ar
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

الذهاب إلى القناة على Telegram

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

تُعد قناة የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 356 مشتركاً، محتلاً المرتبة 6 146 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 357 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 356 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 23 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 507، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 14، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 25.68‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 13.08‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 681 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 875 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 28.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

وصف القناة غير متوفر.

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 24 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

14 356
المشتركون
+1424 ساعات
+1027 أيام
+50730 أيام
أرشيف المشاركات
ቸሪቱ አማላጂቱ ቅድስት ሆሁህ ልጅሽ ይቅር ይለን ዘንድ ለምኝልን! ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን:: አእምሮውን ልበዎውን ጥበቡን በልቡናችን ሳይ
ቸሪቱ አማላጂቱ ቅድስት ሆሁህ ልጅሽ ይቅር ይለን ዘንድ ለምኝልን! ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን:: አእምሮውን ልበዎውን ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን:: ጾሙን የፍሬ የትሩፋትና የበረከት ያድርግልን! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ልዑካንና  የክረምት ሰልጣኝ መምህራን በጉራጌ ሀገረ ስብከት በወልቂጤ ከተማ በመንበረ ጵጵስና ሥር የሚገኙ 2 ሰንበት ትምህርት ቤቶች የአገልግሎት እንቅስቃሴና የሥርዓተ ትምህርቱ ትግበራ ዙርያ የመስክ ምልከታ ተደረገ። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ነሐሴ 5/12/2016 ዓ.ም ከነሐሴ 1 ጀምሮ በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና በጉራጌ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ ክፍል በመተባበር እየተሰጠ በሚገኘው የተተኪ መምህራን ሥልጠና ጎን ለጎን ከየወረዳው የተውጣጡ ሰልጣኞችና አሰልጣኝ መምህራን ልምድን ሊቀስሙባቸው የሚችሉባቸው የአገልግሎት ጉብኝትን በማድረግ ላይ ይገኛሉ። በመስክ ጉብኝቱ በከተማዋ የሚገኙ ሁለት አጥቢያ ወልቂጤ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ፈለገ ቅዱሳን፣ ወልቂጤ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ሰንበት ትምህርት ቤቶች ላይ ምልከታ የተደረገ ሲሆን በሰንበት ትምህርት ቤቶቹ፦ 1- የሥርዓተ ትምህርት አተገባበር ሒደት 2- የአባላት አያያዝና የአገልግሎት መንገድ 3- የልማትና በጎ አድራጎት ሥራዎች 4- የመማርያና የማስተማርያ ቦታዎችን 5- ኢኮኖሚያዊ  ሥራዎችን በተመለከተ ገለጻና የመስክ ጉብኝት ተደርጓል። የመስክ ጉብኝቱን ዓላማ በተመለከተ ሐሳባቸውን የገለጡት የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ቤት ማደራጃ ዋና ክፍል ሓላፊ የሆኑት መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ ብሥራት ገብረ ሥላሴ "በዚህ ጉብኝት ለመምሪያው ልዑካን የሀገረ ስብከቱን የሰንበት ትምህርት ቤቶች እንቅስቃሴ ማሳየትና ከየወረዳው ለተውጣጡ ሰልጣኞች ደግሞ በሚያዩት ልምድ በመነሳሳትና በመንፈሳዊ ቅንዓት በየሰንበት ትምህርት ቤቶቻቸው በሚወርዱበት ጊዜ መተግበር እንዲችሉ ለማድረግ ነው" ብለዋል። በመስክ ጉብኝቱ ከሰንበት ትምህርት ቤቶቹ የተመለከቱት ሥራና የአገልግሎት እንቅስቃሴን በተመለከተ ሐሳባቸውን የገለፁት በመንበረ ፖትርያሪክ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የትምህርት ክፍል ሓላፊ የሆኑት መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ ይታገሱ ደሴ "ቀጣዩን ትውልድ ከመጣበት ዘርፈ ብዙ ችግር መታደግ የምንችልበት ብቸኛው አማራጫችን የተዘጋጀውን ወጥ ሥርዓተ ትምህርት በቁርጠኝነት ማስተግበር ብቻ ነው። በእርግጥ አንድ ሥርዓት ሲዘረጋ በአንድ ጊዜ በተፈለገው መልኩ ይኼዳል ፍጹም ይሆናል ባይባልም በኺደት ግን በተፈለገው መልኩ የተሳካ መሆኑ ስለማይቀር ሊያጋጥሙ የሚችሉ ተግዳሮቶችን በጽናት በማለፍ ለተግባራዊነቱ እግዚአብሔርን አጋዥ በማድረግ እንበርታ ብለዋል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"የሕይወት መድኃኒት ምንጭ ሆይ የፈውስ መድኃኒት ውሀን ከአንቺ የሚቀዱ ሕመም ቁስለ ሥጋ ቁስለ ነፍስ የለባቸውም፡፡ የሰላም ምንጭ ሆይ የምሕረት ውሀን ካንቺ የሚረኩ የሚጠጡም ለዘለዓለም አይጸሙም፡፡"
"የሕይወት መድኃኒት ምንጭ ሆይ የፈውስ መድኃኒት ውሀን ከአንቺ የሚቀዱ ሕመም ቁስለ ሥጋ ቁስለ ነፍስ የለባቸውም፡፡ የሰላም ምንጭ ሆይ የምሕረት ውሀን ካንቺ የሚረኩ የሚጠጡም ለዘለዓለም አይጸሙም፡፡" አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ አርጋኖን) ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን:: አእምሮውን ልበዎውን ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን:: ጾሙን የፍሬ የትሩፋትና የበረከት ያድርግልን! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"ማርያም ሆይ ስለዚህ እንወድሻለን፤ ከፍ ከፍም እናደርግሻለን፤ እውነተኛ የጽድቅ መብልን እና እውነተኛ የሕይወት መጠጥን ወልደሽልናልና።" አባ ሕርያቆስ ቅዳሴ ማርያም ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድ
"ማርያም ሆይ ስለዚህ እንወድሻለን፤ ከፍ ከፍም እናደርግሻለን፤ እውነተኛ የጽድቅ መብልን እና እውነተኛ የሕይወት መጠጥን ወልደሽልናልና።" አባ ሕርያቆስ ቅዳሴ ማርያም ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን:: አእምሮውን ልበዎውን ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን:: ጾሙን የፍሬ የትሩፋትና የበረከት ያድርግልን! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የሥርዓተ ትምህርት ግንዛቤና የተተኪ መምህራን ሥልጠና በጉራጌ ሀገረ ስብከት መንበረ ጵጵስና ከሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ቤት ክፍል ጋር በመተባበር እየሰጠ ይገኛል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ነሐሴ 03/12/2016 ዓ.ም በመንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በ2016 ዓ.ም ፍፃሜ ላይ ከያዛቸው የተተኪ ሰ/ት/ቤቶች መምህራን ሥልጠና ፕሮጀክት አንዱ አካል የሆነውንና በትብብር የሚሰራውን ሥልጠና  በጉራጌ ሀገረ ስብከት በወልቂጤ ከተማ መንበረ  ጵጵስና  ከሀገረ ስብከቱ ወረዳዎች ለተውጣጡ ሰልጣኞች እየሰጠ መሆኑን ገለፀ። ባሳለፍነው ሳምንት በወርሐ ሐምሌ ከ16  አኅጉረ ስብከት ለተውጣጡ 206 ሰልጣኞች ሁለተኛውን ሥልጠና በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩንቨርስቲ በመስጠት ወደ መጡበት ሀገረ ስብከት ለነቃ የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ይተጉ ዘንድ ያስመረቀው አንድነቱ የዚሁ አካል የሆነውን ሥልጠና በጉራጌ ሀገረ ስብከት ከነሐሴ 1 ጀምሮ በመስጠት ላይ ይገኛል። ሥልጠናው በሀገረ ስብከቱ ስር ላሉ ከየወረዳው ለተውጣጡ ከ100 በላይ አሰልጣኝ መምህራን  እየተሰጠ ሲሆን በመክፈቻው መርሐ ግብርላይ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ በመገኘት መርሐ ግብሩን በጸሎት በማስጀመር ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ የሰጡ ሲሆን የሥልጠናውንም ሒደት የሰልጣኞችንም ተሳትፎ ተመልክተዋል። ሥልጠናው እስከ ሱባኤው ፍጻሜ የሚቀጥል መሆኑንና ሰልጣኞች በቂ እውቀትን የሚያገኙበት ግንዛቤያቸውንም የሚያሳድጉበት ወጥነትን ለተላበሰው ለሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ብቁ የሚያደርጋቸው መሆኑ ተመላክቷል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"ማርያም ድንግል ምክሖን ለደናግል፣ ይእቲኬ ቤተ ምስአል፣ ለኩሉ ፍጥረት ትተነብል፤ ድንግል ማርያም የደናግል መመኪያ፣ የጸሎት ቤት ናት፣ ለፍጥረታት ሁሉ የምትለምን አማላጅ ናት።" ቅዱስ ያሬድ ጽንዕ
"ማርያም ድንግል ምክሖን ለደናግል፣ ይእቲኬ ቤተ ምስአል፣ ለኩሉ ፍጥረት ትተነብል፤ ድንግል ማርያም የደናግል መመኪያ፣ የጸሎት ቤት ናት፣ ለፍጥረታት ሁሉ የምትለምን አማላጅ ናት።" ቅዱስ ያሬድ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን:: አእምሮውን ልበዎውን ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን:: ጾሙን የፍሬ የትሩፋትና የበረከት ያድርግልን! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"ናዐብየኪ ኩልነ ኦ እግዝእትነ ወላዲተ አምላክ እስመ ሣህልኪ ይኩን ላዕለ ኩልነ ፤ አምላክን የወለድሽ እመቤታችን ሆይ ሁላችን እናገንሻለን ይቅርታሽ ለሁላችን ይሆን ዘንድ ነውና።" ውዳሴ ማርያም ዘሐ
"ናዐብየኪ ኩልነ ኦ እግዝእትነ ወላዲተ አምላክ እስመ ሣህልኪ ይኩን ላዕለ ኩልነ ፤ አምላክን የወለድሽ እመቤታችን ሆይ ሁላችን እናገንሻለን ይቅርታሽ ለሁላችን ይሆን ዘንድ ነውና።" ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን:: አእምሮውን ልበዎውን ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን:: ጾሙን የፍሬ የትሩፋትና የበረከት ያድርግልን! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በሰላም አደረሰን አድሳችሁ! ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኚልን:: አእምሮውን ልበዎውን ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን:
እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በሰላም አደረሰን አድሳችሁ! ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኚልን:: አእምሮውን ልበዎውን ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን:: ጾሙን የፍሬ የትሩፋትና የበረከት ያድርግልን! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የድሬደዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሀገረ ስብከቱ ለሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የ4ኛ ክፍል የማጠቃለያ ምዘና ሰጠ። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) 30/2016 ዓ.ም በድሬደዋ
+6
የድሬደዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሀገረ ስብከቱ ለሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የ4ኛ ክፍል የማጠቃለያ ምዘና ሰጠ።                                                                (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) 30/2016 ዓ.ም በድሬደዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ለመጀመሪያ ጊዜ በሀገረ ስብከት ደረጃ ሲተገበር የቆየው የ4ኛ ክፍል ማጠቃለያ ምዘና በቀን 27 እና 28/2016 ዓ.ም ሰጥቷል።           በትግበራውም በሀገረ ስብከቱ ስር ከሚገኙ 12 አጥቢያዎች 7ቱ የተሳተፉ ሲሆን በጥቅሉ ከ710 በላይ ተማሪዎችም ፈተናው መውሰድ መቻላቸው ተገልጿል። መረጃው የድሬደዋ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ትምህርት ክፍል ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ጾመ ፍልሰታን በማስመልከት ያስተላለፉት መልእክት፣ ቃለ በረከትና ቡራኬ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል።        መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! በሀገር ውስጥና በተለያዩ ክፍለ ዓለማት የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ! በማሕፀነ ማርያም በፈጸመው እውነተኛ ተዋሕዶ የሰው ልጅን ከኃሣር ወደ ክብር የመለሰ እግዚአብሔር አምላካችን፣ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ስድስት ዓመተ ምሕረት ጾመ ቅድስት ማርያም በደኅና አደረሰን አደረሳችሁ!፤ ‹‹ተፈሥሒ ኦ ምልእተ ጸጋ፣ ተፈሥሒ እስመ ረከብኪ ሞገሰ በኀበ እግዚአብሔር፡- ምልእተ ጸጋ ሆይ ደስ ይበልሽ፤ በእግዚአብሔ ዘንድ ሞገስን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ›› (ሉቃ. 1÷28-30") የክብር አምላክ እግዚአብሔር የሰው ልጅን ከወደቀበት ዐዘቅተ ኵነኔ የሚያድንበት ዕድል እንዳዘጋጀ በብሉይ ኪዳን በስፋት ገልፆል፤ የማዳን ስራውም ከሰው ወገን ከሆነች ቅድስት ድንግል በሚወለደው መሲሕ እንደሚፈጸም አስረድቶአል፤ የማዳን ቀኑ በደረሰ ጊዜም መልእክቱን በፊቱ በሚቆመው በቅዱስ ገብርኤል በኩል ልኮአል፤ ቅዱስ ገብርኤልም የተነገረውን መልእክት ለድንግል ማርያም አድርሶአል፡፡ ቅዱስ ገብርኤል ለድንግል ማርያም እንዲነግር ከታዘዘባቸው መካከል ‹‹ጸጋን የተመላሽ ደስተኛይቱ ሆይ÷በእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ›› የሚል አስደናቂ መልእክት ይገኝበታል፡፡ የተወደዳችሁ ሕዝበ ክርስቲያን! ከእግዚአብሔር መንጭቶ በቅዱስ ገብርኤል በኩል ለድንግል ማርያም የተነገረ ይህ መልእክት፣ የቅድስት ድንግል ማርያምን ክብር ከመግለጽ ባሻገር ለሰው ልጆች ሁሉ ያለው ፋይዳ በእጅጉ የላቀ ነው፤ ‹‹ጸጋ›› የሚለው ቃል እንደ ቅዱስ መጽሐፍ አስተምህሮ ያልተወሰነ፣ ገደብና ቅድመ ሁኔታ የሌለው ስጦታን ሲያመለክት ‹‹ሞገስ›› የሚለው ቃል ደግሞ ተወዳጅነትን ተደማጭነትን ተሰሚነትን የሚያመለክት የክብርና የባለሟልነት መግለጫ ቃል ነው፡፡ እነዚህ ቃላት ከእግዚአብሔር ዘንድ በቅዱስ ገብርኤል በኩል ለቅድስት ድንግል ማርያም ተነግረዋል፤ የእግዚአብሔር ቃል የማይለወጥ ነውና ቃላቶቹ ለድንግል ማርያም ቃል ኪዳን ሆነው የተሰጡ ናቸው፤ የተሰጡበትም ምክንያት ሰውን ለማዳን ስራ እንዲውሉ እንጂ ለሌላ አይደለም፡፡ ምክንያቱም የእግዚአብሔር የማይናወጥ ፈቃድ ሰውን ማዳን ነውና፤ በመሆኑም ቅድስት ድንግል ማርያም ከእግዚአብሔር በተሰጣት በዚህ ገደብ የሌለው ቃል ኪዳኗ ሰውን ልትታደግ በቅታለች፤ይህም በቃና ዘገሊላ ባደረገችው ምልጃ በጭንቀት የተዋጡትን ሠርገኞች እንዴት እንደታደገች በቅዱስ ወንጌል ተጽፎ እናገኘዋለን፤ቅድስት ድንግል ማርያም ቀድሞውኑም ከፍ ያለ ሞገስ ተሰጥቶአታልና የሠርጉ አሳላፊዎችን ‹‹የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ›› በማለት ስታዝዝ እናያለን፤ ይህ ለሰው ልጆች ሁሉ የተሰጠ አስደናቂ የትድግና ስጦታ ነው፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን! የድንግል ማርያም የጸጋ ስጦታ በብሥራተ ገብርኤል ተገልጾ፣ በቃና ዘገሊላ ተተግብሮ በዕለተ ስቅለት ‹‹እነሆ ልጅሽ፣ እነኋት እናትህ›› በሚል መለኮታዊ ማኅተም የታተመ ነው፤ ይህ ቃል እሷ እናታችን መሆኗን፤ እኛም ልጆችዋ መሆናችንን ያረጋገጠ ማኅተመ ቃል ኪዳን ነው፤ የቃል ኪዳኑ ይዘት እሷ በአማላጅነቷ እንደ ልጅ ልትንከባከበን እኛም እንደ እናት  ልናከብራትና ልንማፀናት የሚገባን መሆኑን ያሳያል፤ የእናትነትና የልጅነት ማረጋገጫ የሆነ ይህንን የቃል ኪዳን ማኅተም ሊሰርዝም ሆነ ሊፍቅ ሊደመስስም የሚችል ኃይል የለም፡፡ ይህ ጸጋና ሞገስ በምድር ብቻ ሳይሆን በሰማይም የሚቀጥል እንጂ የሚገደብ አይደለም፤ ሞት፣ ቦታና ዘመንም አይወስኑትም፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን በሞት በቦታና በዘመን አይገደብምና ነው፤ ‹‹ኪዳኑንም ለዘለዓለም ያስባል›› ተብሎ የተገለጸውም ለዚህ ነው፤ (መዝ. )111÷5) መንፈስ ቅዱስም በእሷ አንደበት ‹‹እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ነሽ ይሉኛል›› በማለት የተናገረው ይህንን ለማስረዳት እንደሆነ ማስተዋል ያሻል፡፡ በእግዚአብሔር  ተሰጥቶ፣ በቃል ኪዳን ታትሞ፣ በቅዱስ ገብርኤል ተብራርቶ፣ በጌታችን ተረጋግጦና በሐዋርያት በኩል የተላለፈልን፣ ሰውን ማዳን ግቡ የሆነ የድንግል ማርያም ምልጃ ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊት፣ በሁሉ ያለች፣ አንዲትና ቅድስት ኦርቶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ለሁለት ሺሕ ዓመታት ያህል አምና እና ተቀብላ ስትጠቀምበት ኖራለች፤ አሁንም በዚሁ ትቀጥላለች፡፡ በኦርቶዶክሱ ዓለም ዛሬ የሚጀመረው የጾመ ማርያም ሱባዔም የዚሁ ጭብጥ ማሳያ ነው፤ ዋናው መልእክቱም ድንግል ማርያም በተሰጣት ጸጋና ሞገስ በጸሎቷ ከእግዚአብሔር ዘንድ ምሕረትንና ይቅርታን የምታሰጠን ስለሆነች እሷን በመማፀን ወደ እግዚአብሔር እንቅረብ የሚል ሆኖ ይመሰጠራል፡፡ የተወደዳችሁ ሕዝበ ክርስቲያን ልጆቻችን! ጾም ፈቃደ ሥጋን በማድከምና ፈቃደ ነፍስን በማጎልበት ምሕረተ እግዚአብሔር መሻታችንን የምናሳይበት መንፈሳዊ ማመልከቻ ነው፤ ጾም ከጥንት ጀምሮ የነበረ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ነው፤ ቀደምት አበው በጾም ምክንያት ከጥፋት ድነዋል፤ የለመኑትንም አግኝተዋል፤ ምስጢርም ተገልጾላቸዋል፤ ዲያብሎስም ድል አድርገውበታል፡፡ እኛም ዛሬ ጾምን ስንጾም በሀገራችንም ሆነ በአካባቢያችን ብሎም በዓለም ዙሪያ ሁሉ ስጋትን እየጫረ ያለው የጥፋት እንቅስቃሴ እግዚአብሔር እንዲያስቆምልን ከልብ በመጸለይ ሊሆን ይገባል፤ ይህንንም ስናደርግ በጸሎት ብቻ ሳይሆን ንስሐ በመግባትና ቅዱስ ቁርባንን በመቀበል እንደዚሁም የሰላም የፍቅርና የዕርቅ ሰው ሆኖ በእግዚአብሔር ፊት በመቆም ሊሆን ይገባል፡፡ ችግሮችንና አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ በውይይትና በምክክር ለመፍታት የሚደረገው ጥረትም በእጅጉ ሊደገፍ ይገባል፤ ግጭትና ጦርነት ከሚያጠፋን በቀር ሊያተርፍልን የሚችል አንዳች ጥቅም የለም፡፡ በመሆኑም በየትኛውም የሀገራችን አካባቢ ያላችሁ ልጆቻችን እባካችሁ ለሰላም ለውይይትና ለሰው ልጆች መብት መከበር ቅድሚያ ስጡ፤ ግድያ፣ ዕገታ፣ አብያተ ሃይማኖትን መዳፈር፣ ዘረፋና ቅሚያ፣ የሴት ልጅን መድፈርና ሰውን ማንገላታት አቁሙ፤ እነዚህ ድርጊቶች ሰብአዊነትን ዝቅ የሚያደርጉ፣ እግዚብሔርን የሚያስቆጡ፣ በታሪክም የሚያሳፍሩ ናቸው፤ እነዚህን ሳናርም   የምንጾመው ጾም ትርጉም ስለሌለው ንስሐ ገብተን ከእንደዚህ ያለው ድርጊ ርቀን ጾሙን መጾም ይገባል፤ ይህን ስናደርግ ጾማችን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋ ይኖረዋል፡፡ በመጨረሻም የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ በተለይም በጾመ ማርያም ሱባዔ በንስሐና በጸሎት የሚያሳልፉ ሕዝበ ክርስቲያን ስለ ሃይማኖት መጠበቅ፣ ስለሀገር ሰላምና አንድነት፣ እንደዚሁም ስለሕዝቦች ደኅንነትና ጤንነት አጥብቀው እንዲጸልዩ በእግዚአብሔር ስም መልእክታችንን እናስተላልፋለን፡፡ መልካም የሱባዔ ወቅት ያድርግልን እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን          አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት        ነሐሴ 1 ቀን 2016 ዓ.ም. ዋሽንግተን ዲሲ - ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ