cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

𝚂𝚎𝚢𝚏𝚎𝚕𝙸𝚜𝚕𝚊𝚖 ሰይፈል ኢስላም!

قال ابن تيمية -رحمه الله-: {قوام الدين كتاب يهدي وسيف ينصر وكفى بربك هادياونصيرا} مجموع الفتاوى [10/13] ጠቃሚ መረጃዎችን ለማግኘት በሚመችዎ የማህበራዊ ሚድያ ይከታተሉኝ!👇 https://heylink.me/AzizoSocialLinks.com/

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
328
المشتركون
+324 ساعات
+87 أيام
+4030 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

"የፍርድ ቤት ትዕዛዝና የፖሊስ መጥሪያ በሌለበት ፖሊሶች መጥተው ያስሩናል የመስጂዳችንን መግቢያና መውጫ ዘግተው አጥረውብን ቸርች ነው እያሉ ያዋክቡናል" የሀዋሳ ሀምዛ መስጂድ ጀማዓዎች። .. (ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ፦ግንቦት 6/2016) ....... የሀዋሳ ሀምዛ መስጂድ ጀማዓዎች ከሳሻችን ማነው ስንል ቸርች ነው ይሉናል ምንም ቸርች በሌለበት።የመስጂዳችን መግቢያና መውጫ ዘግተው አጥረውብን ቸርች ነው እያሉ ያዋክቡና በማላት ቅሬታቸውን ለሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ የገለጹ ሲሆን በ2003 ዓል ህጋዊ ፍቃድ ተስጥቶን ገንብተን እየሰገደን  ቢሆንም ከመስኪዱ 20 ሜትር ርቀት ላይ በሸራ ጀምረው በአንድ ምሽት ህገወጥ ግንባታ ገንብተው ቸርች አድርገው በሞንታርቦ መዝሙር እየከፈቱብን በተደጋጋሚ ሶላታችንን በአግባቡ እንዳንሰግድ እያደረጉ የጁማዓ ሰላት ሰዓት ጠብቀው ሞታርቦ እየከፈቱ አምልኮዋችንን በአግባቡ እንዳንፈጽም እያደረጉን ሲሆን እሄንንም ለሚመለከተው የመንግስት አካላት በተደጋጋሚ አቤት ያልን ቢሆንም ምንም አይነት ምላሽ አላገኘንም ብለዋል። .. በአሁን ሰዓት ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤትም ወስደን ክስ መስረተን እየተከታተልን ነው በማለት ያነጋገርናቸው የሀዋሳ ሙስሊም ነዋሪዎች ገልጸውልናል።በአሁን ሰዓት አጥሩ በከተማው ማዘጋጃና ሰላምና ጸጥታ የፈረሰ ቢሆንም በዘላቂነት ችግሩን ለመፍታት የተኬደበት ርቀት ብዙም አይደለም በማለት ሙስሊም ነዋሪዎቹ  የተናገሩ ሲሆን በዚህ ጉዳይ ባለፈው የሀዋሳ ከተማ ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊን በስልክ ማናገራችን የሚታወስ ሲሆን ኃላፊውም በቅርብ ርቀት ላይ ለተለያዩ የእምነት ተቋማት የግንባታ ፍቃድ እንደማይሰጥ መመሪያው ይከልክላል ማለታቸው ይታወቃል። እሄንንም ለማጣራት ለሰኞ መቀጣጣጠራቸውን ነግረውን የነበረ ሲሆን በዛሬው ዕለት የማዘጋጃ ባለሞያዎች ቦታውን ሜትር ይዘው ሲለኩ መመልከት ብንችልም ጉዳዩ ከምን እንደደረሰ ለማጣራት ወደ አቶ ገዛሀኝ የእጅ ስልክ በተደጋጋሚ ስልክ ብንደውልም ስልካቸው አልተነሳም። ... በዚህ ያህል ቅርብ ርቀት ላይ ለተለያዩ እምነት ተቋማት ይቅርና ለተመሳሳይ እምነት ተቋማትም የግንባታ ፍቃድ አይስጥም በማለት የገለጹልን  ደግሞ የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ፕሬዝዳንት ሀጂ አ/ሹኩር  ሀጂ አ/ቃድር ሲሆኑ ጉዳዩንም ኮሚቴ አዋቅረው እየተከታተሉ እንደሆነና  ከሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት ጋር እየተነጋገሩ እንደሆነ ተናግረዋል። ... ¤ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ ስፍራው ተገኝቶ ያጠናቀረው ሙሉ ዘገባ እንደደረሰን የምናቀርብላችሁ ይሆናል። ... ©ሀሩን ሚዲያ https://t.me/Seyfel_Islam
إظهار الكل...
𝚂𝚎𝚢𝚏𝚎𝚕𝙸𝚜𝚕𝚊𝚖 ሰይፈል ኢስላም!

قال ابن تيمية -رحمه الله-: {قوام الدين كتاب يهدي وسيف ينصر وكفى بربك هادياونصيرا} مجموع الفتاوى [10/13] ጠቃሚ መረጃዎችን ለማግኘት በሚመችዎ የማህበራዊ ሚድያ ይከታተሉኝ!👇

https://heylink.me/AzizoSocialLinks.com/

ግንቦት 6፣ 2016 | ዙል ቃይዳ 6፣ 1445 አ.ሂ. بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የሳዑዲ ኤምባሲ ለጠቅላይ ምክር ቤቱ የመጻሕፍት ሥጦታ አበረከተ። •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• በኢትዮጵያ የሳዑዲ አረቢያ ኤምባሲ ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በተለያዩ ርዕሰ-ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ሁለት አይሱዙ የጭነት መኪና ሙሉ መጻሕፍትን በሥጦታ አበረከተ። በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተገኝተው የመጽሐፉን ሥጦታ ያበረከቱት በኢትዮጵያ የሳዑዲ አረቢያ ምክትል አምባሳደር ጧሪቅ አብዱልዓዚዝ ኢድሪስ ናቸው። ሥጦታውን የጠቅላይ ምክር ቤቱ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚደንት ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን እና ዋና ጸሐፊው ሸይኽ ሃሚድ ሙሳ በጋራ በመሆን ተቀብለዋል። በዚሁ ጊዜም የጠቅላይ ምክር ቤቱ የዑለማ ጉባዔ የፈትዋና ምርምር ተጠሪ ሸይኽ አድሪስ ዓሊ ተገኝተዋል። በኢትዮጵያ የሳዑዲ ምክትል አምባሳደር ጧሪቅ አብዱልአዚዝ ኢድሪስ ሥጦታውን ካስረከቡ በኋላ ከተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚደንትና ከዋና ጸሐፊው ሸይኽ ሀሚድ ሙሳ ጋር ተወያይተዋል። ሸይኽ ሐሚድ ሙሳ በዚሁ ጊዜ የሳዑዲ መንግሥት በኤምባሲው አማካኝነት ብዛቱ ሁለት መካከለኛ ቤተ-መጻሕፍት ሊሞላ የሚችል የመጻሕፍት ሥጦታ ስላበረከተ በጠቅላይ ምክር ቤቱ ስም አመሥግነዋል። አምባሳደር ጧሪቅ በበኩላቸው ሀገራቸው ሳዑዲ ዐረቢያ ከኢትዮጵያ ጋር የዳበረ ዲፕሎማሲያዊ ግንኝነት እንዳላት ጠቅሰው፣ ወቅቱ የሐጅ ጊዜ በመኾኑ የሳዑዲ ኤምባሲ ጉዞው የተሳካና የተቀላጠፈ እንዲሆን እየሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የዑለማ ጉባኤ የፈትዋና ምርምር ተጠሪ የኾኑት ሸይኽ አድሪስ ዓሊ በበኩላቸው፣ ለጠቅላይ ምክር ቤቱ የተበረከተው የመጻሕፍት ሥጦታ ጠቅላይ ምክር ቤቱ በማስፋፋት ላይ ላለው ቤተ-መጻሕፍት ትልቅ አቅም ይሆናል ብለዋል። ••••••••••••••••• የኢ.እ.ጉ.ጠ. ም/ቤት ሕዝብ ግንኙነት ይከታተሉን | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | twitter.com/eiasc
إظهار الكل...
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት

ለመስጂዱ የሚሰጠው የመሬት ስፋት የሙስሊሙን ማህበረሰብ ቁጥር ከግምት ያስገባ መሆን ነበረበት።ታዲያ እንደሀገሪቷ ዜጋ፤እንደተወላጅነቱ፤እንደነዋሪቱ፤እንደ ግብር ከፋይነቱ፤ለሀገር አንድነትና ነፃነት እንደሚከፍለው መስዋእትነቱ፤እንደ ዲሞክራሲያዊ መብቱ፤እንደሙስሊሙ ቁጥር ብዛቱ፤እንደከተማ ስፋቱ፤እንደ ሙስሊሙ አስተዋፅኦ…ስንት ካሬ ነው ሚገባው በሀቅ በእውነቱ?… የመስጂዶች ታሪክ በአዲስ አበባ ከሚኒሊክ-ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ መፅሀፍን ከፃፉት ከሼህ አህመድ አሊ ጋር ያደርግነውን ቆይታ ዛሬ ምሽት 1፡00 ሰዓት በሀሩን ሚድያ ይጠብቁን
إظهار الكل...
የአሜሪካና የአውሮፓ ዩኒቨርሲቲዎች ሞልቶ እየፈሰሰ ያለው የጋዛ ግፍ ባንገሸገሻቸው የፍትህ ናፋቂ ተማሪዎችና ፕሮፌሰሮች እየተናወጡ ነው!
إظهار الكل...