Hule Business Review ( HBR)
الذهاب إلى القناة على Telegram
ትክክለኛዉ የሁሌ አዲስ ሚዲያ ገፆች Facebook : bit.ly/42rUuKj WhatsApp : bit.ly/Huleadis_whatsapp YouTube : bit.ly/3p7kj3N Twitter : bit.ly/3NVMRrB Telegram: bit.ly/Huleadis_tele ለጥቆማ ና አስተያየት እንዲሁም ለማስታወቂያ ስራ ተከታዮን አድራሻ ይጠቀሙ bit.ly/3VMy7x7
إظهار المزيد2 251
المشتركون
-124 ساعات
-107 أيام
-5730 أيام
أرشيف المشاركات
ማዕከላዊ ባንኩ ለአራተኛው ሩብ ዓመት 200 ሚሊዮን ዶላር ሊያቀርብ ነው
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የ2018 በጀት ዓመት የመጨረሻ ሩብ ዓመት የውጭ ምንዛሬ ጨረታ መርሃ-ግብርን ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ ለዚሁ ተግባር 200 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር መመደቡን አስታውቋል። ይህ የተመደበው በጀት በሙሉ በሰኔ ወር 2018 ዓ.ም ውስጥ ጥቅም ላይ የሚውል መሆኑን ባንኩ ገልጿል።
የማዕከላዊ ባንኩ መግለጫ እንዳመለከተው፣ ይህ አዲስ የአቅርቦት ስትራቴጂ በበጀት ዓመቱ መጠናቀቂያ ላይ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ለማረጋጋት ታሳቢ ያደረገ ነው።
ባንኩ ባለፈው ዓመት ህዳር ወር ይፋ ካደረገው 520 ሚሊዮን ዶላር አቅርቦት አንጻር፣ በሦስተኛው ሩብ ዓመት የነበረው አሰራር በእያንዳንዱ ጨረታ 70 ሚሊዮን ዶላር በስድስት ክፍለ-ጊዜዎች መከፋፈሉ ይታወሳል።
ይሁን እንጂ አሁን ባለው የሰኔ ወር ዕቅድ መሠረት፣ አጠቃላይ 200 ሚሊዮኑ ዶላር በሁለት ዋና ዋና ጨረታዎች ተከፋፍሎ ይቀርባል፤ ይህም በእያንዳንዱ የጨረታ መስኮት 100 ሚሊዮን ዶላር እንዲኖር ያደርጋል ተብሏል።
በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች በ500,000 እና 400,000 ብር ዋስ እንዲፈቱ ተወሰነ።
መንሱር ጀማል የተባለው ተከሳሽ ግን አቃቢ ህግ መቃወሚያ ስላቀረበበት ዛሬ ከሰዓት ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ለመስጠት ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ከድርጅቱ ጋር በተያያዘ በ1.9 ቢሊዮን ብር የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ ታዋቂ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች፣ የዋስትና መብታቸው ተከብሮ በውጭ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ዛሬ በዋለው ችሎት ፈቅዷል።
ባለፈው ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ከ5 ተከሳሽ መንሱር ጀማል ውጭ ባሉ ተጠርጣሪዎች ከሀገር እንዳይወጡ እና ከፍ ያለ ዋስትና አስይዘው የዋስትና መብታቸው ተከብሮ ከውጭ ሆነው ጉዳያቸውን ቢከታተሉ እንደማይቃወም አስረድቶ እንደነበር ይታወሳል።
ዛሬ በዋለው ዝግ ችሎት ተርጣሪዎቹ የዋስትና መብታቸው ተከብሮላቸው፣ ከእስር ተፈትተው በውጭ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ፍርድ ቤቱ ወስኗል።
በዚህ መሠረት ከአንድ እስከ አራት ያሉ ተከሳሾች ማለትም ሰራዊት ፍቅሬ፣ ሰለሞን ቦጋለ፣ ይገረም ደጀኔና ዳንኤል ተገኝ በ500 ሺህ ብር ዋስ እንዲወጡ ሲፈቀድላቸው።
ስድስተኛና ሰባተኛ ተከሳሽ አብርሀም ግዛውና ካሊድ ናስር በ400 ሺህ ብር እንዲወጡ ፍርድ ቤቱ መወሰኑን ጠበቃ አበባው አበበ ነግረውናል።
አምስተኛ ተከሳሽ መንሱር ጀማል በተመለከተ አቃቢ ህግ ባቀረበው መቃወሚያ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ዛሬ 8 ሰዓት ቀጠሮ መሰጠቱን ጠበቃ አበባው አበበ ተናግረዋል፡፡
ሁሉም ተከሳሾች ከሃገር እንዳይወጡ እገዳም ተጥሎባቸዋል ተብሏል።
(ገዛ ጌታሁን - ሸገር ኤፍኤም)
መቐለ : ዛሬ ጠዋት ምን ተፈጠረ?
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመንገደኞች አውሮፕላን ዛሬ ጧት ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ወደ መቐለ ከበረረ በኋላ አሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ሳያርፍ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰ።
አውሮፕላኑ አሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ማረፍ ያልቻለው፣ ከአውሮፕላን ማረፊያው የኮሚንኬሽን መሳሪያ ብልሽት ጋር በተያያዘ መኾኑን የአየር መንገዱ ሃላፊዎች እንደነገሩት ጠቅሶ የዘገበው ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ነው።
ኾኖም ከሰዓታት በኋላ የኮምንኬሽን መሳሪያው ብልሽት በመስተካከሉ አውሮፕላኑ ወደ መቐለ መጓዙን እንደተረዳ ምንጩ ጠቅሷል።
በታዋቂው የሙዚቃ አቀናባሪ ካሙዙ ካሣ እና በሻኩራ ፕሮዳክሽን ላይ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የንብረት እና የባንክ ሂሳብ እገዳ መጣሉ ተሰማ።
ይህ እርምጃ የተወሰደው "ኢትዮጵያ" በተሰኘው የባህል ማስተዋወቅ ፕሮጀክት ላይ በተሳተፉ 37 አርቲስቶች የቀረበባቸውን የ30.8 ሚሊዮን ብር ክስ ተከትሎ ሲሆን፣ አርቲስቶቹ በቻይና እና በሩሲያ ጨምሮ በተለያዩ ሀገራት 11 የባህል ትርኢቶችን ቢያቀርቡም የተስማሙበት ክፍያ እና የልምምድ አበል እንዳልተከፈላቸው ገልጸዋል።
አቀናባሪ ካሙዙ ካሣ በበኩላቸው ክፍያዎችን በስምምነቱ መሠረት እየፈጸሙ መሆናቸውን በመጥቀስ ክሱን ቢያስተባብሉም፣ ፍርድ ቤቱ ግን ጉዳዩ በህግ ታይቶ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ በአቀናባሪው ስም ያሉ ማናቸውም ንብረቶች እና በአራት ባንኮች የሚገኙ የባንክ ሂሳቦች ለ20 ቀናት ታግደው እንዲቆዩ ትዕዛዝ አስተላልፏል።
" ለሚፈጠረው ችግር ሁሉ የጊዚያዊ አስተዳደሩን ስልጣን በጉልበት በመያዝ ላይ ያለው ኃይል መሆኑ እገልፃለሁ " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ
ባለፈው ማክሰኞ ሚያዝያ 27/2018 ዓ.ም 'ነባር ምክር ቤትና መንግስት መልሻለሁ ' ያለውና ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር)ን የክልሉ ፕሬዝዳንት አድርጎ የሰየመው ህወሓት ዛሬ በደብረፅዮን (ዶ/ር) መሪነት በክልሉ የፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት የመጀመሪያውን የካቢኔ ስብሰባ ማካሄዱን አስታውቋል።
በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) መሪነት የተከናወነው የካቢኔ ስብሰባ በክልሉ የዜና ማሰራጫዎች መነገሩ ተከትሎ በሰዓታት ልዩነት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) በፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፅ አጭር መልስ ሰጥቷል።
የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ምን አሉ ?
" በቅርብ ቀናት የተፈጠረው ሁኔታ ተከትሎ ሊመጣ የሚችለው ጉዳት ለማስቀረት ፤ ችግሩን በጋራ ውይይትና መግባባት ለመፍታት የቀረበውን ጥሪ ወደ ጎን በመተው 'የተመረጥኩኝ ነኝ ' የሚል አካል ዛሬ ሚያዝያ 30/2018 ዓ/ም የፀጥታ አካላት ጥበቃ ተሰጥቶት በጊዚያዊ አስተዳደሩ የመሰብሰብያ አዳራሽ የካቢኔ ስብሰባ ጀምሯል።
ይህ ተግባር ቀጣይ አደገኛ መንገድ የተጀመረበት ቀን ስለሆነ በዚሁ ምክንያት ለሚከተለው አደጋ ሁሉ የጊዚያዊ አስተዳደሩን ስልጣን በጉልበት በመያዝ ላይ ያለ ኃይል መሆኑ እገልፃለሁ " ብለዋል።
በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) መሪነት የተከናወነው የካቢኔ ስብሰባ በዜና ማሰራጫዎች መዘገቡን ተከትሎ ዛሬ አርብ ሚያዝያ 30/2018 ዓ.ም ከቀኑ 5:30 ለሁለተኛ ጊዜ የውግያ ጀት አውሮፕላን በመቐለ ከተማ ሰማይ ላይ መታየቱን የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባል ገልጿል።
ወ/ሮ በረከት ወርቁ (በረከት ገበሬዋ)ን ጨምሮ 4 ሰዎችን በወንጀል እንደሚፈልጋቸው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ።
ፖሊስ በከባድ የሙስና ወንጀል እንደሚፈልጋቸው ነው ያስታወቀው።
ግለሰቦቹ፥ የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ በገበያ ላይ የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት አድርገዋል ተብለው ክስ ከተመሰረተባቸው 13 ግለሰቦች መካከል ናቸው።
ሱዳን በሁለት የኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ ተጨማሪ ኃይልና የአየር መከላከያዎችን እያሰማራች መሆኑ ተገለጸ
የሱዳን ጦር በምዕራብ ኢትዮጵያ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አዋሳኝ በሆነው በብሉ ናይል ግዛት እንዲሁም ከአማራ ክልል ጋር በሚዋሰነው አወዛጋቢው የአል-ፋሻጋ የድንበር አካባቢዎች ላይ ተጨማሪ ወታደሮችንና የአየር መከላከያዎችን እያሰማራ መሆኑ ተዘገበ።
እንደ ብሉምበርግ ዘገባ የሱዳን ጦር በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው በብሉ ናይል ግዛት ተጨማሪ ወታደሮችንና የአየር መከላከያ መሣሪያዎችን አሰማርቷል።
ተጨማሪ ለማንበብ አስታየት መስጫ ስር ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ።
በአዲስአበባ የሚገኘዉ የፋኖ ክንፍ ቅሬታ አነሳ
ለተሃድሶ እየተሰጠ ያለው ስልጠና አጥጋቢ አይደለም ሲል “በአማራ ክልል ትጥቅ ትግል” ላይ የነበረው እና አሁን ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጋር እየተወያየ ያለው ‛የፋኖ ክንፍ’ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በበኩሉ በጫካ ካሉ ከታጣቂዎች ጋር እያካሄደ ያለውን ግንኙነትን በተመለከተ አንዳንድ ጉዳዮች በግልጽ አይነገሩም ብሏል።
‛የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት’ ወታደራዊ አስተዳደር መምሪያ ሀላፊ እያሱ አባተ እንደገለጹት “ለተሃድሶ በትንሹ ዘጠና ቀናት መስጠት ነበረበት” ያሉ ሲሆን አሁን ላይ ግን እየተሰጠ ያለው ለሰባት ቀናት ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።
Via Ankuar Merja
ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ሊመጡ ነው
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ ሊመጡ መሆኑ ተዘግቧል
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኬንያ ናይሮቢ የሚካሄደውን "አፍሪካ ፎርዋርድ" ጉባኤ ካጠናቀቁ በኋላ፣ በመጪው ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለአጭር የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ ታውቋል።
ፕሬዝዳንቱ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡት በጥንቃቄ የተመረጡ የፈረንሳይ ግዙፍ ኩባንያዎች መሪዎችን በማስከተል ሲሆን፣ ጉብኝቱም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ነው ይላል የካፒታል ዘገባ።
በፕሬዝዳንቱ የታጀበው ልዑክ እንደ ካርፉር ያሉ ታዋቂ የችርቻሮ ንግድ ተቋማትን እና ሜሪዲያም የተሰኘውን የኢንቨስትመንት ድርጅት አመራሮችን ያካተተ ሲሆን፣ በተለይም ካርፉር ከኢትዮጵያው ሚድሮክ ጋር በፈጠረው የፍራንቻይዝ ስምምነት አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ ገበያ ለመግባት ማቀዱ የጉብኝቱ አንዱ ዋነኛ ትኩረት መሆኑ ተጠቁሟል።
የዓለም ጤና ድርጅት ማስጠንቀቂያ
በአንድ የቱሪስት መርከብ ላይ በደረሰ የሀንታ ቫይረስ ወረርሽኝ የሦስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ተከትሎ፣ የዓለም ጤና ድርጅት ተጨማሪ ተጠቂዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።
የዓለም ጤና ድርጅት ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ በባሕር ላይ በሚጓዝ የቱሪስት መርከብ ውስጥ የተከሰተው ይህ ወረርሽኝ ለሦስት ተሳፋሪዎች ሞት ምክንያት ሆኗል።
ድርጅቱ አክሎም፤ከሟቾቹ ጋር ንክኪ የነበራቸው ሌሎች ሰዎች ላይም የቫይረሱ ምልክቶች ሊታዩ እንደሚችሉ ስጋቱን ገልጿል።
ይሁን እንጂ፤አስፈላጊው የጥንቃቄ እርምጃዎች በአግባቡ ከተወሰዱ የወረርሽኙን ስርጭት መገደብና በቁጥጥር ስር ማዋል እንደሚቻል ድርጅቱ አስታውቋል።
የዓለም ጤና ድርጅት ሁኔታውን በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ ተሳፋሪዎችና የጉዞው አዘጋጆች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።
ሀንታ ቫይረስ አብዛኛውን ጊዜ ከአይጥ ዝርያዎች ወደ ሰው የሚተላለፍ ከባድ የጤና ችግር ሲሆን፣ ድርጅቱ የወረርሽኙን አድማስ ለማጥበብ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየሰራ መሆኑን ገልጿል ሲል የዘገበው TRT WORLD ነው።
የፍ/ቤት የክርክር መዝገብ እንዲዘጋ ተወሠነ
በእነ ኃይሌ ገብረስላሴና በእነ ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ኦሎምፒክ ኮሚቴ መካከል የነበረው የፍ/ቤት የክርክር መዝገብ እንዲዘጋ ተወሠነ
ከአንድ ዓመት በላይ የፈጀው በእነ ኃይሌ ገብረስላሴና በእነ ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ኦሎምፒክ ኮሚቴ መካከል የነበረው የፍ/ቤት ክርክር እንዲዘጋ ተወሠነ
በእነ ኃይሌ ገብረስላሴና በእነ የተከበሩ ዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስ መካከል የተፈጠረው አለመግባባት በመደበኛ ፍ/ቤት ላሉፉት ሁለት ዓመታት ሲታይ መቆየቱ ይታወሳል።
በእነዚህ ሁለት ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ እነ ኃይሌ በፍ/ቤት የኦሎምፒክን ማንኛውንም እንቅስቃሴ ሲያሳግዱ የእነ ዶክተር አሸብር ኦሎምፒክ በበኩሉ ዕገዳውን ሲያስነሳ ዓመታትን ቅርጥፍ አድርጎ መብላቱ ይታወሳል።
አሁን ከደቂቃዎች በፊት ከሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል ታማኝ ምንጮች እንዳገኘነው ዜና ከሆነ ድል ወደእነ ዶክተር አሸብር እንዳዘነበለች ይጠቁማል።
እንደ እነዚሁ ታማኝ የመረጃ ምንጮቻችን ከሆነ የሁለቱን ወገኖች ክስ ሲመረምር የነበረው የኢ.ፊ.ድ.ሪ የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ዛሬ በዋለው ችሎት በሁለቱ ወገንች መካከል የተከፈተው የክርክር መዝገብ እንዲዘጋና መዝገቡ ወደ መዝገብ ቤት እንዲመለስ ውሳኔ አሳልፏል።
እንደ እነዚሁ ታማኝ የሀትሪክ የመረጃ ምንጮች ከሆነ ጉዳዩን ከአንድ ዓመት በላይ ሲመረምር የነበረው ፍ/ቤት ስፖርታዊ ጉዳዮች መፈታት ያለባቸው በስፖርቱ ህግና ደንቦች እንጂ በመደበኛ ፍ/ቤቶች አይደለም በማለት የክርክር መዝገቡ እንዲዘጋ ውሳኔ መተላለፉና መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መዝገብ ቤት እንዲመለስ የመጨረሻ ውሳኔ መሠጠቱን እነዚሁ ምንጮቻችን ጨምረው ገልፀውልናል።
በቅርቡ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ከአስተዳደር ችግር ጋር በተያያዘ በተፈጠረ ችግር በደጋፊዎች ክስ ቢመሠረትም ጉዳዩ በሽምግልና ቢፈታም ጉዳዩን ወደ መደበኛ ፍ/ቤት የወሠዱት ከሳሾች ጉዳያቸውን በስፖርቱ ህግ የማይፈቱና ክሱን የማያነሱ ከሆነ ፌዴሬሽኑ ክለቡን አግዳለሁ ማለቱ የሚዘነጋ አይደለም።
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
በትግራይ 6 ሺ ድርጅቶች ተዘግተው
100 ሺ ሠራተኞች ተበትነዋል -ቢሮው
በትግራይ ክልል ከጦርነቱ በፊት ተቋቁመው ይንቀሳቀሱ የነበሩ 95 በመቶ የሚሆኑ የንግድ ድርጅቶችና ኢንዱስትሪዎች መውደማቸውን የክልሉ ኢንዱስትሪ ቢሮ ይፋ አደረገ። ቢሮው እንዳስታወቀው፣ የግጭት ማቆም ስምምነቱ በተሟላ ሁኔታ ተግባራዊ ባለመሆኑ ምክንያት ከ100 ሺሕ በላይ ሠራተኞችን የቀጠሩ ከ6 ሺሕ በላይ ድርጅቶች ተዘግተው ይገኛሉ። ዘርፉ በእዳ ጫና፣ በነዳጅና ጥሬ ዕቃ እጥረት፣ እንዲሁም በመሠረተ ልማት ውድመት ሳቢያ እስካሁን ማገገም እንዳልቻለ ተገልጿል።
ምንም እንኳ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደርና የኢንዱስትሪ ቢሮው ችግሩ እንዲፈታና የባንክ ብድሮች እንዲሰረዙ ለፌዴራል መንግሥት በተደጋጋሚ ጥያቄ ቢያቀርቡም፣ እስካሁን ተጨባጭ መፍትሄ አለመገኘቱን ገልጸዋል። በፋይናንስና በንግድ ገደቦች ሳቢያ የክልሉ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ክፉኛ መጎዳቱን የጠቀሰው ቢሮው፣ ከፌዴራል ባለሥልጣናት ጋር የተደረጉ ውይይቶችም የሚፈለገውን ውጤት እንዳላመጡ አስታውቋል።
በ'ፊንቴክ ኢንቨስትመንት' የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ወሰነ
ሆኖም ችሎቱ ተጠርጣሪዎች ለዋስትና የሚያቀርቡትን የገንዘብ መጠን ለመወሰን ለሰኞ ግንቦት 3/2018 ዓም ቀነ ቀጠሮ ሰጥቷል።
አቃቢ ህግ በበኩሉ አምስተኛ ተከሳሽ ከሆነው መንሱር ጀማል በቀር የዋስትና መብታቸው ቢከበር እንደማይቃወም ለችሎቱ አሳውቋል።
ችሎቱ በበኩሉ አቃቢ ህግ በአምስተኛ ተከሳሽ መንሱር ጀማል ዋስትና ጉዳይ ላይ አቃቢ ህግ ያለውን ተቃውሞ በጽሁፍ ለግንቦት ሦስት እንዲያቀርብ ትእዛዝ ሰጥቷል።
UAE በአካል የሚሰጡ የትምህርት ፕሮግራሞች ለአራት ቀናት በርቀት እንዲሰጡ ወሰነች።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የትምህርት ሚኒስቴር ከዛሬ ሜይ 5 ጀምሮ እስከ ሜይ 8/2826 ድረስ በአካል የሚሰጡ ትምህርቶች እንዳይኖሩ አሳስቧል።
ሁሉም የአንደኛ ደረጃ እና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎቻቸውን እና የማህበረሰቡን ደህንነት ማረጋገጥ አለባቸው ብሏል።
በሀገሪቱ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የኢራን ጦርነት ከተጀመረ በኋላ የትምህርት አሰጣጣቸውን ወደ በይነ መረብ ለመቀየር ተገደዋል።
ይሁን እንጅ ሚኒስቴሩ በአካል የሚሰጡ ትምህርቶች እንዲቀሩና በበይነ መረብ እንዲሰጡ የወሰነበትን ምክንያት አላሳወቀም።
በወቅታዊ የመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት ምክንያት ይሁን አይሁን በግልጽ አላስቀመጠም።
የUAE መከላከያ ሚኒስትር በትናንትናው እለት ከኢራን ከተቃጡ አራት ሚሳዔሎች ሶስቱን ማክሸፉን ገልጾ ነበር።
እንዲሁም፣ በፉጃራህ የነዳጅ ማጣሪያ ላይ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት ሶስት ሰዎች ተጎድተው ሆስፒታል መግባታቸውም ተገልጿል። #thepeninsulaquatar
ኢትዮጵያ በሱዳን መንግሥት የተሰነዘረባትን ክስ ውድቅ አደረገች።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፤ የሱዳን መከላከያ ኃይልና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በጋራ በሰጡት መግለጫ ኢትዮጵያ ላይ ያቀረቡት ክስ "መሰረተ ቢስ" ነው ሲል አጣጥሎታል።
የኢትዮጵያ እና የሱዳን ህዝቦች ያላቸውን ታሪካዊ ግንኙነት ከግምት ውስጥ በማስገባት ካሁን በፊት ሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት ወቅት አንዳንድ ታጣቂዎች የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት በመጣስ የሚደርጉት ትንኮሳዎችን ለህዝብ ይፋ ከማድረግ መቆጠቡን አንስቷል፡፡
የሱዳን ጦር "የህወሃት ቅጥረኛ ወታደሮችን በእርስ በርስ ጦርነቱ ውስጥ አሳትፏል፣ ለእነዚህ ቅጥረኛ ወታደሮች የጦር መሳሪያ እና የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ በምዕራብ ኢትዮጵያ ትንኮሳ እንዲፈጽሙ አድርጓል" በማለት ጠቅሷል፡፡
ሚኒስቴሩ "በሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት የህወሃት ቅጥረኛ ወታደሮች በግልጽ ሲንቀሳቀሱ መታየታቸው ሱዳን ለተለያዩ ፀረ ኢትዮጵያ ኃይሎች መናኸሪያ ሆና እያገለገለች መሆኗን የሚያሳይ ታማኝ መረጃ ነው" ብሏል፡፡
ቀደም ሲል በሱዳን ጦር እና ባለስልጣናት የተሰነዘሩ ውንጀላዎች እኩይ አጀንዳዎችን ለማራመድ የሚፈልጉ የውጭ ኃይሎችን ዓላማ ለማሳካት ያለመ መሆኑን አመላክቷል፡፡
"ኢትዮጵያ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ከሱዳን ህዝቦች ጋር አጋርነቷን እና ያላትን ወዳጅነት አጠናክራ ትቀጥላለች ያለው የሚኒስቴሩ መግለጫ፥ ኢትዮጵያ የሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት በውይይት ይፈታል ብላ ታምናለች" ብሏል፡፡
ኢትዮጵያ በሱዳን የሲቪል መንግሥት እንዲመሰረት፣ አስቸኳይ የሰብዓዊ እርዳታ እና ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ እንዲሁም ነጻ፣ ሁሉን አቀፍ እና ግልጽ ሲቪል መር ውይይት ማድረግ አስፈላጊ ነው ብላ እንደምታምን ጠቁሟል፡፡
የግብፅ መንግስት በካርቱም ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ላይ የተፈጸመውን የድሮን ጥቃት በፅኑ አውግዛለች።
ጥቃቱን የሱዳንን ሉዓላዊነት በግልጽ የጣሰ እና በሲቪል መሰረተ ልማቶች እንዲሁም በሱዳን ህዝብ ደህንነት ላይ የተጋረጠ ቀጥተኛ ስጋት እንደሆነም ገልጻለች።
ግብፅ በዛሬው ዕለት ባወጣችው ይፋዊ መግለጫ፤ ይህ ጥቃት የጸጥታና የሰብአዊ ሁኔታውን ይበልጥ የሚያወሳስብና በሱዳን የሰብአዊ ተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ የሚደረገውን ጥረት የሚያደናቅፍ "አደገኛ የሁኔታዎች መባባስ" መሆኑን አረጋግጣለች።
መግለጫው ጥቃቱ የተሰነዘረው ከአንዲት አጎራባች ሀገር ግዛት መሆኑን የሚጠቁሙ ሪፖርቶችን በመጥቀስ፣ "ጥልቅ ስጋትና ውግዘቷን" ገልጻለች። የሱዳን መንግስት ቀደም ብሎ ለጥቃቶቹ ኢትዮጵያን በቀጥታ መክሰሱ ይታወሳል።
የግብፅ መግለጫ እንዲህ ያሉ ድርጊቶች የግጭቱን አድማስ በማስፋት ወደ ጎረቤት አካባቢዎች ሊያሰፉ እንደሚችሉ አስጠንቅቃለች። ይህም በዩናይትድ ስቴትስ የሚመራውና "ኳርትት" (Quartet) በተሰኘው ጥምረት አማካኝነት የተሟላ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስና ከውጭ ጣልቃ ገብነት ነፃ የሆነ፣ በሱዳናውያን ባለቤትነት የሚመራ አጠቃላይ የፖለቲካ ሂደት ለመጀመር የሚደረገውን ዓለም አቀፍ ጥረት እንደሚያደናቅፍ ገልጻለች።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ፣ ግብፅ በማንኛውም የሱዳን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ገብነትን እንደምትቃወም በድጋሚ ገልጻለች። የሱዳን አንድነትና ሉዓላዊነት ሊከበር እንደሚገባ፣ እንዲሁም የመልካም ጉርብትና መርሆችና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቻርተር መከበር እንዳለባቸው አፅንኦት ሰጥታለች።
በመጨረሻም፣ ግብፅ ቀውሱን ለመቆጣጠር የሚደረጉ ማናቸውንም ጥረቶች እንደምትደግፍ ገልጻ፣ ውጥረቶችን ለማርገብ እና ለሱዳን ህዝብ ሰላምና መረጋጋትን የሚያረጋግጡ ሰላማዊ መፍትሄዎችን ቅድሚያ ለመስጠት ከባልደረባ አካላት ጋር በቁርጠኝነት መስራቷን እንደምትቀጥል አስታውቃለች።
ከመደበኛው አሰራር ውጭ በድርድር የሚያሳፍሩ የኤሌክትሮኒክ ታክሲዎችን ወደ ስርዓት ለማስገባት ደንብ እየተዘጋጀ ይገኛል ተባለ
ከመደበኛው አሰራር ውጪ በታሪፍ ክፍያ የሚያስከፍሉ የኤሌክትሮኒክ ታክሲዎች ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዲስ አበባ ትራንስፓርት ቢሮ አስታውቋል።የቢሮው ምክትል ሃላፊ እና የኦፕሬሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት የትራንስፖርት ህግና ደንብን ጥሰው በሚገኙ አካላት ላይ የቁጥጥር ስራ ይከናወናል።
በተለይም የዲጂታል ፍቃድ ወስደው በሚሰሩ የሜትር ታክሲ መኪኖች ላይ በተለየ መልኩ የቁጥጥር ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አቶ ዳኛቸው ገልፀው በቀን ቢያንስ ከ 5 መቶ እስከ 6 መቶ የሚደርሱ የቅጣት እርምጃዎች እንደሚወሰዱ ተናግረዋል።በዚህም በርካት ድርጅቶች ወደ ትክክለኛው መስመር እየገቡ መሆናቸው የተገለፀ ቢሆንም ችግሩ ግን ሙሉ ለሙሉ እንዳልተፈታ ተነግሯል።
እነዚህ መኪኖች በድርድር እንዲሰሩ የሚፈቅድ የህግ አሰራር አለመኖሩን አቶ ዳኛቸው ጠቅሰው በዚህ ተግባራቸው የተነሳ በበርካታ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ዘንድ ቅሬታ እያስነሳ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።እየተደረገ ካለው የቁጥጥር ስራ ባለፈ አሁን ላይ ችግሩን ሙሉ ለሙሉ ለመፍታት የሚያስችል ደንብ እየተዘጋጀ ይገኛል ሲሉ አቶ ዳኛቸው ጨምረው ለጣቢያችን አስረድተዋል።
ከፕሪቶሪያው ስምምነት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ የጦር ጄቶች በመቐለ ሰማይ ላይ ዛሬ መታየታቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ
ጄቶቹ በራራ ያደረጉት ህወሓት የትግራይ ክልል ምክር ቤት ስብሰባን በመጥራት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤልን የክልሉ ፕሬዝዳንት አድርጎ በመረጠበት ወቅት ላይ መሆኑ ታውቋል።
በመቐለ ትናንት ምሽት የቦምብ ፍንዳታ መድረሱን የከተማይቱ ፖሊስ አረጋገጠ
በትግራይ ክልል፣ መቐለ ከተማ፣ ዛሬ ምሽት ሁለት ሰዓት ገደማ የቦምብ ፍንዳታ መከሰቱን የከተማይቱ ፖሊስ ገለጸ።
ፍንዳታው የደረሰው በትግራይ ክልል ምክር ቤት እና በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት መካከል ባለ ቦታ ላይ እንደሆነ የከተማይቱ ፖሊስ አስታውቋል።
ፖሊስ ይህን ከማስታወቁ አስቀድሞ ክስተቱን በተመለከተ በማህበራዊ የትስስር ገጾች የተጋሩ መረጃዎች፤ የቦምብ ፍንዳታው የደረሰው በትግራይ ክልል ምክር ቤት ውስጥ እንደሆነ አመልክተው ነበር። ይህን በተመለከተ ከ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ጥያቄ የቀረበላቸው የመቐለ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ሀዱሽ ህዱግ መረጃዎቹን አስተባብለዋል።
የቦምብ ፍንዳታው የደረሰው የክልሉ ም/ቤትና የጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤቱን ከሚለየው አስፋልት 500 ሜትር ርቆ ካለ ቦታ ላይ እንደሆነ ኮማንደር ሀዱሽ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። በፍንዳታው በሰውም ሆነ በንብረት ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ የገለጹት ኮማንደሩ፤ የከተማው ፖሊስ ድርጊቱን ማን እንዳፈጸመው በማጣራት ላይ መሆኑን አስረድተዋል።
የዛሬ ምሽቱ የቦምብ ፍንዳታ የደረሰው፤ በ2012 ዓ.ም. በተካሄደ አወዛጋቢ ምርጫ የተቋቋመው የትግራይ ክልል ምክር ቤት፤ በነገው ዕለት አስቸኳይ ስብሰባ ሊያካሄድ እንደሆነ በማህበራዊ ገጾች መረጃዎች ሲዘዋወሩ መዋሉን ተከትሎ ነው።
የክልሉ ምክር ቤቱ ስብሰባ ነገ ማክሰኞ እንደሚካሄድ ቢነገርም፤ “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያነጋገረቻቸው ቀድሞ የህወሓት፣ አሁን ደግሞ የስምረት ፓርቲ አባል የሆኑ የምክር ቤት አባላት ግን ምንም ዓይነት ጥሪ እንዳልደረሳቸው ገልጸዋል። (ዘገባው የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ነው)
ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል የትግራይ መንግስት ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ!
ዛሬ በተካሄደው 6ኛው ዘመን 6ኛው መደበኛ የትግራይ ምክር ቤት ጉባኤ ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል በአብዛኛው ድምፅ የክልሉ ፕሬዝዳንት ሆነው በይፋ ተመርጠዋል።
በዚሁ ስብሰባ ላይ ወይዘሮ ኪሮስ ሐጎስ አፈ-ጉባኤ፣ ወይዘሮ ምህረት በርሄ ደግሞ ምክትል አፈ-ጉባኤ ሆነው ተሰይመዋል።
ምክር ቤቱ ስራውን በይፋ የጀመረው የፕሪቶሪያው ስምምነት በፌደራል መንግስቱ በኩል ተጥሷል በሚል ሲሆን፣ አዲሱ ፕሬዝዳንትም እስከ ቀጣዩ ስብሰባ ድረስ በአስፈፃሚው አካል ላይ አስፈላጊውን ማስተካከያና ሹመት እንዲያደርጉ ሙሉ ስልጣን ተሰጥቷቸዋል።
ይህ እርምጃ በትግራይ ፖለቲካዊ መድረክ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ሲሆን፣ ከፌደራል መንግስቱ ጋር ያለውን ግንኙነት ወዴት ሊያመራው እንደሚችል የብዙዎች መነጋገሪያ ሆኗል።
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
