ar
Feedback
Hule Business Review ( HBR)

Hule Business Review ( HBR)

الذهاب إلى القناة على Telegram

ትክክለኛዉ የሁሌ አዲስ ሚዲያ ገፆች Facebook : bit.ly/42rUuKj WhatsApp : bit.ly/Huleadis_whatsapp YouTube : bit.ly/3p7kj3N Twitter : bit.ly/3NVMRrB Telegram: bit.ly/Huleadis_tele ለጥቆማ ና አስተያየት እንዲሁም ለማስታወቂያ ስራ ተከታዮን አድራሻ ይጠቀሙ bit.ly/3VMy7x7

إظهار المزيد
2 210
المشتركون
-224 ساعات
-77 أيام
-2930 أيام

جاري تحميل البيانات...

سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
يوليو '26
يوليو '26
+4
في 0 قنوات
يونيو '26
+4
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '26
+5
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+4
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '26
+17
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+5
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '26
+9
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+17
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+21
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '25
+11
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '25
+19
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '25
+11
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '25
+15
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '25
+13
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '25
+16
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '25
+24
في 2 قنوات
Get PRO
مارس '25
+26
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '25
+16
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '25
+22
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '24
+26
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '24
+34
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '24
+45
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '24
+35
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '24
+54
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '24
+27
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '24
+29
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '24
+35
في 1 قنوات
Get PRO
أبريل '24
+62
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '24
+47
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '24
+31
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '24
+55
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '23
+67
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '23
+21
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '23
+28
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '23
+18
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '23
+38
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '23
+71
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '23
+61
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '23
+61
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '23
+42
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '23
+47
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '23
+53
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '23
+64
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '22
+46
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '22
+79
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '22
+73
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '22
+74
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '22
+101
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '22
+147
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '22
+86
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '22
+72
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '22
+64
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '22
+54
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '22
+93
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '22
+28
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '21
+28
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '21
+51
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '21
+42
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '21
+38
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '21
+42
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '21
+69
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '21
+62
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '21
+40
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '21
+34
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '21
+50
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '21
+36
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '21
+42
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '20
+6 755
في 0 قنوات
التاريخ
نمو المشتركين
الإشارات
القنوات
23 يوليو0
22 يوليو0
21 يوليو0
20 يوليو0
19 يوليو0
18 يوليو0
17 يوليو+1
16 يوليو+1
15 يوليو0
14 يوليو0
13 يوليو+1
12 يوليو+1
11 يوليو0
10 يوليو0
09 يوليو0
08 يوليو0
07 يوليو0
06 يوليو0
05 يوليو0
04 يوليو0
03 يوليو0
02 يوليو0
01 يوليو0
منشورات القناة
ለፈተና ትቀመጣላችሁ ተብሏል! በቀድሞው ዲፕሎማ ወይም ከ12+2 ወይም ከ10+3 የተመረቁና ትክክለኛነቱ የተረጋገጠ የትምህርት ማስረጃ ኖሯቸው ነገር ግን የደረጃ ስድስት የብቃት ማዕቀፍ ሳይኖራቸው በመጀመሪያ ዲግሪ ተምረው የተመረቁ ተማሪዎችን የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥ የሚያስችል መመሪያ ሊዘጋጅ ነው፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር አስተያየት እንዲሰጥበት ይፋ ባደረገው የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫና የአቻ ግመታ መመሪያ ማሻሻያ ላይ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ የተመረቁና የመውጫ ፈተና ተፈትነው ያለፉ ተማሪዎች የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑም ተጠቁሟል፡፡ እንዲሁም ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ሳይፈተኑ የመጀመሪያ ዲግሪ፣ የሁለተኛ ዲግሪ እንዲሁም የሦስተኛ ዲግሪ የያዙ ተማሪዎች ሚኒስትሩ በሚያወጣው የትምህርት ደረጃ ፈተና ተፈትነው ሲያልፉ የትምህርት ማስረጃቸው የሚረጋገጥላቸው እንደሚሆነም አስፍሯል፡፡ ይህ ማሻሻያ መመሪያ የትምህርት ማስረጃ ሰነድ ማረጋገጫ ሂደቶችን በአስፈላጊነቱ አገልግሎት ለመስጠትና ለማሻሻል አስፈላጊ በመሆኑ የተዘጋጀ መሆኑንም ተገልጿል፡፡ የማሻሻያ መመሪያው በኢትዮጵያ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ ማንኛውም የመንግስትና የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተመረቁ ተማሪዎች ላይ የሚተገበር ነው፡፡ እንዲሁም በዲግሪ መግቢያ መስፈርት የተቀመጠውን የደረጃ ስድስት የብቃት ማረጋገጫ ፈተና ሳይወስዱ ዲግሪ ተምረው የተመረቁትን፤ ወይም በዲግሪ ትምህርት ከተመዘገቡ በኋላ የደረጃ ስድስት የብቃት ማረጋገጫ ፈተና የወሰዱትን ተመራቂዎች የሚያጠቃልል ነው፡፡

2
በአዲስ አበባ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% መደረጉ ተገለጠ ከ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቤት ኪራይ ገበያ ላይ የሚታየውን ያልተገባ አሰራር በዘላቂነት ለመግታትና የነዋሪዎችን የኑሮ ጫና ለማቃለል ያለመ አዲስ መመሪያ ይፋ አድርጓል። በዚህም መሠረት ለ2019 በጀት ዓመት የሚተገበረው ዓመታዊ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ብቻ ሆኖ እንዲገደብ መወሰኑን የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታውቋል። * ቀደም ሲል በወጣው የቤት ኪራይ ቁጥጥር አዋጅ መሠረት፣ የአከራይና ተከራይ አዲስ የውል እድሳት ምዝገባ ከዛሬ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም ክፍለ ከተሞች በሚገኙ የቤቶች አስተዳደር ፅሕፈት ቤቶች በይፋ መተግበር ጀምሯል። * ቢሮው እንዳመለከተው፤ ይህ የዋጋ ማስተካከያ የተደረገው በዘፈቀደ ሳይሆን፣ የሕዝቡን እውነተኛ የመክፈል አቅምና ወቅታዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ ያገናዘበ ሰፊ ሳይንሳዊ ጥናት ከተካሄደ በኋላ ነው። * አዲሱ አሰራር በአንድ በኩል አከራዮች ፍትሐዊና ተመጣጣኝ ገቢ እንዲያገኙ የሚያስችል ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ ተከራዮች ካልተገባ የዋጋ ጭማሪና ከማኅበራዊ ቀውስ ድነው የተረጋጋ ሕይወት እንዲመሩ ያግዛል። "የአከራይ-ተከራይ ግንኙነትን በሕግ ማዕቀፍ በመምራት የጋራ ተጠቃሚነትን እናረጋግጣለን!" ይህ ርምጃ በከተማዋ እየተስተዋለ ያለውን የኑሮ ውድነት ጫና በከፍተኛ ደረጃ የመቀነስ፣ የጎላ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የመልካም አስተዳደር ፋይዳዎች እንዳሉት ተገልጿል። ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት የጭማሪው ማሳያ ምሳሌዎች (በ11.5% ስሌት መሠረት)፦ አዲሱ አዋጅ በሚፈቅደው ከፍተኛው የ11.5% የኪራይ ጭማሪ ጣሪያ መሠረት የወደፊቱ ክፍያ በሚከተለው መልኩ ይተመናል፦ 1. በአሁኑ ወቅት የቤት ኪራይ 15,000 ብር ለሚከፍሉ ተከራዮች ፦ ህጋዊው የጭማሪ መጠን 1,725 ብር ብቻ ስለሚሆን አዲሱ ጠቅላላ የቤት ኪራይ 16,725 ብር ይሆናል ማለት ነው። 2. በአሁኑ ወቅት የቤት ኪራይ 10,000 ለሚከፍሉ ተከራዮች ህጋዊው የጭማሪ መጠን 1,150 ብር ብቻ ስለሚሆን አዲሱ ጠቅላላ የቤት ኪራይ 11,150 ብር ይሆናል ማለት ነው። 3. በአሁኑ ወቅት የቤት ኪራይ 20,000 ብር ለሚከፍሉ ተከራዮች ህጋዊው የጭማሪ መጠን 2,300 ብር ብቻ ስለሚሆን አዲሱ ጠቅላላ የቤት ኪራይ 22,300 ብር ይሆናል። 4. በአሁኑ ወቅት የቤት ኪራይ 5,000 ብር ለሚከፍሉ ተከራዮች ህጋዊው የጭማሪ መጠን 575 ብር ብቻ በመሆኑ፣ አዲሱ አጠቃላይ ክፍያቸው ከ 5,575 ብር ይሆናል::
421
3
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሊዮን በረራ ጀመረ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፈረንይ ሊዮን ከተማ የመንገደኞች በረራ አገልግሎት ማስጀመሩን ይፋ አድርጓል። ይህም ለአየር መንገዱ በፈረንሳይ 3ኛ፣ በ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሊዮን በረራ ጀመረ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፈረንይ ሊዮን ከተማ የመንገደኞች በረራ አገልግሎት ማስጀመሩን ይፋ አድርጓል። ይህም ለአየር መንገዱ በፈረንሳይ 3ኛ፣ በአውሮፓ 23ኛ እንዲሁም የዓለም አቀፍ መዳረሻዎቹን ቁጥር 146 የሚያደርሰው መሆኑ ተመላክቷል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው በወቅቱ እንዳሉት፤ የበረራ አገልግሎቱ መጀመር አየር መንገዱ አፍሪካን ከዓለም ጋር የማገናኘት ጉዞው ተጨማሪ ስኬት ነው። ወደ ሊዮን የጀመረው በረራ ለዓለም አቀፍ ተጓዦች ተጨማሪ ዕድል የሚፈጥር ስለመሆኑም አብራርተዋል፡፡ መንገደኞችን ከማመላለስ ባሻገር የሀገራት ሁለንተናዊ ትስስሮች እንዲጠናከሩ አቅም መፍጠር እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡
548
4
ዜና፦ ቮዳኮም በሳፋሪኮም ውስጥ ያለውን የአብላጫ ድርሻ ግዥ ማጠናቀቁን ገለጸ፤ በኢትዮጵያ ያለውን የማደግ ፍላጎትም ጠቅሷል ​በደቡብ አፍሪካ መሥሪያ ቤቱን ያደረገው ቮዳኮም ግሩፕ  በሳፋሪኮም ኃ/የተ/የግል ማኅበር ውስጥ የነበረውን ድርሻ በ20% በማሳደግ፣ ጠቅላላ የባለቤትነት ድርሻውን ወደ 55% አካባቢ ማድረሱንና በኬንያ እና በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሰውን የቴሌኮሙኒኬሽን ኩባንያ የአብላጫ ባለቤትነት መብት መረከቡን አስታውቋል። ​ኩባንያው ሰኔ 23 ቀን  ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ሰኔ 19 ቀን የኬንያ የይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ቀደም ሲል ተጥሎ የነበረውን ዕገዳ ማንሳቱንና የቀሩት ቅድመ ሁኔታዎች በሙሉ መሟላታቸውን ተከትሎ ግብይቱ በይፋ መጠናቀቁን ገልጿል። ​እንደ ኩባንያው ገለጻ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ በታኅሣሥ 2018 ዓ.ም  ይፋ የተደረገው ይህ የ2.1 ቢሊዮን ዶላር ስምምነት፤ ከኬንያ መንግሥት የ15% ድርሻን እንዲሁም ከቮዳፎን ግሩፕ የ5% ድርሻን በአንድ አክሲዮን በ34 የኬንያ ሺሊንግ መግዛትን ያጠቃልላል። የኬንያ መንግሥት በናይሮቢ የአክሲዮን ገበያ ላይ ተመዝግቦ የሚገኘውን የሳፋሪኮምን 20% ድርሻ ይዞ ይቀጥላል። ​ቮዳኮም ይህ ግዥ የሳፋሪኮምን የፋይናንስ ውጤቶች በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሪፖርት አቀራረብ ደረጃዎች (IFRS) መሠረት እንደ ተባባሪ ኩባንያ ከመቁጠር ይልቅ፣ በቀጥታ ከራሱ የሒሳብ መግለጫዎች ጋር አጠቃሎ ለማሳየት እንደሚያስችለው ገልጿል። ​ኩባንያው ይህ ግዥ በምሥራቅ አፍሪካ ያለውን ተደራሽነት እንደሚያጠናክርለት የገለጸ ሲሆን፣ በተለይም ሳፋሪኮም ወደ ሀገሪቱ የቴሌኮም ዘርፍ ከገባ ጀምሮ ወደ 14 ሚሊዮን ገደማ ደንበኞችን ያፈራባትን ኢትዮጵያን እንደ ዋና የማደጊያ ገበያ ጠቅሷታል። ​የቮዳኮም ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሻሚል ጁሱብ ግብይቱ “በኬንያ እና በኢትዮጵያ የዲጂታል እና የፋይናንስ አካታችነትን በሰፊው ለማሳደግ አዳዲስ ዕድሎችን ይከፍታል” ያሉ ሲሆን፣ ኩባንያው ሥራውን እያሰፋ ሲሄድ ከሁለቱም ሀገራት መንግሥታት ጋር አብሮ ለመሥራት እንደሚፈልግ አክለዋል። ​
463
5
የዱባይ ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ ለመግባት ዝግጅት እያደረጉ መሆኑ ተገለጠ ​በአቡ ዳቢ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እንደገለጸው፣ የዱባይ ንግድ ምክር ቤት አባል የሆኑ ኩባንያዎች፣ ሀገሪቱ የፋይናንስ ዘርፉን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ለማድረግ የወሰነችውን ውሳኔ ተከትሎ “ወደ ኢትዮጵያ የፋይናንስ እና የባንክ ዘርፍ ለመግባት ዝግጅት” ጀምረዋል። ​በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች  የኢትዮጵያ አምባሳደር ጀማል በከር፣ ከዱባይ ንግድ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ መሐመድ አሊ ራሺድ ሉታህ ጋር ዛሬ ተወያይተዋል። ኤምባሲው እንደገለጸው፣ ውይይቱ ከዱባይ የሚመጣውን ኢንቨስትመንት ለማመቻቸት ቀደም ሲል ከተደረጉ ስብሰባዎች ቀጣይነት ያለው ሲሆን፣ በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደውን የ“ዱባይ-ኢትዮጵያ ቢዝነስ ኮኔክት” መድረክን ውጤት የተመለከተ ነው። ​ሉታህ በ36 አባላት የተዋቀረ የንግድ ልዑካን ቡድንን በመምራት በቅርቡ በአዲስ አበባ ስላደረጉት ጉብኝት አንስተው፤ ልዑካን ቡድኑ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በተግባር መመልከቱን ኤምባሲው ጠቅሷል። ​እሳቸውም ማሻሻያዎቹ “ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢ አየር” መፍጠራቸውንና ይህም በዱባይ በሚገኙ ባለሀብቶች ዘንድ “ከፍተኛ መነቃቃትን” መፍጠሩን ገልጸዋል። ​ይህንን ተከትሎም በምክር ቤቱ ስር ያሉ “ትላልቅ ኩባንያዎች” በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ላይ ለመሰማራት ፍላጎት ማሳየታቸውን እና በቅርቡ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ወደተደረገው የኢትዮጵያ “የፋይናንስ እና የባንክ ዘርፍ” በይፋ ለመግባት “ከፍተኛ ዝግጅት መጀመራቸውን” አስታውቀዋል። ​ኤምባሲው አክሎም፣ አምባሳደር ጀማል የዱባይ ንግድ ምክር ቤት በአዲስ አበባ ጉብኝቱ ወቅት ላመቻቸው የንግድ ለንግድ  ትስስር ምስጋና ማቅረባቸውን የገለጸ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ መንግሥት በፋይናንስ፣ በግብርና፣ በታዳሽ ኃይል እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች ላይ ዕድሎችን ለሚፈልጉ የዱባይ ኩባንያዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እና የኢንቨስትመንት ማበረታቻዎችን ለመስጠት ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።
331
6
ስደተኞችን የተቃወመው የደቡብ አፍሪካውያን ሠላማዊ የተባለሠልፍ በተለያዩ አካባቢዎች እየተጀመረ ነው። የደቡብ አፍሪካ መገናኛ ብዙኃን ከማለዳው ጀምሮ ስደተኞችን በተቃወመው የደቡብ አፍሪካውያን አስፈሪ
ስደተኞችን የተቃወመው የደቡብ አፍሪካውያን ሠላማዊ የተባለሠልፍ በተለያዩ አካባቢዎች እየተጀመረ ነው። የደቡብ አፍሪካ መገናኛ ብዙኃን ከማለዳው ጀምሮ ስደተኞችን በተቃወመው የደቡብ አፍሪካውያን አስፈሪ የተቃውሞ ሠልፍ ዙሪያ የሚያጠነጥኑ ሽፋኖችን በመስጠት ተጠምደዋል። በተለይም በጠዋቱ የዘገባ ሠዓታቸውየደቡብ አፍሪካ ፖሊስ ሙሉ በሙሉ ተዘጋጅቶ የተቃውሞ ሠልፉ ወደመጥፎ ክስተት እንዳይቀየር እየሰራ ስለመሆኑ በተለያዩ ከተማዎች ያሉ ሁኔታዎችን በማሳየት በስፋት ሲዘግቡተስተውለዋል። ከደቂቃዎች በፊት እየተሰሙ ያሉ መረጃዎች የማርች ኤንድ ማርች ንቅናቄ የሚመራው የተቃውሞ ሠልፍ በደርባን ኢተክዊኒ እና ምስራቅ ኬፕታውን አካባቢ ተጀምሯል። አፍሪካን ሬኔሳንስ ቴሌቪዥን ባገኘው መረጃ ሠልፉ በስፋት እንደሚከናወን ከተነገረባቸው ከተሞች አንዷበሆነችው ፕሪቶሪያ ፤ በተለይም የስደተኛ ሱቆች ሙሉ በሙሉ ማለት ይቻላል ተዘግተዋል።እንዲሁም በአካባቢው ያሉ የፀጥታ ኃይሎች በተጠንቀቅ ቆመው እየታዩ ነው። (Arts TV)
302
7
ቤተሳይዳ አሜሪካን ሜዲካል ፕላዛ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የ‘ጄሲአይ’ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ማግኘቱ ተነገረ ቤተሳይዳ አሜሪካን ሜዲካል ፕላዛ ከጆይንት ኮሚሽን ኢንተርናሽናል (ጄሲአይ) የላቀ የሕክምና አገልግሎት ጥራትና የሕሙማን ደህንነት ማረጋገጫ ዕውቅና በማግኘት በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሆስፒታል ሆኗል። ይህ በሀገሪቱ የጤናው ዘርፍ ትልቅ ምዕራፍ ተብሎ የተጠቀሰው ስኬት የተሰማው ሆስፒታሉ የተመሰረተበትን አንደኛ ዓመት ባከበረበት ወቅት ነው። የጄሲአይ ዕውቅና በዓለም አቀፍ ደረጃ በጤና ተቋማት የጥራት ቁጥጥርና የሕሙማን ደህንነት ጥበቃ ረገድ እጅግ ከፍተኛውና ተደራሽ ለመሆን አስቸጋሪው መመዘኛ እንደሆነ ይታወቃል። አንድ የሕክምና ተቋም ይህንን ዕውቅና ለማግኘት የክሊኒካዊ እንክብካቤ ደረጃን፣ የኢንፌክሽን መከላከያና መቆጣጠሪያ ስልቶችን፣ የመድኃኒት አያያዝን፣ የተቋማዊ አመራር ብቃትንና አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸምን ጨምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ ጥብቅ መስፈርቶችን ማሟላት ይጠበቅበታል። ይህንን ስኬትና የሆስፒታሉን አንደኛ ዓመት በዓል አስመልክቶ በተዘጋጀው ሥነ-ሥርዓት ላይ የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላትና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች ተገኝተዋል። በወቅቱ ንግግር ያደረጉት ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የተገኘው ዕውቅና ለኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ ትልቅ ኩራት መሆኑን ገልጸው፣ ሀገሪቱ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁና የሕሙማንን ደህንነት የሚያረጋግጡ የሕክምና ተቋማትን መገንባትና ማስተዳደር እንደምትችል ማረጋገጫ ነው ብለዋል። አክለውም መንግሥት የሀገሪቱን የሕክምና አገልግሎት ደረጃ ከፍ ለሚያደርጉና በጥራት ላይ ለሚሰሩ የግል የጤና ተቋማት አስፈላጊውን ድጋፍና ማበረታቻ ማድረጉን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። የሆስፒታሉ አመራሮች በበኩላቸው፣ ይህንን ዓለም አቀፍ ዕውቅና ለማግኘት በሕክምና ሥርዓቱ፣ በመሰረተ ልማት እና በባለሙያዎች ልማት ላይ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ መፈሰሱን ገልጸዋል። ስኬቱ የተገኘውም ከመላው የሕክምናና የአስተዳደር ሰራተኞች የተቀናጀ ጥረትና ለላቀ አገልግሎት ከነበራቸው ቁርጠኝነት በመነጨ እንደሆነ ጠቅሰዋል። ይህ ዕውቅና ቤተስዳ ሆስፒታልን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተገዢነታቸውን ካረጋገጡ ጥቂት ተቋማት ተርታ የሚያሰልፈው ሲሆን፣ በሀገሪቱ የመንግሥትም ሆነ የግል የጤና ተቋማት የሕክምና ጥራትንና የአሠራር ሥርዓትን እንዲያሻሽሉ ምሳሌ እንደሚሆን የዘርፉ ባለሙያዎች ገልጸዋል። ስኬቱ የኅብረተሰቡን በሀገር ውስጥ ሕክምና ላይ ያለውን እምነት ከማሳደጉም በላይ፣ ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና በሕክምናው ዘርፍ ያላትን ስም እንደሚያጠናክረው ይጠበቃል።
349
8
+2
لا يوجد نص...
472
9
ማዕከላዊ ባንኩ ለአራተኛው ሩብ ዓመት 200 ሚሊዮን ዶላር ሊያቀርብ ነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የ2018 በጀት ዓመት የመጨረሻ ሩብ ዓመት የውጭ ምንዛሬ ጨረታ መርሃ-ግብርን ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ ለ
ማዕከላዊ ባንኩ ለአራተኛው ሩብ ዓመት 200 ሚሊዮን ዶላር ሊያቀርብ ነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ  የ2018 በጀት ዓመት የመጨረሻ ሩብ ዓመት የውጭ ምንዛሬ ጨረታ መርሃ-ግብርን ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ ለዚሁ ተግባር 200 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር መመደቡን አስታውቋል። ይህ የተመደበው በጀት በሙሉ በሰኔ ወር 2018 ዓ.ም ውስጥ ጥቅም ላይ የሚውል መሆኑን ባንኩ ገልጿል። ​የማዕከላዊ ባንኩ መግለጫ እንዳመለከተው፣ ይህ አዲስ የአቅርቦት ስትራቴጂ በበጀት ዓመቱ መጠናቀቂያ ላይ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ለማረጋጋት ታሳቢ ያደረገ ነው። ​ባንኩ ባለፈው ዓመት ህዳር ወር ይፋ ካደረገው 520 ሚሊዮን ዶላር አቅርቦት አንጻር፣ በሦስተኛው ሩብ ዓመት የነበረው አሰራር በእያንዳንዱ ጨረታ 70 ሚሊዮን ዶላር በስድስት ክፍለ-ጊዜዎች መከፋፈሉ ይታወሳል። ይሁን እንጂ አሁን ባለው የሰኔ ወር ዕቅድ መሠረት፣ አጠቃላይ 200 ሚሊዮኑ ዶላር በሁለት ዋና ዋና ጨረታዎች ተከፋፍሎ ይቀርባል፤ ይህም በእያንዳንዱ የጨረታ መስኮት 100 ሚሊዮን ዶላር እንዲኖር ያደርጋል ተብሏል።
388
10
በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች በ500,000 እና 400,000 ብር ዋስ እንዲፈቱ ተወሰነ። መንሱር ጀማል የተባለው ተከሳሽ ግን አቃቢ ህግ መቃወሚያ ስላቀረበበት ዛሬ ከሰዓት ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ለመስጠት ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ ከድርጅቱ ጋር በተያያዘ በ1.9 ቢሊዮን ብር የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ ታዋቂ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች፣ የዋስትና መብታቸው ተከብሮ በውጭ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ዛሬ በዋለው ችሎት ፈቅዷል። ባለፈው ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ከ5 ተከሳሽ መንሱር ጀማል ውጭ ባሉ ተጠርጣሪዎች ከሀገር እንዳይወጡ እና ከፍ ያለ ዋስትና አስይዘው የዋስትና መብታቸው ተከብሮ ከውጭ ሆነው ጉዳያቸውን ቢከታተሉ እንደማይቃወም አስረድቶ እንደነበር ይታወሳል። ዛሬ በዋለው ዝግ ችሎት ተርጣሪዎቹ የዋስትና መብታቸው ተከብሮላቸው፣ ከእስር ተፈትተው በውጭ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ፍርድ ቤቱ ወስኗል። በዚህ መሠረት ከአንድ እስከ አራት ያሉ ተከሳሾች ማለትም ሰራዊት ፍቅሬ፣ ሰለሞን ቦጋለ፣ ይገረም ደጀኔና ዳንኤል ተገኝ በ500 ሺህ ብር ዋስ እንዲወጡ ሲፈቀድላቸው። ስድስተኛና ሰባተኛ ተከሳሽ አብርሀም ግዛውና ካሊድ ናስር በ400 ሺህ ብር እንዲወጡ ፍርድ ቤቱ መወሰኑን ጠበቃ አበባው አበበ ነግረውናል። አምስተኛ ተከሳሽ መንሱር ጀማል በተመለከተ አቃቢ ህግ ባቀረበው መቃወሚያ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ዛሬ 8 ሰዓት ቀጠሮ መሰጠቱን ጠበቃ አበባው አበበ ተናግረዋል፡፡ ሁሉም ተከሳሾች ከሃገር እንዳይወጡ እገዳም ተጥሎባቸዋል ተብሏል። (ገዛ ጌታሁን - ሸገር ኤፍኤም)
570
11
መቐለ : ዛሬ ጠዋት ምን ተፈጠረ? የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመንገደኞች አውሮፕላን ዛሬ ጧት ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ወደ መቐለ ከበረረ በኋላ አሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ሳያርፍ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰ። አውሮፕላኑ አሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ማረፍ ያልቻለው፣ ከአውሮፕላን ማረፊያው የኮሚንኬሽን መሳሪያ ብልሽት ጋር በተያያዘ መኾኑን የአየር መንገዱ ሃላፊዎች እንደነገሩት ጠቅሶ የዘገበው ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ነው። ኾኖም ከሰዓታት በኋላ የኮምንኬሽን መሳሪያው ብልሽት በመስተካከሉ አውሮፕላኑ ወደ መቐለ መጓዙን እንደተረዳ ምንጩ ጠቅሷል።
513
12
በታዋቂው የሙዚቃ አቀናባሪ ካሙዙ ካሣ እና በሻኩራ ፕሮዳክሽን ላይ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የንብረት እና የባንክ ሂሳብ እገዳ መጣሉ ተሰማ። ይህ እርምጃ የተወሰደው "ኢትዮጵያ" በተሰኘው የባህል
በታዋቂው የሙዚቃ አቀናባሪ ካሙዙ ካሣ እና በሻኩራ ፕሮዳክሽን ላይ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የንብረት እና የባንክ ሂሳብ እገዳ መጣሉ ተሰማ። ይህ እርምጃ የተወሰደው "ኢትዮጵያ" በተሰኘው የባህል ማስተዋወቅ ፕሮጀክት ላይ በተሳተፉ 37 አርቲስቶች የቀረበባቸውን የ30.8 ሚሊዮን ብር ክስ ተከትሎ ሲሆን፣ አርቲስቶቹ በቻይና እና በሩሲያ ጨምሮ በተለያዩ ሀገራት 11 የባህል ትርኢቶችን ቢያቀርቡም የተስማሙበት ክፍያ እና የልምምድ አበል እንዳልተከፈላቸው ገልጸዋል። አቀናባሪ ካሙዙ ካሣ በበኩላቸው ክፍያዎችን በስምምነቱ መሠረት እየፈጸሙ መሆናቸውን በመጥቀስ ክሱን ቢያስተባብሉም፣ ፍርድ ቤቱ ግን ጉዳዩ በህግ ታይቶ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ በአቀናባሪው ስም ያሉ ማናቸውም ንብረቶች እና በአራት ባንኮች የሚገኙ የባንክ ሂሳቦች ለ20 ቀናት ታግደው እንዲቆዩ ትዕዛዝ አስተላልፏል።
491
13
" ለሚፈጠረው ችግር ሁሉ የጊዚያዊ አስተዳደሩን ስልጣን በጉልበት በመያዝ ላይ ያለው ኃይል መሆኑ እገልፃለሁ " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ ባለፈው ማክሰኞ ሚያዝያ 27/2018 ዓ.ም 'ነባር ምክር ቤትና መንግስት መልሻለሁ ' ያለውና ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር)ን የክልሉ ፕሬዝዳንት አድርጎ የሰየመው ህወሓት ዛሬ በደብረፅዮን (ዶ/ር) መሪነት በክልሉ የፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት የመጀመሪያውን የካቢኔ ስብሰባ ማካሄዱን አስታውቋል። በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር)  መሪነት የተከናወነው የካቢኔ ስብሰባ በክልሉ የዜና ማሰራጫዎች መነገሩ ተከትሎ በሰዓታት ልዩነት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) በፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፅ አጭር መልስ ሰጥቷል። የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ምን አሉ ? " በቅርብ ቀናት የተፈጠረው ሁኔታ ተከትሎ ሊመጣ የሚችለው ጉዳት ለማስቀረት ፤ ችግሩን በጋራ ውይይትና መግባባት ለመፍታት የቀረበውን ጥሪ ወደ ጎን በመተው 'የተመረጥኩኝ ነኝ ' የሚል አካል ዛሬ ሚያዝያ 30/2018 ዓ/ም የፀጥታ አካላት ጥበቃ ተሰጥቶት በጊዚያዊ አስተዳደሩ የመሰብሰብያ አዳራሽ የካቢኔ ስብሰባ ጀምሯል። ይህ ተግባር ቀጣይ አደገኛ መንገድ የተጀመረበት ቀን ስለሆነ በዚሁ ምክንያት ለሚከተለው አደጋ ሁሉ የጊዚያዊ አስተዳደሩን ስልጣን በጉልበት በመያዝ ላይ ያለ ኃይል መሆኑ እገልፃለሁ " ብለዋል። በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) መሪነት የተከናወነው የካቢኔ ስብሰባ በዜና ማሰራጫዎች መዘገቡን ተከትሎ ዛሬ አርብ ሚያዝያ 30/2018 ዓ.ም ከቀኑ 5:30 ለሁለተኛ ጊዜ የውግያ ጀት አውሮፕላን በመቐለ ከተማ ሰማይ ላይ መታየቱን የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባል ገልጿል።    
384
14
ወ/ሮ በረከት ወርቁ (በረከት ገበሬዋ)ን ጨምሮ 4 ሰዎችን በወንጀል እንደሚፈልጋቸው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ። ፖሊስ በከባድ የሙስና ወንጀል እንደሚፈልጋቸው ነው ያስታወቀው። ግለሰቦቹ፥ የኢ
ወ/ሮ በረከት ወርቁ (በረከት ገበሬዋ)ን ጨምሮ 4 ሰዎችን በወንጀል እንደሚፈልጋቸው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ። ፖሊስ በከባድ የሙስና ወንጀል እንደሚፈልጋቸው ነው ያስታወቀው። ግለሰቦቹ፥ የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ በገበያ ላይ የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት አድርገዋል ተብለው ክስ ከተመሰረተባቸው 13 ግለሰቦች መካከል ናቸው።
295
15
ሱዳን በሁለት የኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ ተጨማሪ ኃይልና የአየር መከላከያዎችን እያሰማራች መሆኑ ተገለጸ የሱዳን ጦር በምዕራብ ኢትዮጵያ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አዋሳኝ በሆነው በብሉ ናይል ግዛት እ
ሱዳን በሁለት የኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ ተጨማሪ ኃይልና የአየር መከላከያዎችን እያሰማራች መሆኑ ተገለጸ የሱዳን ጦር በምዕራብ ኢትዮጵያ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አዋሳኝ በሆነው በብሉ ናይል ግዛት እንዲሁም ከአማራ ክልል ጋር በሚዋሰነው አወዛጋቢው የአል-ፋሻጋ የድንበር አካባቢዎች ላይ ተጨማሪ ወታደሮችንና የአየር መከላከያዎችን እያሰማራ መሆኑ ተዘገበ። እንደ ብሉምበርግ ዘገባ የሱዳን ጦር በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው በብሉ ናይል ግዛት ተጨማሪ ወታደሮችንና የአየር መከላከያ መሣሪያዎችን አሰማርቷል። ተጨማሪ ለማንበብ አስታየት መስጫ ስር ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ። ​​
254
16
በአዲስአበባ የሚገኘዉ የፋኖ ክንፍ ቅሬታ አነሳ ለተሃድሶ እየተሰጠ ያለው ስልጠና አጥጋቢ አይደለም ሲል “በአማራ ክልል ትጥቅ ትግል” ላይ የነበረው እና አሁን ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጋር እየተወያየ
በአዲስአበባ የሚገኘዉ የፋኖ ክንፍ ቅሬታ አነሳ ለተሃድሶ እየተሰጠ ያለው ስልጠና አጥጋቢ አይደለም ሲል “በአማራ ክልል ትጥቅ ትግል” ላይ የነበረው እና አሁን ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጋር እየተወያየ ያለው ‛የፋኖ ክንፍ’ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በበኩሉ በጫካ ካሉ ከታጣቂዎች ጋር እያካሄደ ያለውን ግንኙነትን በተመለከተ አንዳንድ ጉዳዮች በግልጽ አይነገሩም ብሏል። ‛የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት’ ወታደራዊ አስተዳደር መምሪያ ሀላፊ እያሱ አባተ እንደገለጹት “ለተሃድሶ በትንሹ ዘጠና ቀናት መስጠት ነበረበት” ያሉ ሲሆን አሁን ላይ ግን እየተሰጠ ያለው ለሰባት ቀናት ብቻ መሆኑን ገልጸዋል። Via Ankuar Merja
335
17
ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ሊመጡ ነው የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ ሊመጡ መሆኑ ተዘግቧል የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኬንያ ና
ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ሊመጡ ነው የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ ሊመጡ መሆኑ ተዘግቧል የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኬንያ ናይሮቢ የሚካሄደውን "አፍሪካ ፎርዋርድ" ጉባኤ ካጠናቀቁ በኋላ፣ በመጪው ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለአጭር የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ ታውቋል። ፕሬዝዳንቱ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡት በጥንቃቄ የተመረጡ የፈረንሳይ ግዙፍ ኩባንያዎች መሪዎችን በማስከተል ሲሆን፣ ጉብኝቱም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ነው ይላል የካፒታል ዘገባ። በፕሬዝዳንቱ የታጀበው ልዑክ እንደ ካርፉር ያሉ ታዋቂ የችርቻሮ ንግድ ተቋማትን እና ሜሪዲያም የተሰኘውን የኢንቨስትመንት ድርጅት አመራሮችን ያካተተ ሲሆን፣ በተለይም ካርፉር ከኢትዮጵያው ሚድሮክ ጋር በፈጠረው የፍራንቻይዝ ስምምነት አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ ገበያ ለመግባት ማቀዱ የጉብኝቱ አንዱ ዋነኛ ትኩረት መሆኑ ተጠቁሟል።
291
18
የዓለም ጤና ድርጅት ማስጠንቀቂያ በአንድ የቱሪስት መርከብ ላይ በደረሰ የሀንታ ቫይረስ ወረርሽኝ የሦስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ተከትሎ፣ የዓለም ጤና ድርጅት ተጨማሪ ተጠቂዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ ማስጠን
የዓለም ጤና ድርጅት ማስጠንቀቂያ በአንድ የቱሪስት መርከብ ላይ በደረሰ የሀንታ ቫይረስ ወረርሽኝ የሦስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ተከትሎ፣ የዓለም ጤና ድርጅት ተጨማሪ ተጠቂዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል። የዓለም ጤና ድርጅት ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ በባሕር ላይ በሚጓዝ የቱሪስት መርከብ ውስጥ የተከሰተው ይህ ወረርሽኝ ለሦስት ተሳፋሪዎች ሞት ምክንያት ሆኗል። ድርጅቱ አክሎም፤ከሟቾቹ ጋር ንክኪ የነበራቸው ሌሎች ሰዎች ላይም የቫይረሱ ምልክቶች ሊታዩ እንደሚችሉ ስጋቱን ገልጿል። ይሁን እንጂ፤አስፈላጊው የጥንቃቄ እርምጃዎች በአግባቡ ከተወሰዱ የወረርሽኙን ስርጭት መገደብና በቁጥጥር ስር ማዋል እንደሚቻል ድርጅቱ አስታውቋል። የዓለም ጤና ድርጅት ሁኔታውን በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ ተሳፋሪዎችና የጉዞው አዘጋጆች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል። ሀንታ ቫይረስ አብዛኛውን ጊዜ ከአይጥ ዝርያዎች ወደ ሰው የሚተላለፍ ከባድ የጤና ችግር ሲሆን፣ ድርጅቱ የወረርሽኙን አድማስ ለማጥበብ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየሰራ መሆኑን ገልጿል ሲል የዘገበው TRT WORLD ነው።
306
19
የፍ/ቤት የክርክር መዝገብ እንዲዘጋ ተወሠነ በእነ ኃይሌ ገብረስላሴና በእነ ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ኦሎምፒክ ኮሚቴ መካከል የነበረው የፍ/ቤት የክርክር መዝገብ እንዲዘጋ ተወሠነ ከአንድ ዓመት በላይ የፈጀው በእነ ኃይሌ ገብረስላሴና በእነ ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ኦሎምፒክ ኮሚቴ መካከል የነበረው የፍ/ቤት ክርክር እንዲዘጋ ተወሠነ በእነ ኃይሌ ገብረስላሴና በእነ የተከበሩ ዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስ መካከል የተፈጠረው አለመግባባት በመደበኛ ፍ/ቤት ላሉፉት ሁለት ዓመታት ሲታይ መቆየቱ ይታወሳል። በእነዚህ ሁለት ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ እነ ኃይሌ በፍ/ቤት የኦሎምፒክን ማንኛውንም እንቅስቃሴ ሲያሳግዱ የእነ ዶክተር አሸብር ኦሎምፒክ በበኩሉ ዕገዳውን ሲያስነሳ ዓመታትን ቅርጥፍ አድርጎ መብላቱ ይታወሳል። አሁን ከደቂቃዎች በፊት ከሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል ታማኝ ምንጮች እንዳገኘነው ዜና ከሆነ ድል ወደእነ ዶክተር አሸብር እንዳዘነበለች ይጠቁማል። እንደ እነዚሁ ታማኝ የመረጃ ምንጮቻችን ከሆነ የሁለቱን ወገኖች ክስ ሲመረምር የነበረው የኢ.ፊ.ድ.ሪ የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ዛሬ በዋለው ችሎት በሁለቱ ወገንች መካከል የተከፈተው የክርክር መዝገብ እንዲዘጋና መዝገቡ ወደ መዝገብ ቤት እንዲመለስ ውሳኔ አሳልፏል። እንደ እነዚሁ ታማኝ የሀትሪክ የመረጃ ምንጮች ከሆነ ጉዳዩን ከአንድ ዓመት በላይ ሲመረምር የነበረው ፍ/ቤት ስፖርታዊ ጉዳዮች መፈታት ያለባቸው በስፖርቱ ህግና ደንቦች እንጂ በመደበኛ ፍ/ቤቶች አይደለም በማለት የክርክር መዝገቡ እንዲዘጋ ውሳኔ መተላለፉና መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መዝገብ ቤት እንዲመለስ የመጨረሻ ውሳኔ መሠጠቱን እነዚሁ ምንጮቻችን ጨምረው ገልፀውልናል። በቅርቡ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ከአስተዳደር ችግር ጋር በተያያዘ በተፈጠረ ችግር በደጋፊዎች ክስ ቢመሠረትም ጉዳዩ በሽምግልና ቢፈታም ጉዳዩን ወደ መደበኛ ፍ/ቤት የወሠዱት ከሳሾች ጉዳያቸውን በስፖርቱ ህግ የማይፈቱና ክሱን የማያነሱ ከሆነ ፌዴሬሽኑ ክለቡን አግዳለሁ ማለቱ የሚዘነጋ አይደለም። ✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
342
20
በትግራይ 6 ሺ ድርጅቶች ተዘግተው 100 ሺ ሠራተኞች ተበትነዋል -ቢሮው በትግራይ ክልል ከጦርነቱ በፊት ተቋቁመው ይንቀሳቀሱ የነበሩ 95 በመቶ የሚሆኑ የንግድ ድርጅቶችና ኢንዱስትሪዎች መውደማቸውን የክልሉ ኢንዱስትሪ ቢሮ ይፋ አደረገ። ቢሮው እንዳስታወቀው፣ የግጭት ማቆም ስምምነቱ በተሟላ ሁኔታ ተግባራዊ ባለመሆኑ ምክንያት ከ100 ሺሕ በላይ ሠራተኞችን የቀጠሩ ከ6 ሺሕ በላይ ድርጅቶች ተዘግተው ይገኛሉ። ዘርፉ በእዳ ጫና፣ በነዳጅና ጥሬ ዕቃ እጥረት፣ እንዲሁም በመሠረተ ልማት ውድመት ሳቢያ እስካሁን ማገገም እንዳልቻለ ተገልጿል። ምንም እንኳ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደርና የኢንዱስትሪ ቢሮው ችግሩ እንዲፈታና የባንክ ብድሮች እንዲሰረዙ ለፌዴራል መንግሥት በተደጋጋሚ ጥያቄ ቢያቀርቡም፣ እስካሁን ተጨባጭ መፍትሄ አለመገኘቱን ገልጸዋል። በፋይናንስና በንግድ ገደቦች ሳቢያ የክልሉ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ክፉኛ መጎዳቱን የጠቀሰው ቢሮው፣ ከፌዴራል ባለሥልጣናት ጋር የተደረጉ ውይይቶችም የሚፈለገውን ውጤት እንዳላመጡ አስታውቋል።
292