የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
تُعد قناة የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 319 مشتركاً، محتلاً المرتبة 6 154 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 360 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 319 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 22 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 507، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 11، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 49.23%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 13.09% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 0 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 875 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 0.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 23 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
14 319
المشتركون
+1124 ساعات
+1077 أيام
+50730 أيام
أرشيف المشاركات
+1
በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ በኩል በዓመቱ የተሠሩ ዋና ዋና ሥራዎች ሪፖርት ቀረበ።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ጥቅምት 04/02/2017 ዓ.ም
እየተከናወነ በሚገኘው በ፵፫ኛው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ ሪፖርታቸውን ካቀረቡ መምሪያዎች መካከል የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ አንዱ ሲሆን መምሪያው በዓመቱ ውስጥ ያከናወናቸውን ዋና ዋና ሥራዎች በንቡረ እድ ኤልያስ አብርሃ በመንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የመንፈሳዊ ዘርፍ ዋና ምክትል ሥራ አስኪያጅ በኩል አቅርቧል።
በሪፖርቱም ሥርዓተ ትምህርቱን መሠረት በማድረግ ከ1-4ኛ ክፍል በአራት ጥራዝ የተዘጋጁ 23 መጻሕፍት የአርትኦት ሥራን በማጠናቀቅ 23,508 ኮፒ ያለውን መጻሕፍት ማሳተሙና ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያት ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በተገኙበት ማስመረቁና ይህም ወደ ሌሎች ቋንቋዎች በማስተርጎም ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ከ5ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ያሉት 22 የመማርያ መጻሕፍት የመጀመርያ ረቂቅ የአርትኦት ሥራ ተጠናቆ በቅርብ ለሕትመት የሚበቃ መሆኑ ተነግሯል።
በተጨማሪም ለሥርዓተ ትምህርቱ ትግበራ የሚያግዝ ሀገረ ስብከቶች ወጪ እንዲጋሩ በማድረግና ከቅድስት ሥላሴ ዩንቨርስቲ ዶርምና ማስተማርያ ስፍራ በማስፈቀድ ከ7 አህጉረ ስብከት ለተውጣጡ 105 የሰ/ት/ቤት መምህራን የአሰልጣኞች ሥልጠና በመስጠት የአገልግሎት ስምሪት ማድረጉም ተነግሯል።
በቀጣይ ቀናት በሚኖሩት የ፵፫ኛው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ የሥርዓተ ትምህርት መጻሕፍት ሥርጭትና ሌሎች የሰንበት ትምህርት ቤት ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ይተላለፋል ተብሎ ይጠበቃል።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በየዓመቱ የሚደረገው የመንበረ ፖትርታርክ የጠቅላይ ቤተክህነት የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ለ፵፫ኛ ግዜ በዛሬው ዕለት ተጀመረ።
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ጥቅምት 04/02/2017 ዓ.ም
በመክፈቻው ጉባኤ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያት ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት "እንደ ዐስራ ኹለቱ ሐዋርያት መንጋውን ትጠብቁት ዘንድ መንገዱን አሳምሩ" በሚለው በቅዱስ ያሬድ ቃል ተነስተው በሁለት ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መልዕክትን አስተላልፈዋል።
የመጀመርያው መልዕክታቸው አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሲሆን "በዚህ ዘመን በሐዋርያት መንበር ላይ ለመንጋውና ለመንግሥተ እግዚአብሔር የተሾምን እንደመሆናችን በመልካም አስተዳደርና በቀና እምነት ልናስተዳድር ይገባል። በአሁን ሰዓት የቤተክርስቲያን አስተዳደር ችግር በብዛት የሚስተዋልበት እንደመሆኑ ይህን ችግር ለመቅረፍ በጥናት ላይ በመመስረት በፍጥነት መስራት ይጠበቅብናል" ብለዋል።
ኹለተኛው መልዕክታቸውም የምዕመናንና የአገልጋዮች ሰቆቃና ሞት ላይ ያተኮረ ነው። በምዕመናንና በአገልጋዮች ላይ እስከ አሁኗ ሰዓት እያጋጠመ ያለውና ያልተቋረጠው እንግልትና ሞት እንደ ምሳሌ በምስራቅ ሸዋ ከነቤተሰቦቻቸው የተገደሉትን አባት በማንሳት እንዲህ አይነቱ ተግባር ሊቆም እንዲገባ መልዕክትን በማስተላለፍ ስብሰባው በይፋ መጀመሩን አብስረዋል።
በመቀጠል ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕርዳርና ምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የሰበካ ጉባኤን ጅማሮና አሁን እስካለበት ድረስ ያለውን ታሪክ በማንሳት ይህን ሥርዓት ላበጁ አባቶች ክብርና ለዚህ ያደረሰንን አምላክ ልናመሰግን ይገባል ብለዋል። በመቀጠልም የመንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የተከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎችን ሪፖርት አቅርበዋል።
ጉባኤውም እስከ ጥቅምት 10 የሚቀጥል ሲሆን የየሀገረ ስብከቶችን የሥራ ሪፖርትና በተለያዩ ጉዳዮች ውሳኔ ይተላለፍበታል ተብሎ ይጠበቃል።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
+4
የሰንበት ተማሪዎች እና የቅድመ ግቢ ጉባዔ ተማሪዎች ሽኝት ተከናወነ!!!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ጥቅምት 03/02/2017 ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን ከአዲስ አበባ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ጋር በመተባበር በየዓመቱ የሚያዘጋጀው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሽኝት መርሐ ግብር በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል አዳራሽ ተከናወነ።
በመርሐ ግብሩ ላይ በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን የተፈተኑ ከ700 በላይ ተማሪዎች የተሳተፉ ሲሆን በመርሐግብሩ ላይም ብፅኡ አቡነ ፊሊጶስ የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብክት ሊቀ ጳጳስ እና የቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ፕሬዝዳት የተገኙ ሲሆን ተማሪዎች አካሄዳቸውን ከእግዚአብሔር ጋር ማድረግ እንዳለባቸው እና ትልቅ አደራ እንዳለባቸውም መልእክት አስተላልፈዋል በመርሀ ገብሩ ላይም በሊቀ ሊቃውንት ዮሴፍ ደሳለኝ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ሁለት ተማሪዎችም በብፁነታቸው የማበረታቻ ሽልማትም ተበርክቶላቸዋል።
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
ሁለተኛው የ12ኛ ክፍል የምርቃት መርሐ ግብር ተከናወነ።
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ጥቅምት 02/02/2017 ዓ.ም
በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት በተዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት መሠረት በሙከራ የቅድመ ትግበራ ሲተገብሩ የነበሩ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት 7 እና ከጉራጌ ሀገረ ስብከት ደግሞ 1 በጠቅላላ 8 አጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የምረቃ መርሐ ግብራቸው በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ በዛሬው ዕለት ተከናውኗል። በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ዋና ሐላፊ ፣ የአንድነቱ የሥራ አመራር አባላት ፣ ተመራቂ ተማሪዎች እና ወላጆች ተገኝተዋል። መርሐ ግብሩን ብፁዕ አቡነ በርናባስ የዋግህምራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በጸሎት የከፈቱት ሲሆን ብፁዕ አቡነ አብርሃምም ባስተላለፉት አባታዊ መልእክት "ለጠቢብ ሰው ትምህርትን ስጠው ጥበብንም ያበዛል። ጽድቅንም አስተምረው ዕውቀትንም ያበዛል። ጥበብን ፈላጊዎችና ራሳችሁን ለጥበብ ያዘጋጃችሁ በመሆኑ ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ዕውቀት ጥበብ ሥጋዊና ጥበብ መንፈሳዊን በነጻ ሰጥታችኋለችና የተማራችሁትን ወደ ተግባር ለውጡ። ቤተ ክርስቲያናችሁ ከናንተ ብዙ ትጠብቃለች" ብለዋል። በመጨረሻም ለስምንቱም አጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ፣ ለተመራቂ ተማሪዎች የዕውቅና ምስክር ወረቀት ከብፁዕአ አቡነ አብርሃምና ከብፁዕ አቡነ ሰላማ የም/ጎንደር ሊቀ ጳጳስ እጅ ተቀብለዋል። ከስምንቱ አጥቢያ ሰ/ት/ቤቶችም ጠቅላላ ውጤት አንደኛ በመውጣት ሳሪስ ምዕራፈ ቅዱሳን ፈለገ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስና አቡነ አረጋዊ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
እንኳን ደስ አላችሁ!
በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት በተዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት መሠረት በሙከራ ትግበራ 12ኛ ክፍል ያስፈተኑ አጥቢያዎች እና ምዘናውን የወሰዱ ተማሪዎች የምርቃት መርሐ ግብር የፊታችን ቅዳሜ ጥቅምት 2 ቀን 2017 ዓ.ም በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ከቀኑ 7፡00 ጀምሮ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ የአድባራትና የገዳማት አስተዳዳሪዎች ልዩ ልዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተመራቂዎችና ቤተሰቦቻቸው በተገኙበት የሚከናወን ይሆናል።
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
✞✞✞ እናታችን ቅድስት አርሴማን በምን እንመስላታለን? እርሷ በአድማስ ላይ ተቀምጦ እንደሚያበራ እንቁ ናትና ክብሯ ብዙ ነው:: መድኃኒታችን ክርስቶስ በወንጌል እንዳለው "በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሠወር አይቻላትምና" የሰማዕቷ ሕይወት በፊታችን እንደ ብርሃን ተገልጦ ይታያል።
በዚህች ዕለት እናታችን ቅድስት አርሴማ ተጋድሎዋን በክብር የፈጸመችበት ቀን ነው። በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ይደርብን!
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
+2
የ2017 ዓ.ም የሰንበት ትምህርት ቤቶች የትምህርት መርሐ ግብር በተለያዪ አኅጉረ ስብከቶች በይፋ ተጀመረ፡፡
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) መስከረም 27/01/2016 ዓ.ም
በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አዘጋጅነት ለሰንበት ትምህርት ቤቶች የተዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት መሠረት በዕድሜ ተከፋፍሎ ከአንደኛ እስከ ዐሥራ ኹለተኛ ክፍል የሚሰጠው ትምህርት የ2017 ዓ.ም ትግበራ በሀገረ ስብከቶች መጀመሩ ተገለጸ፡፡
የክረምቱን ጊዜ በመምህራንና በመማርያ ቦታዎች ዝግጅት እንዲሁ መማርያ ቁሳቁስ በማሟላት የመጻሕፍት ግዢና ሥርጭትን በማከናወን የቆዩት በአብዛኛው በየአኅጉረ ስብከት የሚገኙ አጥቢያዎች ሀገር አቀፍ አንድነቱ ባወጣው የትምህርት መርሐ ግብር መሠረት መስከረም 18 እና 19 ጀምሮ መስጠት ጀምረዋል፡፡
የሥርዓተ ትምህርት ትግበራውን መስጠት ከጀመሩ ሀገረ ስብከቶች መካከል ባሌ፣ ምስራቅ ሸዋ ፣ማዕከላዊ ጎንደር ፣ድሬደዋ፣ ሰሜን ሸዋ፣ ባሕር ዳር እና አዲስ አበባ ሀገረ ስብከቶች ይገኙበታል፡፡ እንደ ጅማ ፣ ደቡብ ወሎ ያሉ ሀገረ ስብከት አንድነቶች ደግሞ ከጥቅምት 2 ጀምሮ የዚህን ዓመት ትግበራ እንደሚጀምሩ ታውቋል።
በባለፈው የትምህርት ዓመት ሥርዓተ ትምህርቱን ለመተግበር የግንዛቤና ወቅታዊ የሰላም እጦት ፈተና እንደሆነባቸውም ተገልጿል።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
+3
የምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የመንበረ ጵጵስና ወረዳ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት 25ተኛ ዓመት ጠቅላላ ጉባኤውን መስከረም 26/2017 ዓ.ም አከናውኗል።
በጠቅላላ ጉባኤውም የሀገረስብከቱ ተወካዮች ፣ ከየሰንበት ትምህርት ቤቶች የተወከሉ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት ፣ የሰንበት ትምህርት ቤቶች የጽሕፈት ቤት ሐላፊዎች ፣ የማህበረ ቅዱሳን አዳማ ማዕከል ተወካዮች እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ተካሂዷል። በጠቅላላ ጉባኤውም የአንድነቱ የሥራ ሪፓርት እና ስልታዊ ዕቅድ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን በመጨረሻም የአንድነቱ የአመራር ምርጫ ተደርጎ በጠቅላላ ጉባኤው ጸድቋል።
መረጃው የአዳማ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ነው።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
