ar
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

الذهاب إلى القناة على Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

إظهار المزيد
2 755
المشتركون
-124 ساعات
+57 أيام
+4130 أيام
أرشيف المشاركات
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! አንድነታችን ለቤተክርስቲያናችን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የጠቅላላ ጉባኤ የአቋም መግለጫ 1. በአንድነቱ የቀረበውን ዕቅድ ያፀደቅን ሲሆን ሁላችንም ለተግባራዊነቱ እንተጋለን ፡፡ 2. የሰ/ት/ቤትን ዝማሬን በተመለከተ ጉባኤው ተወያይቶ ባፀደቀው መሰረት ሁሉም ሰ/ት/ቤት የሚጠቀምበትን ልብሰ ስብሀት የካህናት በተለይም የዲያቆናት  አክሊል የሆነና ተመሳሳይ የሆነ ከዚህ በኋላ የትኛውም ሰ/ት/ቤት እንዳይጠቀም፡፡ የልብሰ ስብሐትና የአክሊል ዓይነት ተወስኖ በመመሪያ እስኪወርድ ድረስ ከካህናትና ከዲያቆናት አልባሳትና አክሊል ውጪ ሰ/ት/ቤቶች ባላቸው ልብሰ ስብሐት እየተጠቀሙ እንዲቆዩ ተስማምተናል፡፡ 3. አዘማመርን በተመለከተ ያሬዳዊ ዜማን የጣሰ ወደ ጭፈራ ያደላ አዘማመር እንዲቆም ይህንንም ለማስፈፀም ከክፍለ ከተማ አንድነት ክትትል እንዲያደርግ ተስማምተናል፡፡ 4. የአጫበር ስም እየተተገበረ ያለ አዘማመርን በተመለከተ የዘርፉ ሊቃውንትን ጨምሮ ብዙአባቶችን እና ምዕመናንን ያሳዘነ ጉዳይ በመሆኑ በሊቃውንት ተጠንቶ በቅድስት ቤተክርስቲያን ውሳኔ ተላልፎ እስኪተገበር ድረስ ሁሉም ሰንበት ትምህርት ቤት የአጫበር ስም የሚደረግ ዝማሬን እንዲያቆሙ፡፡ 5. ከላይ በተጠቀሱት የአለባበስና አዘማመር ጉዳይ በሀገረ ስብከት መመሪያ እንዲተላለፍ እና ሰበካ ጉባኤያት ቁጥጥር እንዲያደር ተስማምተናል፡፡ 6. የ2018ዓ.ም የአጥቢያ የሰ/ት/ቤት የአመራር ምርጫ ለማስፈፀም ጉባኤው የተስማማ ሲሆን የምርጫ ወቅቱ እስከሚደርስ ድረስ አሁን ያለ ሁሉም  አመራር በአዲስ እያደራጀ እንዲቆይ እና ምንም አይነት የሰንበት ትምህርት ቤት አመራር ምርጫ እንዳይካሄድ እና የተለየ ችግር ያለባቸው ሰ/ት/ቤቶች ብቻ ክክፍለ ከተማ አንድነቱ ጋር እየተወያዩ አደራጅ ጊዜያዊ ኮሚቴ እንዲያቋቁሙ ተስማምተናል ፡፡ 7.  የሰንበት ትምህርት ቤቶችን መረጃ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለማራጀት በአንድነቱ በተዘጋጀው ፖርታል እንድንጠቀም የራሳቸው ዳታ ቤዝ ያላቸው ሰ/ት/ቤቶች ከሀገረ ስብከቱ አንድነት ዳታ ቤዝ ጋር እንዲያናብቡ እና በየደረጃው የሚያድገውን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ሁሉም ሰ/ት/ቤቶች ሀዋርያዊ አገልግሎታችንን ለመፈፀም በጋራ ለመስራት ተስማምተናል፡፡  © የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

''ቅዱስ አማኑኤል '' አማኑኤል ማለት እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው።
''ቅዱስ አማኑኤል '' አማኑኤል ማለት እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት 11ኛ አመት 2ተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ተጀመረ። በትላንትናው እለት ሐምሌ 26 ቀን 2017 ዓ.ም ለሁለት ቀን የሚቆየው የአዲስ አበባ ሀገረ
+5
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት 11ኛ አመት 2ተኛ መደበኛ  ጠቅላላ ጉባኤ ተጀመረ። በትላንትናው እለት ሐምሌ 26 ቀን 2017 ዓ.ም  ለሁለት ቀን የሚቆየው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትቤቶች አንድነት 11ኛ አመት 2ተኛ መደበኛ  ጠቅላላ ጉባኤ በመንበረ ፓትሪያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት  ተጀምሯል ። በጉባኤው የአንድነቱ  የ6 ወራት የእቅድ አፈፃጸም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በቀረበው ሪፖርት ዙሪያ ከተሳታፊዎች ጥያቄና አስተያየት ተነስቶ ወይይት እና ምላሽ ተሰጥቶበታል ። በመጨረሻም ጉባኤው በ2018 ዓ.ም የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሥራ  አመራር አባላት ምርጫ ተከናውኖ የጉባኤው የመጀመሪያ ቀን ወሎ ተፈጽሟል።   ©የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የሐዘን መግለጫ የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነው የአቶ እንዳለ ሰይፉ(ዐበይ) ባለቤት አርፋለች ሥርዓተ ቀብሯዎ ነገ ቅዳሜ ሐምሌ 26/2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 በገነተ ኢየሱስ ቤ/ክ ይፈጸማል የምትችሉ አባላት በቀብሩ ላይ በመገኘት እንድናጽናናቸው ይሁን። የእህታችንን ነፍስ ይማርልን ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12

ለፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት አባላት በሙሉ ===================== ለቀጣዩ ሶስት ዓመታት የሰንበት ትምህርት ቤታችንን ሊመሩ የሚችሉ የስራ አመራር አባላትን ለመምረጥ ነሐሴ 18/2017 ዓ.ም
ለፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት አባላት በሙሉ    ===================== ለቀጣዩ ሶስት ዓመታት የሰንበት ትምህርት ቤታችንን ሊመሩ የሚችሉ የስራ አመራር አባላትን ለመምረጥ  ነሐሴ 18/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:00 ቀነ ቀጠሮ በአስመራጭ ኮሚቴው የተያዘ በመሆኑ የወጣትና የባለትዳር ጉባኤ አባላት በዕለቱ በመገኘት ምርጫውን በእግዚአብሔር ፈቃድ እንድናከናውን በአምላከ ቅዱስ ሚካኤል ስም ጥሪያችንን እናቀርባለን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ለፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት አባላት በሙሉ    ===================== በቀጣይ የሰንበት ትምህርት ቤታችንን ሊመሩ የሚችሉ የስራ አመራር አባላትን ለመምረጥ ነሐሴ 18/2017 ዓ.ም ቀነ ቀጠሮ በአስመራጭ ኮሚቴው የተያዘ በመሆኑ የወጣትና የባለትዳር ጉባኤ አባላት በዕለቱ በመገኘት ምርጫውን በእግዚአብሔር ፈቃድ እንድናከናውን በአምላከ ቅዱስ ሚካኤል ስም ጥሪያችንን እናቀርባለን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

''ሥርዓተ አምልኮ ዘፍልሰታ'' የዕለቱ መምህር ሥርዓተ አምልኮ ዘፍልሰታ የሚለውን መጽሐፍ ያዘጋጁት መምህር ዲ/ን ጥላዬ አያሌው የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር የፊታችን ቅዳሜ ሐምሌ 26/2017 ዓ.ም
''ሥርዓተ አምልኮ ዘፍልሰታ''            የዕለቱ መምህር  ሥርዓተ አምልኮ ዘፍልሰታ የሚለውን መጽሐፍ ያዘጋጁት መምህር          ዲ/ን ጥላዬ አያሌው የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር  የፊታችን ቅዳሜ  ሐምሌ 26/2017 ዓ.ም ከምሽቱ  11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ  ይምጡ ይማሩ በብዙ ያተርፋሉ እንዳይቀሩ። የቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ክፍል ሐዋርያዊ ጉዞ አከናወነ። የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ከአዲስ አበባ 325 ኪ.ሜ ርቀ
+9
የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ክፍል ሐዋርያዊ ጉዞ አከናወነ።      የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ከአዲስ አበባ 325 ኪ.ሜ ርቀት በመጓዝ በሀላባ ጠንባሮ ዞን የሚገኙትን ሀላባ ጠንባሮ ሆዶ ቅዱስ ገብርኤል፣ በጠንባሮ ወረዳ የሚገኝ ከ100 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠረውን ቤ/ክ ጨምሮ ከ24 አብያተ ቤተክርስቲያናት ምዕመናንን በመሰብሰብ በወንጌል ፣ ትምህርትና በተለያዩ ቤተክርስቲያናዊ ጉዳዮች ስልጠና በመስጠት ሐዋርያዊ ተልዕኮ አከናውኗል ።   በዚህ ጉዞ ላይ ለአንድ ቤተ ክርስቲያን አንድ ካህን የተመደበባቸውን አብያተ ክርስቲያናት፣ የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናት ፣ኦርቶዶክሳውያን ምዕመናን ለሚጠይቁት ጥያቄ ምላሽ መስጠት ባለመቻላቸው ተጨንቀው ሲሄዱ መፍትሔ ያጡ ኑዛዜ የሚሰጣቸው ካህናት ፣የሚቀበሩበት ቦታ ባለማግኘታቸው ምክንያት በአጠገባቸው በቅርብ ወደአገኙት የፕሮቴስታንት አዳራሽ ገብተዋል ነገር ግን ሰ/ት/ቤታችን በዚህ ጉዞ ምዕመናኑን በመሰብሰብ ትምህርትና ስልጠና በመስጠት የማጽናት ሥራ ተከናውኗል ቅዱስ እግዚአብሔር በደሙ የመሰረታትን ቅድስት ቤተክርስቲያን ይጠብቅልን ምዕመናኑንም  በሃይማኖታቸው ያጽናልን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የሐዘን መግለጫ የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነው የአቶ ተክሉ ማሞ አባት አርፈዋል ሥርዓተ ቀብራቸው ዛሬ ሐሙስ ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰአሊተ ምሕረት ቤ/ክ ይፈጸማል የምትችሉ አባላት በቀብሩ ላይ በመገኘት እንድናጽናናቸው ይሁን። የአባታችንን ነፍስ ይማርልን ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የሰንበት ትምህርት ቤታችን ዓመታዊ ጉዞ የሚከናወንበት ቀን ደረሰ!!
የሰንበት ትምህርት ቤታችን ዓመታዊ ጉዞ የሚከናወንበት ቀን ደረሰ!!

ሐምሌ20/2017 የጋብቻ በዓላችንን በጋራ እናክብር ጉባኤ ማስታወሻ