ar
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

الذهاب إلى القناة على Telegram

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

تُعد قناة የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 477 مشتركاً، محتلاً المرتبة 6 026 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 324 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 477 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 29 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 526، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 12، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 38.31‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 10.22‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 538 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 477 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 33.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

وصف القناة غير متوفر.

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 30 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

14 477
المشتركون
+1224 ساعات
+1357 أيام
+52630 أيام
أرشيف المشاركات
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የተሰጠ መግለጫ፤ ******* ሐምሌ ፲፯ ቀን ፳፻፲፭ ዓ/ም አዲስ አበባ """"""""""""""""""""""""""""""""""""""" 1. በክልል ትግራይ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት በክልሉ ከሚገኙት አህጉረ ስብከት ጋር ተቋርጦ የነበረውን መዋቅራዊ ግንኙነት ችግር በውይይት እንዲፈታ ቅዱስ ሲኖዶስ ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪና ልዑካኑን በአካል ልኮ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ባለበት ወቅት በክልሉ የሚገኙ ብፁዓን አባቶች ሕገ ቤተ ክርስቲያንንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በመጣስ ቅዱስ ፓትርያርኩ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ተብለው በሚጠሩበት በማዕከላዊ ትግራይ ዞን አክሱም ሀገረ ስብከት በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን ሐምሌ 15 እና 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በተከናወነ ሕገ ወጥ ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት መፈጸሙን በመገናኛ ብዙኃን ለማወቅ ችለናል፡፡ በመሆኑም በዚህ የዶግማና የቀኖና ጥሰት ተግባር የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት በእጅጉ አዝኗል፡፡ 2. በመሆኑም የተከሰተው የዶግማ፣ የቀኖና እና አስተዳደራዊ ጥሰት አስመልክቶ ተወያይቶ ተገቢውን ለመወሰን ለሐምሌ 25 ቀን 2015 ዓ.ም. አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጥሪ ተላልፏል፡፡ 3. የስብሰባው ቀን ሊራዘም የቻለው በውጭው ክፍለ ዓለማት ያሉት ሊቃነ ጳጳሳት መገኘት ስላለባቸው የጉዞ ቀኑ እንዳያጥር እና በሀገር ውስጥ የሚገኙትም ሊቃነ ጳጳሳት ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል ምክንያት ለአገልግሎት ወደ አህጉረ ስብከታቸው የሄዱ በመሆኑ ለመመለሻ የሚያስፈልገውን ጊዜ ታሳቢ በማድረግ ነው፡፡ 4. በየደረጃ ያሉ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የሥራ ኃላፊዎች እና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም ምዕመናን ከአሁን ቀደም በቤተ ክርስቲያናችን ላይ በደረሰው ፈተና በሐዘንና በጸሎት ከቤተ ክርስቲያናችን ጎን በመቆም ላሳያችሁት ጽናት እያመሰገንን አሁንም በደረሰው ፈተና እንዳሁን ቀደሙ ሁሉ በሐዘንና በጸሎት ከቤተ ክርስቲያናችን ጎን ጸንታችሁ እንድትቆሙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ 5. በመላው ዓለም የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በጉዳዩ ላይ ተወያይቶ ተገቢውን ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ በትግዕስት እንድትጠብቁ እናሳስባለን፡፡ 6. ምንም እንኳን ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በሙሉ ጥሪው በደብዳቤ የተላለፈ ቢሆንም የመልእክቱ በፍጥነት መድረስ ካለው ስጋት አንጻር የችግሩን ተደጋጋሚነትና አሳሳቢነት ከግምት ውስጥ በማስገባት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭው ክፍለ ዓለማት የምትገኙ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በሙሉ እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ ተጠቃላችሁ ወደ ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ እንድትመጡ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡ 7. ሁሉም የቤተ ክርስቲያናችን ሚዲያዎችና ሌሎች መገናኛ ብዙኃን ይህን መልዕክት ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን መልእክቱን በማስተላለፍ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ በቤተ ክርስቲያናችን ስም እንጠይቃለን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ሐምሌ 17 ቀን 2015 ዓ.ም.

በአዲስ አበባ በሀገረ ስብከት ደረጃ የተዘጋጀ የሥርዓተ ትምህርት ፈተና ተሰጠ ---- ሰኞ ሐምሌ 17 ቀን 2015ዓ.ም፤ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኙ ቁጥራቸው 79 የሚሆኑ ሰንበት ትምህር
+3
በአዲስ አበባ በሀገረ ስብከት ደረጃ የተዘጋጀ የሥርዓተ ትምህርት ፈተና ተሰጠ ---- ሰኞ ሐምሌ 17 ቀን 2015ዓ.ም፤ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኙ ቁጥራቸው 79 የሚሆኑ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በአዲሱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት በሀገረ ስብከት ደረጃ የተዘጋጀውን የ4ኛ እና የ6ኛ ክፍል ፈተና ሐምሌ 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በተለያዩ ደብራት ወስደዋል። [የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት]

የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ከሰንበት ትምህርት ቤቶች አመራሮች ጋር ተወያየ ---- ቅዳሜ ሐምሌ 15 ቀን 2015 በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ በነበረው ውይይት ፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይም ከጥር ፲፬ በኋላ ቤተ ክርስቲያናችን የተለያዩ ፈተናዎችን እያስተናገደች ትገኛለች በአሁኑ ሰዓትም በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ከተፈጠረው ጦርነት ጋር ተያይዞ በቤተ ክርስቲያን የበላይ መዋቅር እና በትግራይ ክልል ከሚገኙ አህጉረ ስብከት መካከል የተፈጠረው አለመግባባት እንዲፈታ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ፓትርያሪክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘ ኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የሚመራ ልዑካን ቡድን ወደ ትግራይ ክልል መጓዙ ይታወቃል ሂደቱ እንዴት ነበር? ምን ውጤት ተገኘ? የሚሉ ጥያቄዎችን አስመልክቶ በሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በኩል ለሰንበት ትምህርት ቤቶች አመራሮች ገለጻ ተደርጓል። ከተነሱ ነጥቦች ውስጥም፤ በትግራይ ክልል የሚገኙ የአኅጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳት የትግራይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት መስርተናል በመሆኑም በዛ በኩል ደብዳቤ ይድረሰን የሚል አቋም እንዳላቸው ከዛም አልፎ ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት ለመፈፀም ምርጫ እንዳካሄዱና ይህም ወደ ቀኖናዊ ጥሰት እያመራ እንደሆነና ይህንንም ለመፍታት በብፁዕ አባታችን የተመራ ልዑክ ቦታው ድረስ በመሄድ ችግሩን ለማጥራት እና መፍትሔ ለመስጠት ቢፈለግም የዕርቅ ጥያቄዉን ሳይቀበሉ የቤተ መቅደስ በር እስከ መዝጋት እና አባቶች ከውጭ ኪዳን የደረሠ ድርጊት ተፈፅሞል። የትግራይ አህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳትም የሚያነሡት ጥያቄ ቀጥታ ከቤተ ክርስቲያን ጋር የማይገናኝ እና አግባብነት የሌላቸው እንደሆኑ ተነስቷል። በጥር ወር በኦሮሚያ ክልል ተመሣሣይ ችግር ተከስቶ ቤተ ክርስቲያን ሕጋዊ ሹመት እንጂ ሕገ ወጥ ሹመት አልቀበልም በማለቷ እና በማውገዟ ከዛም በኋላ በነበረው ንግግር ወደ ዕርቅ እና መግባባት ላይ ተደርሶ ሐምሌ 9 ቀን 2015 ዓ.ም. በሕጋዊ መንገድ ዘጠኝ አዳዲስ ኤጲስ ቆጶሳት በዓለ ሢመታቸው ተከናውኗል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት በምርጫው አካሄድ ላይ ጥያቄ እንደነበረው እና ይሄንንም ሃሣብ በተደጋጋሚ እንዳነሳ ተገልፆ ሆኖም ግን አሁን በተሾሙት አባቶች ላይ የጐላ ክፍተት እንዳላየና ውሣኔውን እንደሚቀበል ተነስቷል። እንዲሁም በአሁኑ ሰዓት በትግራይ ክልል እየተፈፀመ ያለውን ቀኖናዊ ጥሠት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት እንደማይቀበለው እየሔዱበት ያለው መንገድ ልክ እንዳልሆነ አስገንዝቧል። አያይዘውም አስተዳደራዊ ስህተቶችን እንዴት እንቅረፍ ፤ አንድነቱን እንዴት እናጠናክር የሚለውን በመወያየት ስብሰባው አጠናቀዋል። [የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት] ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

ይቅርታና ክረምት ---- በወርሐ ክረምት ከሚታሰቡ እና ከሚናፈቁ ነገሮች አንዱ አዲሱን ዓመት መቀበል፣ ስለ አዲሱ ዓመት ማሰብ ፣አዲስ ተስፋ፣ አዲስ ምኞትና በአዲሱ ዓመት ስለ ሚሠሩ ሥራዎች፣ ስለምና
ይቅርታና ክረምት ---- በወርሐ ክረምት ከሚታሰቡ እና ከሚናፈቁ ነገሮች አንዱ አዲሱን ዓመት መቀበል፣ ስለ አዲሱ ዓመት ማሰብ ፣አዲስ ተስፋ፣ አዲስ ምኞትና በአዲሱ ዓመት ስለ ሚሠሩ ሥራዎች፣ ስለምናሳካቸው ተግባራት እቅድ ማቀድ ነው። አብዛኞቻችን ከማናስበው ነገር አንዱ አሮጌውንስ ዓመት እንዴት እንሸኘው የሚለውን ነው:: ሁሌም ይሄ ሲታሰብ ወደ አእምሮ ከሚመጡ ነገሮች ዉስጥ ጾመ ፍልሠታ አንዱ ነው። በተለይም ደግሞ ከአዲስ ዓመት በፊት መምጣቱ አሮጌውን ዓመት ለመሸኘት ጥሩ አጋጣሚ ነው። በፍልሰታ ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ምዕመን በመሚባል ደረጃ ከሕፃን እስከ አዋቂ የሚጾምበት የሚያስቀድስበት ወቅት ነው። ግን ምን ያህሎቻችን ነን ቅዳሴ ስንሄድ የካህኑን "በልቦናው ቂምን ያዘለ ክፋትን ያሰበ ቢኖር እዚህ አይቁም" የሚለውን ቃል ልብ የምንል የሚለው ሌላ ጥያቄ ነው። ... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/ይቅርታና-ክረምት/ ይቅርታና ክረምት ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

ከእግዚአብሔር ጋር መታገል ---- ንስሐ ገብተህ ኃጢያትን ለማስወገድ ትፈልጋለህ? አንድ ነገር አስታውስ። ኃጥያትን ለማሸነፍ የሚደረገው ትግል በሰው ጉልበት ብቻ ውጤታማ ሊሆን አይችልም። ኃጥያት ጠን
ከእግዚአብሔር ጋር መታገል ---- ንስሐ ገብተህ ኃጢያትን ለማስወገድ ትፈልጋለህ? አንድ ነገር አስታውስ። ኃጥያትን ለማሸነፍ የሚደረገው ትግል በሰው ጉልበት ብቻ ውጤታማ ሊሆን አይችልም። ኃጥያት ጠንካራ በመሆኗ "ወግታ የጣለቻቸው ብዙዎች ናቸው። እርሷም የገደለቻቸው ብዙዎች ናቸው" ምሳሌ(7፥26) ተብሎ ተጽፏል። ... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/ከእግዚአብሔር-ጋር-መታገል/ ከእግዚአብሔር ጋር መታገል ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

የሰንበት ትምህርት ቤቶች የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ የመምህራን ሥልጠና ተጀመረ ---- ከትላንት በስትያ ረቡዕ ሐምሌ 12 ቀን 2015 ዓ.ም ፤ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ዓለም አቀፍ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የተዘጋጀው የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ የመምህራን ሥልጠና በቅድስት ሥላሴ ዩንቨርስቲ መሰጠት ተጀመረ። ሥልጠናው ከሐምሌ 12 እስከ ሐምሌ 27 እንደሚቆይና ከአዲስ አበባ፣ ሰሜን ሸዋ ፣ ምስራቅ ሸዋ ፣ ጅማና ሀዋሳ አኅጉረ ስብከት ለተወጣጡ ቁጥራቸው ከ100 በላይ ለሚሆኑ መምህራን የሚሰጥ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በመጀመሪያው የሥልጠና ቀን የመክፈቻ ንግግሩን ያደረጉት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት መ/ር ስንታየሁ ምስጋናው ነበሩ። በንግግራቸውም ይህ ሥልጠና የተዘጋጀው በዋነኛነት ሥርዓተ ትምህርቱን ከማስገንዘብና ከመተግበር አኳያ መሰረታዊ በሆነ መልኩ ለማየት እንዲሁም የማስተማርያ ሥነ-ዘዴዎችን ማለማመድን ጨምሮ መሆኑን ገልጸገዋል። በመቀጠልም በሰንበት ት/ቤት ማደራጃ መምሪያ ም/ኃላፊ የሆኑት መጋቤ ሐዲስ ቀሲስ ጸጋ ወ/ትንሣኤ ተከታዩን መልዕክት ለሠልጣኝ መምህራን አስተላልፈዋል፤ “ቅዱስ ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ በላከው መልዕክቱ ላይ፤ ‘ማደግህ በነገር ሁሉ እንዲገለጥ ይህን አስብ’ እንዳለው እናንተም ዛሬ የምትማሩት ነገ እንዲፈራ ነው። ክርስቲያን መተከል፣ ማደግና ማፍራት አለበት፣ ስንማር እናድጋለን፣ ስናስተምር እናፈራለን፣ የተማርነውን ማስተማር ማፍራት ነው። ነገ እዚህ የተማራችሁትን ሄዳችሁ ታስተምራላችሁና ስታድጉ በዕውቀት ብቻ ሳይሆን በምግባርም ጭምር ይሁን። መምህር በነገሩ ሁሉ አርአያ መሆን ስላለበት የሚኖራችሁን ቆይታ ያለመሰልቸት እንዲሆን” በማለት አሳስብዋል። በመቀጠልም የሀገር አቀፍ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ጸሐፊ ቀሲስ አርአያ ተሾመ ለመምህራኑ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክትና ማሳሰቢያ ንግግር አድርገዋል። በንግግራቸውም፤ “በእነዚህ 15 ቀናት ውስጥ የሥርዓተ ትምህርቱን እርሾ የሚሆነውን ነገር እንማማራለን እንጂ ሙሉ ሥርዓተ ትምህርት እናጠናቅቃለን ማለት አይደለም። ይህ የሥልጠና ቆይታ አዕምሮአችንን ሰብስበን ገዳም እንደሄደ ምዕመን ሆነን እንቆያለን። በምናሳልፈው ቀናትም በቡድን በመሆን በመሥራት፣በመማማር በመሳተፍ፣ ስልጠናው የታቀደበትንና የተዘጋጀበትን ዓላማ እናሳካለን” ብለዋል። ሠልጣኝ መምህራኑ እርስ በእርስ የመተዋወቅና የአገልግሎት ሁኔታቸውን በመግለፅ ሥልጠናውን የጀመሩ ሲሆን፤የመጀመሪያውን ሥልጠና የትምህርት ፍልስፍና በሚል ርዕስ የሰጡት መ/ር ጥበቡ ጌታቸው እንደተናገሩት፤ “የሰንበት ት/ት ቤት ሥራ የሚሠራው በራስ፣ ለራስ፣ ከራስ ነው። ይህም ከሌሎች ዓለም ላይ ከሚገኙ የሥራ መስኮች የተየለየ እንዲሆን ያደርገዋል። የሚማረው ያስተምራል፣ የሚያስተምረው ይማራል፣ ስለዚህ እኛም ከዚህ ሥልጠና በኋላ ሥልጠናውን ራሳችን ለራሳችን የምንጠቀመው ይሆናል ማለት ነው።” የጠዋቱን የሥርዓተ ትምህርት ስልጠና መርሃ ግብር ዘግተዋል። በሁለተኛው የሥልጠና ዕለትም ብጹዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂና የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሥልጠናው ላይ በመገኘት ለሰልጣኝ መምህራን አባታዊ ቡራኬ እና ቃለ ምዕዳን ሰጥተዋል። [የሰ/ት/ቤት አንድነት] ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

ቤተ ክርስቲያን ለምን ለውጥ ያስፈልጋል? በዘመናችን ቤተ ክርስቲያን እጅግ በከፋ መንፈሳዊ ጉድለትና አስተዳደራዊ ግድፈት እየታመሰች ነው። ይህን ሐቅ በአገልግሎት ቀጥተኛ ሱታፌ ላላቸው ካህናትና ምእመ
ቤተ ክርስቲያን ለምን ለውጥ ያስፈልጋል? በዘመናችን ቤተ ክርስቲያን እጅግ በከፋ መንፈሳዊ ጉድለትና አስተዳደራዊ ግድፈት እየታመሰች ነው። ይህን ሐቅ በአገልግሎት ቀጥተኛ ሱታፌ ላላቸው ካህናትና ምእመናንን መንገር የዓዋጁን በጆሮ ይሆናል፡፡ ሀብተ ውልድ ያላቸው ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች ከቤተ ክርስቲያን ጋር ያላቸው ትሥሥር የላላ ነው ተብለው ለሚታሰቡት ክርስቲያኖች እንኳ ግድፈቱ ክሡት ነው፡፡ ይህ የተገለጸ እውነት ቤተ ክርስቲያን ለውጥ ያስፈልጋታል የሚለው ሐሳብ አከራካሪ እንዳይሆን ያደርገዋል፡፡ ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሚነሣ አንዳች የማያከራክር መሠረታዊ እውነት አለ፤ እርሱም ምን ዓይነት ለውጥ ለሚለው ጥያቄ የሚሰጥ መልስ ይሆናል፤ አስተዳደራዊ ለውጥ፡፡ ... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/ቤተ-ክርስቲያን-ለምን-ለውጥ-ያስፈልጋል/ ቤተ ክርስቲያን ለምን ለውጥ ያስፈልጋል? ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

በሰማይ የሀሉ ልብክሙ - ልቡናችሁ በሰማይ ይኑር ቅዳሴ እግዚእ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንም ሆነ በአኃት አብያተ ክርስቲያን ጸሎተ ቅዳሴ የሚጀመረው ካህኑ ከምእመናን ጋር በሚያደርገው ተዋሥዖ (ምልልስ
በሰማይ የሀሉ ልብክሙ - ልቡናችሁ በሰማይ ይኑር ቅዳሴ እግዚእ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንም ሆነ በአኃት አብያተ ክርስቲያን ጸሎተ ቅዳሴ የሚጀመረው ካህኑ ከምእመናን ጋር በሚያደርገው ተዋሥዖ (ምልልስ) ነው፡፡ ብሔራውያን ሊቃውንት ከመጽሐፈ ኪዳን የወሰዱትን አኮቴተ ቁርባን ቅዳሴ እግዚእ (የጌታ ቅዳሴ) ብለው ሰይመውታል፡፡ የዚህ ቅዳሴ አውስኦ የሚጀምረው በዲያቆኑ ‹‹በሰማይ የሀሉ ልብክሙ-ልባችሁ በሰማይ ይኑር›› በሚል ቃል ነው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከትንሣኤው በኋላ ከሐዋርያት ጋር ለዐርባ ቀናት ያህል ሲቆይ ያስተማራቸው እና ከሰባቱ ኪዳናት አንዱ ነው፡፡ ሊቃውንቱ ይህ ቃል ጌታ አስቀድሞ በጸሎተ ሐሙስ ሕብስቱን ያከበረበት በለሆሳስ የደገመው ቃል መሆኑን ይነግሩናል፡፡ ይህንኑ ቃል ከትንሣኤው በኋላ ለሐዋርያት እንዳስተማራቸውም ያስረዳሉ፡፡ ... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/በሰማይ-የሀሉ-ልብክሙ-ልቡናችሁ-በሰማይ-ይ/ በሰማይ የሀሉ ልብክሙ – ልቡናችሁ በሰማይ ይኑር ቅዳሴ እግዚእ ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

በሕገ ወጥ ሹመት የተሳተፉ አባቶችን ዕጩ አድርጎ ማቅረብ ያለው ዳፋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በግንቦት ፳፻፲፭ ዓ.ም በነበረው የርክበ ካህናት መደበኛ ጉባኤው አዲስ
በሕገ ወጥ ሹመት የተሳተፉ አባቶችን ዕጩ አድርጎ ማቅረብ ያለው ዳፋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በግንቦት ፳፻፲፭ ዓ.ም በነበረው የርክበ ካህናት መደበኛ ጉባኤው አዲስ ኤጲስ ቆጶሳትን ለመሾም አስመራጭ ኮሚቴ መሠየሙ ይታወቃል።ኮሚቴው ዕጩ ኤጲስ ቆጶሳትን እንዲያቀርብ ከመሠየም ውጪ ቅዱስ ሲኖዶስ ጉዳዩን በምሥጢር እንዲያከናውን የሰጠው ትእዛዝ የለም። ... የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤም ኮሚቴው በዘጠኙ አህጉረ ስብከት የሚመደቡ ዘጠኝ ተሿሚዎችን ለመለየት የመጨረሻዎቹን ፲፰ ዕጩዎች ማቅረቡን በመግለጽ ሪፖርት ሲያደርግ በምርጫ ዘጠኙን በመለየት ሹመታቸው ሐምሌ ፱ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም እንደሚፈጸም ውሳኔውን ይፋ አድርጓል። ኮሚቴው ካቀረባቸው ዕጩዎች ውስጥ ሰባቱ ጥር ፬ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም በሕገ ወጡ ሢመት ተሳታፊ የነበሩ ናቸው። ከእነዚህ ውስጥ ሦስቱ በቅዱስ ሲኖዶስ ተመርጠዋል። የእነዚህ አካላት በዕጩነት መቅረብ እጅግ ብዙ ውስብስብ ችግሮችን የሚፈጥር መሆኑ አያጠራጥርም። ... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/በሕገ-ወጥ-ሹመት-የተሳተፉ-አባቶችን-ዕጩ-አ/ በሕገ ወጥ ሹመት የተሳተፉ አባቶችን ዕጩ አድርጎ ማቅረብ ያለው ዳፋ ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይን አስመልክቶ ከሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የተሰጠ መግለጫ! በሰሜኑ የአገራችን ክፍል ከተፈጠረ ጦርነት ጋር ተያይዞ በቤተ ክርስቲያን የበላይ መዋቅርና በትግራይ ክልል በሚገኙ አህጉረ ስብከት መካከል የነበረው አስተዳደራዊ መዋቅር ተቋርጦ መቆየቱ ይታወቃል። የተፈጠረው አለመግባባት በውይይት ተፈቶ መዋቅራዊ አንድነቱ ተጠናክሮ እንዲቀጠል ሀገራዊ የሰላም እርቁ ከተፈጸመበት ማግስት ጀምሮ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፊርማ በተደጋጋሚ በደብዳቤ ሲጠየቅ መቆየቱም ይታወሳል፡፡ በትግራይ ክልል በሚገኙ አህጉረ ስብከት ያሉ አራቱ ሊቃነ ጳጳሳት ግን የሰላም ጥያቄውን በመግፋት መዋቅራዊ አደረጃጀቱን በመጣስ መንበረ ሰላማ የትግራይ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት መሥርተናል በማለት ተገቢነት የሌለው መግለጫ ከመስጠት አልፈው ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት ለመፈጸም ለሐምሌ 9 ቀን 2015 ዓ.ም. ቀጠሮ መያዛቸውን በተለያዩ መገናኛ ብዙኀን እየገለጹ ይገኛሉ። የተከሰተውን የቤተ ክህነት አስተዳደር ክፍተት በማስፋት ወደ ቀኖና ጥሰት ለመውሰድ የሚደረገው ሒደት በእግዚአብሔርና በታሪክ ፊት ተጠያቂነትን ያስከትላል። በሊቃነ ጳጳሳቱ በቤተ ክርስቲያን ደረሰብን በሚል የሚጠቀሱ ጉዳዮች አግባብነት የሌላቸው ከመሆናቸውም በላይ በግለሰብ ደረጃ ተነገሩ የተባሉ ንግግሮችንም በመውሰድ ቤተ ክርስቲያንን በምልዓት እንደ ጥፋተኛ መቁጠሩ ተገቢ ሆኖ አላገኘነውም። ይልቁንም አሁን ያለውን ችግር የበለጠ የሚያወሳስብ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ ተከስቶ ከነበረው ችግር ጋር ተያይዞ ፈጥኖ ለመፍትሔ አለመዘጋጀትና ሰላም እና አንድነት ለማምጣት መዘግየት እንደነበረ ባይካድም በስተመጨረሻ ቅዱስ ሲኖዶስ ችግሩ የመጨረሻ እልባት እንዲያገኝ  በይፋ ይቅርታ ከመጠየቅ ጀምሮ በቅዱስ ፓትርያርኩ የተመራ የሰላም ልዑክ በመላክ አንድነቱን ለማምጣት የተሔደበት ርቀት የሚደነቅ ነው። ይሁን እንጂ አራቱ ሊቃነ ጳጳሳት የሰላም ልዑካኑን የአንድነትና የእርቅ ጥያቄ በመግፋት፣ ቤተ መቅደስ እስከ መዝጋት የደረሰ ፈጽሞ የማይገባ አሳዛኝ ድርጊት ፈጽመዋል። እንዲሁም  ቤተ ክርስቲያንን ለማዳከም፣ ለመክፈል ብሎም ለማጥፋት በሚሠሩ አጽራረ ቤተ ክርስቲያን እና የዘውግ ፖለቲካ አቀንቃኞች ድጋፍና ጫና ኢቀኖናዊ በሆነ መንገድ አዲስ አደረጃጀት ለመፍጠርና ኤጲስ ቆጶሳትን ለመሾም ዝግጅት መደረጉን ከሚወጡት መረጃዎች ተረድተናል። በመሆኑም ይህን ኢቀኖናዊ ሕገ ወጥ አካሄድና አጠቃላይ ቅዱስ ፓትርያርኩ ከሚመሩት የሰላም ልዑክ ጋር የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ከነበረው ሱታፌና ተጨባጭ ምልከታ አንጻር የሚከተለውን የአቋም መግለጫ አውጥቷል። 1ኛ. ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ እና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጥር ፲፬ ፳፻፲፭ ዓ.ም በተፈጸመው የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት ወቅት በቁርጠኝነት ሕገ ቤተ ክርስቲያንን ለማስከበር በተሔደበት ርቀት ልክ አሁን ላይ የቤተ ክርስቲያንን መዋቅራዊ አደረጃጀት በመክፈል፣ ሕገ ወጥ የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ለመፈፀም የተወጠነውን እኩይ ሴራ ለማስቆም በመንፈስ ቅዱስ መሪነት እንደ ከዚህ ቀደሙ በጥብዓት፣ በታላቅ ጥበብና በአንድነት በመቆም ታሪካዊ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ እንጠይቃለን። 2ኛ. በትግራይ ክልል የምትገኙ ብፁዓን አባቶች፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ካህናት፣ ምእመናን፣ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት እና ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ማኅበራት ይህ ፈተና የውጫዊ አካላት ጫና ያለበትና ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንን ለማዳከም የታለመ ሴራ መሆኑን  በመረዳት፣ የቤተክርስቲያንን አንድነት በማስቀደም እየተፈጸመ ያለውን ኢቀኖናዊ ጥሰት በማስቆም የኦርቶዶክሳውያን አንድነት እንዳይከፈል የበኩላችሁን መንፈሳዊ ኃላፊነት  እንድትወጡ ጥሪያችንን እናቀርባለን። 3ኛ. ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጀምሮ እስከ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያን በአገልግሎት ላይ ያላችሁ አንዳንድ አገልጋዮች የሰላምና የአንድነቱ አካል ከመሆን ይልቅ ችግሩን በማባባስ በመጠመዳችሁ ከዚህ እኩይ ተግባር በመቆጠብ አንድነት እና ሰላም እንዲሰፍን ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ እና የመፍትሔው አካል እንድትሆኑ በአጽንዖት እናሳሰባለን። 4ኛ. በቅዱስ ፓትርያርኩ ዙሪያ ሆናችሁ የዚህ ታሪካዊ ስሕተት ደጋፊ የሆናችሁ እና የቤተ ክርስቲያንን ታሪክ ለማበላሸት  የተሰለፋችሁ  አካላት ከአፍራሽ አካሔዳችሁ እንድትቆጠቡ እየጠየቅን በስሑት አካሔዳችሁ ምክንያት የሚነሣው እሳት ወላፈኑ መጀመሪያ የሚያገኘው እናንተን መሆኑን በመረዳት ከዚህ ግብራችሁ እንድትታቀቡ በጥብቅ እናሳስባለን። በመጨረሻም  ቤተ ክርስቲያንን  ለመጠበቅ እንዲሁም ሕግ እና ሥርዓት  ለማስከበር በሚደረገው ሒደት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት በአስፈላጊ ጉዳዮች ሁሉ  ቅዱስ ሲኖዶስን በመታዘዝ የልጅነት ድርሻውን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ያረጋግጣል።

እንኳን ለቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዚህ ዕለት ቅድስት ሥላሴ ለአበ ብዙኅን አብርሃም ተገልጠው በቤቱ የተስተናገዱበት ቀን ነው። ዘፍ 18፡1 ✍️YouTube 👇 http
እንኳን ለቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዚህ ዕለት ቅድስት ሥላሴ ለአበ ብዙኅን አብርሃም ተገልጠው በቤቱ የተስተናገዱበት ቀን ነው። ዘፍ 18፡1 ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ልዩ ልዩ ብዙኃን መገናኛዎች በያዝነው ዓመት ሊደረግ የታሰበው የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ የእምነቱን ተከታዮች በሁለት ከፍሎ ደጋፊና ተቃዋሚ አድርጎ እያነታረከ ነው። ጉዳዮን ማኅበራዊ
የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ልዩ ልዩ ብዙኃን መገናኛዎች በያዝነው ዓመት ሊደረግ የታሰበው የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ የእምነቱን ተከታዮች በሁለት ከፍሎ ደጋፊና ተቃዋሚ አድርጎ እያነታረከ ነው። ጉዳዮን ማኅበራዊና ብዙኃን መገናኛዎች እየዘገቡት ያለው በሚከተለው መልኩ ነው። ግዮን መጽሔት የዘገበው በጥብቅ ምሥጠር የተያዘው የዕጩ ኤጲስ ቆጶስ ተጠቋሚ መነኰሳትስም ይፋ እንዲደረግ መጠየቁን አስመልክቶ የዘገበው “የዕጩ ኤጲስ ቆጶሳት አስመራጭ ኮሚቴ፣ ከ18 እስከ 20 ተጠቋሚዎችን መለየቱን፣ ከ25ቱ በኢቀኖናዊ ሢመት ተሳታፊዎች መካከል ስድስቱ የተጠቆሙ ሲሆን ሦስቱ ለሹመት እንደሚቀርቡ፣ ኮሚቴው ኀሙስ ሰኔ 22 የሚያደርገው ... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/የኤጲስ-ቆጶሳት-ምርጫ-ልዩ-ልዩ-ብዙኃን-መገ/ የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ልዩ ልዩ ብዙኃን መገናኛዎች ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ጉባኤ ዛሬ ለኹለተኛ ቀን እየተካሄደ ነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ጉባኤ፤ በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ እና በአዲስ አበባ አቅራቢያ
የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ጉባኤ ዛሬ ለኹለተኛ ቀን እየተካሄደ ነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ጉባኤ፤ በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ እና በአዲስ አበባ አቅራቢያ ያሉ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ትናንት ከቀኑ 10:00 ሰዓት በቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽ መካሄድ ጀምሯል፡፡ በትናንቱ የቋሚ ቅዱስ ሲኖዶስ መደበኛ ስብሰባ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ውይይትና ውሳኔ በማስፈለጉ፤ የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት እንዲጠራ መወሰኑን አዲስ ማለዳ ከቤተክርቲያኒቷ ቅርብ አካላት አረጋግጣለች፡፡ አስቸኳይ ምልአተ ጉባኤ እንዲጠራ ያስፈለገበት ምክንያት፤ “ባሳለፍነው ሰኞ ወደ ትግራይ ክልል ለእርቀ ሰላም ጉዳይ በቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት የተጓዘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የልዑካን ቡድን፤ የገጠመውን እክል በመገምገም፤ አሁን ያለው የቤተክርስቲያኒቷን ወቅታዊ ሁኔታ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ውይይትና ውሳኔ እንደሚያስፈልገው በመታመኑ ነው፡፡” ተብሏል። በዛሬው አስቸኳይ ጉባኤ በሚደርሰው ስምምነት መሠረትም፤ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ በኹሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አህጉረ ስብከት ያሉ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ሊጠሩ እንደሚችሉ እና ምልአተ ጉባዔ ሊደረግ እንደሚችልም የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት አስታውቋል ።

የተወገዙት በዕጩነት እንዳይቀርቡ ቤተ ክርስቲያን የምትቃወምባቸው መሠረታዊ ምክንያቶች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በግንቦት ፳፻፲፭ ዓ.ም በነበረው የርክበ ካህናት መደ
የተወገዙት በዕጩነት እንዳይቀርቡ ቤተ ክርስቲያን የምትቃወምባቸው መሠረታዊ ምክንያቶች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በግንቦት ፳፻፲፭ ዓ.ም በነበረው የርክበ ካህናት መደበኛ ጉባኤው ዘጠኝ አዲስ ኤጲስ ቆጶሳትን ለመሾም አስመራጭ ኮሚቴ መሠየሙ ይታወቃል። አስመራጭ ኮሚቴውም አዲስ ኤጲስ ቆጶሳት በሚመደብባቸው ዘጠኝ አህጉረ ስብከት ተሿሚዎችን በመምረጥ የመጨረሻዎቹን ፲፰ ዕጩዎችን በመለየት አቅርቦ ዘጠኙ በቅዱስ ሲኖዶስ ተመርጠው ለሹመት በመዘጋጀት ላይ ይገኛሉ። ... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/የተወገዙት-በዕጩነት-እንዳይቀርቡ-ቤተ-ክ/ የተወገዙት በዕጩነት እንዳይቀርቡ ቤተ ክርስቲያን የምትቃወምባቸው መሠረታዊ ምክንያቶች ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

እንኳን ለብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebo
እንኳን ለብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

የተማረ ግብረ ገብ ይሾም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከኤጲስ ቆጶሳት ሢመት ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ እየተነሡ ያሉ ጉዳዮች አሉ። አንደኛውና ዋናው ከእኛ ዘር፣ ጎሣና ቋንቋ ተናጋሪ
የተማረ ግብረ ገብ ይሾም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከኤጲስ ቆጶሳት ሢመት ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ እየተነሡ ያሉ ጉዳዮች አሉ። አንደኛውና ዋናው ከእኛ ዘር፣ ጎሣና ቋንቋ ተናጋሪ በኤጲስ ቆጶስነት አልተሾሙም የሚል ሲሆን፣ ሌላው ደግሞ ቅዱስ ሲኖዶስን የአንድ አካባቢ አባቶች የተሰበሰቡበት ነው የሚል ነው። ይህም ቅዱስ ሲኖዶስን በመንፈስ ቅዱስ እንደሚመራ የቤተ ክርስቲያን አካል ሳይሆን የዘር ውክልና ያለበት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አድርጎ የመውሰድ የተሳሳተ አረዳድ ወይም ክፉ አሳብ ነው። ብዙ ጊዜ ይህን አሳብ የሚያራምዱት ግን ምእመናን ሳይሆኑ በአቋራጭ ጳጳስ እንሆናለን ብለው የሚያስቡ አካላትና ደጋፊዎቻቸው ናቸው። ጥያቄውም ከመንፈሳዊነት ይልቅ ወደ ፖለቲካዊነት ያጋደለ ነው። ... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/የተማረ-ግብረ-ገብ-ይሾም/ የተማረ ግብረ ገብ ይሾም ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg