ar
Feedback
AALTO -አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት

AALTO -አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد
6 677
المشتركون
+324 ساعات
+957 أيام
+13630 أيام
أرشيف المشاركات
ቀን 16/10/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለባለ በጀት መስሪያ ቤት ግብር ከፋዮች በአገልግሎት አሰጣጥና ገቢ አሰባሰብ፣ በኢ ፋ
+7
ቀን 16/10/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለባለ በጀት መስሪያ ቤት ግብር ከፋዮች በአገልግሎት አሰጣጥና ገቢ አሰባሰብ፣ በኢ ፋይሊንግ እና በኢ ፔይመንት ላይ በዛሬዉ ቀን የሰጠዉ ስልጠና  እና ከስልጠና መልስ በየስራ ክፍሎች የተደረገዉ ጉብኝት በፎቶ

ለሴት ግብር ከፋዮች በታክስ ሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያና በኢ-ክሊራንስ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ ጽ/ቤት የሴት ግብር ከፋዮችን ግንዛቤ ለማሳደግና የታክስ ህግ ተገዥነትን ለማጠናከር ታስቦ በቀን 11/10/2018 ዓ.ም ስልጠና ተሰጠ። ስልጠናው በዋናነት በታክስ ሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ቁጥር 176/2014 እና በቅርቡ ስራ ላይ በዋለው የኢ-ክሊራንስ (E-clearance) አሰራር ዙሪያ ያተኮረ ነበር። በመድረኩ ላይ ከተለያዩ የንግድ ዘርፎች የተወጣጡ የሴት ከፍተኛ ግብር ከፋዮች፣ የሂሳብ ባለሙያዎችና የድርጅት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። በስልጠናው ግብር ከፋዮች የሂሳብ መዛግብቶቻቸውን ህጋዊ አሰራርን በተከተለና ግልፅ በሆነ መንገድ መያዝ በሚችሉባቸው ነጥቦች ላይ ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቷል። ሁለተኛውና የዕለቱ ዋነኛ አጀንዳ የነበረው የኢ-ክሊራንስ (የታክስ ነፃ መረጃ ዕውቅና ማረጋገጫ) አሰጣጥ አሰራር ነው። ይህ አዲስ ዲጂታል አሰራር ግብር ከፋዮች በአካል ቢሮ ሳይመላለሱ በኦንላይን አማካኝነት ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑ ተብራርቷል። በአሰልጣኙ "የኢ-ክሊራንስ አሰራር የወረቀት ንክኪንና አላስፈላጊ ቢሮክራሲን በማስቀረት የነጋዴውን ማህበረሰብ ጊዜና ወጪ በከፍተኛ ደረጃ እንደሚቀንስ እና ይህ ስልጠናም ደንበኞቻችን አዲሱን የቴክኖሎጂ አሰራር በቀላሉ እንዲለምዱት ለማገዝ መዘጋጀቱን” ገልጸዋል። መጨረሻም የስልጠናው ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት፥ በተለይም በመመሪያ ቁጥር 176/2014 ዙሪያ የነበሩባቸውን ብዥታዎች ለመቅረፍ ስልጠናው ትልቅ እገዛ ማድረጉን ጠቁመዋል። የኢ-ክሊራንስ አሰራርም በቴክኖሎጂ የታገዘ በመሆኑ ስራቸውን እንደሚያቀልላቸው ያላቸውን እምነት ገልጸው፣ መሰል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል። በገቢዎች ቢሮ  የአዲስ አበባ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ ጽ/ቤት የትምህርት እና ስልጠና የሰራ ሂደት  ኃላፊ እና ሥልጠናውን የሰጡት አቶ አስረስ ገቢሳ  በማጠቃለያ ሃሳባቸው  የታክስ አሰባሰብ ስርዓቱን ዘመናዊና ፍትሃዊ ለማድረግ የጀመረውን የቴክኖሎጂ ሽግግርና የግንዛቤ ፈጠራ ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

ለሴት ግብር ከፋዮች በታክስ ሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያና በኢ-ክሊራንስ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ ጽ/ቤት የሴት ግብር ከፋዮችን ግ
+6
ለሴት ግብር ከፋዮች በታክስ ሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያና በኢ-ክሊራንስ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ ጽ/ቤት የሴት ግብር ከፋዮችን ግንዛቤ ለማሳደግና የታክስ ህግ ተገዥነትን ለማጠናከር ታስቦ በቀን 11/10/2018 ዓ.ም ስልጠና ተሰጠ። ስልጠናው በዋናነት በታክስ ሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ቁጥር 176/2014 እና በቅርቡ ስራ ላይ በዋለው የኢ-ክሊራንስ (E-clearance) አሰራር ዙሪያ ያተኮረ ነበር። በመድረኩ ላይ ከተለያዩ የንግድ ዘርፎች የተወጣጡ የሴት ከፍተኛ ግብር ከፋዮች፣ የሂሳብ ባለሙያዎችና የድርጅት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። በስልጠናው ግብር ከፋዮች የሂሳብ መዛግብቶቻቸውን ህጋዊ አሰራርን በተከተለና ግልፅ በሆነ መንገድ መያዝ በሚችሉባቸው ነጥቦች ላይ ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቷል። ሁለተኛውና የዕለቱ ዋነኛ አጀንዳ የነበረው የኢ-ክሊራንስ (የታክስ ነፃ መረጃ ዕውቅና ማረጋገጫ) አሰጣጥ አሰራር ነው። ይህ አዲስ ዲጂታል አሰራር ግብር ከፋዮች በአካል ቢሮ ሳይመላለሱ በኦንላይን አማካኝነት ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑ ተብራርቷል። በአሰልጣኙ "የኢ-ክሊራንስ አሰራር የወረቀት ንክኪንና አላስፈላጊ ቢሮክራሲን በማስቀረት የነጋዴውን ማህበረሰብ ጊዜና ወጪ በከፍተኛ ደረጃ እንደሚቀንስ እና ይህ ስልጠናም ደንበኞቻችን አዲሱን የቴክኖሎጂ አሰራር በቀላሉ እንዲለምዱት ለማገዝ መዘጋጀቱን” ገልጸዋል። መጨረሻም የስልጠናው ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት፥ በተለይም በመመሪያ ቁጥር 176/2014 ዙሪያ የነበሩባቸውን ብዥታዎች ለመቅረፍ ስልጠናው ትልቅ እገዛ ማድረጉን ጠቁመዋል። የኢ-ክሊራንስ አሰራርም በቴክኖሎጂ የታገዘ በመሆኑ ስራቸውን እንደሚያቀልላቸው ያላቸውን እምነት ገልጸው፣ መሰል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች ተጠናክረው እን

ቀን 06/10/2018 ዓ ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮችና ሠራተኞች ከዋናዉ መስሪያ ቤት በተላለፈዉ የቪዲዮ ኮንፈረንስ ላይ በመሳተፍ
+3
ቀን 06/10/2018 ዓ ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮችና ሠራተኞች ከዋናዉ መስሪያ ቤት በተላለፈዉ የቪዲዮ ኮንፈረንስ ላይ በመሳተፍ በገቢ አሰባሰብ አፈጻጸም፣በህግ ማስከበር በመልካም አስተዳደር እና በአገልግሎት አሰጣጥ፣በተቀናጀ አመራር አሰጣጥ እና በየደረጃዉ ሊፈቱ በሚገባቸዉ ችግሮች ላይ ሰፊ ዉይይት አካሄደዋል፡፡ በዉይይቱም በ2018 በጀት ዓመት ባለፉት አስራ አንድ ወራት በተቋሙ በተከናወኑ የገቢ አሰባሰብ፣የህግ ማስከበር ስራዎች፣የአገልግሎት አሰጣጥ እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም እንዲሁም እነዚህ ስራዎች የተመሩበት የተቀናጀ አመራር የተዳሰሰ ሲሆን የእስካሁኑ አፈጻጸም መልካም እንደሆና በቀረዉ ወርም ከዚህ በበለጠ የተያዘዉን ዕቅድ የማሳካት ስራ መሰራት እንደሚገባ ተመላክቷል፡፡ በዉይይት መድረኩ ላይ የቢሮዉ ኃላፊ ገለጻን መነሻ በማድረግ የዉይይቱ ተሳታፊዎች በርካታ ሐሳቦችን ያነሱ ሲሆን በተላይ እንደ አዲስ አበባ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የገቢ አሰባሰብ እንቅስቃሴ፣የህግ ማስከበር ሂደት እና የአገልግሎት አሰጣጥ ሁኔታ የተመራበት የተቀናጀ አመራር እንዲሁም ዘመናዊ የታክስ አሰባሰብ አሰራርን ለማረጋገጥ የተሄደበት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ጥረት የስራ ተነሳሽነትን የሚፈጥር እና አሁንም የታቀደዉን ገቢ ሙሉ በሙሉ ማሳካት እንደሚቻል አቅም ያለ መሆኑ ተነስቷል፡፡ በመጨረሻም የቅ/ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ዑመር አብደላ እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የገቢ ሒሳቦች አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ጥላሁን ግርማ ከተሳታፊዎች ለተነሱት ሐሳቦች ሰፊ ማብራሪያ በመስጠትና በተለይ በቀጣይ ወር በትኩረት መሰራት ያለባቸዉን ስራዎች አቅጣጫ በማስቀመጥ የዕለቱ የዉይይት መድረክ ተጠናቋል፡፡