SOA COMMUNITY GEjA 2 CAMPUS
الذهاب إلى القناة على Telegram
ይህ ድህረ ገፅ የተለያዩ የትምህርት አይነቶች አጠቃሎ የያዘ ሲሆን የሚለቀቁት ጥያቄዎችም ሆኑ ማስታወሻዎች በቀላሉ ታገኛላችሁ። በ 👉👉👉 @SOA2C
إظهار المزيد1 238
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
-330 أيام
أرشيف المشاركات
Repost from N/a
“ከስክሪን ቀንሰን – መጽሐፍት እንግለጥ!”
ከተማ አቀፍ የንባብ ፌስቲቫል ሳምንት
ከነሐሴ 21-25/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
ንባብ የእውቀት በር፣ የምናብ መስኮትና የትውልድ ግንባታ መሠረት ነው። በዲጂታል ዘመን የስክሪን አጠቃቀም የዕለት ተዕለት ሕይወታችን አካል እየሆነ በመጣበት ወቅት፣ መጽሐፍ ለማንበብ የሚኖረንን ጊዜና ትኩረት እንደገና ማስመለስ የጋራ ኃላፊነት አለብን።
በዚህ መሠረት “ከስክሪን ቀንሰን – መጽሐፍት እንግለጥ!” በሚል መሪ ቃል የሚከበረው የከተማ አቀፍ የንባብ ፌስቲቫል ሳምንት፣ የንባብ ባህልን ለማስፋፋት፣ መጽሐፍ አንባቢዎችን ለማበረታታትና በተለይም በሕፃናትና በወጣቶች ዘንድ የንባብ ፍላጎትን ለማዳበር የተዘጋጀ የንባብ ንቅናቄ ሳምንት ነው።
የፌስቲቫሉ መሪ ቃል “ከስክሪን ቀንሰን – መጽሐፍት እንግለጥ!” ቴክኖሎጂን መቃወም ሳይሆን የስክሪን አጠቃቀማችንን ሚዛናዊ በማድረግ ለንባብ፣ ለማሰብ፣ ለመወያየት እና ለመማር የሚያስፈልገንን ጊዜ እንድናስተካክል የቀረበ ጥሪ ነው።
አንድ ሰዓት ከስክሪን ቀንሰን አንድ ምዕራፍ ከመጽሐፍ ማንበብ፣ ከልጆቻችን ጋር መጽሐፍ ማንበብ፣ መጽሐፍ በስጦታም ሆነ በትውስት መለዋወጥና ባነበብነው ላይ መወያየት ትንሽ ተግባር ቢመስልም ትልቅ የትውልድ ግንባታ መሰረት ነው።
ውድ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች፣ ደራሲያን፣ አሳታሚዎች፣ ወጣቶች፣ መምህራን… የንባብ ሳምንቱ ከነሀሴ 21-25/2018 በከተማችን በሚገኙ 72 ቤተመጽሐፍት በሁሉም የሚካሄድ በመሆኑ በየአካባቢያችሁ በሚገኙ ቤተመጽሐፍት በመገኘት በንባብ ባህል ግንባታ የራሳችሁን ሚና እንድትወጡ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
ይህ ሳምንት የንባብ ሳምንት ብቻ ሳይሆን፣ የንባብ ልማድን የምንጀምርበት ሳምንት እናድርገው!
“ስክሪንን በሚዛን፣ መጽሐፍን በፍቅር እናብብ!
ትውልዳችንን እናንቃ!”
Via Hirut Kassaw
https://www.facebook.com/share/r/1HmLTw2Npm/
ቅዳሜ ጠዋት ልጆቻችሁን አብረሆት ቤተመፃህፍት ውሰዱ
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
የ19 ዓመቱ ታዳጊው የ4.1 ሚሊዮን ዶላር ስኮላርሺፕ እንዴት አሸነፈ ?
ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር ቆይታ አድርጓል፤ ይከታተሉ👇
https://youtu.be/fJszX23u_-A?si=geN2Jps6HY6gMcnp
