ar
Feedback
የስንኝ ቋጠሮ

የስንኝ ቋጠሮ

الذهاب إلى القناة على Telegram

የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!

إظهار المزيد
2 046
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
የሀገሬ እንግልት ልፋቷና አሳሯ ምነው እንደ አንዲት ሴት ዘጠኝ ብቻ ቢሆን የእርግዝና ወሯ ደሟ ሳይፈስባት ምጧ ሳይበረታ ከጥበበኛ ሰው አዋልዳት ነበር በፍቅር በደስታ። @gitmv ✍በአክሊሉ

ከመሰለን! ለሆድ ኑሮ ማለፍ ፣ ለመብላት መባላት ከሆነ ትግላችን ፤ መሴይጠን ከነበር ፣ ከሰው ተራ መውጣት አውሬነታችን፤ ምነው ባናወራ ስለ ገነት አንባ፤ ምነው ባናወርድ ከቶ ያሀዘን እንባ። @Gitmv 26/10/2014 ከሻንበል ዋቅጋሪ ጅማ

እኔ እወድሻለሁ ክረምቱም ተተካ በጋውም አለፈ ከቤትሽ አመጣኝ ፍቅር እያከነፈ እትቱ በርዶኛል ጋቢ ደርቢልኝ ከሌለ ግድ የለም በእቅፍሽ አሙቂኝ እኔም መጥቻለሁ አብረን እንድንሆን ክረምቱ ሲወጣ እንለያያለን @gitmv

ሀገሬ እንዲህ ናት... ሀገሬ እርጉዝ ናት ሀገሬ ነፍሰጡር፡ ሀገሬ ድርስ ናት የመውለጃ ቀኗን ስትጠብቅ የምትኖር፡ ሀገሬ በካር ናት፡ ምጥ ላይ ያለች እንስት፡ በወለደች ጊዜ የወለደችውን ወንድ ልጇን ጥላ፡ የእንግዴ ልጇን 'ምታሳድግ አዝላ። @gitmv

መለየት ነው ቆርጦ መሄድ ነው እርቆ ምንድን ነው የሙጥኝ ከሰው ሰው ተጣብቆ @gutmv ✍✍ ባንተጊዜ

#ሴትሆይ ስከተልሽ ኖርኩኝ ካስጠጋሽኝ ብዬ የልቤን ስነግርሽ ሳልደብቅ ሚስጥሬ ክብርሽን ጠብቂ አክብሬ ባነግስሽ ጉራ አናትሽ ላይ እናም አልገባአለኝ ሀሳብሽ ሴትሆይ ስሚኝ አንዴ ከቀልብሽ ሁኚና ጅል ሆኜ እንዳይመስልሽ ስልልሽ ጎምበስ ቀና ለፍቅር ብዬ ነው እድሌ እስኪቃና @gitmv@samueltsegaye

ያኔ ያኔ ያልታሰበው ሲፈጠር በሂወቴ፣ ከባዱ ፈተና ሲጫን በጫንቃዬ፣ የማያልፍ ይመስል ተዛብቶ መንገዴ፣ ክፋትን ያስመኘኝ ደካማው ጉድለቴ፣ ምናለ አይቶት ቢሆን የዛሬ እኔነቴን። @gitmv አዲስአለም

*የፎረሸ ስሜት* ወይ ቀረሁ ብለሽኝ መሄጃ አላበጀሁ ወይ መጥተሽ አግኜሽ ናፍቆቴን አልሸኘሁ እንዲሁ ትመጭ ይሆን እያልኩ በር በር እንዳየሁ በምኞት ጥላ ስር በቀቢፀ ተስፋ ስንት ዘመን ቆየሁ። ✍Ab

ስሚኝ እወድሽ ነበረ ፍቅሬ ባይገባሽም፣ የኔ መዉደድ ላንቺ እውነት ባይመሰልሽም አይንሽ እንባ ሲያዝል ሆድሽ ባር ባር ሲለው፣ እኔም ከፍቶኝ ነበር እውነቱ ይሄ ነው። @gitmv ምህረት 26/10/2014

የፈጠርከው ፍጡር ~ከሰይጣን ሰይጥኖ ልጆችህን ሲገለን ~ህግጋትክን ተቃርኖ ስለምን ዝምአልከው~ ስንቴስ እንቀጣ ውረድና ፍረድ !! አልያ ህግክን ሻርልን ~እራሳችን እንድንቀጣ!! @gitmv #bluefish

#ሺህ _አመት_ይንገሱ ትንሽ አይከብድም ወይ መቶ አመት ኖሮ ሺህ አመት መንገስ፣ ታምቡር የሚበጥሱ ጩኸቶችን መሰረታዊ ጥያቄዎችን አጎንብሶ አለመመለስ፣ ለእናት እንባ ለህፃን ምኞት ቶሎ አለመድረስ። @gitmv 🖊መኮንን ዮሴፍ(ባቢ)🖊

ቀንን የጠበቀ ጊዜውን ያወቀ ድንገት ሲፈነዳ ቆስቋሹን እንዳለ ይዞት ገደል ገባ ቢያብሱት አይደርቅም ብሶት ያዘለ እንባ። ዮኒ @gitmv ኣታን @yonatoz

ደቂቃዎች ቀርተውታል ልክ ሶስት ሰአት እንደሞላው ውድድሩን እንጀምራለን!! ጓደኞቻችሁን ወደቻናሉ ጋብዟቸው!! ስልሳ ላይክ ቀድሞ የሞላ የካርድ ሽልማት አለው!! @gitmv

ከ አራት ስንኝ ያልበለጠ ግጥም በማንኛውም ርዕስ ፅፋችሁ ላኩልኝ @gitmv ግጥም ለመላክ @mogea ሌሎቹ ህግጋት እንደተጠበቁ ናቸው እስከ ሶስት ሰአት ድረስ ላኩ

ውድ አባሎቻችን ረጅም ጊዜ እንደጠፋን እናውቃለን ይቅርታ ይደረግልን እንጠይቃለን። ስለዚህ ታላቁን የግጥም ውድድር ልንጀምር ስላሰብን ዛሬ ምሽት የግጥም ውድድር ይኑር የምትሉ…

ጀግና አንጀቷን ቢወጋ በሆድ ኑሮ ባን'ዳ ፣ አብሮ ከጠላት የእናት ቤት ሲከዳ ፣ ተነሳ ተቆጣ!፦ ልክ ግብሩን ሊያሳይ ነቅቶ በማለዳ ፤ ነጆ ያበቀለው እትብተ ወለጋ ፣ ምሎ ለኪዳኗ ጎህ ሲገፍ ሲውጋጋ ፣ ተነሳ ማለዳ ጠላቷን ፍለጋ ፤ በማለዳው ነቅቶ ፣ የጠላቱን ዱካ ካለበት አሽትቶ ፣ ኦኔ እያ'ነሳሳ በአጀብ በቀረርቶ ፤ ድል እያደረገ ቢያ'ዝም በጠላት ፣ እኛን ምሰል ቢሉት ቢሰጡት ዜግነት ፣ መሞት የመረጠ ክዶ ለባርነት ፤ እሱ... የማይደራደር ከቶ ባገር ጉዳይ ፣ እትዮጵያን ከፍ አርጎ በሮም አደባባይ ፣ ከፎቅ ያመለጠ በእራፊ ትልታይ ፤ ጀግናው አብዲሳ አጋ !። ከሻምበል ዋቅጋሪ ከ ጅማ 20/08/201

የግጥም መናሐሪያ 📚📖✒️ 👉ግጥም ተራ https://t.me/yegitimmeneharia

ልረሳሽ እየጣርሁ ነው (በእውቀቱ ስዩም) በጣራው ላይ ሲረማመድ፥ የዝናቡ ልዝብ ኮቴ መጋረጃው ሲውለበለብ፥ ሰንደቅ ሆኖ ለመስኮቴ ዋርካው በቅጠል ጽዋ ውሀ ሲያቁር ከሕዋ የምድርን ጉሮሮ ሊያርስ መሬት ፍጥረትን ስትፀንስ በዚህ ሁሉ ጸጋ መሀል፥ ያንቺን መሄድ ስተምነው ኢምንት ነው፥ ምንም ነው ልረሳሽ እየጣርሁ ነው:: መጣ፥ መጣ ፥ መጣ ፥ የዝናቡ ኮቴ አየለ ክረምት የፍጥረት መሲሕ፥ በቀጠሮው ከተፍ አለ ስሱ የጉም አይነርግብ፥ ውብ ገጽሽን ሸፋፈነው የርጥብ አፈር ፥ ርጥብ ሽታ፥ ውብ ሽቶሽን አዳፈነው ልረሳሽ እጣርሁ ነው :: የዝናቡ ኮቴ ይደምቃል እንደ ብስል ሾላ ፍሬ ፥ አሮጌው ሰማይ ይወድቃል አዲስ ሰማይ ይነቃል፥ እንኳንስ የግርሽ ኮቴ ፥ ጎዳናሽም ታጥቦ ያልቃል ልረሳሽ እየጣርኩ ነው ። (የማለዳ ድባብ)

አስታወሰኝ አስታውሰኝ ስረሳ... ፍጡር ሰው አይደለሁ፣ ተዘንግቶህ እንጂ... ፊቱን እረሳለሁ፣ አዎ እኔ ረሺ ነኝ ባለፈብኝ ሀሉ፣ በተረማመደኝ መሬት ብሆን ቅሉ፣ ክፉ በሆነብኝ ክፋት ላላወሳ፣ ምህላ ና ፀሎቴ ጥፋትን ልረሳ፣ በሱባዬው ምህፅን ብዋዋል ከእግዜሩ፣ የመርሳት ግንብ አጥር ተከፍቶልኝ በሩ ፣ በዚያ በኩል ሳልፍ ክፉ አልተከተለኝ፣ መጥፎን አስረሳና ደጉን አስታወሰኝ። 27/09/2014 @*** 18

የባከነ ሌሊት!!!! (በእውቀቱ ስዩም) ወይ ሮንድ አላደርኩ ወይ ኮኮብ አልቆጠርኩ ወይ ደልቶኝ አልጨፈርሁ ወይ ውስኪ አልተዳፈርሁ የባለጌ ወንበር :ኮርቻ አልተሳፈርሁ ወይ ሰአታት ቁሜ ቤተክስያን ስሜ ሰይጣን አላሳፈርሁ:: ሌቦች ደብድበውት አንዱን ምስኪን ላሥር ባምቢስ ድልድዩ ሥር ቆስሎ የወደቀ ገላው በላዩ ላይ :እንደጨርቅ ያለቀ ፊቱ ተሸፍኖ : በደምና አቧራ "በኡራኤል ርዱኝ " ብሎ የሚጣራ ምስኪን አባወራ ብብት ሥር ገብቼ አፋፍሼ አንስቼ ተሸክሜ አድኜ ስፈልግ አምቡላንስ :ሲሻኝ ዶክተር ሁኜ ወይ ምግባር አልሠራሁ ወይ ጀብድ አልፍፀምኩኝ : ወይ ፅድቅ አላፈራሁ:: አንድ በትረ-ሙሴ ሁለት ስስ አሎሎ ከጭኔ መሀከል ሲያመሽ ተንጠልጥሎ ሲባክን ዝምብሎ " እሸኝ የኔ ጀግና እንደሰነፍ ቆሎ" የምትል መለሎ ልቤን ሳትሰውረው አልጋየን ሳትሰብረው:: ወግ ቢጤ ሞንጭሬ: ፌስቡክ ላይ ሳለጥፍ " እናትዋን ጨረቃ" የሚል ግጥም ሳልጥፍ:: አንዲት ሴት- አዳሪ :ቺቺንያ ምንገድ ላይ እድሉዋ ሰባራ :ሰውነቱዋ አማላይ ካፍያውና እንባዋ : ተጋግዞ ሚያረጥባት ደምበኛ ስትጠበቅ :ደመኛ ጥሎባት አምስት ደፋሪዎች : ከበው ሲያዋክቧት ሲገፉ ሲስቧት " እረ በናታችሁ በወላድ ማህፀን እህት የላችሁም?" ብላ ስትማፀን ልመናዋ ስቦኝ እንዳበጀ በለው : በደሏ አንገብግቦኝ ከሁዋላ ደርሼ ነበልባል ለብሼ: ነበልባል ጎርሼ እንደብሩስሊ: እንዳየሩ ጋኔን እግሬን ወንጨፍ ወንጨፍ ወዝወዝ ወዝወዝ ጎኔን በማረግ ቃኝቼ ከሁዋላ ነው ሲሉኝ ከፊት ተገኝቼ ካምስቱ መከከል አራቱን ነጥየ ከቻልኩ በካራቲ ካልቻልኩ በሳቅ ጥየ:: ድል ሳላስመዘግብ ውጥረት ሳለረግብ ወይ ታሪክ ሳልሰራ -ወይ ታሪክ ሳልዘግብ ያለምንም ጣጣ : ያለምንም ፀጋ አለሰበብ መሽቶ አለሰበብ ነጋ::