🟢"
ከውስጥ መስመር ወስዋሶች ማስጠንቀቅ"
የጥመት ሰዎች በግልፅ የሚያነሱት ብዥታ ሁሉ በመረጃ ምላሽ ስለሚሰጥበትና ሀቅን የሚጋፈጡበት አቅም ስለሌላቸው በውስጥ መስመር መጎትጎት (መወስወስ) ያበዛሉ።በተደጋጋሚ የተብራራን ሀቅ መላልሰው ያምታታሉ። ይህ ወስዋስ አደገኛ ነውና ፊት አንስጠው። ከሀቅ ወዲያ ባጢል እንጂ የለም።
እንዴት ለአምታቾች ወስዋስ የአይናችን ፣ የጆሯችን እና የልባችንን በር እንከፍታለን⁉️
⏩ አላህ እንዲህ እያለ:
﴿لَا خَيْرَ فِي كَثِيرٍ مِنْ نَجْوَاهُمْ إِلَّا مَنْ أَمَرَ بِصَدَقَةٍ أَوْ مَعْرُوفٍ أَوْ إِصْلَاحٍ بَيْنَ النَّاسِ وَمَنْ يَفْعَلْ ذَلِكَ ابْتِغَاءَ مَرْضَاتِ اللَّهِ فَسَوْفَ نُؤْتِيهِ أَجْرًا عَظِيمًا} النساء (114)
{ከድብቅ ውይይታቸው በአብዛኛው መልካም የለበትም። በሰደቀህ ያዘዛ ወይም በመልካም( ያዘዘ) ወይም በሰዎች መካከል ማስታረቅ ካልሆነ በስተቀር። የአላህን ውዴታ በመፈለግ ይህን የሚተገብር ሁሉም በእርግጥ ትልቅ ምንዳን (ደሞዝ) እንሰጠዋለን።}
⏩የአላህ መልዕክተኛ(ﷺ)እንዲህ እያሉ
عَنْ أَبِي أُمَامَةَ قَالَ : قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ : " مَا ضَلَّ قَوْمٌ بَعْدَ هُدًى كَانُوا عَلَيْهِ إِلَّا أُوتُوا الْجَدَلَ ". ثُمَّ تَلَا رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ هَذِهِ الْآيَةَ : " { مَا ضَرَبُوهُ لَكَ إِلَّا جَدَلًا بَلْ هُمْ قَوْمٌ خَصِمُونَ } " [الزخرف: 58] قال الترمذي: حسن صحيح، وحسنه الألباني في ((صحيح الجامع)) (5633).
"የትኞቹም ህዝቦች ከነበሩበት ቅን መንገድ አይጣመሙም ሙግትን የተሰጡ ቢሆን እንጂ" ከዚያም የሚከተለውን ቁርኣን አነበቡ {
ለሙግት እንጂ (ለአንተ የደረጉትን ምሳሌ) አላደረጉልህም። ይልቁንም እነርሱ (በግፍ) ተከራካሪ ህዝቦች ናቸው}"
👉 ከዚህ ሀዲስ ልብ እንደምንለው ሀቅ ላይ የነበሩና ከዚያም ተጣመው የተንሸራተቱ አካለት በሙግት የተካኑ ዋስዋሶች ስለሆኑ ከፍተኛ ጥንቃቄ ያስፈልጋል።
⏩ አል ኢማም አልበርበሃሪይ እንዲህ እየመከሩን:
【واعلم رحمك الله أنه ما كانت زندقة قط ولا كفر ولا شك ولا بدعة ولا ضلالة ولا حيرة في الدين إلا من الكلام وأهل الكلام والجدال ...】
【እወቅ አላህ ይዘንልህና: እነሆ ኒፋቅ ወይም ክህደት ወይም ጥርጣሬ ወይም ቢድዐህ ወይም ጥመት ወይም መወዛገብ በዲን ውስጥ አልተከሰተም በፍልስፍና እና ከፋላስፋዎች ፣ ከሞጋቾችና ከተከራካሪዎች በኩል ቢሆን እንጂ።】
📚የሌሎችም ሰለፎቾ አቋም የታወቀ ነው። ከሙብተዲዕ ግማሽ የቁርን አንቀፅ እንኳን አንሰማም የሚሉ ነበሩ።ዛሬ ከካፊሮችና ከሙብተዲዖች ሹቡሃት (ብዥታዎችን) የምትጋተው ወገኔ ለነፍስህ እዘንላት።
ተላቀቅ❗️
👉የታወቁ አጥማሚዎች የሚልኩትን የተቀነባበረ ድምፅ ወይም ፅሁፍ ትኩረት እንደሰጠነው ካወቁ የልብ ልብ ይሰማቸዋልና በፍፁም ልንሰማላቸውም ይሁን ልናነብላቸው አይገባም አስፈላጊ ከሆነም ምንም አንመልስላቸው። ከእነርሱ የሚገኝ ጠቃሚ እውቀትም አይኖርም። ወስዋስና ማምታቻ እንጂ መረጃ አያመጡም።
ጠቃሚ እውቀት ለፈለገ ባለቤት አለው።
👉
የሸር ወስዋሶችን የክርክር መስመር አቋርጦ ሰላም ያልሆነ ሁሉ የጥመት ገደል ጫፍ ላይ መሆኑን ይገንዘብ። ከመውደቁ በፊት ገደል መሆኑን ጠንቀቆ ቢያውቅም ከወደቀ በኋላ አይታየውም።
"السلامة لا يعدلها شيء"
✍አቡ ሀመዊየህ
http://t.me/Abuhemewiya