ar
Feedback
Venue

Venue

قناة بسيطة

መድረሻ ባይኖር ፣ መጓዝ ብርቅ ነበር! : መራመድ ባልከፋ ፣ መድረሻም ባልጠፋ ነገ ላይ ለመድረስ ፣ ሰው ባያጣ ተስፋ ።

إظهار المزيد
3 791
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-27 أيام
+330 أيام
أرشيف المشاركات
Venue
3 791
በእርግጥም ልንለያይ እንገናኛለን፣ ልንገናኝም እንለያያለን! « #Venue በአጠቃላይ ወደ 8 አመታት ያህል እዚሁ ቴሌግራም ላይ ቆይቷል። በእነዚህ አመታት ውስጥ ፅሁፎቹ እዚህ ቻናል ላይ አልተገደቡም
በእርግጥም ልንለያይ እንገናኛለን፣ ልንገናኝም እንለያያለን! « #Venue በአጠቃላይ ወደ 8 አመታት ያህል እዚሁ ቴሌግራም ላይ ቆይቷል። በእነዚህ አመታት ውስጥ ፅሁፎቹ እዚህ ቻናል ላይ አልተገደቡም። በተለያየ መንገድ ከቻናሉ ውጪም ብዙ ሰዎች ጋር ደርሷል። እንግዲህ በተነሱት ሀሳቦች ሰዎች ተጠቅመውበታል አልተጠቀሙበትም የሚለውን አላህ ያውቃል። እስካሁን የምታውቁትን ተዋውሰንበታል። ተመካክረንበታል። በአላህ ፍቃድ መልካም ሰዎችንም የተዋወቅኩበት እና ያፈራሁበት ቤት ነው። አሁን ለራሴ ስል ቬኑን መተው ያለብኝ ጊዜ ላይ ነኝ። ቬኑ ቆይታውም፣ የነበረውም፣ እዚህ ጋር ይጠናቀቃል(ተጠናቋል!)። ይህ የልቤ ውሳኔ ሲሆን ድንገት ያሰብኩት ሳይሆን ረጅም ጊዜ ስብሰለሰልበት የነበረ ነው። ልቤ ልክ ስለመሆኑ አለመሆኑ ረጅም ጊዜ ተብሰልስዬበታለሁ፣ በጊዜ ውስጥም መልሴን አግኝቻለሁ። እናም የልቤን ውሳኔ ማክበርን መርጫለሁ። ለምን? እንዴት? የሚለውን ማስረዳት አልችልም ከይቅርታ ጋር። አንዳንድ ስንብቶችም መገናኘቶችም ድንገተኛ ይሆናሉ። ህይወት አይደል እንዲህ ነው። ነገራት እንዴት ሊቀየሩ እንደሚችሉ አይታወቁም። በተጓዝነው ጉዞ ሁሉ መልካሙን ሀሳብ ብቻ አስታውሱ፣ የማይሆናችሁን እርሱት። በዚህ በቬኑ ላይ ይህ የመጨረሻ ስንብቴ ነው። በምን መንገድ ዳግም ልንገናኝ እንደምንችል አላውቅም፣ በመጥፎው ፈፅሞ እንዳንገናኝ ግን መሻቴ ነው። #Venue ይባል በነበረ የቴሌግራም ቻናል አንዳንድ ሀሳቦችን ለማንሳት ይሞክር የነበረና በቬኑ ቻናል ሰበብ የምታውቁት የነበረው ሰው ይወዳችኋል። ያከብራችኋልም። መልካሙንም ከሚመኝላችሁ ነው። እስከዛሬ ድረስ ስለነበረን ስላሳለፍናቸው ጊዜያት ሁሉ ከልብ አመሰግናለሁ። አላህ ያክብርልኝ! ሰላም ለልባችሁ! » [ አብዱልሀኪም ሰፋ ]

Venue
3 791
ሰላም ለልባችሁ! : @Venuee13 @Venuee13
ሰላም ለልባችሁ! : @Venuee13 @Venuee13

Venue
3 791
ማቅፈው ፍቅር ስጠኝ ልቤን የሚያሞቀው ምኞት አታሳጣኝ አንተን ‘ምጠይቀው እያደር 'ሚጣፍጥ መውደድን አድለኝ ከወደድከው ባርያህ ፍፁም አትነጥለኝ። እንዳልዘም እንዳልጠም እንድበጅ ለራሴ በፍቅርህ ሸሽገ
ማቅፈው ፍቅር ስጠኝ ልቤን የሚያሞቀው ምኞት አታሳጣኝ አንተን ‘ምጠይቀው እያደር 'ሚጣፍጥ መውደድን አድለኝ ከወደድከው ባርያህ ፍፁም አትነጥለኝ። እንዳልዘም እንዳልጠም እንድበጅ ለራሴ በፍቅርህ ሸሽገኝ ከምትስተው ነፍሴ። ያ ወዱድ ያ ወዱድ! [ አብዱልሀኪም ሰፋ ] : @Venuee13 @Venuee13

Venue
3 791
ባይገባኝ ባላውቀው አንተን ይዤ ብጓዝ እንደማልረታ አለቅሳለሁ ደክሞኝ አንዴም ሳልበረታ። አታስጠቃም አንተ አሳልፈህ አትሰጥም በተቅዋ ካልሆነ አታበላልጥም። አብልጠኝ በፍቅርህ አፈራርሰህ ስራኝ አዳማጭ
ባይገባኝ ባላውቀው አንተን ይዤ ብጓዝ እንደማልረታ አለቅሳለሁ ደክሞኝ አንዴም ሳልበረታ። አታስጠቃም አንተ አሳልፈህ አትሰጥም በተቅዋ ካልሆነ አታበላልጥም። አብልጠኝ በፍቅርህ አፈራርሰህ ስራኝ አዳማጭ አድርገኝ እዝነትህ ሲጠራኝ። ያ ወዱድ ያ ወዱድ! [ አብዱልሀኪም ሰፋ ] : @Venuee13 @Venuee13

Venue
3 791
ያ ወዱድ ያ ወዱድ! : @Venuee13 @Venuee13
ያ ወዱድ ያ ወዱድ! : @Venuee13 @Venuee13

Venue
3 791
በያዝኩት ሳልረካ የሰው እየተመኘሁ ትሻልን ፈትቼ ትብስን አገኘሁ። ያበጀኸው ንቆ የሚያበጅ ለራሱ ከአኼራም በፊት እዚሁ ያገኛል መልሱ። እኔ የሩቅ አሳሽ የጎኔን የማላይ የትሻልን እንባ አነባሁ እንደጉ
በያዝኩት ሳልረካ የሰው እየተመኘሁ ትሻልን ፈትቼ ትብስን አገኘሁ። ያበጀኸው ንቆ የሚያበጅ ለራሱ ከአኼራም በፊት እዚሁ ያገኛል መልሱ። እኔ የሩቅ አሳሽ የጎኔን የማላይ የትሻልን እንባ አነባሁ እንደጉድ በትብስ ስሰቃይ ያበጀኸው ‘ምወድ አድርገኝ በእዝነትህ የመረጥከው ንቄ እንዳልቆም ከፊትህ። ያ ወዱድ ያ ወዱድ! [ አብዱልሀኪም ሰፋ ] : @Venuee13 @Venuee13

Venue
3 791
እንደ ጨርቅ ሳስቶ ህልምሽ ተቀደደ ጭድ እንዳየው እሳት ሰላምሽ ነደደ። ጥርስሽ ውሸት አውቆ ከእውነት ተጣላ ትላንት ላይ ቆሞ ቀረ ወደ ኋላ። ምነው የኔ ጌታ በልብሽ አነሰ ጸጋው እኩል ሰጥቶን ላንቺ
እንደ ጨርቅ ሳስቶ ህልምሽ ተቀደደ ጭድ እንዳየው እሳት ሰላምሽ ነደደ። ጥርስሽ ውሸት አውቆ ከእውነት ተጣላ ትላንት ላይ ቆሞ ቀረ ወደ ኋላ። ምነው የኔ ጌታ በልብሽ አነሰ ጸጋው እኩል ሰጥቶን ላንቺ ያልደረሰ? ዱዓዬን ምትሸሺ ሌት ቀን ስለምነው ማን ቀማሽ ጌታዬን ልቤን የጠገነው? የካሰኝ ያስደሳኝ ያላስከፋኝ ጌታ ላንቺም አደላድሏል ሰላምና ደስታ። እቴ ያይኔ አበባ ከፍቶሻል አውቃለሁ ክፈቺለት ተስፋን ያ ወዱድ ብያለሁ። ያ ወዱድ ያ ወዱድ! [ አብዱልሀኪም ሰፋ ] : @Venuee13 @Venuee13

Venue
3 791
አኑሬው ሸሽጌው ልቤን ከሰው ደጃፍ ሲረገጥ አመመኝ ተጥሎ ትቢያ ጫፍ በወጪ ወራጁ በአፍ እየቆሸሸ ፍቅር የተመኘው ከአብሮነት ሸሸ። ምሬቴን ጨክኜ አኝኬ እንዳልውጠው ከመኖር ማኩረፌ ሀሞቴን መጠጠው። ወ
አኑሬው ሸሽጌው ልቤን ከሰው ደጃፍ ሲረገጥ አመመኝ ተጥሎ ትቢያ ጫፍ በወጪ ወራጁ በአፍ እየቆሸሸ ፍቅር የተመኘው ከአብሮነት ሸሸ። ምሬቴን ጨክኜ አኝኬ እንዳልውጠው ከመኖር ማኩረፌ ሀሞቴን መጠጠው። ወትሮስ ካንተ ርቆ እርም ነው መኗኗር ምኞት ላይሳካ ልብ ይበላል አሳር ማን አለኝ የሚያብር ከራሴ ስታገል አበርታኝ ጌታዬ ውልግድ ነው የኔ አመል። ያ ወዱድ ! ያወዱድ! [ አብዱልሀኪም ሰፋ ] : @Venuee13 @Venuee13

Venue
3 791
« አል ወዱድ፣ የፍቅር ምንጩ፣ ወዳጁ አፍቃሪው የልብን ያውቃልና፣ ይጠግናልና ያ ወዱድ ያ ወዱድ እንላለን! » : @Venuee13

Venue
3 791
« ፀሀይ የተውበትን ያህል አታበራም። ፀሀይ ብርሀኗ ውስጥ ማቃጠል አለው፣ ተውበት ግን አያቃጥልም፣ ይልቁኑ ምንም በማይጎረብጥ መልኩ ይሞቃል፣ ያሞቃል። የፀሀይ ብርሀን የሚደርስበትን የርቀት መጠን የሰው ልክ ተመራምሮ ሊያውቅ ይችላል። ተውበት ግን ረቂቅ ነው የሚደርስበትን ርቀት ከአላህ በቀር ማንም አያውቅም! ፀሀይ ልብ ውስጥ አትበራም። ተወበት ግን ሁሉም ነገር በሚመሰጠርበትና አላህ ብቻ በሚመለከተው ልብ ውስጥ በርቶ ሰዎች መመልከት በሚችሉት ገፅታ ላይ ይንፀባረቃል። ፀሀይ እጅ የምትሰጥለት ጽልመት አለ፣ ተውበት ግን ድል የማያደርገው አንድም ጽልመት የለም። በምንም ነገር ውስጥ አልፈው፣ በስተመጨረሻ ወደ አላህ ተመልሰው ንፅህናን በደረቡ፣ ውበትን በጨመሩ፣ በመልካሙ መንገድ ላይ በፀኑ ላይ ሁሉ የአላህ ሰላም ይስፈን። » [ አብዱልሀኪም ሰፋ ] : @Venuee13 @Venuee13

Venue
3 791

Venue
3 791
« የልብ አፍያ ተራ ነገር አይደለም፣ የሰላም ዋሻ ነው። ፍቅር ክብሩ የሚጠበቀው ልባቸው አፍያ በሆኑ ሰዎች ዘንድ ነው። አፍያ የሆነ ልብ የትኛውንም ጥንካሬ ያስከነዳል። አንዳንድ ውድ የሆኑ ነገራትን ልባችን አፍያ ባለመሆኑ ሰበብ የምናጣቸው ይሆናሉ። አፍያ የሆነች ልብ ጌታዋን እንጂ ከእሱ አብልጣ የምታተልቀው የላትም። ከእርሱም ይበልጥ የምታወሳው አይኖራትም። የልባችን አፍያ እንዴት ነው ግን? » [ አብዱልሀኪም ሰፋ ] : @Venuee13 @Venuee13

Venue
3 791
« ወድቀሻል? አዝነሻል? ከፍቶሻል? ተሰብረሻል? የምትወጂውን አጥተሻል? ብቸኝነት ይሰማሻል? ጥንካሬሽ ከድቶሻል? ስለ ወደፊት ማሰብ ታክቶሻል? ሰላም ከሚሰጡሽ ሰዎች ርቀሻል? በናፍቆት በትዝታ ተፈትነሻል? ሰላም አጥተሻል? የሚርረዳሽን አጥተሻል? የሚሰማሽን መግለፅ አቅቶሻል? ግራ ግብት ብሎሻል? እንኳን ደስ አለሽ! እነሆ ውብ የሆነውን አንቺነትሽን ታገኚ ዘንድ ወደ ጌታሽ ጥቅልል ብለሽ እንድትሄጂ ታጭተሻል! አሁን ጥያቄው ይህ ነው! ይህንን እድል ትጠቀሚበታለሽ ወይስ በህይወትሽ በገጠሙሽ ፈተናዎች ሰበብ ለሚሰሙሽ ስሜቶች እጅ ሰጥተሽ ትቀርያለሽ? እቴ ውሳኔው ያንቺ ቢሆንም ይህንን እወቂ በድሎሽ የማያውቀው ጌታዬ ዘንድ ምንም አታጪም! የምወድሽዋ ሰላም ለልብሽ! » [ አብዱልሀኪም ሰፋ ] : @Venuee13 @Venuee13

Venue
3 791
እናንተ የምወዳችሁ የቬኑ ቤተሰቦች። ሰላም ለልባችሁ! : @Venuee13 @Venuee13
እናንተ የምወዳችሁ የቬኑ ቤተሰቦች። ሰላም ለልባችሁ! : @Venuee13 @Venuee13

Venue
3 791
ደግሞ የምንወዳችሁ ቤተሰቦቻችን የሆናችሁ ሰዎች እንደምንወዳችሁ፣ እንደምናከብራችሁ ውዴታችንን ስንገልፅላችሁ እንደዚህ የምትሆኑት ነገር አቁሙ። ግን ቢሆንም እንወዳችኋለን! : @Venuee13
ደግሞ የምንወዳችሁ ቤተሰቦቻችን የሆናችሁ ሰዎች እንደምንወዳችሁ፣ እንደምናከብራችሁ ውዴታችንን ስንገልፅላችሁ እንደዚህ የምትሆኑት ነገር አቁሙ። ግን ቢሆንም እንወዳችኋለን! : @Venuee13

Venue
3 791
« የከፋው ልብ ለእርግማን ቅርብ ነው። በቅርቡ ሰው በፍቅር የማይዳበስ ልብ የአፈ ቀላጤ መጫወቻ ለመሆን ይመቻቻል። ወላጅን መጦር፣ ማገዝ ስራ ይዞ ዱንያ አካብቶ ገንዘብ መወርወር ብቻ አይደለም። በገንዘብ ሰበብ የሚቀረፉ ችግሮች እንዳሉ ሁሉ በገንዘብ የማይቀረፉ ነገራት አሉ። ማክበር፣ ማድመጥ፣ መታዘዝ፣ መተናነስ፣ ወላጆችን ከማገዝ፣ ከመጦር ነው። የዱንያ ቀዳዳን ለመሙላት ብቻ ትኩረት አድርገን፣ የምንወዳቸው፣ የምንሳሳላቸው ሰዎች ልብ ፍቅር አጥቶ እንዳይለፋብን ጥንቃቄ ማድረግ አለብን። ሰው በድርጊቴ ይገባዋል፣ ያውቃል፣ ይረዳል ተብሎ እንደሚወዱት ሳይነግሩት መኖር መሞኘት ነው። ሰው እንኳን በይረዳል በያውቃል ቀርቶ የሚያውቀውንም ያረጋገጠውንም ተደጋግሞ የሚነገረው ነው። ግድየላችሁም ቤተሰቤ ለምትሉት ውዴታችሁን ከመግለፅ አትስነፉ። ብቻ ልቤ እንዲህ ይለኛል። » [ አብዱልሀኪም ሰፋ ] : @Venuee13 @Venuee13

Venue
3 791
« ለቤተሰብ ውዴታን መግለፅ ነውር አይደለም፣ አትፍሩት። ቤተሰብን(ማንኛውም ከእናት አባት እህት ወንድም ሌላም) እወድሀለሁ፣ እወድሻለሁ ማለት የሚያሳፍር ወይም ስርዓት ማጣት አይደለም። ቤተሰቦቻችን ፍቅር የማይገባቸው አይደሉም። ውዴታና ፍቅራችንን የመስማት መብትም ሀቅም አላቸው። አንዳንድ የህይወት ሸክሞች ከራስ ሰው በሚሰማ የውዴታ የፍቅር ቃል ይራገፋሉ። ፍቅርን ውዴታን ለሚወዱት ቤተሰብ ለመግለፅ መስነፍ ቆይቶ የሚጠዘጥዝ ፀፀት ለመሸከም መመቻቸት ነው። » [ አብዱልሀኪም ሰፋ ] : @Venuee13 @Venuee13

Venue
3 791
« ኢክሩ ምን አለች በህይወቴ እንደ አሳማ የምጠላው እንስሳት የለም። ከአሳማ አጠገብ ከምሆን አንበሳ ቢበላኝ ይሻለኛል። ከርከሮም ያስጠላኛል አለች። ባቢ አንተስ የምትወደው እንስሳት ምንድን ነው አለ እስማኤል ፈረስ አልኩ። ቀጠለ ወሬው። እባብ ሳየው ያስፈራኛል የሆነ ቅፍፍ ይላል አለች ኢክሩ። ብቻ እንዲህ እያለን ጉዳዩ እንዴት እንደተነሳ አላውቅም እና በወሬያችን መሀል ስለ ፍርሀት ማውራት ጀመርን። አንዳንድ ፍርሀት እኛ አዕምሯችን የሚፈጥረው ወይም በተለያየ ምክንያት በተደረገብን ጫና የሚመጣ ነው። የእባብ ፍርሀት ተፈጥሯዊ አይደለም። እንደውም ባለፈው አንድ የተደረገ ጥናት ቪድዮ ስመለከት መርዛቸው የተወገደ እባቦች ህፃናቶች ጋር አድርገዋቸው ህፃናቶቹ ምንም ሳይፈሩ ሲጫወቱ ነበር። አልኩ አጋጣሚውን አስታክኬ። ኢክሩ አሀ አለች። ጋሽ እስማኤል ምን አለ ልጆቹ እባቦቹን ያልፈሩት እንደኔ ልባቸው ንፁህ ስለሆነ ነው ብሎ እርፍ። እሺ የእኛ መልዓክ ኧረ ባክህ… እያልን ሙድ ተያይዘን ተሳሳቅን። በእርግጥ ስለ ልብ ንፅህና በደንብ አያውቅም ይሆናል። ነገር ግን የልጆች ልብ እንደ ትልልቅ ሰዎች እንዳልሆነ ያውቃል። ወንድም እህቶቻችሁ ጋር ጨዋታ፣ እውቀትም፣ ሀሳብም፣ ጥፋትም፣ ደስታም ሀዘንም፣ ማወቅም አለማወቅም አለ። አውሯቸው፣ ተቃለዷቸው፣ ምከሯቸው፣ ስሟቸው፣ ሙድ ይያዙባችሁ ያዙባቸው፣ እንደምትወዷቸው ንገሯቸው ይንገሯችሁ፣ እቀፏቸው ሳሟቸው፣ አክብሯቸው። እናንተ ከስራ ውላችሁ አልያም ከሆነ ጉዳይ ስትመለሱ ቤቱ እንዲከብዳቸው አታድርጉ። ታላቆች ከሆናችሁ በድርጊታችሁ፣ በቃልኪዳናችሁ ታመኑላቸው። » [ አብዱልሀኪም ሰፋ ] : @Venuee13 @Venuee13

Venue
3 791
« እስቲ ደግሞ ፈገግ ካሰኙኝ ገጠመኞች መሀል አንዱን ላካፍላችሁ። ቲቪ ላይ ፊልም እያየን ነበር ከእህቴ ጋር እናም ገፀ ባህሪው ሊያገባት ላሰባት ሴት ፍቅሩን እየገለፀላት ነው። የሌለ እየገለፀላት እሷም ሙክክ እያለች ነው። እኔ ወንድማችሁ " ኧረ ሰውዬ ለአላህ ብለህ ፍታ እኛም እየቀለጥን ነው" ብዬ መሳቅ፣ ከዛስ ከታናሽ እህቴ በኩል መብረቃዊ ነቆራ ማስከተል። ምን አለች " እስቲ ተማር እንዴት እንደሚባል" ከዛ መሳቅ። ማለት? አሁን እንዲህ መባል ነበረብኝ ዎይ? በላጤዎች ላይ የሚደርስ የአግባ ትንኮሳ ይቁም! በዚ ነጅዋ ቤት ኢክሩ እየተዛዘንን እንጂ! ለማንኛውም አውሩ ከእህት ወንድሞቻችሁ ጋር፣ ጠላቶቻችሁ አይደሉም ቅረቧቸው፣ ለመቅረብም ሞክሩ። ስለተቀላለዷችኋቸው ክብራችሁ አይቀንስም፣ ሁሌም ኮስተር ስለምትሉባቸው ስለምትቆጧቸው ብቻ ስርዓት አይዙም። ባይሆን በእነሱ እድሜና አረዳድ ልክ በየአጋጣሚው ልትነግሯቸው የምትፈልጉትን ማወቅ ያለባቸውን መንገራችሁን አትርሱ። » [ አብዱልሀኪም ሰፋ ] : @Venuee13 @Venuee13

Venue
3 791
እናንተ መልካሙን ሁሉ የምመኝላችሁ ሰላም ብያለሁ! 🙌🙌