2ኛ. በአዋጅ ቁጥር 216/2011 ውስጥ የተደነገገው የሥልጣን ክፍፍል እና የችሎት መሰየም ሥርዓት ጉዳዮች የሚታዩበትን የሥነ-ሥርዓት ሕግ ልዩነት መሠረት ያደረገ ሳይሆን፣ የወንጀሉን ከባድነት እና የሚያስከትለውን ቅጣት፣ የአስተዳደር ወጪ ውጤታማነትን፣ ፍትሕ የማግኘት መብትን፣ የጉዳዩን ውስብስብነት እንዲሁም ልዩ ትኩረት የሚሻ መሆኑን መሠረት ያደረገ መሆኑ ይታወቃል። በተመሳሳይ ሁኔታ በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 29(4(ሀ)) ሥር ከ15 ዓመት በላይ የሚያስቀጡ ወንጀሎችን የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ እና ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች በሦስት ዳኞች ችሎት ተሰይመው ማየት እንዳለባቸው ደንግጎ ይገኛል። ይህም የሚያሳየው፣ እነዚህ አዋጆች አንድ የወንጀል ጉዳይ በአንድ፣ በሦስት፣ በአምስት ወይም በሰባት ዳኞች ችሎት መታየት አለበት የሚሉት ጉዳዩ የሚታይበትን የሥነ-ሥርዓት ሕግ ዓይነት ሳይሆን የወንጀሉን ከባድነት፣ ውስብስብነቱን (ሕጋዊ ክርክር የሚያስነሱ ነጥቦችን፣ የሚያስፈልገውን የማስረጃ ዓይነትና ብዛት፣ የሕግ ትርጉም ቴክኒካላዊነትን ወዘተ) እና ሕጉ እንዲሰጠው የሚፈልገውን ልዩ ትኩረት መሠረት በማድረግ መሆኑን ነው። ስለዚህ በአንድ ወይም በሦስት ዳኞች መሰየም ጉዳዩ የሚታይበት ከሥነ-ሥርዓት ሕጉ ዓይነት ጋር የተያያዘ ሆኖ አይታይም። 3ኛ. በተጨማሪም፣ ዕድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናት ከ10 ዓመት በላይ የሚያስቀጣ ከባድ ወንጀል ሲፈጽሙ ጉዳያቸው የሚታይበት ሥነ-ሥርዓት ቀላል ልዩ ሥነ-ሥርዓት ስለሆነ በአንድ ዳኛ መታየት አለበት የሚለው እሳቤ፣ የሕፃናት ወንጀል ጉዳይ የሚታይበትን የልዩ ሥነ-ሥርዓት ሕግ ባህሪ በአግባቡ የተገነዘበ አይመስልም። እንዲያውም አሁን በሥራ ላይ ያለውንም ሆነ አዲሱን የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ በቅርበት ካየነው፣ ዕድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች በሆኑ ሕፃናት በተፈጸመ ከባድ የወንጀል ጉዳይ ላይ ክሱ በፍርድ ቤት ትእዛዝና ቁጥጥር ሥር የሚቀርብና ለሕፃኑ የሚነበብለት መሆኑ፣ የእምነት ቃል የሚወሰድበት እና ማስረጃም የሚሰማበት መሆኑ በግልጽ ተደንግጓል (ለምሳሌ፡ የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ቁጥር 1410/2018 አንቀጽ 370-373 ማየት ይቻላል)።

语音消息02:50

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#መግለጫ : የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ባቀረበው ጥያቄና ከተለያዩ አካላት ጋር ባደረገው ጥረት፣ በዛሬው ዕለት ከ600 በላይ ሰዎች ከእስር መፈታታቸውን ገልጿል። ኮሚሽኑ በላከልን
#መግለጫ : የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ባቀረበው ጥያቄና ከተለያዩ አካላት ጋር ባደረገው ጥረት፣ በዛሬው ዕለት ከ600 በላይ ሰዎች ከእስር መፈታታቸውን ገልጿል። ኮሚሽኑ በላከልን መግለጫ፣ በተለያዩ ወንጀሎች የተፈረደባቸው እና ጉዳያቸው በፍርድ ሂደት ላይ የሚገኙ ዜጎች ጉዳያቸው በልዩ ሁኔታ እንዲታይ ጥያቄ አቅርበዋል። ኢሰመኮም ይህንን ጥያቄ መነሻ በማድረግ ጉዳዩን ለመንግሥት አቅርቧል። ኮሚሽኑ እንደገለጸው፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጉዳዩን በአዎንታ ተቀብለው፣ የሕግ የበላይነትን በጠበቀ መልኩ ለሰላም፣ ለሀገራዊ መግባባትና ለዴሞክራሲ የሚያግዙ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ለሚመለከታቸው የመንግሥት መዋቅሮች አቅጣጫ ሰጥተዋል። በዚህ መሠረት በተቀመጠው የሕግና የይቅርታ ሂደት መሠረት፣ በተለያዩ ወንጀሎች የተፈረደባቸው በይቅርታ እንዲፈቱ፣ በክስ ሂደት ላይ ያሉ ተከሳሾችም ክሳቸው ተቋርጦ ከእስር እንዲለቀቁ ተወስኗል ሲል ኢሰመኮ ገልጿል። ኢሰመኮ ይህንን ውሳኔ ለሰላም፣ ለሀገራዊ መግባባትና ለዴሞክራሲ ግንባታ ጠቃሚ እርምጃ በማለት አድንቋል። በቀጣይም ተመሳሳይ የሰላም ግንባታ ጥረቶች እንዲጠናከሩ ጠይቋል። ከእስር የተለቀቁት ዜጎች ወደ መደበኛ ሕይወታቸው በመመለስ በሕጋዊና ሰላማዊ መንገድ በሀገራዊ የሰላም ግንባታና ልማት ላይ እንዲሳተፉም ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል። በተጨማሪም በኢትዮጵያ ያሉ ችግሮች በትጥቅ ትግል ይፈታሉ ብለው የሚያምኑ ኃይሎች ወደ ሰላማዊ ድርድር እንዲመጡ ኢሰመኮ አሳስቧል። ኮሚሽኑ በተጨማሪም በዛሬው ዕለት ከእስር የተለቀቁት ዜጎች ወደ አካባቢያቸው ሲመለሱ ወደ መደበኛ ሕይወታቸው እንዲቀላቀሉ የሚደረገውን የማቋቋም ሥራ የመንግሥትና የሲቪል ማኅበረሰብ አካላት እንዲያግዙ ጠይቋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ጳጉሜን 5 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
አቶ ክርስቲያን ታደለን ጨምሮ ከ600 በላይ እስረኞች በይቅርታና ክሳቸው ተቋርጦ ከእስር መፈታታቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አሳወቀ። ከእስር እንዲፈቱ ኢሰመኮ ከመንግስት ጋር
አቶ ክርስቲያን ታደለን ጨምሮ ከ600 በላይ እስረኞች በይቅርታና ክሳቸው ተቋርጦ ከእስር መፈታታቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አሳወቀ። ከእስር እንዲፈቱ ኢሰመኮ ከመንግስት ጋር ላለፉት 5 ወራት ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን ገልጿል። በፍርድ ቤት ውሳኔ ታሰረው የነበሩት በይቅርታ፣ በክስ ሂደት ላይ የነበሩት ደግሞ ክሱ እንዲቋረጥ ተደርጎ ከ600 በላይ እስረኞች በዛሬው እለት እንዲፈቱ መደረጉን የኢሰመኮ ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ አሳውቀዋል። ከእስር መፈታት ብቻ ሳይሆን በህግ የታገዱ መብቶቻቸው እንዲመለሱ መደረጉ ተመላክሯል። ይህ ቁጥር ክልሎች በየራሳቸው ከሚፈቷቸው ውጭ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ የተፈቱት እስረኞች ከአማራ እና ከኦሮሚያ በፌደራል ደረጃ የታሰሩ እንደነበሩ ተገልጿል። በተመሳሳይ መዝገብ የሚገኙ 28 እስረኞች የይቅርታ ጥያቄ ባለማቅረባቸው ከእስር እንዳልተፈቱ ኢሰመኮ አሳውቋል። #ኤፍኤምሲ #ኢቢሲ ጳጉሜን 5 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
እነ ክርስቲያን ታደለን ጨምሮ በሽብር ወንጀል ተከሰው ለአመታት በእስር ላይ የነበሩ ከ300 በላይ እስረኞች ዛሬ ሊፈቱ እንደሆነ ተሰማ። በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን አደራዳሪነት የተለያዩ ቅድመ
እነ ክርስቲያን ታደለን ጨምሮ በሽብር ወንጀል ተከሰው ለአመታት በእስር ላይ የነበሩ ከ300 በላይ እስረኞች ዛሬ ሊፈቱ እንደሆነ ተሰማ። በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን አደራዳሪነት የተለያዩ ቅድመ ሁኔታዎችን ፈርመው በይቅርታ እንዲፈቱ መጠየቁና ከተወሰኑ እስረኞች ውጭ በርካቶች መፈረማቸው የሚታወስ ሲሆን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን ከተከታተሉ አካል እንደሰማው ከሆነ የፈረሙት ዛሬ ይፈታሉ ተብሎ ይጠበቃል። ከአንድ የኢሰመኮ ከፍተኛ ኃላፊ ዛሬ በደረሳቸውን መረጃ መሰረት አድርገው እኚሁ አካል በሰጡን ቃል፣ " ዛሬ እንደሚፈቱ ነው የተገጸልኝ። 'የቀሩ አንድ ሁለት ሂደቶች (የሚፈረሙ ነገሮች) አሉ እነሱ ዛሬውኑ ተጠናቀው፤ ይፈታሉ ነው ያሉን' ያለው ነገር ዛሬ ይፈታሉ የሚል ነው " ብለዋል። ባላቸው መረጃ አጠቃላይ የታሰሩት 362 መሆናቸውን፣ ከእነዚህ መካከል በይቅርታ ለመፈታት የቀረበው ቅድመ ሁኔታ ላይ ያልፈረሙት 24ቱ ብቻ መሆናቸውን ነግረውናል። ይፈታሉ ተብሎ ከሚጠበቁት መካከል ፦ - አቶ ክርስቲያን ታደለ፣ - ዶ/ር ካሳ ተሻገር፣ - ዶ/ር ጫኔ ከበደ፣ - ረ/ፕሮፌሰር ማረጉ ቢያዝን እንደሚገኙበት እኚሁ የታሳሪዎቹ የቅርብ ሰው አስረድተዋል። በዚህ የይቅርታ መንገድ ከማይፈቱት መካከል ደግሞ፦ - እነ አቶ ዮሐንስ ቧያለው፣ - ዶ/ር ወንድወሰን፣ - ዶ/ር ሲሳይ፣ - ጋዜጠኛ መስከረም፣ - ጋዜጠኛ ገነት አስማማው፣ - ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ፣ - ጋዜጠኛ ዳዊት ጋሻው እንደሚገኙበት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ጠቁመዋል። ሂደቱን በተመለከተ ምን አሉ ? " የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ በጉዳዩ ላይ መስራት ከጀመሩ ወደ ስድስት ወር አስቆጥሯል። እኛ አናውቅም ነበረ፤ በኋላ ግማሹ ላይ እኛም አውቀናል። በይቅርታ መንገድ ነው የሚወጡት የሚባል ነገር መጣ። ይህ ሲሆን እስረኞቹ፣ ' ማስረጃ ሳይቀርብብን ለምንድን ነው በይቅርታ የምንወጣው ? ክስ ነው መቋረጥ ያለበት ' ብለው ነበር። ይህን የታሳሪዎቹን ቅሬታ ተከትሎ እኔ እና አንድ ሌላ አካል ኢሰመኮን አነጋግረናል። ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎን አነጋግረናቸዋል፤ ሁሉንም ነገር ነገሩን። በዚህም መንግስት የሚፈልገው እስረኞቹ እንዲፈርሙ በቀረበላቸው ቅድመ ሁኔታ መሰረት በይቅርታ እንዲፈቱ መሆኑን ነው የተገለጸልን። ጉዳዩ በዚህ መልኩ እንዲከናወን የሆነበት ምክንያት እስረኞቹ ከተፈቱ በኋላ ችግር ሊፈጥሩ ይችላሉ አይነት ነገር ስላለ ነው። ይህም ከአማራ ታጣቂዎች ጋር ሆነው ችግር ሊጥሩ ይችላሉ የሚል ነው። የእነ አቦይ ስብሃት፣ ጃዋር መሐመድ፣ አብዲ ኢሌ አፈታት በዚህ መንገድ አልነበረም። ለምንድን ነው እነዚህን በይቅርታ የምትፈቷቸው ? በሚል ከኢሰመኮ ጋር ስንነጋገር ' አሁን ጦርነት አለ፤ ቢፈቱ ጦርነቱን ያባብሱታል ' ተብሎ እንደተሰጋ፣ ከዚህ አኳያ ' መንግስት በይቅርታ መፍታት ነው የሚችለው፤ ከዚያ ውጭ አይቻልም ' የሚል ምላሽ ነው የተሰጠን። ይቅርታ ራሱ አልተፈለገም ነበር፤ ግን ከበላይ አካል የመጣ መሆኑ ነው የተነገረን።  ከዚያ ውጭ ፍትህ ሚኒስቴር ራሱ ' ማስረጃ አለኝ፤ እከሳለሁ፤ አስወስንባቸዋለሁ ' የሚል አቋም ነው ያለው የሚል ማብራሪያ በወቅቱ ተሰጥቶናል። ታሳሪዎቹ ከ3 አመት በላይ በመታሰራቸው ቤተሰቦቻቸውን ለብዙ ማህበራዊ ቀውስ ተዳርገዋል። ትዳር የፈረሰባቸው፣ በጣም አስቀያሚ ነገሮች በመኖራቸው፣ እንዲሁም አቶ ክርስቲያንም ሌሎቹም የታመሙ ስላሉ በሕይወት መቆየት ስላለባቸው በተባለው መንገድ እንዲፈቱ ተወስኗል " ብለዋል። እስረኞቹ እንዲፈርሙ የቀረበላቸውን ጉዳይ በተመለከተ ምን አሉ ? " እስረኞቹ በማህበራዊ ሚዲያው፥ ' አማራ ክልል ባለው ጦርነት ለሞቱት፣ ለወደሙ ንብረት ኃላፊነት እንወስዳለን' አሉ ተብሎ ሲሰራጭ ነበር። ግን ለሁሉም እስረኞች አይደለም። ክሳቸውም ይለያያል። ሆኖም በአማራ ክልል በጦርነት የተፈጸመውን ጉዳይ በተመለከተ የተከሰሱ ሰዎች አሉ። በይቅርታ ለመፈታት በዚሁ ጉዳይ ኃላፊነት ለመውሰድ ቅድሚያ ፈርሙ ሲባል ካልተቀበሉት መካከል እነዚሁ እስረኞች ይገኙበታል። አንወጣም ካሉት እስረኞች ውስጥ እንደዛ እንዳለ ሰምቻለሁ፤ የክርስቲያንን ኬዝ ብናይ ግን እንደዛ አይደለም። የቀረበው ቅድመ ሁኔታ ላይ ፈርመው በይቅርታ ለመውጣት የተስማሙት እስረኞች፣ ክሳቸው ቀላል የሆነላቸው ናቸው። ለእንደዚህ አይነት እስረኞች ' ይህን አጥፍቻለሁ ' ማለት ከባድ አይደለም። የክርስቲያን ክስ ራሱ 'ህገወጥ የጦር መሳሪያ በመያዝ' ነው የተባለው፤ የጦር መሳሪያው ደግሞ ህጋዊ ነው፤ ማስረጃ አለው። ሌላው ክስ፣ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ወቅት፥ መከላከያ ቀድሞ ገብቶ ስለነበር ' አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከመታወጁ በፊት መግባት አይችልም ' በሚል የተቃወሙትን የሚመለከት ነው። ይሄ ደግሞ በፍርድ ቤትም የተናገረው ነገር ነው። የስልክ ሪከርድም አለ። እኛም አለን። ለፍርድ ቤት ማስረጃ ተብሎ የቀረበው እሱ ነው። ግን ምንም የወንጀል ፍሬ ነገር የለበትም። ክርስቲያንም ያመነው ነገር ነው። አንድ የአብን አመራር ጋር ያደረገው የስልክ ውይይት ነው። ይህ ስለሆነ ምንም ችግር አያመጣብኝም ብሎ ነው የፈረመው " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል። የሌሎቹም እንደዚሁ ቀላል ያለ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። አክለው ፦ " በእርግጥ የድምፅ ማስረጃ የተገኘባቸው አሉ። አንዳንዶች አሉ ማስረጃ እጅ ከፍንጅ የተገኘባቸው፤ ለምሳሌ ከጦርነት ጋር በተገናኘ። እሱን ራሳቸው ካመኑ ይቅርታ ማለት አይከብድም፤ እጅ ከፍንጅ ሲያዙ። ከዚያ ውጭ ከታዋቂ ሰዎች ጋር ግንኙነት አላቸው የሚል ነው፣ አብዛኞቹ ወጣቶች ናቸው ገና። ጊዜያቸውን እዚያ ማባከን አይፈልጉም። ሁሉም ' አማራ ክልል ላይ በጦርነት ለተፈጸመው ኃላፊት እንወስዳለን ' በሚል ግን አይደለም። እንዲያውም፣ በሰበብ አስባቡ እንዳይከሷቸው ተነጋግሪያለሁ። በዚህ አይነት መንገድ ፈትተው መልሰው በሰበባስባቡ የሚያስገቧቸው ከሆነ አይሆንም። ንግግር አለ። ኢሰመኮ በተደጋጋሚ እየሄደ እያነጋገራቸው ነው " ብለዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው ሁለት የታሳሪ ቤተሰቦች ደግሞ፣ ስለጉዳዩ እምብዛም በግልጽ እንዳላወቁ፣ ይህ ዘገባ በተዘጋጀበት ወቅትም የተፈታ እስረኛ እንደሌለ ገልጸዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ጳጉሜን 5 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

语音消息04:37

语音消息02:44

语音消息01:30