አ/ም ሰንበት ት/ቤት ትምህርት ክፍል official channel
الذهاب إلى القناة على Telegram
ይህ በቦሌ ሰ/ም/ፀ/ቅ/ጊዮርጊስ እና ቅ/አርሴማ ቤተ ክርስቲያን አንቀፀ ምስራቅ ሰ/ት/ቤት መንፈሳዊ ጽሑፎችን እንዲሁም ወቅታዊ የቤተ-ክርስቲያን መረጃዎችን የምንለቅበት የቴሌግራም ገፃችን ነው።
إظهار المزيد731
المشتركون
+224 ساعات
+77 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
"ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩሁ ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ።" ትን.ዮና. 3÷8
🕯ሳምንታዊው የአርብ ጸሎት🕯
👉 ውዳሴ ማርያም
👉 መሐረነ አብ
👉 መዝሙረ ዳዊት
👉ስንክሳር
🗓 ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም
⏰ ከቀኑ 12:00ሰዓት ጀምሮ
💒 በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ
ኑ በህብረት ስለ ሀገራችንና ስለ ቤተክርስቲያናችን ሰላም እና አንድነት ወደ ፈጣሪያችን በጋራ እንጸልይ‼
የሰንበት ትምህርት ቤታችን አንዱ እና ዋነኛው መረሐ ግብር የጸሎት ፕሮግራም ስለሆነ ማንም እንዳይቀር
አባላት እባካችሁ አትቅሩ አታርፍዱ በጊዜ ተገኝተን በጊዜ ወደየቤታችን እንድንመለስ
ሰላም ውድ የአንቀጸ ምስራቅ ሰንበት ት/ቤት አባላት እንዴት አመሻችሁ? ይህን መልዕክት በትኩረት እንድትመለከቱት ስንል በጥብቅ እናሳስባለን ሌሎችም የምታዩትም ወንድም እህቶች ለጓደኞቻችሁ አጋሩላቸው።
የ8ኛ እና የ10ኛ ክፍል በመማር ያሳለፋችሁ ተፈታኞች ተማሪዎች
👉 የፈተና ቦታ እና ሰዓት፦ ሐምሌ 26 ከጠዋቱ 1:00 ሰዓት ''ሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ '' መገኘት ይኖርባችኋል።
👉ቅዳሜ 11 ሰዓት ላይ ሁላችሁም ተገኝታችሁ የሚሰጠውን መልዕክት(orientation) መከታተል ይኖርባችኋል።
👉የመፈተኛም ኮድም ቅዳሜ ስለሚሰጥ በጊዜ ተገኙ።
👉የመፈተኛው ቀን ፈተናው በማጥቆር ስለሆነ ላጲስ እና እርሳስ ይዛችሁ እንድትገኙ ስንል እናሳስባለን።
‼️‼️‼️‼️‼️
ማሳሰቢያ፡ መልዕክቱንም እንድታነቡ እና ቴሌግራም መጠቀም ለማይችሉ ወንድም እህቶቻችሁ እየደወላችሁ እንድታሳውቁ ስንል እንጠይቃለን።
"የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።" መዝ 33(34) ፡ 7
እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ! ሐምሌ 19 በዚህች ዕለት ቅዱስ ገብርኤል ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስን እና እናቱን ቅድስት እየሉጣን ከእሳት ያደነበት ዕለት ነው!
መልካም በዓል!
እንዴት ዋላችሁ የ4ኛ,8ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማሪዎች የሀገረስብከቱ ፈተና የፊታችን እሑድ 26/11/2018 ዓ.ም ይሰጣል።
የመልስ መስጫ ወረቀቱ ናሙናው የሚከተለውን ይመስላል።
ሁሉም ተፈታኝ አርሳስና ላጲስ ይዘው እንዲመጡ።
በዚህ ስለሆነ መልስ የሚሰጠው እየተለማመዳችሁ ቆዩ።
እርሳስ እና ላጲስ ብቻ ነው መጠቀም የሚቻለው ይዛችሁ መምጣት እንዳትረሱ።
እንዴት አደራችሁ። ለሰንበት ትምህርት ቤታችህ አባላት በሙሉ አሁን የእናተን እርዳታ የምንፈልግበት ጊዜ ላይ ደርሰናል። ስለሆነም እሁድ 11፡00 ሰዓት ላይ ተገናኝተን የሰንበት ትምህርት ቤታችንን የመማሪያ ክላሶች ለአርማታ ከመደረጉ በፊት ማዘጋጀት ስላለብን ይሄንን ደግሞ በጉልበታችን ማገልገል ስላለብን ማለትም ጉልበታችንን እግዚአብሔር እንዲባርክልን አግልግሎታችንን እዲባርክልን ሁላችንም እሁድ ማታ 11፡00 ሰዓት ላይ እንድንገናኝ አሳስባለሁ። ሁላችሁም ወንዶችም ሴቶችም ስትመጡ አካፋ፣ ዶማ እና ለመቆፈሪያ የሚያገለግሉ ነገሮችን ይዛችሁ እንድትገኙ ስንል በአክብሮት ጠርትናችኋል። በቅዱስ ጊዮርጊስ እና በቅድስት አርሴማ ስም እና በሰንበት ትምህርት ቤታችን አንቀጸ ምስራቅ ስምም ጠርተናችኋል። ጥሪያችንን አክብራችሁ ስለምትመጡ እናመሰግናለን።
እንዴት ዋላችሁ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት ወላጆች እና አባላት በሙሉ" ለሁሉም ጊዜ አለዉ" እንዳለ ጠቢቡ ሰሎሞን እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ የሰንበት ትምህርት ቤቱን ጊዜያዊ መማሪያ ክፍል መስራት ተጀምሯል። ስለሆነም ሁላችሁም ወላጆች ከጎናችን እንድትሆኑ እናሳስባለን።
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ውስጥ ለምትገኙ ሰንሰበት ት/ቤቶች በሙሉ እንደሚታወቀው በ2018 ዓ.ም የትምህርት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የ4ኛ ፣8ኛ እና 10ኛ ክፍል የማጠቃለያ ሀምሌ 26/2018 ዓ.ም መሆኑን እናሳውቃለን ። ስለሆነም ጠዋት 1፡30 ላይ እንድትገኙ እናሳዉቃለን።
ሥጋ ሁሉ እንደ ሣር ክብሩም ሁሉ እንደ ሣር አበባ ነውና ። ሣሩ ይጠወልጋል አበባውም ይረግፋል ። 1ጴጥ 1:24
ለምንኩስና ለተጠሩት ቡሩካን ይህ እኛ ሥጋውያን የምንጓጓለት ሠርግ፣ ትዳር፣ ወግማዕረጉ ክብሩ እነሱ የሚሸሹት ነገር ነው ። እነዚህ ነገሮች በራሳቸው ሐጢአት ስለሆኑ ሳይሆን ምድራዊው ነገር ለአንድ ደቂቃ እንኳን ልባቸውን እንዲሰርቅባቸው ስለማይፈልጉ ነው ። ቀንም ማታም ማሰብ የሚፈልጉት ክርስቶስንና መንግስቱን ነው ። መድኃኔዓለምን የሚወዱበት ፍቅር እንዲህ ሊባል የማይቻልና በቅናት የተመላ ነው። ሽርፍራፊ ሰከንድ ልባቸው ያለክርስቶስ እንዲያስብ አይፈቅዱም ። እንደኛ ቅዳሴ ላይ ሆነው ልባቸውን አስር ቦታ የበተኑ አይደሉም ። እንደ ቅዱስ ገብረክርስቶስ እጣቢና ቆሻሻ እየተደፋባቸው ምህረት እየለመኑ የማያልፈውን መዓዛ ኢየሱስ ክርስቶስን የገለጡ ናቸው እንጂ ። 💛
የሙሽራው ገብረክርስቶስና የቅዱሳን መነኮሳት ሁሉ በረከታቸው ይደርብን ።
📢 በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ስር ለምትገኙ 61ዱም ሰንበት ትምህርት ቤቶች
ጥበብ አካዳሚ ከለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጋር በደረሰው የጋራ መግባባት መሠረት፣ በአንድነቱ ስር በሚገኙ 61ዱም ሰንበት ትምህርት ቤቶች ውስጥ ለሚገኙ መስፈርቱን ለሚያሟሉ አባላት የሥራ እድል አመቻችቷል።
💼 የክፍት ሥራ መደቦች እና መስፈርቶች
1. መምህር
የትምህርት ደረጃ: ዲግሪ ወይም ዲፕሎማ
የሥራ ልምድ: 0 ዓመት
2. ረዳት መምህር
የትምህርት ደረጃ: ዲግሪ ወይም ዲፕሎማ
የሥራ ልምድ: 0 ዓመት
3. ጥበቃ
የትምህርት ደረጃ: 8ኛ ክፍል እና ከዚያ በላይ
የሥራ ልምድ: 0 ዓመት
4. ጽዳት
የትምህርት ደረጃ: 6ኛ ክፍል እና ከዚያ በላይ
የሥራ ልምድ: 0 ዓመት
ደሞዝ በአካዳሚው እስኬል መሠረት 📌 ተጨማሪ መስፈርት
የሰንበት ትምህርት ቤት አባል የሆነ/ች እና ከሰንበት ትምህርት ቤቱ በሰብሳቢ የተፈረመ የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችል/ምትችል።
📝 አመዘጋገብ
መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ዛሬ 14/11/2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ከታች ባለው ሊንክ አማካኝነት መረጃችሁን እና የሕይወት ታሪካችሁን (CV) በመላክ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፦
🔗 የመመዝገቢያ ሊንክ: @Davoethio2016
💡 መረጃው ለሌሎች የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት እንዲደርስ መረጃውን ያጋሩ!
እንዴት አደራችሁ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት በሙሉ
እንደሚታወቀው ወር በገባ በ14 የፃድቁ አባታችንን ወርሃዊ መታሰቢያ በዓልን እናከብራለን በነገው እለትም ሀምሌ 14/11/2018 ዓ.ም በደብራችን አውደምህረት እናከብራለን ሁሉም የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባል ከ11:30 ሰዓት ጀምሮ እንድትገኙ እናሳስባለን።
ጸሎት በአንድ ላይ እንድናደርስ በጊዜ እንገኝ።
ሰዓት ይከበር
ክፍት የሥራ ማስታወቂያ ለ0 ዓመት/ 2018 ዓ.ም ተመራቂዎች
በ accounting (ብዛት 2 ፣ ፃታ ሴት)
በ management (ብዛት 1 ፣ ፃታ ሴት)
በ software engineering (ብዛት 4)
👉 የተሟላ cv በtelegram account @bettybee12 ይላኩ
ፈተና ላለፋችሁ ሁሉም አባላት በሙሉ
ፈተና የመጨረሻ ግዜ የሚሰጠው ዛሬ ስለሆነ አሳማኝ ምክንያት አምጥታችሁ እንድትፈተኑ እናሳስባለን።
#ኮከበ_ገዳም_አባ_ብሾይ
ኮከበ ገዳም የተባለው ቅዱስ አባ ብሶይ (ብሾይ) በጽኑ ተጋድሎ፣ በትሕትና እና በፍቅር የኖረ ታላቅ አባት ሲኾን፣ በሰፊው ተጋድሎት ካለፈ በኋላ ሐምሌ 8 ቀን በ417 ዓ.ም ዐርፏል።
በሕፃንነቱ የተመረጠው ለጌታ አገልግሎት የተለየው ይኽ ቅዱስ፣ በገዳመ ሲሐት በጾምና በጸሎት በመጽናት እጅግ ከፍ ያለ የቅድስና ማዕረግ ላይ ደርሷል፤ ጌታችንን በነዳይ አምሳል እግሩን በማጠብ፣ በአረጋዊ አምሳልም በጀርባው አዝሎ በመውጣት ባሳየው ትሕትና ምክንያት ቅዱስ ሥጋው ሳይበሰብስና ሳይፈርስ እስከ ዛሬ ድረስ በገዳሙ ተአምራትን እያደረገ ይገኛል።
በመንፈስ ቅዱስ ህልውና ላይ ክህደት የነበረበትን ሰው በመጽሐፍ ቅዱስ ምሳሌዎች አስተምሮ የመለሰው አባ ብሶይ፣ በቅድስና ሕይወቱ ለብዙዎች አባትና መሪ ሆኖ አልፏል።
