cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
17 088
المشتركون
+124 ساعات
+1317 أيام
+1 11630 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

አወዛጋቢ ሁኖ የቆየው በፍትሕ ሚንስትር የተዘጋጀው "የሀይማኖት ጉዳዮች አዋጅ" በሰላም ሚኒስቴር አማካኝነት ውይይት ተካሄደበት! ... ሀሩን ሚዲያ፥ ግንቦት 21/2016፤አዲስ አበባ … በፍትህ ሚኒስቴር የተዘጋጀው የሀይማኖት ጉዳዮች አዋጅ በተለይም ሂጃብና ኒቃብን ሚከለክል ፤በቡድን ሆኖ በየትምህርት ቤቶች ማምለክ እንደማይቻል  ይህ ደሞ ከእስልምና አስተምሮ ጋር ሚጋጭ በመሆኑ የኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ቅሬታውን በደብዳቤ መግለፁ ይታወሳል። … ሂጃብና ኒቃብ ለአንድ ሙስሊም ሴት ከፈጣሪዋ የታዘዘ የሀይማኖት ግዴታ በመሆኑ ማንም ህግ አውጥቶ መከልከል እንደማይችል እና ይህ የአምልኮ ስርዓትን የሚጋፋ በመሆኑ አዋጁ እንዲሻሻል በውይይቱ ላይ ተነስቷል። ሙስሊሙ ማህበረሰብ በሀገሩ ላይ እንደማንኛውም ዜጋ የትኛውም ቦታ ላይ ሀይማኖታዊ አለባበሱን ለብሶ መስራት፤መማር እንዲችል እንዲሁም ሙስሊሙን በሚመጥነው ልክ ማምለክያ ቦታዎች እንዲሰጡት ፤በአለባበስ ምክንያት ሙስሊሙን ከስራ እና ከትምህርት ለማራቅ የሚደረጉ እርምጃዎች ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲቀሩ ጥሪ ቀርቧል። … ©ሀሩን ሚድያ
إظهار الكل...
17👍 6
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዛሬ ግንቦት 21/2016 ዓ.ል በሚካሄደው የምክክር ምዕራፍ መርሃግብር በአድዋ ሙዚየም እያካሄደ ይገኛል! . ¤ሀሩን ሚዲያ በቦታው በመገኘት ዝግጅቱን እየተከታተለ ሲሆን ተጨማሪ መረጃዎችን ወደናንተ ያደርሳል! ... ©ሀሩን ሚዲያ
إظهار الكل...
👍 15 1
Photo unavailableShow in Telegram
ኢናሊላሂ ወኢና  ኢላይሂ ራጂዑን በአወሊያ ሙስሊም አንደኛ ደረጃ ት/ት ቤት የአርብኛ ቋንቋ መምህርት የነበረችው እና አሁን ላይ ደሞ የአወሊያ ኮሌጅ አርብኛ ቋንቋ በማስተማር ላይ የነበረችው ዑስታዛ በድሪያ ኑርአዲስ ትላንት ማክሰኞ ግንቦት 20/2016 ዓ/ል ወደ አኼራ ሄዳለች። ዑዝታዛ በድሪያን አላህ ጀነቱል ፍርደውስ እንድወፍቃት ለቤተሰቦቿም አላህ ሰብር እንድሰጣቸው ሀሩን ሚዲያ ይመኛል።
إظهار الكل...
😢 48👍 4
በሰሜን አሜሪካ በየዓመቱ የሚካሄደው  ታላቁ የICNA ፕሮግራም በታላቅ ድምቀት የተከናወነ ሲሆን የዘንድሮው ፕሮግራም በዋነኛነት ለፍልስጤሞች ታላቅ ትኩረት የተሰጠበት ሁኗል! ... (ሀሩን ሚዲያ፦ግንቦት 20/2016) ... ICNA (The Islamic Circle of North America )በሰሜን አሜሪካ የሚገኙ  ሙስሊሞች በጋራ ታላቅ ፕሮግራም የሚያካሂዱበት ተቋም ሲሆን  በSeptember 1st, 1968  የተመሰረተ ታላቅ ድርጅት ነው ። ... በየዓመቱ  ታላላቅ ዳኢዎች የሚሳተፉበት ፣ኢስላማዊ ተቋማት የሚሳተፉበት  ዝግጅት የሚያካሂድ ሲሆን በዘንድሮው በሜሪላንድ ባልቲሞር ኮንፌንሽን ሴንተር ከሜይ  25 እስከ 27 ድረስ ተካሂዷል።በዝግጅቱ ላይ ፕሮግራም ከ30 ሺ በላይ የሚሆኑ ታዳሚዎች ተሳትፈውበታል ። ... የ ICNA-MAS ኮንቬንሽን በተለያዩ አዳራሾች የተለያዩ ፕሮግራሞች የቀረቡ ሲሆን በታዋቂ  ዳኢዎች እና ምሑራን ከቀረቡ ፕሮግራሞች ባሻገር   ልዩ የወጣቶች ኮንፈረንስ እና አጠቃላይ አጀንዳዎችን የሚያጠቃልሉ  ንግግሮች፣ የተግባር ተኮር አውደ ጥናቶች ተካሂደዋል ። ... በዋነኛነት በፍልስጤም ሙስሊሞች እየተፈጸመ ያለውን ግፍ በመቃወም በተመለከተ እየተደረገ ያለው ትግል ተጠናክሮ መቀጠል  እንዳለበት ተገልጿል ። ... ©ሃሩን ሚዲያ
إظهار الكل...
👍 49 8
6. በመጨረሻም ሀገራችን በአሁኑ ወቅት በተለያዩ ግጭቶች ውስጥ መሆኗ እና በእነዚህ ግጭቶች ሳቢያ በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ከፍተኛ የሰላም እጦት እና የፖለቲካ አለመረጋጋት መስፈኑ ይታወቃል። መንግስት ከሁሉ አስቀድሞ ለሀገር ሰላም እና የፖለቲካ መረጋጋት ትኩረት አድርጎ መስራት በሚገባው በዚህ ወቅት፣ ሌላ የፖለቲካ ትኩሳት ሊፈጥር የሚችል ተግባር ውስጥ እንዳይገባ፣ መንግስት ህጉን አጽድቆ ከማውጣቱ በፊት ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ግልጽ እና እውነተኛ ውይይት እንዲያደርግ እናሳስባለን። ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ግንቦት 20፣ 2016 አዲስ አበባ
إظهار الكل...
👍 47🔥 8🤔 1
👍 12👏 1👌 1
"መንግስት የእምነት ነጻነትን የሚሸራርፉ ህጎችን ከማውጣት ይቆጠብ"ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ ... (ሀሩን ሚዲያ፦ግንቦት 20/2016) ... ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ በፍትህ ሚኒስትር የተዘጋጀውን የሀይማኖት ጉዳዮች ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል። ... ሙሉ መግለጫው እንደሚከተለው ቀርቧል ረቂቁ “የሃይማኖት ጉዳዮች አዋጅ” የዜጎችን የእምነት እና የአምልኮ ህገ መንግስታዊ መብቶች እንዳይገድብ ጥንቃቄ ይደረግ!! የሃይማኖት እና የመንግስት ግንኙነትን በተመለከተ የኢፌ.ድ.ሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 11 የመንግስት እና ሃይማኖት መለያየትን እና መንግስት እና ሃይማኖት አንዱ በሌላው ጣልቃ እንደማይገቡ በግልጽ እና በማያሻማ መልኩ ደንግጓል። በተመሳሳይ የኢፌድሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 27 (1) ማንኛውም ሰው የመረጠውን ሃይማኖት ወይም እምነት የመያዝ ወይም የመቀበል፣ ሃይማኖቱን እና እምነቱን ለብቻ ወይም ከሌሎች ጋር በመሆን በይፋ ወይም በግል የማምለክ፣ የመከተል፣ የመተግበር፣ የማስተማር ወይም የመግለጽ መብት እንዳለው ደንግጓል። ከላይ የተገለጹት ህገ መንግስታዊ ድንጋጌዎች ከሞላ ጎደል በብዙ የዓለም ሀገራት የሚተገበሩ እና ዓለም አቀፍ እውቅና ያላቸው ህጎች ናቸው። በሀገራችን ታሪክ በተለያየ ወቅት ሀገሪቱን የገዙ መንግስታት የፖለቲካ ስልጣናቸውን ድንበር አልፈው ሃይማኖትን አስመልክቶ ባወጧቸው ህጎች እና በወሰዷቸው እርምጃዎች የዜጎችን የእምነት ነጻነት በመጋፋት ለተቃውሞ እና ለግጭት ምክንያት ሆነዋል። የመንግስት አካላት የዜጎችን የእምነት እና የአምልኮ ነጻነት የሚቃረኑ፣ ሰብአዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን የሚሸራርፉ፣ አለባበስን እና አመጋገብን ጨምሮ በዜጎች የኑሮ ዘይቤ ጣልቃ የሚገቡ ረቂቅ ህጎችን “በሴኩላሪዝም” ስም በህዝብ ላይ ለመጫን ባደረጉት ሙከራ ለግጭት እና ለሀገር ሰላም መደፍረስ ምክንያት መሆናቸው ይታወሳል። በቅርቡ መንግስት “የሃይማኖት ጉዳዮች አዋጅ” በማዘጋጀት ላይ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ረቂቅ አዋጁንም ተመልክተናል። ረቂቅ አዋጁ ባለፉት ሳምንታት የመገናኛ ብዙሃንን ትኩረት መሳቡን እና ዜጎች በስጋት እና በጥርጣሬ ውስጥ ሆነው በረቂቅ አዋጁ ዙሪያ ሀሳብ በስፋት ሲለዋወጡ አስተውለና። ረቂቅ አዋጁ በሚመለከታቸው የእምነት ተቋማት በቂ ውይይት ሳይደረግበት ህግ ሆኖ እንዲወጣ የተጣደፈ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ለመረዳት ችለናል። ረቂቅ አዋጁ በተለያዩ ቤተ እምነቶች ዘንድ ተቃውሞ ያስነሳ ሲሆን ይህ መግለጫ እስከ ተዘጋጀበት ጊዜ ድረስ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስትያናት ካውንስል እና የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ረቂቅ አዋጁን አስመልክቶ በይፋ ቅሬታ ማሰማታቸው ታውቋል። ረቂቅ አዋጁ በህገ መንግስት የተረጋገጠውን የዜጎች የሃይማኖት እና የአምልኮ ነጻነት እንዳይገድብ ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል። ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በኢፌድሪ ህገ መንግስት የተረጋገጠው የሃይማኖት ነጻነት እና እኩልነት እንዲሁም በመንግስት እና በሃይማኖቶች መካከል የተቀመጠው ወሰን ሊከበር ይገባል ብሎ የሚያምን ሲሆን፣ ይህንኑ የፖለቲካ እምነቱን በፓርቲው ፕሮግራም በግልጽ አስቀምጧል። ነእፓ የዜጎች ህገ መንግስታዊ የሃይማኖት እና የአምልኮ ነጻነት ሳይሸራረፍ ሊከበር ይገባል ብሎ በጽኑ የሚያምን ሲሆን፣ ለዜጎች የተሟላ ስብዕና እና ጤናማ ስነ-ልቦና ሃይማኖቶች የማይተካ ሚና እንዳላቸው ይገነዘባል። ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ “በሴኩላሪዝም” ስም የሚወጡ ህጎች የሀገራችንን እና የህዝቦችን ወግ፣ ባህል እና ታሪክ ታሳቢ ያደረጉ ሊሆኑ ይገባል ብሎ ያምናል። የሴኩላሪዝም ጽንሰ ሀሳብ በዋናነት ሁለት መሰረታዊ ጉዳዮችን ያካትታል። የመጀመሪያው መንግስት በሃይማኖቶች መካከል እኩልነትን ማረጋገጥ እና አለማዳለት ሲሆን ሁለተኛ መንግስት እና የሃይማኖት ተቋማት አንዱ በሌላው የውስጥ ጉዳይ አለመግባትን ይመለከታል። ከዚህ ጠቅላላ ሀሳብ በመነሳት “ሴኩላሪዝም” በፍሬ ሀሳብ ደረጃ ‘ጸረ ሃይማኖት’ አለመሆኑን እና አተገባበሩም የሀገራትን ታሪክ፣ ባህል፣ ስነ ህዝብ፣ ማህበራዊ ውቅር ወዘተ ታሳቢ ያደረገ መሆን እንዳለበት ነእፓ ይገነዘባል። ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በህገ መንግስት የተደነገገውን የመንግስት እና የሃይማኖት ግንኙነት አተገባበርን አስመልክቶ አዋጅ እንዲሁም ዝርዝ¬¬ር ደንብ እና መመሪያዎች መዘጋጀታቸው አስፈላጊ እንደሆነ ይገነዘባል። ይሁን እንጂ ሃይማኖትን እንዲሁም የመንግስት እና የሃይማኖት ግንኙነትን አስመልክቶ የሚወጡ ማናቸውም ህጎች ሊያከብሯቸው የሚገቡ ሀገራዊ እሴቶች እና የህግ ማውጣቱ ሂደቱ ሊከተላቸው የሚገቡ ስርአቶች ሊኖሩ ይገባል ብሎ ያምናል። ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ከላይ የተጠቀሱትን ህግ መንግስታዊ ድንጋጌዎች፣ ዓለም አቀፍ ተሞክሮ እንዲሁም የሀገራችንን ባህላዊ እና ሃይማኖታዊ ሀቆች ከግንዛቤ በማስገባት፣ ረቂቅ አዋጁ የሚከተሉትን የህግ፣ የታሪክ፣ የፖለቲካ፣ የሀገር ሰላም እና ደህንነት እንዲሁም ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮችን ታሳቢ ያደረገ እንዲሆን ያሳስባል፤ 1. ረቂቅ አዋጁ ከመጽደቁ በፊት ከሚመለከታቸው የሃይማኖት ተቋማት ጋር ውይይት ማድረግ፣ በቂ ግብአት መሰብሰብ፣ በረቂቅ አዋጁ ላይ የሃይማኖት ተቋማቱ እና ጠቅላላ ዜጎች ያሏቸው አስተያየቶች እና ስጋት በሚገባ ሊወሰዱ እና በአዋጁ ውስጥ ማካተት፣ 2. ኢትዮጵያውያን ለሃይማኖትና ሃይማኖተኛነት ከፍተኛ ዋጋ እና ክብር ይሰጣሉ። በመሆኑም ሃይማኖትን በተመለከተ የሚወጡ ህጎች፣ ደንቦች፤ መመሪያዎች እና አሰራሮች (በአንዳንድ የአውሮፓ ሀገሮች እንደሚታየው) ሃይማኖት የለሽነትን ለማስፋፋት ወይም ሃይማኖቶች በኢትዮጵያዊያን ህይወት ውስጥ (በግልም ሆነ በቡድን) ያላቸውን ከፍተኛ ቦታ እና ክብር የመገደብ ዓላማ ያላቸው እንዳይሆኑ ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ፣ 3. ነእፓ የሁሉም ሃይማኖቶች መሰረታዊ መልዕክት ሰላም፣ ፍቅር፣ ሰብዓዊነትና ወንድማማችነት ነው ብሎ ያምናል። በዚህ መሰረት ሃይማኖቶችን በስጋት የሚመለከቱ መጤ አስተሳሰቦችን እንዲሁም በሃይማኖቶች እና አማኙ ማህበረሰብ ላይ ምክንያት የለሽ ክልከላ እና ገደቦችን መጣል የዜጎችን ተፈጥሯዊ እና ህገ መንግስታዊ መብት የሚሸርሽር በመሆኑ መንግስት እነዚህን የመሰሉ ህጎችን ከመደንገግ እንዲቆጠብ፣ 4. ሃይማኖትን አስመልክቶ የሚወጡ ህጎች እና ደንቦች በአንድ በኩል በሀገራችን የሚገኙ የሁሉንም እምነቶች የወል ባህሪያት በሌላ በኩል የእያንዳንዱን እምነት ልዩ ባህሪያት እና ድንጋጌዎች በተቻለ መጠን ከግምት ውስጥ ያስገቡ ይሆኑ ዘንድ ጥንቃቄ እንዲደረግ፣ 5. የመንግስት እና የሃይማኖት ግንኙነት በሀገራችን መሰረታዊ የፖለቲካ ጉዳይ ሆኖ ለረዥም ዘመናት ቆይቷል። በሀገራችን ታሪክ የእምነት ነጻነትን እና እኩልነት አስመልክቶ መንግስታት ይከተሏቸው የነበሩ የተዛቡ ህጎች እና አሰራሮች በተደጋጋሚ የልዩነት እና የግጭት ምክንያቶች ሲሆኑ ተስተውሏል። በመሆኑ የመንግስት እና የሃይማኖትን ግንኙነት አስመልክቶ በሀገራችን በቀጣይ ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው ሀገራዊ ምክክር ሰፊ እና ጥልቅ ውይይት እንዲሁም መግባባት እስኪደረስ ድረስ መንግስት የተቻኮለ እና ችግሩን ይበልጥ ሊያወሳስብ ከሚችል ተግባር እንዲቆጠብ፣
إظهار الكل...
👍 36 6
"ከ90 በመቶ በላይ ሙስሊም በሆነባቸው አፋርና ሱማሌ እንኳን ሀገራዊ ምክክሩ ያደረገው የተሳታፊ ልየታ ሙስሊሙን ያገለለ ነው ተባለ! … (ሀሩን ሚዲያ፦ግንቦት 20/2016) ... በሀገራዊ ምክክሩ ላይ "የሙስሊሞች ውክልና አነስተኛነው "በሚል ላቀረበው ቅሬታ ምላሽ እንዳልተሰጠው የፌደራል መጅሊሱ ገለፀ! … በሀገራዊ ምክክሩ ላይ ከወረዳ እስከ ክልል የሚሳተፉ ተወካዮችን በተመለከተ ሙስሊም ተወካዮች ቁጥራቸው እጅግ አነስተኛ በመሆኑ እንደ ሙስሊም አጀንዳዎቹን ለማስጨበጥና በጋራ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ መግባባት ላይ ለመድረስ በበቂ ተወካዮቹ  አለመወከላቸውን የመጅሊሱ ዋና ስራአስኪያጅ አቶ ከማል ሀሩን ተናግረዋል ... የሙስሊም ውክልና አናሳ በመሆኑ ጉዳይ ላይ ከኮሚሽኑ ከፍተኛ ኃላፊዎች ጋር ተደጋጋሚ ውይይት ብናደርግም እሺ ከማለት ውጭ የሰጡት መፍትሄ እንደሌለ አስረድተዋል ። ... በነባር የተለያዩ  የማህበረሰብ አደረጃጀቶች ተወካዮች የተመረጡበት ሂደት የሙስሊሙን ተወካዮችን ቁጥር  እጅግ አነስተኛ እንዳደረገውና ተወካዮች  የተመረጡበት መንገድ  ትክክል ያለመሆኑን መስፈርቱም  በሁሉም ክልሎች  በተመሳሳይ መልኩ የተሰራ መሆኑ ተገልጿል። ... ከዘጠና ከመቶ በላይ ሙስሊም በሆኑባቸው አፋርና ሱማሌ ክልል በማህበረሰብ አደረጃጀት ውክልና በሚል በክልሉ ለሙስሊሙ የተሰጠው ውክልና ከአምሳ ከመቶ  እንደማይበልጥ ተናግረዋል ። ... ምክር ቤቱ አጀንዳዎቹን ያካተተበትን ሰነድ ማቅረቡን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ትናንት ሰኞ ግንቦት 19/2016 በዋና ጽሕፈት ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አረጋግጧል።ይሁንና አጀንዳዎችን ከመጅሊሱ ጋር በመወያየት እናያቸዋለን ከማለት የዘለለ ምላሽ ከኮሚሽኑ አልተሰጠም። ... በሀገራዊ የጋራ ጉዳዮች መተማመን ፣ መግባባትና እርስ በእርስ  እውቅና ያለመሰጣጣት ፈተናዎች ውስጥ የምንገባበት አንዱ ምክንያት ገና ከመነሻው የማህበረሰብ  ወኪሎች በትክክል አለመወከላቸውና አለመወከላቸው እየታወቀ ለማስተካከል አልመፍቀድ በመሆኑ  ኮሚሽኑ ሳይዘገይ ምላሽ እንድሰጥበት ተጠይቋል። ... ©ሀሩን ሚዲያ
إظهار الكل...
👍 63🤔 6
4
ኢትዮጲያውያን ሙስሊሞች ሚያቀርቧቸውን "አጀንዳዎች" ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በትኩረት እንዲመለከታቸው ጥሪ ቀረበ! … (ሀሩን ሚድያ ግንቦት 20/2016፤አዲስ አበባ) … የኢትዮጲያ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሚያካሂደው አጀንዳ ማሳባሰብ ሂደት በኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የቀረቡትንን እና በሙስሊሙ ማህበረሰብ ሚቀርቡ አጀንዳዎች በዋነኝነት ትኩረት እንዲሰጣቸው ጥሪ ቀርቧል። … "ሀሩን ሚድያ" ሀገራዊ ምክክርን አስመልክቶ ባዘጋጀው ውይይት ላይ ተሳታፊዎች እንደገለፁት "ኢትዮጲያውያን ሙስሊሞች" ከዚህ በፊት በነበሩ ስርዓቶች በርካታ በደሎችን፤መገፋቶችን፤ በሁሉም አካባቢ ማስተናገዳቸውን ገልፀው በምክክሩ ቀዳሚ አጀንዳ መሆን ያለበት የኢትዮጲያውያን ሙስሊሞች ጥያቄ እና መፍትሄ ያልዋቸውን ሀሳቦች ተቀብሎ ወደስራ ማስገባት አለበት ብለዋል። … ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በትላትናው ዕለት በሰጠው መግለጫ በኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አማካኝነት የኢትዮጲያውያን ሙስሊሞች ጥያቄዎች መቅረባቸውን አምኖ ውይይት እንደሚደረግበትም በሰጠው መግለጫ ላይ ገልጿል። … ©ሀሩን ሚድያ
إظهار الكل...
👍 31👎 1