የስንኝ ቋጠሮ
رفتن به کانال در Telegram
የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!
نمایش بیشتر2 046
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
2 046
#ሴትሆይ
ስከተልሽ ኖርኩኝ ካስጠጋሽኝ ብዬ
የልቤን ስነግርሽ ሳልደብቅ ሚስጥሬ
ክብርሽን ጠብቂ አክብሬ ባነግስሽ
ጉራ አናትሽ ላይ እናም አልገባአለኝ ሀሳብሽ
ሴትሆይ ስሚኝ አንዴ ከቀልብሽ ሁኚና
ጅል ሆኜ እንዳይመስልሽ ስልልሽ ጎምበስ ቀና
ለፍቅር ብዬ ነው እድሌ እስኪቃና
@gitmv
ከ @samueltsegaye
2 046
*የፎረሸ ስሜት*
ወይ ቀረሁ ብለሽኝ መሄጃ አላበጀሁ
ወይ መጥተሽ አግኜሽ ናፍቆቴን አልሸኘሁ
እንዲሁ
ትመጭ ይሆን እያልኩ በር በር እንዳየሁ
በምኞት ጥላ ስር በቀቢፀ ተስፋ ስንት ዘመን ቆየሁ።
✍Ab
2 046
ውድ አባሎቻችን ረጅም ጊዜ እንደጠፋን እናውቃለን ይቅርታ ይደረግልን እንጠይቃለን። ስለዚህ ታላቁን የግጥም ውድድር ልንጀምር ስላሰብን ዛሬ ምሽት የግጥም ውድድር ይኑር የምትሉ…
2 046
ጀግና
አንጀቷን ቢወጋ በሆድ ኑሮ ባን'ዳ ፣
አብሮ ከጠላት የእናት ቤት ሲከዳ ፣
ተነሳ ተቆጣ!፦
ልክ ግብሩን ሊያሳይ ነቅቶ በማለዳ ፤
ነጆ ያበቀለው እትብተ ወለጋ ፣
ምሎ ለኪዳኗ ጎህ ሲገፍ ሲውጋጋ ፣
ተነሳ ማለዳ ጠላቷን ፍለጋ ፤
በማለዳው ነቅቶ ፣
የጠላቱን ዱካ ካለበት አሽትቶ ፣
ኦኔ እያ'ነሳሳ በአጀብ በቀረርቶ ፤
ድል እያደረገ ቢያ'ዝም በጠላት ፣
እኛን ምሰል ቢሉት ቢሰጡት ዜግነት ፣
መሞት የመረጠ ክዶ ለባርነት ፤
እሱ...
የማይደራደር ከቶ ባገር ጉዳይ ፣
እትዮጵያን ከፍ አርጎ በሮም አደባባይ ፣
ከፎቅ ያመለጠ በእራፊ ትልታይ ፤
ጀግናው
አብዲሳ አጋ !።
ከሻምበል ዋቅጋሪ
ከ ጅማ
20/08/201
2 046
ልረሳሽ እየጣርሁ ነው
(በእውቀቱ ስዩም)
በጣራው ላይ ሲረማመድ፥ የዝናቡ ልዝብ ኮቴ
መጋረጃው ሲውለበለብ፥ ሰንደቅ ሆኖ ለመስኮቴ
ዋርካው በቅጠል ጽዋ
ውሀ ሲያቁር ከሕዋ
የምድርን ጉሮሮ ሊያርስ
መሬት ፍጥረትን ስትፀንስ
በዚህ ሁሉ ጸጋ መሀል፥ ያንቺን መሄድ ስተምነው
ኢምንት ነው፥ ምንም ነው
ልረሳሽ እየጣርሁ ነው::
መጣ፥ መጣ ፥ መጣ ፥ የዝናቡ ኮቴ አየለ
ክረምት የፍጥረት መሲሕ፥ በቀጠሮው ከተፍ አለ
ስሱ የጉም አይነርግብ፥ ውብ ገጽሽን ሸፋፈነው
የርጥብ አፈር ፥ ርጥብ ሽታ፥ ውብ ሽቶሽን አዳፈነው
ልረሳሽ እጣርሁ ነው ::
የዝናቡ ኮቴ ይደምቃል
እንደ ብስል ሾላ ፍሬ ፥ አሮጌው ሰማይ ይወድቃል
አዲስ ሰማይ ይነቃል፥
እንኳንስ የግርሽ ኮቴ ፥ ጎዳናሽም ታጥቦ ያልቃል
ልረሳሽ እየጣርኩ ነው ።
(የማለዳ ድባብ)
2 046
አስታወሰኝ
አስታውሰኝ ስረሳ...
ፍጡር ሰው አይደለሁ፣
ተዘንግቶህ እንጂ...
ፊቱን እረሳለሁ፣
አዎ እኔ ረሺ ነኝ
ባለፈብኝ ሀሉ፣
በተረማመደኝ
መሬት ብሆን ቅሉ፣
ክፉ በሆነብኝ
ክፋት ላላወሳ፣
ምህላ ና ፀሎቴ
ጥፋትን ልረሳ፣
በሱባዬው ምህፅን
ብዋዋል ከእግዜሩ፣
የመርሳት ግንብ አጥር
ተከፍቶልኝ በሩ ፣
በዚያ በኩል ሳልፍ
ክፉ አልተከተለኝ፣
መጥፎን አስረሳና
ደጉን አስታወሰኝ።
27/09/2014
@*** 18
2 046
የባከነ ሌሊት!!!!
(በእውቀቱ ስዩም)
ወይ ሮንድ አላደርኩ
ወይ ኮኮብ አልቆጠርኩ
ወይ ደልቶኝ አልጨፈርሁ
ወይ ውስኪ አልተዳፈርሁ
የባለጌ ወንበር :ኮርቻ አልተሳፈርሁ
ወይ ሰአታት ቁሜ
ቤተክስያን ስሜ
ሰይጣን አላሳፈርሁ::
ሌቦች ደብድበውት
አንዱን ምስኪን ላሥር
ባምቢስ ድልድዩ ሥር
ቆስሎ የወደቀ
ገላው በላዩ ላይ :እንደጨርቅ ያለቀ
ፊቱ ተሸፍኖ : በደምና አቧራ
"በኡራኤል ርዱኝ " ብሎ የሚጣራ
ምስኪን አባወራ
ብብት ሥር ገብቼ
አፋፍሼ አንስቼ
ተሸክሜ አድኜ
ስፈልግ አምቡላንስ :ሲሻኝ ዶክተር ሁኜ
ወይ ምግባር አልሠራሁ
ወይ ጀብድ አልፍፀምኩኝ : ወይ ፅድቅ አላፈራሁ::
አንድ በትረ-ሙሴ
ሁለት ስስ አሎሎ
ከጭኔ መሀከል ሲያመሽ ተንጠልጥሎ
ሲባክን ዝምብሎ
" እሸኝ የኔ ጀግና እንደሰነፍ ቆሎ"
የምትል መለሎ
ልቤን ሳትሰውረው
አልጋየን ሳትሰብረው::
ወግ ቢጤ ሞንጭሬ: ፌስቡክ ላይ ሳለጥፍ
" እናትዋን ጨረቃ" የሚል ግጥም ሳልጥፍ::
አንዲት ሴት- አዳሪ :ቺቺንያ ምንገድ ላይ
እድሉዋ ሰባራ :ሰውነቱዋ አማላይ
ካፍያውና እንባዋ : ተጋግዞ ሚያረጥባት
ደምበኛ ስትጠበቅ :ደመኛ ጥሎባት
አምስት ደፋሪዎች : ከበው ሲያዋክቧት
ሲገፉ ሲስቧት
" እረ በናታችሁ በወላድ ማህፀን
እህት የላችሁም?" ብላ ስትማፀን
ልመናዋ ስቦኝ
እንዳበጀ በለው : በደሏ አንገብግቦኝ
ከሁዋላ ደርሼ
ነበልባል ለብሼ: ነበልባል ጎርሼ
እንደብሩስሊ: እንዳየሩ ጋኔን
እግሬን ወንጨፍ ወንጨፍ
ወዝወዝ ወዝወዝ ጎኔን
በማረግ ቃኝቼ
ከሁዋላ ነው ሲሉኝ ከፊት ተገኝቼ
ካምስቱ መከከል አራቱን ነጥየ
ከቻልኩ በካራቲ ካልቻልኩ በሳቅ ጥየ::
ድል ሳላስመዘግብ
ውጥረት ሳለረግብ
ወይ ታሪክ ሳልሰራ -ወይ ታሪክ ሳልዘግብ
ያለምንም ጣጣ : ያለምንም ፀጋ
አለሰበብ መሽቶ አለሰበብ ነጋ::
