የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
تُعد قناة የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 477 مشتركاً، محتلاً المرتبة 6 026 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 324 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 477 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 29 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 526، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 12، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 38.31%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 10.22% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 538 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 477 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 33.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 30 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
14 477
المشتركون
+1224 ساعات
+1357 أيام
+52630 أيام
أرشيف المشاركات
ለሰንበት ትምህርት ቤት አባላት የኢኮኖሚ ምጣኔ ሀብትና የአመለካከት ለውጥ ሥልጠና መሰጠት ተጀመረ።
ረቡዕ ሐምሌ 26 2016 ዓ.ም ፤ ከልደታ፣ ኮልፌና ፣አራዳ ክፍለ ከተሞች ለተወጣጡ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት የኢኮኖሚ ምጣኔ ሀብት እንዲሁም የአመለካከት ለውጥ ሥልጠና መሰጠት ተጀምሯል።
ሥልጠናው መንፈሳዊነትና ሥራን አብሮ ለማስኬድ መንገድ የሚጠቁም እንዲሁም ፤ የሚስተዋሉ ቸልተኝነትና ስንፍናን በመቅረፍ የአመለካከት ለውጥ ለማምጣት የሚያግዝ ከመሆኑም ባሻገር የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ከአሐዱ ባንክ እና ከዮቶር ብድር እና ቁጠባ ተቋማት ጋር ባደረገው ስምምነት መሰረት የተለያዩ የሥራ ዕድል ፈጠራዎችና የብድር ሁኔታን ማመቻትንና አባላቱን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችል ነው።
በዕለቱ የተደረገው የመጀመሪያ ዙር ሥልጠና ሲሆን በቀጣይ በሁሉም ክፍለ ከተሞችና ሰንበት ትምህርት ቤቶች ላይ ተደራሽ እንደሚሆን ተገልጿል።
[ የሰንበት ት/ት ቤቶች አንድነት ]
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
✍️ FaceBook 👇
https://www.facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
✍️Twitter👇
https://twitter.com/tibeb_feleg
✍️Tiktok👇
https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion
የአምቡላንሱ ችግር የሰርክ ችግር እንዳይሆን
ጥር ፲፬ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም. የተፈጸመው ሕገ ወጥ ሢመተ ጳጳሳት በነገ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ እና በዛሬው አገልግሎቷ ጥቁር አሻራ የተወ ክሥተት ሆኖ እየታወሰ ይኖራል፡፡ ሕገ ወጥ ሹመቱ የፈጠረውን ችግር ለማረም ቅዱስ ሲኖዶስ የሔደበትን መንገድ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን እና በሕገ ቤተ ክርስቲያን ሚዛን መዝነው የሚተቹ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እና ሌሎች የቤተ ክርስቲያን ልጆች በርካታ ናቸው፡፡ የሲኖዶስ አባላት የሆኑ ሊቃነ ጳጳሳት ደግሞ የችግሩን ምንጭ ያደርቃል ብለው ያሰቡትን ወስነዋል፡፡ በውጤቱም የተከሠተውን ችግር ለመፍታት በዋናነት ኦሮሚያ ክልል ለሚገኙ ሀገረ ስብከቶች በአፋን ኦሮሞ ማስተማር የሚችሉ ኤጲስ ቆጶሳትን መርጠው ሾመዋል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ የወሰደውን የመፍትሔ አቅጣጫ ለሕዝበ ክርስቲያኑ ለማስረዳት ብፁዐን አበው በቤተ ክርስቲያኗ መገናኛ ብዙኃን ቀርበው መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በመግለጫው ላይ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ሲኖዶሱ የቆየበትን ፈታኝ ቅርቃር እንደሚከተለው በፈሊጥ ነበር የገለጹት፡፡
ማንበብ ይቀጥሉ ...
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://eotc-gssu.org/a/የአምቡላንሱ-ችግር-የሰርክ-ችግር-እንዳይ/
የአምቡላንሱ ችግር የሰርክ ችግር እንዳይሆን
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
✍️ FaceBook 👇
https://www.facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
✍️Twitter👇
https://twitter.com/tibeb_feleg
✍️Tiktok👇
https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion
“የመንበረ ሰላማ” እና “የትግራይ ጠቅላይ ቤተ ክህነት” ጉዳይ
በትግራይ ክልል የሚገኙ አህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳት በሰሜኑ የአገራችን ክፍል በተከሠተው ጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን የአስተዳደር ክፍተት በማስተካከል ግንኙነቱ እንዲቀጥል በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ለተጻፉ ደብዳቤዎችም ሆነ በአካል በመሔድ ያቀረቡትን የሰላም ጥያቄ በመግፋት ክልላዊ ሲኖዶስ ለማቋቋም የሚያደርጉትን ሒደት አጠናክረው ቀጥለዋል። መንበረ ሰላማ የሚባል መንበር፣ የትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቃነ ጳጳሳት ጉባኤ ጽ/ቤት የተሰኘ መዋቅር እንደፈጠሩ በደብዳቤዎቻቸውና በመግለጫዎቻቸው አሳውቀዋል።
ማንበብ ይቀጥሉ ...
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://eotc-gssu.org/a/የመንበረ-ሰላማ-እና-የትግራይ-ጠቅላ/
“የመንበረ ሰላማ” እና “የትግራይ ጠቅላይ ቤተ ክህነት” ጉዳይ
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
✍️ FaceBook 👇
https://www.facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
✍️Twitter👇
https://twitter.com/tibeb_feleg
✍️Tiktok👇
https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion
ቋሚ ሲኖዶስ በክልል ትግራይ በተፈጸመው ሕገ ወጥ ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት ጉዳይ ሐምሌ 26 ቀን 2015 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ስብሰባ እንዲካሄድ ወሰነ።
ሰኞ ሐምሌ 24 2015 ዓ.ም ፤ በክልል ትግራይ በማእከላዊ ዞን አክሱም ሀገረ ስብከት በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሐምሌ 16 ቀን 2015 ዓ.ም. ሕገ ወጥ ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት ተፈጽሞ በመገኘቱ አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ እንዲጠራ አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን ለኢኦተቤ ቴቪ የተላከው መግለጫ ያስረዳል፡፡ በመሆኑም 1ኛ ሐምሌ 25 ቀን 2015 ዓም ለሁሉም የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ጥሪ እንዲተላለፍ፣ 2ኛ የመክፈቻ ጸሎቱ ሐምሌ 25 ቀን 2015 ዓ.ም. በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በ10፡00 ሰዓት እንዲከናወን 3ኛ ሐምሌ 26 ቀን 2015 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ስብሰባ እንዲካሄድ በማለት ቋሚ ሲኖዶስ መወሰኑን የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ለመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት በላከው መግለጫ አስታውቋል ፡፡
[ኢኦተቤ]
[ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ]
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
✍️ FaceBook 👇
https://www.facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
✍️Twitter👇
https://twitter.com/tibeb_feleg
✍️Tiktok👇
https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion
✝በዛሬው ዕለት ትምህርታችሁን አጠናቃችሁ ስለተመረቃችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ፣
የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በአዲሱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ያስተማራቸውን ተማሪዎች አስመረቀ ።
ሐምሌ 23 ቀን 2015 ዓ.ም
️የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በ2015 በጀት ዓመት በአዲሱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ትግበራ ሲያካሂዱ የነበሩ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ 3100 በላይ ተማሪዎችን ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ የገዳማት አድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ ተመራቂ ተማሪዎች ፣ በተገኙበት በደብረ ጽዮን ሰላም አድርጊው ማርያም ሰ/ቤት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ አስመርቋል።
👉ብፁዕ አቡነ አብርሃም ለተመራቂዎች ባስተላለፋት መልዕክት በዛሬው ዕለት ትምህርታችሁን አጠናቃችሁ ስለተመረቃችሁ እንኳን ደስ አላችሁ በማለት የጀመሩት ብፁዕነታቸው በማቴ 26:44 ላይ በሚገኘው ቃል "ስለዚህ እናንተም ደግሞ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ " ዝግጅታችሁ አጠናቃችሁ የፈተናውን ወቅት አልፋችሁ በዚህ ቅድመ ዝግጅት ያጠናችሁ ፣ ያነበባችሁ በዛሬ ስትመረቁ ፣ በሌላ በኩል ተማሪ መስለው ያላነበቡ ያላጠኑ ቅድመ ዝግጅት ያላደረገ ይህንን እድል ሊያገኙ አይችሉም። ቅድመ ዝግጅት ስንል በጸሎት እግዚአብሔርን በመጠየቅ ፣ አስቀድሞ ማሰብ ማሰላሰል ቀድሞ በመዘጋጀት ስራችን ልንሰራ ይገባል በዚህ ወቅት ባለመዘጋጀታችን ቤተክርስቲያን እየተፈተነች ትገኛለች ። ከአሁኑ ጀምሮ በመዘጋጀት ስራችን ልንሰራ ይገባል በማለት አባታዊ ትምህርት እና መምሪያ በመስጠት ለወደፊት በዚህ እንድትቀጥሉ አደራ በመስጠት አባታዊ ቡራኪያቸውን ለተመራቂዎች ከ ፩ኛ እስከ ፫ኛ የወጡ ተማሪቂዎችን የምስክር ወረቀት በመስጠት ተጠናቋል።
ባሳለፍነው ሳምንት ዕለተ ማክሰኞ ሐምሌ 18 2015 ዓ.ም የአዲስ አበባ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ከዮቶር የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃ/የተ/መሰረታዊ /የህብረት/ስራ/ማህበር ጋር የጋራ ስምምነት አደረገ
----
የአዲስ አበባ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ከዮቶር የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃ/የተ/መሰረታዊ/የህብረት/ስራ/ማህበር ጋር የጋራ ስምምነት አደረገ።
የአንድነቱ ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ ላዕከ ኄራን መንክር ግርማ፤ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት በአንድነቱ ስም ገልጸዋል።
የኅብረት ሥራ ማኅበሩ ቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሶፎኒያስ እሸቱ እና የአንድነቱ ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ ላዕከ ኄራን መንክር ግርማ የጋራ ስምምነቱን የተፈራረሙ ሲሆን። የቦርዱ ሰብሳቢ አቶ ሶፎንያስ "ተቋማችን በየግል ደረጃ ያሉ የግል ፍላጎቶቻችንን በጋራ ለመሥራት የተመሠረት በመሆኑ በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዘርፍ በኩል ለሚገጥሙን ተግዳሮቶች በዛሬው ዕለት ያደረግነው ስምምነት ወደ ሥራ ስንገባ የሚፈቱ ናቸው ለዚህም ደስተኞች ነን" በማለት አብስረዋል።
በዕለቱ በተደረገው የጋራ ስምምነት ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የኢኮኖሚ ምጣኔ ሀብት ማስተባበሪያ ክፍል ኃላፊ የሆኑት መምህር ተገኝ በላይ እንደተናገሩት፤ "ጥቅምት 14 2006 ዓ.ም በሲኖዶስ በፀደቀው የውስጥ መመሪያ አንቀጽ 13 ቁጥር 4 ላይ ወጣቶችን በሥነ ምግባር የታነጹ ፣ ሠርተው መለወጥን መርህ የሚያደርጉ ፣ ከኢኮኖሚ ጥገኝነት ነጻ የወጡ ፣ ለሀገርም ሆነ ለቤተ ክርስቲያን መልካም ዜጋ እንዲሆኑ ማብቃት ፣ በሚለው መመሪያ መሠረት አንዱ የቤ/ን ወጣቶች በኢኮኖሚ ራሳቸውን የሚችሉበት መንገድ ማመቻቸት በመሆኑ መመሪያውን ተከትሎ ወደ ሥራ ተገብቷል።" ሲሉ ተናግረዋል።
የስምምነቱ ዓላማም ወጣቶችን በማህበራዊና ኢኮኖምያዊ ዘርፎች ማብቃት ሲሆን ይህም በስራ እድል ፈጠራ ፣ በብድር አገልግሎት ፣ ለሰንበት ትቤቶች ለመንፈሳዊ አገልግሎት የሚያግዝ ተጨማሪ የልማት ገቢ ማስገኛ እንደሆኑ ተገልጿል።
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
✍️ FaceBook 👇
https://www.facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
✍️Twitter👇
https://twitter.com/tibeb_feleg
✍️Tiktok👇
https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion
መልአከ ሰላም ጋሽ ታዬ አብርሃም ስለ ሰንበት ት/ቤት አገልጋዮች የተናገሩት
https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion/video/7261339486066494766
ሁሉም ብፁዓን አባቶች ሐምሌ 25 2015 ዓ/ም ለተጠራው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ እንዲገኙ የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት በድጋሜ ጥሪውን አስተላለፈ።
ቅዳሜ ሐምሌ 22 2015 ዓ/ም ፤ በትግራይ ክልል በአክሱም ርእሰ አድባራት ጽዮን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሐምሌ ፲፮/፳፻፲፭ ዓ/ም የተፈጸመውን ኢ ቀኖናዊና ሕገወጥ ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳትን አስመልክቶ ለመምከር የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ለሐምሌ 25 2015 ዓ/ም መጠራቱ የሚታወስ ነው።
ይሁን እንጂ ቤተ ክርስቲያናችን የገጠማት ፈተና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን መሠረት በማድረግ በጉዳዩ ላይ ምክክር እንዲደረግበት የተጠራ አስቸኳይ ምልዓተ ጉባኤ መኖሩ ቢታወቅም አንዳንድ ብፁዓን አባቶች ግን ከወዲሁ በተለያየ ምክንያት እንደማይካፈሉ እየገለጹ ይገኛሉ።
ስለሆነም ከአቅም በላይ ያጋጠመ ችግር ቢኖርም እንኳ ከኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አንድነት ጉዳይ የሚበልጥ ባለመኖሩና የቤተ ክርስቲያን ቀኖናና አንድነት በከፍተኛ ደረጃ ሲፈተን እያዩ በጉባኤው አለመገኘት የተጠሩለት የቤተ ክርስቲያን እውነትን የመጠበቅ ተልእኮ እንደመግፋት ስለሚያስመስል በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ባሉ አህጉረ ስብከት የምትገኙ ብፁዓን አባቶች በተጠራው ቀን በጉባኤ እንድትገኙ በድጋሜ ጥሪ እናስተላልፋለን ብሏል።
በመሆኑም በተጠራው ምልዓተ ጉባኤ የማይገኙ አባቶች ካሉ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በእነሱ ላይ የሚወስነውን ውሳኔ የመቀበል ግዴታ ይኖርባቸዋል በማለት የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት አስታውቋል።
መረጃውን ያደረሰን የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ነው።
[ ኢኦተቤ ]
[ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ]
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
✍️ FaceBook 👇
https://www.facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
✍️Twitter👇
https://twitter.com/tibeb_feleg
✍️Tiktok👇
https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በቲክቶክ መጥቷል።
https://vm.tiktok.com/ZM2sBqQ3j/
ለቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊው ለውጥ መቼ?
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ያልተበረዘ ክርስቶሳዊ ትምህርት ምንጭ ናት፡፡ ነቅ አልባ አስተምህሮዋ መቼም ቢሆን ለድርድር አይቀርብም፡፡ ከጥንትም መሥሯቿ ኢየሱስ ክርስቶስ ነውና ፍጽምት አድርጎ ነው የሠራት። መንገድ እና ሕይወት እኔ ነኝ ያለው ጌታ የመሠረታት ሕይወት የሚገኝባት መንገድ ናት ተዋሕዶ፡፡ ሐቁ ከእርሷ የተሻለ መንገድ የለም ሳይሆን ከእርሷ ሌላ የሕይወት መንገድ የለም ነው። አስተዳደራዊ ሥርዓትን በተመለከተ ግን ነገሮች የሚከወኑበት ሁልጊዜም ከዘመን ዘመን የተሻሻለ መንገድ ይመጣል።
ማንበብ ይቀጥሉ ...
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://eotc-gssu.org/a/ለቤተ-ክርስቲያን-አስተዳደራዊው-ለውጥ-መ/
ለቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊው ለውጥ መቼ?
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
✍️ FaceBook 👇
https://www.facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
✍️Twitter👇
https://twitter.com/tibeb_feleg
ራስን በራስ መሾም በቤተ ክርስቲያን ላይ ያስከተለው መዘዝ
ከቤተ ክርስቲያን ታሪክ የተማርነው አባቶቻችን “ኤጲስ ቆጶስ ሆናችሁ ሕዝበ ክርስቲያኑን ምሩ” ሲባሉ አደገኛ አውሬ እንዳየ የቤት እንስሳ ሸሽተው ይደበቁ ነበር። አባቶች ሢመቱን ይሸሹት የነበረው አንድም በትሕትና ሁለትም በራስ ኃጢአት ብቻ ሳይሆን በሌሎች ጥፋት መጠየቅ ስላለበት ነው። በዘመናችን የኤጲስ ቆጶስነት ግብሩ የተለየ እስከሚመስል ድረስ ራስን በራስ እስከመሾም ተደርሷል። ከዚያ መንፈሳዊ ልዕልና ወርደን ለዚህ ውድቀት የተዳረግነው የኤጲስ ቆጶስነት ዓላማውና ግብሩ በመለወጡ ነው። ቤተ ክርስቲያ ለመከራ የተዳረገችውም ምእመናንን የሚጠብቁ ሳይሆኑ ምእመናንን ለኃላፊው ነገር መጠቀሚያ የሚያደርጉ ሰዎች አባት መሆን ሳይችሉ አባት ለመሆን መጣራቸው ነው።
ማንበብ ይቀጥሉ ...
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://eotc-gssu.org/a/ራስን-በራስ-መሾም-በቤተ-ክርስቲያን-ላይ-ያ/
ራስን በራስ መሾም በቤተ ክርስቲያን ላይ ያስከተለው መዘዝ
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
✍️ FaceBook 👇
https://www.facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
✍️Twitter👇
https://twitter.com/tibeb_feleg
የሊቀ መልዐኩ የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በድምቀት ተከብሮ ውሏል
----
ዛሬ ረቡህ ሐምሌ 19 ቀን 2015 ዓ.ም፤ ሊቀ መልዐክ ቅዱስ ገብርኤል ሕፃኑ ቂርቆስንና እናቱን ቅድስት እየሉጣን ክርስቲያን በመሆናቸው፣ አማናዊና ዘላለማዊ አምላክን ባለመካዳቸው ምክንያት ወደ እቶን እሳት ሲጣሉ ፅናትን የሰጠበትና ያዳነበትን እለት ዓመታዊ ክብረ በዓል ከዋዜማ ጀምሮ በተለያዪ ደብራት በድምቀት ሲከብር ውሏል። በመዲናችን በአዲስ አበባም በ54 ደብራት በሕዝበ ምእመኑ ሱታፌ በድምቀት ተከብሯል። [የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት]
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
✍️ FaceBook 👇
https://www.facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
✍️Twitter👇
https://twitter.com/tibeb_feleg
የአዲስ አበባ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ከዮቶር የገንዘብ ቁጠባና ብድር አክሲዮን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ጋር የጋራ ስምምነት አደረገ
----
የአዲስ አበባ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ከዮቶር የገንዘብ ቁጠባና ብድር አክሲዮን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ጋር የጋራ ስምምነት አደረገ።
የአንድነቱ ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ ላዕከ ኄራን መንክር፤ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት በአንድነቱ ስም ገልፀው፤ " አሁን ያለንበት ዘመን ቤተ ክርስቲያናችንን ከነሙሉ ክብሯ እምነቷ ፣ ዶግማዋና ቀኖናዋ ፣ ትውፊቷ እና ታሪኳ ፣ ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ አሁን ያለው ታዳጊ እና ወጣት ኦርቶዶክሳዊ በሃይማኖታዊ ፣ ማኅበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፍ ብቁ ሆኖ መገኘት ለነገ የማይባል የቤት ሥራ በመሆኑ ብቁ መሆን ከሚያስፈልግበት አንዱ የኢኮኖሚ ጉዳይ ሰንበት ት/ቤቶች በሚፈለግባቸው መጠን በመሥራት ውጤት ማምጣት እንደሚገባ ይገባናል፣ ጉዞው ተጀመረ እንጂ ገና ረጅም መንገድ ይቀረናል” በማለት ተናግረዋል። የማኅበሩ ቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሶፎኒያስ እሸቱ እና የአንድነቱ ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ ላዕከ ኄራን መንክር ግርማ የጋራ ስምምነቱን ተፈራርመዋል። የቦርዱ ሰብሳቢ አቶ ሶፎኒያስ እንደገለፁት፤ "ተቋማችን በየግል ደረጃ ያሉ የግል ፍላጎቶቻችንን በጋራ ለመሥራት የተመሠረት በመሆኑ በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዘርፍ በኩል ለሚገጥሙን ተግዳሮቶች በዛሬው ዕለት ያደረግነው ስምምነት ወደ ሥራ ስንገባ የሚፈቱ ናቸው ለዚህም ደስተኞች ነን" በማለት አብስረዋል።
በዛሬው ዕለት በተደረገው የጋራ ስምምነት ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የኢኮኖሚ ምጣኔ ሀብት ማስተባበሪያ ክፍል ኃላፊ የሆኑት መምህር ተገኝ በላይ እንደተናገሩት፤ "ጥቅምት 14 2006 ዓ.ም በሲኖዶስ በፀደቀው የውስጥ መመሪያ አንቀጽ 13 ቁጥር 4 ላይ ወጣቶችን በሥነ ምግባር የታነጹ ፣ ሠርተው መለወጥን መርህ የሚያደርጉ ፣ ከኢኮኖሚ ጥገኝነት ነጻ የወጡ ፣ ለሀገርም ሆነ ለቤተ ክርስቲያን መልካም ዜጋ እንዲሆኑ ማብቃት ፣ በሚለው መመሪያ መሠረት አንዱ የቤ/ን ወጣቶች በኢኮኖሚ ራሳቸውን የሚችሉበት መንገድ ማመቻቸት በመሆኑ መመሪያውን ተከትሎ ወደ ሥራ ተገብቷል።" በማለት ለማሳያ ያህልም የአሐዱ ባንክን አንስተው በዛሬው ዕለት ደግሞ ከዮቶር ብድርና ቁጠባ አክስዮን ማኅበር ጋር በተለያዩ ምድቦች በሚደረጉ ሥልጠናዎች ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚቻል ገልፀዋል። የስምምነቱ ዓላማም ወጣቶችን በማህበራዊና ኢኮኖምያዊ ዘርፎች ማብቃት ሲሆን ይህም በስራ እድል ፈጠራ ፣ በብድር አገልግሎት ፣ ለሰንበት ትቤቶች ለመንፈሳዊ አገልግሎት የሚያግዝ ተጨማሪ የልማት ገቢ ማስገኛ እንደሆኑ ተገልጿል።
[የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት]
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
✍️ FaceBook 👇
https://www.facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
✍️Twitter👇
https://twitter.com/tibeb_feleg
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፤
<<የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸውማል>> መዝ 33፥ 7
መላእክት በዕለተ እሑድ የተፈጠሩ ረቂቃን የሆኑ የማይሞቱ ናቸው። እግዚአብሔርን አመስግነው ክብሩን ለመውረስ ከተፈጠሩት ፍጥረታት መካከል መላእክት ይገኙበታል። መላእክት በሁለት ይከፈላሉ እነዚህም የእግዚአብሔር መላእክት ወይም ብርሃናዊ መላእክት እና የጨለማው አብጋዞች ወይንም ጽሉማን መላእክት ይባላሉ። መላእክት ከተሰጣቸው ጸጋዎች መካከል አንዱ ማዳን ወይንም ሰውን መራዳት ነው። እዚህ ጋር ልብ ልንለው የሚገባን ነገር ቢኖር መላእክት የሚያድኑት መልአክ በመሆናቸው ብቻ አይደለም ። ይልቁንም የእግዚአብሔር መላእክት በመሆናቸው እንጂ። በትንቢተ ዳንኤል ምዕራፍ ሦስት ላይ የምናገኛቸው ሦስት ሕፃናትን ከተፈረደባቸው የሞት ፍርድ ያዳናቸው እግዚአብሔር መላእክቱን ልኮ ነው። በሐምሌ 19 ቀን ይህንን በትንቢተ ዳንኤል የተደረገውን ተዓምር አብነት ያደረጉ ቅዱሳን ሰማእታት ቅዱስ ቂርቆስ እና ቅድስት ኢየሉጣ ሰማእትነት የተቀበሉበት ቀን ነው። በዚችም እለት ገና በልጅነት በሦስት ዓመቱ ለአምልኮ ጣኦት አልገዝም ብሎ አማልክተ ጣኦታትን በመርገም ለሞት የተዘጋጀውን ሕፃን እና እናቱን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ከሚነደው እሳት ያዳነበትን እያሰብን የምናከብርበት ነው። የእምነት ጽናት ምስክሮች የሆኑት እናት እና ልጅ የእግዚአብሔርን መንግሥት በማሰብ ራሳቸውን ለሞት አሳልፈው ሰጥተዋል። በርሱ ለሚያምኑት ለሚመሰክሩት የሚመሰክር አምላክ በቅዱስ ገብርኤል አማካኝነት ለሰው ከሚከብደው ለማመን ከሚያስቸግረው እቶን እሳት አድኗቸዋል። እኛም እነዚህ አብነቶቻችን የሚሆኑ ቅዱስ ቂርቆስ እና እናቱ ቅድስት እየሉጣን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እንዳዳናቸው በማሰብ እና የመላእክትን ማዳን በማመን እንዲሁም በረከታቸው እንዲደርሰን በመለመን በዓሉን ልናከብር ይገባል። ቅዱስ ቂርቆስንና ቅድስት ኢየሉጣን ያዳነ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል እኛንም ከሚነደው የኃጢአት እሳት እንዲያድነን የአምላካችን ቅዱስ ፈቃዱ ይሁን።'
[የሰ/ት/ቤቶች አንድነት]
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
✍️ FaceBook 👇
https://www.facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
✍️Twitter👇
https://twitter.com/tibeb_feleg
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት አዲስ ለሚሠራው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን መሠረት ባርከው አኖሩ!
----
ሐምሌ 18 ቀን 2015፤ ቅዱስነታቸው ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና ከድሬዳዋ ከንቲባ ከአቶ ከድር ጁሀር ጋር በመሆን በትናንትናው እለት፤ በድሬዳዋ ከተማ ኢንዱስትሪ መንደር አዲስ ለሚሠራው የመካነ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ ወልደታ ለማርያም ወአቡነ ሳሙኤል ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን የመሠረተ ድንጋይ አኑረዋል።
በተያያዘም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ጋር በመሆን የሰበታ ገዳም ቅርንጫፍ በሆነው በድሬዳዋ መልክአ ጀብዱ አቡነ አረጋዊ ሴቶች ገዳም ጉብኝት አድርገዋል። ቅዱስነታቸው ለገዳሙ መነኮሳይያትና በገዳሙ ለሚያድጉ ሕፃናት ሰፊ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል ። [ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል]
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
