Deborah School
الذهاب إلى القناة على Telegram
4 339
المشتركون
+724 ساعات
+107 أيام
-930 أيام
أرشيف المشاركات
4 339
ውድ ወላጆች/አሳዳጊዎች
ነገ ሰኔ 5 : 2018 ዓም ከ 1ኛ - 4ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች ትምህርታዊ ጉዞ ማለትም ( Unity park) ለመጎብኘት ይሄዳሉ። ስለሆነም በዕለቱ (አረብ ሰኔ 5) የመዋዕለ ህፃናት እና ከ5ኛ 12ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች ትምህርት ይሰጣል።
ማሳሰብያ:-
1. በጉብኝቱ ላይ የሚሳተፉ ተማሪዎች የተሟላ ዩኒፎርም ማድረግ አለባቸው። ዩኒፎርም ያልለበሰ ተማሪ አናስተናግድም። (በቦርሳ ውስጥ ሌላ ልብስ ይዞ መምጣት ወይም ልብስ ደርቦ መምጣት አይቻልም)
2. ተማሪዎች ምሳቸውን ይዘው መምጣት ይኖርባቸዋል።
3. በጉብኝቱ ላይ መሳተፍ የሚችሉት ትኬት የገዙ ተማሪዎች ብቻ መሆኑን እንገልፃለን።
4. ምንም አይነት ኤሌክትሮኒክስ (ሞባይል፣ ታብሌት) ይዞ መምጣት አይፈቀድም።
5. የጉዞ መነሻ ጠዋት 2ሰዐት ሲሆን ወደ ትምህርት ቤት መመለሻ ቀን 9 ሰዐት መሆኑን እንገልፃለን። በመሆኑም ተማሪዎች ከጉዞ መነሻ ሰዐት ቀደም ብላችሁ እንድትገኙ።
ትምህርት ቤቱ
4 339
ለ6 እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች፣
ለ6ኛ እና 8 ኛ ክፍል ተማሪዎች አርብ ሰኔ 5/2018 ዓ.ም ኦረንቴሽን ስለሚሰጥ ጠዋት 1:30 ሰዐት ላይ የተሟላ የትምህርት ቤት የደንብ ልብስ በመልበስ ትምህርት ቤት እንድትገኙ እናሳስባለን። ኦረንቴሽን ለግማሽ ቀን ብቻ ስለሆነ የ6ኛ እና የ 8ኛክፍል ተማሪዎች ከቀኑ 6 ሰዓትላይ ወደ ቤታቸው ይመለሳሉ።
ትምህርት ቤቱ።
4 339
ሰኔ 2: ቀን 2018
ውድ ወላጆች / አሳዳጊዎች
ት/ቤታችን የ2018 ዓመት ትምህርትን ወደ ማጠቃለሉ መድረሱን ስናሳውቃችሁ በታላቅ ደስታ ነው:: በመሆኑም በቀጣይ የሚከናወኑ ኘሮግራሞች እንደሚከተለው መሆኑን እንገልፃለን
1. ከ ሰኞ ሰኔ 8- እሮብ ሰኔ 10/2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ይሰጣል፡
2. ከሐሙስ ሰኔ 11- አርብ ሰኔ 12/2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ይሰጣል፡
3. ማክሰኞ :ሰኔ 9:2018 በማጠቃለያ ፈተና ውስጥ ያልተካተቱ ትምህርቶች ለክልልና አገር አቀፍ ተፈታኝ ላልሆኑ ክፍሎች (1,2,3,4,5, 7, 9,10 እና 11) የማጠቃለያ ፈተና ይሰጣል።
4. ከ እሮብ: ሰኔ 10- አርብ:ሰኔ 12/ 2018 ዓ.ም የ2ኛ ወሰነ ትምህርት የማጠቃለያ ፈተና ለ ክልልና አገር አቀፍ ተፈታኝ ላልሆኑ ክፍሎች (1,2,3,4,5,7,9,10 እና 11) በፈተና ፕሮግራም መሰረት ፈተና ይሰጣል፡፡
5. ሰኞ ሰኔ 15: 2018 ዓ.ም :- የታረሙ የፈተና ወረቀቶች /ውጤት/ ለወላጅ/አሳዳጊ ብቻ የሚሰጥበት ቀን መሆኑን ተገንዝባችሁ ወላጆች/አሳዳጊዎች ከጠዋቱ 2: 00 ሰዐት ጀምሮ እስከ ቀን 6:00 ሰዐት ድረስ ትምህርት ቤት በመምጣት የልጆቻችሁን የታረመ የፈተና ወረቀት እንድትወስዱ ትምህርት ቤቱ ይጠይቃል።
ማሰሰብያ፣ በእለቱ ማንም ተማሪ ትምህርት ቤት ካለ ወላጅ መምጣት እንደማይችል እንገልፃለን።
6. ከሰኞ ሰኔ 15- አርብ ሰኔ 19/2018 ዓ.ም የተማሪዎች የዉጤት ማጠቃለያ የሚሰራበት ይሆናል፡፡
6. ቅዳሜ: ሰኔ 20: 2018 ዓም የትምህርት ቤት የመዝጊያ ዝግጅት (Closing Day Ceremony) የሚደረግበት ቀን ሲሆን እርስዎም በእለቱ እንዲገኙ ተጋብዘዋል።
7. ሰኞ ሰኔ 22: 2018 የተማሪዎች የዉጤት መግለጫ ካርድ መስጫ ቀን ሲሆን፣ በእለቱ ካርድ የሚሰጠው ለወላጅ ብቻ መሆኑን እንገልፃለን።
8. ከሐምሌ 1 - ሐምሌ 10: 2018 ዓ.ም ለ2018ዓም ለነባር ተማሪዎች ምዝገባ ወቅት ሲሆን፣ ያለን ቦታ ውስን በመሆኑ፣ በወቅቱ ልጁን ላላስመዘገበ ወላጅ ሊፈጠር ለሚችለው ችግር ትምህርት ቤቱ ኃላፊነት አይወስድም።
8. ከሐምሌ 20- ነሐሴ 20 :2018 ዓ.ም የክረምት የማጠናከርያ ትምህርት የሚሰጥበት ወቅት ሲሆን በተለይ የ2019 ዓ•ም የክልልና አገር አቀፍ ተፈታኝ ክፍሎች (6,8 እና 12) በዚህ የማጠናከርያ ትምህርት ውስጥ መሳተፍ ይኖርባቸዋል።
9. ከሰኔ 24 - ሐምሌ 17: 2018 ዓ.ም የ12ተኛ ክፍል የዩንቨርስቲ መግቢያ ፈተና በሁለት ዙር በበይነ መረብ ይሰጣል።
ትምህርት ቤቱ
4 339
ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች
ማሳሰብያ
1. ከሰኞ ሰኔ 1: እሮብ ሰኔ 3:2018 ዓም የማጠቃላያ ሞዴል ፈተና በተላከው ፕሮግራም መሰረት በወረቀት ይሰጣል።
2. አድሚሽን ካርዳችሁን ለመውሰድ ያለባችሁን ማንኛውንም የትምህርት ክፍያ በማጠናቀቅ እና ከፋይናንስ ቢሮ clearance በማምጣት መውሰድ ትችላላችሁ።
3ኛ፡ የተሟላ ዩኒፎርም ያደረገ እና ፀጉር (Clean cut) ብቻ የተቆረጠ ተማሪ የምናስተናገድ ሲሆን ይሄንን ላላሟላ ተማሪ ወደ ት/ቤት ቅጥር ግቢ የማናስገባ ሲሆን በነዚህ ተማሪዎች ላይ ትቤቱ ኃላፊነት አይወስድም።
4ኛ ፡ ፈተናው በሙሉቀን ፕሮግራም የሚሰጥ በመሆኑ ፡ ተማሪዎች ምሳቸውን ይዘው እንዲመጡ። ማንም ተማሪ ለምሳ ከት/ቤት መውጣት አይችልምም ምሳም ከደጅ ማስመጣት አይችልም ።
5ኛ፡ ሞባይል ይዞ የተገኘ ተማሪ ሞባይሉ ተወርሶ ከፈተና ላይ ይታገዳል።
ትምህርት ቤቱ
4 339
ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች
ውድ ተማሪዎች ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመግባት የተዘጋጀውን የመለማመጃ ጥያቄዎችን(mock exam) በመስራት እንድትለማመዱ እናሳስባለን።
http://mock3.ethernet.edu.et
ት/ቤቱ
4 339
ሰላም እንዴት አደራችሁ የአስፈታኝ ት/ቤቶች ር/መ/ራንና ባለድርሻ አካላት?
አንደሚታወቀው ከነገ ማለትም ግንቦት 27 እና 28//2018 ዓ.ም በክ/ከተማ ደረጃ ወጥ በሆነ ፕሮግራም በሁሉም የ12ኛ ክፍል ጣቢያዎች የሙከራ ፈተና እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም ከፈተኛ የሆነ የተፈታኝ ቁጥር ያላችሁ ተቋማት ቅዳሜና እሁድን በመጨመር በየዙሩ የሚፈተኑ ተማሪዎችን ድልድል በአይዲ ቁጥራቸው ቅደም ተከተል መሰረት እኩል ለሁለት በመክፈል የመጀመሪያዎቹን ግማሽ ተማሪዎች በዙር አንድ ( ሀሙስ) ሲሆን የሁለተኛዎቹን ግማሽ ደግሞ በዙር ሁለት(ቅዳሜ) እንዲሁም የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችንም በተመሳሳይ በዙር አንድ (አርብ) እነዲሁም በዙር ሁለት (እሁድ) እንዲተገበር ለማሳሰብ እንወዳለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
ሁሉም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚፈተኑ ተማሪዎች ልምምዱን ግዴታ በወጣው ፕሮግራም መሰረት መወስድ እንደሚኖርባቸው ለተፈታኞች እንድታሳውቁ እያልን በክ/ከተማ ደረጃ በሁሉም የፈተና ጣቢያዎች ተግባሩ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት የተጠናከረ ክትትል እንደሚደረግ ለማስገንዘብ እንወዳለን፡፡
ሁሉም ጣቢያዎች የተሰሩ የኔትወርክ፤ኤሌክትሪክና የኮምፒዩተሮችን አቅም ለመፈተሸ እንዲረዳ ፈተናውን በተመሳሳይ ሰዓት በSafe Exam Browser ብቻ መስጠት ይኖርባችኋል!!
4 339
ሰላም እንዴት አደራችሁ የአስፈታኝ ት/ቤቶች ር/መ/ራንና ባለድርሻ አካላት?
አንደሚታወቀው ከነገ ማለትም ግንቦት 27 እና 28//2018 ዓ.ም በክ/ከተማ ደረጃ ወጥ በሆነ ፕሮግራም በሁሉም የ12ኛ ክፍል ጣቢያዎች የሙከራ ፈተና እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም ከፈተኛ የሆነ የተፈታኝ ቁጥር ያላችሁ ተቋማት ቅዳሜና እሁድን በመጨመር በየዙሩ የሚፈተኑ ተማሪዎችን ድልድል በአይዲ ቁጥራቸው ቅደም ተከተል መሰረት እኩል ለሁለት በመክፈል የመጀመሪያዎቹን ግማሽ ተማሪዎች በዙር አንድ ( ሀሙስ) ሲሆን የሁለተኛዎቹን ግማሽ ደግሞ በዙር ሁለት(ቅዳሜ) እንዲሁም የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችንም በተመሳሳይ በዙር አንድ (አርብ) እነዲሁም በዙር ሁለት (እሁድ) እንዲተገበር ለማሳሰብ እንወዳለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
ሁሉም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚፈተኑ ተማሪዎች ልምምዱን ግዴታ በወጣው ፕሮግራም መሰረት መወስድ እንደሚኖርባቸው ለተፈታኞች እንድታሳውቁ እያልን በክ/ከተማ ደረጃ በሁሉም የፈተና ጣቢያዎች ተግባሩ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት የተጠናከረ ክትትል እንደሚደረግ ለማስገንዘብ እንወዳለን፡፡
ሁሉም ጣቢያዎች የተሰሩ የኔትወርክ፤ኤሌክትሪክና የኮምፒዩተሮችን አቅም ለመፈተሸ እንዲረዳ ፈተናውን በተመሳሳይ ሰዓት በSafe Exam Browser ብቻ መስጠት ይኖርባችኋል!!
4 339
ውድ ወላጆች/ አሳዳጊዎች
ከትምህርት ፅ/ቤት በተገለጸልን መሰረት ከግንቦት 24 እስከ ግንቦት 26 ትምህርት ቤት ዝግ በመሆኑ ተማሪዎች ቤት የሚቆዩ ይሆናል ። ተማሪዎች ወደ ት/ቤት የሚመለሱት ሐሙስ ግንቦት 27 ፣ 2018 ዓ.ም መሆኑን እያሳወቅን ፣ ተማሪዎች ቤት በሚቆዩበት ሰዓት የፈተና ወቅት የቀረበ በመሆኑ ተማሪዎች ራሳቸውን ለፈተና እንዲያዘጋጁ አስፈላጊውን ድጋፍ እና ጠንካራ ክትትል በማድረግ ሃላፊነትዎን እንዲወጡ እንጠይቃለን ።
ት/ቤቱ
Dear Parents/Guardians,
Based on the information we received from the Education Office, the school will be closed from June 1st to June 3rd. Therefore, students will stay at home during this period.We would like to inform you that students will return to school on Thursday, June 4, 2026. As the examination period is approaching, we kindly request that you fulfill your responsibility by providing the necessary support and close supervision to help your children prepare for their exams while they are at home.
The School
4 339
ውድ ወላጆች/አሳዳጊዎች
ነገ ግንቦት 21: 2018 ዓም ከ5ኛ -11ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች ትምህርታዊ ጉዞ ማለትም ( ብሔራዊ ሙዚየም እና የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የሚገኘውን ገነተ ልዑል ቤተ መንግስት ሙዚያም) ለመጎብኘት ይሄዳሉ። ስለሆነም በዕለቱ (አረብ ግንቦት 21) ከመዋዕለ ህፃናት - 4ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች ትምህርት የሚኖር ሲሆን ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ግን የበይነ መረብ ፈተና በትምህርት ቤት ልምምድ ያደርጋሉ።
ማሳሰብያ:-
1. በጉብኝቱ ላይ የሚሳተፉ ተማሪዎች የተሟላ ዩኒፎርም ማድረግ አለባቸው። ዩኒፎርም ያልለበሰ ተማሪ አናስተናግድም። (በቦርሳ ውስጥ ሌላ ልብስ ይዞ መምጣት ወይም ልብስ ደርቦ መምጣት አይቻልም)
2. ተማሪዎች ምሳቸውን ይዘው መምጣት ይኖርባቸዋል።
3. በጉብኝቱ ላይ መሳተፍ የሚችሉት ትኬት የገዙ ተማሪዎች ብቻ መሆኑን እንገልፃለን።
4. የጉዞ መነሻ ጠዋት 2ሰዐት ሲሆን ወደ ትምህርት ቤት መመለሻ ቀን 9 ሰዐት መሆኑን እንገልፃለን። በመሆኑም ተማሪዎች ከጉዞ መነሻ ሰዐት ቀደም ብላችሁ እንድትገኙ።
ትምህርት ቤቱ
4 339
ውድ ውላጆች
ነገ ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም. ለሚካሄደው ጉብኝት ትኬት ነገ ጠዋት እስከ 2፡30 ሰዓት ድረስ መግዛት እንደሚችሉ ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
