Venue
Canal cerrado
መድረሻ ባይኖር ፣ መጓዝ ብርቅ ነበር! : መራመድ ባልከፋ ፣ መድረሻም ባልጠፋ ነገ ላይ ለመድረስ ፣ ሰው ባያጣ ተስፋ ።
Mostrar más3 791
Suscriptores
Sin datos24 horas
-27 días
+330 días
Archivo de publicaciones
3 791
በእርግጥም ልንለያይ እንገናኛለን፣ ልንገናኝም እንለያያለን!
« #Venue በአጠቃላይ ወደ 8 አመታት ያህል እዚሁ ቴሌግራም ላይ ቆይቷል። በእነዚህ አመታት ውስጥ ፅሁፎቹ እዚህ ቻናል ላይ አልተገደቡም። በተለያየ መንገድ ከቻናሉ ውጪም ብዙ ሰዎች ጋር ደርሷል። እንግዲህ በተነሱት ሀሳቦች ሰዎች ተጠቅመውበታል አልተጠቀሙበትም የሚለውን አላህ ያውቃል። እስካሁን የምታውቁትን ተዋውሰንበታል። ተመካክረንበታል። በአላህ ፍቃድ መልካም ሰዎችንም የተዋወቅኩበት እና ያፈራሁበት ቤት ነው። አሁን ለራሴ ስል ቬኑን መተው ያለብኝ ጊዜ ላይ ነኝ። ቬኑ ቆይታውም፣ የነበረውም፣ እዚህ ጋር ይጠናቀቃል(ተጠናቋል!)።
ይህ የልቤ ውሳኔ ሲሆን ድንገት ያሰብኩት ሳይሆን ረጅም ጊዜ ስብሰለሰልበት የነበረ ነው። ልቤ ልክ ስለመሆኑ አለመሆኑ ረጅም ጊዜ ተብሰልስዬበታለሁ፣ በጊዜ ውስጥም መልሴን አግኝቻለሁ። እናም የልቤን ውሳኔ ማክበርን መርጫለሁ። ለምን? እንዴት? የሚለውን ማስረዳት አልችልም ከይቅርታ ጋር። አንዳንድ ስንብቶችም መገናኘቶችም ድንገተኛ ይሆናሉ። ህይወት አይደል እንዲህ ነው። ነገራት እንዴት ሊቀየሩ እንደሚችሉ አይታወቁም። በተጓዝነው ጉዞ ሁሉ መልካሙን ሀሳብ ብቻ አስታውሱ፣ የማይሆናችሁን እርሱት። በዚህ በቬኑ ላይ ይህ የመጨረሻ ስንብቴ ነው። በምን መንገድ ዳግም ልንገናኝ እንደምንችል አላውቅም፣ በመጥፎው ፈፅሞ እንዳንገናኝ ግን መሻቴ ነው። #Venue ይባል በነበረ የቴሌግራም ቻናል አንዳንድ ሀሳቦችን ለማንሳት ይሞክር የነበረና በቬኑ ቻናል ሰበብ የምታውቁት የነበረው ሰው ይወዳችኋል። ያከብራችኋልም። መልካሙንም ከሚመኝላችሁ ነው።
እስከዛሬ ድረስ ስለነበረን ስላሳለፍናቸው ጊዜያት ሁሉ ከልብ አመሰግናለሁ። አላህ ያክብርልኝ! ሰላም ለልባችሁ! »
[ አብዱልሀኪም ሰፋ ]
3 791
እንደ ጨርቅ ሳስቶ ህልምሽ ተቀደደ
ጭድ እንዳየው እሳት ሰላምሽ ነደደ።
ጥርስሽ ውሸት አውቆ ከእውነት ተጣላ
ትላንት ላይ ቆሞ ቀረ ወደ ኋላ።
ምነው የኔ ጌታ በልብሽ አነሰ
ጸጋው እኩል ሰጥቶን ላንቺ ያልደረሰ?
ዱዓዬን ምትሸሺ ሌት ቀን ስለምነው
ማን ቀማሽ ጌታዬን ልቤን የጠገነው?
የካሰኝ ያስደሳኝ ያላስከፋኝ ጌታ
ላንቺም አደላድሏል ሰላምና ደስታ።
እቴ ያይኔ አበባ ከፍቶሻል አውቃለሁ
ክፈቺለት ተስፋን ያ ወዱድ ብያለሁ።
ያ ወዱድ
ያ ወዱድ!
[ አብዱልሀኪም ሰፋ ]
:
@Venuee13
@Venuee13
3 791
« ፀሀይ የተውበትን ያህል አታበራም። ፀሀይ ብርሀኗ ውስጥ ማቃጠል አለው፣ ተውበት ግን አያቃጥልም፣ ይልቁኑ ምንም በማይጎረብጥ መልኩ ይሞቃል፣ ያሞቃል። የፀሀይ ብርሀን የሚደርስበትን የርቀት መጠን የሰው ልክ ተመራምሮ ሊያውቅ ይችላል። ተውበት ግን ረቂቅ ነው የሚደርስበትን ርቀት ከአላህ በቀር ማንም አያውቅም! ፀሀይ ልብ ውስጥ አትበራም። ተወበት ግን ሁሉም ነገር በሚመሰጠርበትና አላህ ብቻ በሚመለከተው ልብ ውስጥ በርቶ ሰዎች መመልከት በሚችሉት ገፅታ ላይ ይንፀባረቃል። ፀሀይ እጅ የምትሰጥለት ጽልመት አለ፣ ተውበት ግን ድል የማያደርገው አንድም ጽልመት የለም።
በምንም ነገር ውስጥ አልፈው፣ በስተመጨረሻ ወደ አላህ ተመልሰው ንፅህናን በደረቡ፣ ውበትን በጨመሩ፣ በመልካሙ መንገድ ላይ በፀኑ ላይ ሁሉ የአላህ ሰላም ይስፈን። »
[ አብዱልሀኪም ሰፋ ]
:
@Venuee13
@Venuee13
3 791
« ወድቀሻል? አዝነሻል? ከፍቶሻል? ተሰብረሻል? የምትወጂውን አጥተሻል? ብቸኝነት ይሰማሻል? ጥንካሬሽ ከድቶሻል? ስለ ወደፊት ማሰብ ታክቶሻል? ሰላም ከሚሰጡሽ ሰዎች ርቀሻል? በናፍቆት በትዝታ ተፈትነሻል? ሰላም አጥተሻል? የሚርረዳሽን አጥተሻል? የሚሰማሽን መግለፅ አቅቶሻል? ግራ ግብት ብሎሻል?
እንኳን ደስ አለሽ!
እነሆ ውብ የሆነውን አንቺነትሽን ታገኚ ዘንድ ወደ ጌታሽ ጥቅልል ብለሽ እንድትሄጂ ታጭተሻል! አሁን ጥያቄው ይህ ነው! ይህንን እድል ትጠቀሚበታለሽ ወይስ በህይወትሽ በገጠሙሽ ፈተናዎች ሰበብ ለሚሰሙሽ ስሜቶች እጅ ሰጥተሽ ትቀርያለሽ?
እቴ ውሳኔው ያንቺ ቢሆንም ይህንን እወቂ በድሎሽ የማያውቀው ጌታዬ ዘንድ ምንም አታጪም! የምወድሽዋ ሰላም ለልብሽ! »
[ አብዱልሀኪም ሰፋ ]
:
@Venuee13
@Venuee13
3 791
« የከፋው ልብ ለእርግማን ቅርብ ነው። በቅርቡ ሰው በፍቅር የማይዳበስ ልብ የአፈ ቀላጤ መጫወቻ ለመሆን ይመቻቻል። ወላጅን መጦር፣ ማገዝ ስራ ይዞ ዱንያ አካብቶ ገንዘብ መወርወር ብቻ አይደለም። በገንዘብ ሰበብ የሚቀረፉ ችግሮች እንዳሉ ሁሉ በገንዘብ የማይቀረፉ ነገራት አሉ። ማክበር፣ ማድመጥ፣ መታዘዝ፣ መተናነስ፣ ወላጆችን ከማገዝ፣ ከመጦር ነው። የዱንያ ቀዳዳን ለመሙላት ብቻ ትኩረት አድርገን፣ የምንወዳቸው፣ የምንሳሳላቸው ሰዎች ልብ ፍቅር አጥቶ እንዳይለፋብን ጥንቃቄ ማድረግ አለብን። ሰው በድርጊቴ ይገባዋል፣ ያውቃል፣ ይረዳል ተብሎ እንደሚወዱት ሳይነግሩት መኖር መሞኘት ነው። ሰው እንኳን በይረዳል በያውቃል ቀርቶ የሚያውቀውንም ያረጋገጠውንም ተደጋግሞ የሚነገረው ነው።
ግድየላችሁም ቤተሰቤ ለምትሉት ውዴታችሁን ከመግለፅ አትስነፉ። ብቻ ልቤ እንዲህ ይለኛል። »
[ አብዱልሀኪም ሰፋ ]
:
@Venuee13
@Venuee13
3 791
« ለቤተሰብ ውዴታን መግለፅ ነውር አይደለም፣ አትፍሩት። ቤተሰብን(ማንኛውም ከእናት አባት እህት ወንድም ሌላም) እወድሀለሁ፣ እወድሻለሁ ማለት የሚያሳፍር ወይም ስርዓት ማጣት አይደለም። ቤተሰቦቻችን ፍቅር የማይገባቸው አይደሉም። ውዴታና ፍቅራችንን የመስማት መብትም ሀቅም አላቸው።
አንዳንድ የህይወት ሸክሞች ከራስ ሰው በሚሰማ የውዴታ የፍቅር ቃል ይራገፋሉ። ፍቅርን ውዴታን ለሚወዱት ቤተሰብ ለመግለፅ መስነፍ ቆይቶ የሚጠዘጥዝ ፀፀት ለመሸከም መመቻቸት ነው። »
[ አብዱልሀኪም ሰፋ ]
:
@Venuee13
@Venuee13
3 791
« ኢክሩ ምን አለች በህይወቴ እንደ አሳማ የምጠላው እንስሳት የለም። ከአሳማ አጠገብ ከምሆን አንበሳ ቢበላኝ ይሻለኛል። ከርከሮም ያስጠላኛል አለች። ባቢ አንተስ የምትወደው እንስሳት ምንድን ነው አለ እስማኤል ፈረስ አልኩ። ቀጠለ ወሬው። እባብ ሳየው ያስፈራኛል የሆነ ቅፍፍ ይላል አለች ኢክሩ። ብቻ እንዲህ እያለን ጉዳዩ እንዴት እንደተነሳ አላውቅም እና በወሬያችን መሀል ስለ ፍርሀት ማውራት ጀመርን። አንዳንድ ፍርሀት እኛ አዕምሯችን የሚፈጥረው ወይም በተለያየ ምክንያት በተደረገብን ጫና የሚመጣ ነው። የእባብ ፍርሀት ተፈጥሯዊ አይደለም። እንደውም ባለፈው አንድ የተደረገ ጥናት ቪድዮ ስመለከት መርዛቸው የተወገደ እባቦች ህፃናቶች ጋር አድርገዋቸው ህፃናቶቹ ምንም ሳይፈሩ ሲጫወቱ ነበር። አልኩ አጋጣሚውን አስታክኬ። ኢክሩ አሀ አለች። ጋሽ እስማኤል ምን አለ ልጆቹ እባቦቹን ያልፈሩት እንደኔ ልባቸው ንፁህ ስለሆነ ነው ብሎ እርፍ።
እሺ የእኛ መልዓክ ኧረ ባክህ… እያልን ሙድ ተያይዘን ተሳሳቅን።
በእርግጥ ስለ ልብ ንፅህና በደንብ አያውቅም ይሆናል። ነገር ግን የልጆች ልብ እንደ ትልልቅ ሰዎች እንዳልሆነ ያውቃል። ወንድም እህቶቻችሁ ጋር ጨዋታ፣ እውቀትም፣ ሀሳብም፣ ጥፋትም፣ ደስታም ሀዘንም፣ ማወቅም አለማወቅም አለ። አውሯቸው፣ ተቃለዷቸው፣ ምከሯቸው፣ ስሟቸው፣ ሙድ ይያዙባችሁ ያዙባቸው፣ እንደምትወዷቸው ንገሯቸው ይንገሯችሁ፣ እቀፏቸው ሳሟቸው፣ አክብሯቸው። እናንተ ከስራ ውላችሁ አልያም ከሆነ ጉዳይ ስትመለሱ ቤቱ እንዲከብዳቸው አታድርጉ። ታላቆች ከሆናችሁ በድርጊታችሁ፣ በቃልኪዳናችሁ ታመኑላቸው። »
[ አብዱልሀኪም ሰፋ ]
:
@Venuee13
@Venuee13
3 791
« እስቲ ደግሞ ፈገግ ካሰኙኝ ገጠመኞች መሀል አንዱን ላካፍላችሁ። ቲቪ ላይ ፊልም እያየን ነበር ከእህቴ ጋር እናም ገፀ ባህሪው ሊያገባት ላሰባት ሴት ፍቅሩን እየገለፀላት ነው። የሌለ እየገለፀላት እሷም ሙክክ እያለች ነው። እኔ ወንድማችሁ " ኧረ ሰውዬ ለአላህ ብለህ ፍታ እኛም እየቀለጥን ነው" ብዬ መሳቅ፣ ከዛስ ከታናሽ እህቴ በኩል መብረቃዊ ነቆራ ማስከተል። ምን አለች
" እስቲ ተማር እንዴት እንደሚባል" ከዛ መሳቅ።
ማለት? አሁን እንዲህ መባል ነበረብኝ ዎይ? በላጤዎች ላይ የሚደርስ የአግባ ትንኮሳ ይቁም! በዚ ነጅዋ ቤት ኢክሩ እየተዛዘንን እንጂ!
ለማንኛውም አውሩ ከእህት ወንድሞቻችሁ ጋር፣ ጠላቶቻችሁ አይደሉም ቅረቧቸው፣ ለመቅረብም ሞክሩ። ስለተቀላለዷችኋቸው ክብራችሁ አይቀንስም፣ ሁሌም ኮስተር ስለምትሉባቸው ስለምትቆጧቸው ብቻ ስርዓት አይዙም። ባይሆን በእነሱ እድሜና አረዳድ ልክ በየአጋጣሚው ልትነግሯቸው የምትፈልጉትን ማወቅ ያለባቸውን መንገራችሁን አትርሱ። »
[ አብዱልሀኪም ሰፋ ]
:
@Venuee13
@Venuee13
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
