uz
Feedback
🎓University's

🎓University's

Kanalga Telegram’da o‘tish

ሀገራዊና አለም አቀፍ የዩኒቨርሲቲዎች መረጃዎች እንዳያመልጦ! ‎አስተማማኝ እና እውነተኛ  ዜናዎችን ለማግኘት ዛሬውኑ ተቀላቀሉ#university #ministry of education # Ethiopian university # GATExam #ExitExam

Ko'proq ko'rsatish
937
Obunachilar
-324 soatlar
-137 kunlar
-2830 kunlar
Postlar arxiv
በአዲስ አበባ የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 95.85% ተማሪዎች ማለፋቸውን የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል። በአዲስ አበባ የ2018 ትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂ
በአዲስ አበባ የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 95.85% ተማሪዎች ማለፋቸውን የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል። በአዲስ አበባ የ2018 ትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 95.85% ተማሪዎች 50 እና ከዛ በላይ ውጤት ማስመዝገባቸውን የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ገልጿል። በመዲናዋ የ8ኛ ክፍል ፈተና የወሰዳችሁ ውጤታችሁን ለመመልከት 👇 https://aa.ministry.et/#/result በአዲስ አበባ ከተማ ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም የተሰጠውን ከተማ አቀፍ የ8ኛ ክፍል ፈተና፣ ከ86 ሺህ በላይ ተማሪዎች መውሰዳቸው ይታወሳል።

#ESSLCE የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ተፈታኞች ወደየተመደቡባቸው የመፈተኛ ማዕከላት መግባት ጀምረዋል። የ2018 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና ከነገ ሰኔ 23/2018 ዓ.ም
#ESSLCE የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ተፈታኞች ወደየተመደቡባቸው የመፈተኛ ማዕከላት መግባት ጀምረዋል። የ2018 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና ከነገ ሰኔ 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ በስድስት ዙሮች ይሰጣል። የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም በበይነ መረብ እና በወረቀት የሚሰጥ ሲሆን፤ ፈተናውን ለመውሰድ 563,501 ተፈታኞች መመዝገባቸው ይታወቃል።

ቅሬታችሁን እስከ ሰኔ 23/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ ማቅረብ ትችላላችሁ። - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከመውጫ ፈተና ውጤት ጋር በተያያዘ ቅሬታ ያላችሁ ተፈታኞች፣ ቅሬታችሁን ማቅረብ የም
ቅሬታችሁን እስከ ሰኔ 23/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ ማቅረብ ትችላላችሁ። - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከመውጫ ፈተና ውጤት ጋር በተያያዘ ቅሬታ ያላችሁ ተፈታኞች፣ ቅሬታችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል። ውጤት ያያችሁበትን ሊንክ https://result.ethernet.edu.et/usernamepage በመጠቀም፣ በገፁ ላይ የሚገኘውን "Submit Complaint" የሚለውን አማራጭ በመጫን ቅሬታችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን አገልግሎቱ አስረድቷል። ቅሬታ የማቅረቢያ ጊዜ 👇 ከሰኔ 17-23/2018 ዓ.ም ቅሬታ አቅራቢዎች በአካል ወደ  የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መሔድ ሳይጠበቅባችሁ በኦንላይን ብቻ ቅሬታችሁን እንድታቀርቡ ተብሏል።

ውጤትዎን ይመልከቱ! ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት መታየት ጀምሯል። ውጤትዎን ለማየት 👇 https://result.
ውጤትዎን ይመልከቱ! ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት መታየት ጀምሯል። ውጤትዎን ለማየት 👇 https://result.ethernet.edu.et ሊንኩን ከተጫኑ በኋላ 'Exit Examination' ላይ 'View Results' የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ @universityidea

ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው ሀገር አቀፍ የቅድመ-ምረቃ ትምህርት የመውጫ ፈተና መጠናቀቁን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። የ2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና አኃዛዊ መረጃዎች
ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው ሀገር አቀፍ የቅድመ-ምረቃ ትምህርት የመውጫ ፈተና መጠናቀቁን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።   የ2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና አኃዛዊ መረጃዎች፦   224,234 ➫ ፈተናውን የወሰዱ ተፈታኞች 287 ➫ የቅድመ-ምረቃ የፈተና ዓይነቶች 47 ➫ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የፈተና ዓይነቶች 88 ➫ የፈተና ማዕከላት >5000 ➫ የፈተና አስፈጻሚዎች

#ቅሬታ ትናንት ሰኔ 10/2018 ዓ.ም በተሰጠው የፋርማሲ ትምህርት የመውጫ ፈተና ላይ ስርቆት ተፈፅሟል ሲሉ በርካታ ተፈታኝ ተማሪዎች ቅሬታቸውን እያቀረቡ ነው፡፡ "የፋርማሲ ትምህርት የመውጫ ፈተና
#ቅሬታ ትናንት ሰኔ 10/2018 ዓ.ም በተሰጠው የፋርማሲ ትምህርት የመውጫ ፈተና ላይ ስርቆት ተፈፅሟል ሲሉ በርካታ ተፈታኝ ተማሪዎች ቅሬታቸውን እያቀረቡ ነው፡፡ "የፋርማሲ ትምህርት የመውጫ ፈተና አስቀድሞ ተሰርቋል" ያሉት ቅሬታ አቅራቢ ተማሪዎቹ፤ የሚመለከተው የመንግሥት አካል ማብራሪያ እንዲሰጥም ጠይቀዋል። ለፈተናው ዝግጅት ሲያደርጉ ቢቆዩም፣ ኃላፊነት በማይሰማቸው አካላት አማካኝነት ፈተናው ቀድሞ ወጥቶ መሰራጨቱን የሚያሳዩ መረጃዎች እንደደረሷቸው ቅሬታ አቅራቢ ተማሪዎቹ ገልፀዋል። ይህ መሆኑም በከፍተኛ ጥረትና በራሳቸው ልፋት የተፈተኑ ተማሪዎችን ስነ-ልቦና በእጅጉ የጎዳና ፍትሃዊነትን የጎደለው ተግባር መሆኑን ጠቁመዋል። ጉዳዩ በትምህርት ሚኒስቴር፣ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም በኢትዮጵያ ፋርማሲስቶች ማኅበር በኩል በአስቸኳይ ታይቶ፣ አስፈላጊው ማጣሪያ እንዲደረግና ተገቢው ምላሽ እንዲሰጣቸው ተፈታኞቹ ጠይቀዋል። ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ከተፈታኝ ተማሪዎች የቀረበውን ይህንን ቅሬታ መነሻ በማድረግ፣ በጉዳዩ ላይ ከሚመለከታቸው የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች ማብራሪያ ለማግኘት ያደረገው ሙከራ አልተሳካም። ተጨማሪ ማብራሪያ እንዳገኘን የምናደርሳችሁ ይሆናል። ምስል፦ ተፈታኝ ተማሪዎች ወጥቷበማለት ያጋሩን የመልስ ማውጫ @universityidea

የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች የመውጫ ፈተና (Exit Exam) መሰጠት ጀምሯል፡፡ ፈተናው ከዛሬ ሰኔ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሰባት ቀናት (ቅዳሜ እና እሑድ ሳይጨምር) በኦንላይን ይሰጣል፡፡ ለመጀመ
የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች የመውጫ ፈተና (Exit Exam) መሰጠት ጀምሯል፡፡   ፈተናው ከዛሬ ሰኔ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሰባት ቀናት (ቅዳሜ እና እሑድ ሳይጨምር) በኦንላይን ይሰጣል፡፡   ለመጀመሪያ ጊዜ እና በድጋሜ ለመውጫ ፈተናው የሚቀመጡ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የመንግሥት እና የግል ተፈታኞች ፈተናውን ይወስዳሉ፡፡   ተፈታኞች ስለፈተናው አጠቃላይ ገለጻ ዛሬ ጠዋት የተሰጣቸው ሲሆን፤ በዛሬው የመጀመሪያ ቀን የፈተና ውሎ በጠዋት እና ከሰዓት መርሐግብር (ከ5፡00-7፡00 እና ከ8፡30-11፡00) የ62 ትምህርት አይነት ፈተናዎች እንደሚሰጡ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የወጣው መርሐግብር ያሳያል፡፡   የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ እየተሰጠ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ ምስል፦ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ፣ ወልድያ ዩኒቨርሲቲ እና ወራቤ ዩኒቨርሲቲ

የ2018 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና መርሐግብር (Exit Exam Schedule) የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል። @universityidea

የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት ብሔራዊ ፈተናዎች የጊዜ ሰሌዳ ትምህርት ሚኒስቴር ለተማሪዎች እና ለሚመለከታቸው አካላት ይፋ ባደረገው መርሃ-ግብር መሰረት፦ የማጠናከሪያ (Remedial) ፕሮግራም
የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት ብሔራዊ ፈተናዎች የጊዜ ሰሌዳ ትምህርት ሚኒስቴር ለተማሪዎች እና ለሚመለከታቸው አካላት ይፋ ባደረገው መርሃ-ግብር መሰረት፦ የማጠናከሪያ (Remedial) ፕሮግራም ብሔራዊ ፈተና፦ ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ.ም (May 25 – 28, 2026) ይሰጣል። የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና (Exit Exam)፦ ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም (June 9 – 19, 2026) ይሰጣል። የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና (ESSLCE)፦ ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም (July 1 – 24, 2026) ይሰጣል። የድህረ-ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT)፦ ከነሐሴ 1 እስከ ነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ.ም (August 6 – 7, 2026) ይሰጣል። ለተማሪዎች በሙሉ መልካም የዝግጅት ጊዜ ይሁንላቸው

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚታየውን የተሽከርካሪዎች እጥረት ለመቅረፍ በኪራይ ለመሸፈን መደረጉ ለከፍተኛ የሀብት ብክነትና ለመልካም አስተዳደር ችግር ምክንያት መሆኑ ተገለጸ። መንግሥት ልዩ ት
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚታየውን የተሽከርካሪዎች እጥረት ለመቅረፍ በኪራይ ለመሸፈን መደረጉ ለከፍተኛ የሀብት ብክነትና ለመልካም አስተዳደር ችግር ምክንያት መሆኑ ተገለጸ። መንግሥት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ግዢ ሊፈፀም እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል። በሕ/ተ/ም/ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በተለይ “የአራተኛ ትውልድ ዩኒቨርሲቲዎች ለመኪና ኪራይ ብቻ ከ70-100 ሚሊዮን ብር በዓመት እያወጡ ይገኛሉ” ብለዋል። ይህ የኪራይ ወጪ ለአንድ ዩኒቨርሲቲ መኪና ለመግዛት ከሚያስፈልገው በጀት ጋር የሚቀራረብ ቢሆንም፣ በውጭ ምንዛሬ እጥረት ምክንያት ግዢው ሳይፈጸም ረዥም ጊዜ መቆየቱን አንስተዋል። ለችግሩ መፍትሔ እንዲሰጥ በ2016 ዓ.ም ደብዳቤ መጻፉን አስታውሰዋል። ጉዳዩ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደረጃ አጀንዳ ሆኖ መቅረብ እንዳለበትም አሳስበዋል። 1,265 መኪኖች እንዲገዙ ቢታዘዝም እስካሁን ድረስ እንዳልተገዙ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) አንስተዋል። በሚኒስቴሩ የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው ከአንድ ዓመት በፊት በተደረገ ጥናት መሠረት ዩኒቨርሲቲዎች በዓመት ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ለተሽከርካሪ ኪራይ የሚያወጡ መሆኑን ተናግረዋል። አሁን ላይ በተቋማቱ የሚገኙ መኪኖች 15 ዓመትና በላይ እድሜ የሞላቸው በመሆኑ፣ ለነዳጅና ለጥገና የሚጠይቁት ወጪ እጅግ ከፍተኛና ለሥራ ውጤታማ ያልሆኑ ናቸው ብለዋል። ችግሩን ለመፍታት ምን አይነትና ስንት መኪናዎች መገዛት እንዳለባቸው የሚያሳይ ዝርዝር ጥናት ተጠናቅቆ ለገንዘብ ሚኒስቴር መቅረቡንና ውጤቱንም እየተጠባበቁ መሆኑን ሚኒስትር ዲኤታው ገልፀዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪዎች ወጥ የክፍያ ማዕቀፍ ሊያዘጋጅ ነው፡፡ ማዕቀፉ በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ከፍለው የሚማሩ ተማሪዎች በፈለጉት ሳይሆን፣ ወጥ የክፍያ ሥርዓት ገደብ
ትምህርት ሚኒስቴር በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪዎች ወጥ የክፍያ ማዕቀፍ ሊያዘጋጅ ነው፡፡ ማዕቀፉ በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ከፍለው የሚማሩ ተማሪዎች በፈለጉት ሳይሆን፣ ወጥ የክፍያ ሥርዓት ገደብ ተቀምጦለት እንዲመራ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል። የክፍያ ማዕቀፉ በዋናነት የዩኒቨርሲቲዎች የክፍያ ሥርዓት እንዴት መመራት እንደሚኖርበት የሚጠቁም መሆኑን በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ  ኮራ ጡሹኔ ገልፀዋል፡፡ ማዕቀፉ አንድ ዩኒቨርሲቲ የክፍያ ተመን ሲያወጣ የገበያ ሁኔታ ብቻ አይቶ ሳይሆን፣ የተማሪዎችን የመክፈል አቅምና አካታችነት ማየት እንደሚኖርበት አክለዋል፡፡ በዚህም የተቋማቱን ወቅታዊ የመማር ማስተማር ሁኔታ ያገናዘበ ክፍያ እንዲኖር ማዕቀፉ ያስችላል ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ኮራ ተናግረዋል፡፡ የሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ክፍያ ተመሳሳይ ይሆናል ማለት እንዳልሆነ ስረዱት ሚኒስትር ደኤታው፤ ለአብነትም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ለመማር የሚፈጸም ክፍያ ተመሳሳይ ሊሆን እንደማይችል አስገንዝበዋል፡፡ ማዕቀፉ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎችን ብቻ የሚመለከት እንደሚሆን፣ ይህ ማለት ግን ወደፊት የግል ከፍተኛ ተቋማት ጉዳይ አይታይም ማለት እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡

photo content

#RemedialExam የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ በዩኒቨርሲቲዎች እንደሚሰጥ ይጠበቃል፡፡ በትምህርት ሚኒስቴር የሚሰጠው የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ
+1
#RemedialExam የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ በዩኒቨርሲቲዎች እንደሚሰጥ ይጠበቃል፡፡ በትምህርት ሚኒስቴር የሚሰጠው የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና ደግሞ በግንቦት ወር አጋማሽ እንደሚሆን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተናን አስመልክቶ ያጋራው መርሐግብር ፈተናው በኦንላይን እንደሚሰጥ ጠቁሟል (ምስሉ ከላይ ተያይዟል)፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር እስካሁን የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና መቼ እንደሚሰጥ በይፋ ያወጣው መረጃ የለም፡፡ የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች ከህዳር አጋማሽ ጀምሮ በትምህርት ላይ እንደሚገኙ ይታወቃል።

#ጥቆማ የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ በአቪዬሽን ማኔጅመንትና ኦፐሬሽንስ ዲግሪ ትምህርት (BSc in Aviation Management and Operations) አመልካቾች ምዝገባ እያደረገ ነው። ትም
#ጥቆማ የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ በአቪዬሽን ማኔጅመንትና ኦፐሬሽንስ ዲግሪ ትምህርት (BSc in Aviation Management and Operations) አመልካቾች ምዝገባ እያደረገ ነው። ትምህርቱ ኤርፖርቶችን ለመምራት እና አየር መንገዶችን ለማስተዳደር የሚያስፈልግዎን እውቀትና ክህሎት የሚያገኙበት ነው። ለማመልከት 👉 https://eau.edu.et ለበለጠ መረጃ፦ Email: etauinfo@ethiopianairlines.com | eaainfo@ethiopianairlines.com Phone: +251115174600 / +251115178598 @universityidea

ተራዝሟል! በፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በሁለተኛው ሲሚስቴር ተጨማሪ ተማሪዎችን ለመቀበል ባወጣው ማስታወቂያ ለመማር ተመዝግባችሁ በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ተማሪዎች ሪፖርት አድርጉ
ተራዝሟል! በፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በሁለተኛው ሲሚስቴር ተጨማሪ ተማሪዎችን ለመቀበል ባወጣው ማስታወቂያ ለመማር ተመዝግባችሁ በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ተማሪዎች ሪፖርት አድርጉ ተብሏል። ተመዝግባችሁ የመግቢያ ፈተናውን ለመውሰድ ፈቃደኛ የሆናችሁ ተማሪዎች በተመዘገባችሁበት ሊንክ በመግባት በድጋሜ እንድትመዘገቡ ትምህርት ሚኒስቴር ጠይቋል። በተሰጠው የመመዝገቢያ ጊዜ በርካታ ተማሪዎች ያልተመዘገቡ በመሆናቸው ምዝገባውን መራዘሙን ሚኒስቴሩ አሳውቋል። በመሆኑም ያልተመዘገባችሁ ተማሪዎች እስከ አርብ መጋቢት 25/2018 ዓ.ም ድረስ ምዝገባው የተራዘመ በመሆኑ እንድትመዘገቡ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ፡ 52 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንዲዘጉ ታዘዘ!    የኢትዮጵያ የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን (ETA) በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 52 የግል ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች á‰ áŠ á‹áŒŁáŠ እንዲዘጉ ለክልል መንግስታትና ለጸጥታ አካላት ጥብቅ መመሪያ አስተላልፏል።     ለምን ተዘጉ? እነዚህ ተቋማት እንዲዘጉ የተወሰነባቸው ዋና ዋና ምክንያቶች፦ የፈቃድ መታደስ፦ á‹¨á‰°á‰€áˆ˜áŒ á‹áŠ• የጥራት መስፈርት አሟልተው በድጋሚ ባለመመዝገባቸው። የጥራት ጉድለት፦ á‰ 2017 ዓ.ም (2025 G.C) የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካለፉት ተማሪዎች መካከል 8.4% á‰Ľá‰ť መሆናቸው በትምህርት ጥራት ላይ ከፍተኛ ጥያቄ አስነስቷል። ህጋዊ እውቅና፦ á‰°á‰‹áˆ›á‰ą የመንግስትን የቁጥጥር መመሪያዎች ባለማክበራቸው የነበራቸው የስራ ፈቃድ ተሰርዟል።   ለተማሪዎችና ለወላጆች የተሰጠ ምክር፦ ምዝገባ ከመፈጸምዎ በፊት፦ áˆ›áŠ•áŠ›á‹áˆ ተማሪ ወደ ግል ኮሌጅ ከመግባቱ በፊት የተቋሙ ፈቃድ መታደሱንና ህጋዊ መሆኑን በባለስልጣኑ ድረ-ገጽ ወይም በአካል ማረጋገጥ እንዳለበት ተመክሯል። የተመዘገቡ ተማሪዎች፦ á‰ áŠĽáŠá‹šáˆ… ተቋማት ውስጥ ትምህርት የጀመሩ ተማሪዎች እጣ ፈንታ ምን እንደሚሆን ባለስልጣኑ በቀጣይ ዝርዝር መመሪያ እንደሚሰጥ ይጠበቃል። ምንጭ፦ á‹¨á‰ľáˆáˆ…áˆ­á‰ľáŠ“ ስልጠና ባለስልጣን (ETA) @universityidea

#ETA በትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የተላለፈባቸውን ውሳኔ ተግባራዊ ባላደረጉና በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ተሰማርተው በሚገኙ 52 ተቋማት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ባለሥልጣኑ ጠየቀ፡፡ ባለሥልጣኑ በቀ
+1
#ETA በትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የተላለፈባቸውን ውሳኔ ተግባራዊ ባላደረጉና በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ተሰማርተው በሚገኙ 52 ተቋማት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ባለሥልጣኑ ጠየቀ፡፡ ባለሥልጣኑ በቀን 16/07/2018 ዓ.ም ለሁሉም ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤቶች፣ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት፣ ለድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት፣ ለሁሉም ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮዎች፣ ለሁሉም ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ጽ/ቤቶች እና ከተማ አስተዳደር ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ጽ/ቤቶች እንዲሁም ለሁሉም ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮዎች በጻፈው ደብዳቤ በተቋማቱ ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቋል፡፡ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የዳግም ምዝገባ ስርዓት ውስጥ ባለመግባታቸው ምክንያት ከከፍተኛ ትምህርት ሴክተር እንዲወጡ የታዘዙ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ ተቋማቱ አራት ጊዜ በስልክ እንዲሁም አንድ ጊዜ በአካል ቀርበው እንዲያስረዱ ጥሪ የቀረበላቸው ቢሆንም የሚጠበቅባቸውን መስፈርት እና ሒደት በማሟላት ከትምህርት ሴክተር ያልወጡ መሆኑን ደብዳቤው ያስረዳል፡፡ በመሆኑም "ተቋማቱ የተላለፈውን ውሳኔ ተግባራዊ ባለማድረጋቸው ህጋዊነታቸው የተቋረጠ ሰለሆነ በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ተሰማርተው ዜጎች ላይ ጉዳት እንዳያደርሱ የከፍተኛ ትምህርት አገልግሎት መስጠት እንዲያቆሙ እንድታደርጉ እንዲሁም እስካሁን ያደረሱት ጉዳት ካለ በመፈተሽ አስፈላጊ የህግ እርምት እርምጃ እንዲወሰድባቸው" የተቋማቱን ስም ዝርዝር በማያያዝ ባለሥልጣኑ ጠይቋል፡፡ (የተቋማቱ ስም ዝርዝር ከላይ ተያይዟል፡፡) @universityidea

የትምህርት አብዮት በአዲስ አበባ፦ 12 አዳዲስ መተግበሪያዎች ለተማሪዎች! በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም እየተካሄደ ባለው የኤድቴክ (EdTech) ሳምንት፣ የኢትዮጵያን የትምህርት ስርዓት ወደ ዲጂታል
የትምህርት አብዮት በአዲስ አበባ፦ 12 አዳዲስ መተግበሪያዎች ለተማሪዎች! በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም እየተካሄደ ባለው የኤድቴክ (EdTech) ሳምንት፣ የኢትዮጵያን የትምህርት ስርዓት ወደ ዲጂታል የሚቀይር ትልቅ ስምምነት ዛሬ ተፈርሟል። በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን የሚደገፉ 12 የሀገር በቀል የቴክኖሎጂ ውጤቶች áŠ¨á‰ľáˆáˆ…áˆ­á‰ľ ሚኒስቴር ይፋዊ የጥናት ፖርታል (study.moe.gov.et) ጋር እንዲቀናጁ ተወስኗል።            ተማሪዎች የትምህርት ሚኒስቴር ድረ-ገጽን በመጠቀም እነዚህን 12 ዘመናዊ መተግበሪያዎች በነጻ ማግኘት ይችላሉ።               ትምህርቶች በቪዲዮ፣ በጨዋታ መልክ (Gamification) እና በይነ-ተግባራዊ (Interactive) በሆነ መንገድ የቀረቡ በመሆናቸው ተማሪዎች ሳይሰለቹ እንዲማሩ ይረዳሉ።      áŠ á‰Ľá‹›áŠžá‰š መተግበሪያዎች አንዴ ከተጫኑ በኋላ ያለ ኢንተርኔት መስራት የሚችሉ በመሆናቸው ለገጠሩ የሀገሪቱ ክፍል ትልቅ ተስፋ ሆኗል። የፖሊሲ አውጭዎችና የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ዛሬ ባደረጉት ውይይት፣ ይህ እርምጃ ኢትዮጵያ በ2026 የ12ኛ ክፍል ፈተናን በኦንላይን ለመስጠት ለያዘችው ግብ እንደ ትልቅ ስኬት እንደሚቆጠር ገልጸዋል @universityidea

የአፍሪካ መምህራን ጉባኤ በአዲስ አበባ በስኬት ተጠናቀቀ! ላለፉት ሶስት ቀናት በአፍሪካ ህብረት ዋና መሥሪያ ቤት ሲካሄድ የቆየው አህጉራዊ የመምህራን ልማት ጉባኤ ዛሬ መጋቢት 18/2018 ዓ.ም ተጠ
የአፍሪካ መምህራን ጉባኤ በአዲስ አበባ በስኬት ተጠናቀቀ! ላለፉት ሶስት ቀናት በአፍሪካ ህብረት ዋና መሥሪያ ቤት ሲካሄድ የቆየው አህጉራዊ የመምህራን ልማት ጉባኤ ዛሬ መጋቢት 18/2018 ዓ.ም ተጠናቋል። ጉባኤው በመምህራን ብቃትና ማበረታቻ ዙሪያ አዲስ á‹¨áŠ ááˆŞáŠŤ መምህራን የብቃት ማዕቀፍ (Continental Teachers Qualification Framework) áˆ‹á‹­ መግባባት ላይ ደርሷል። ይህ ማዕቀፍ መምህራን በመላው አፍሪካ እኩል ዕውቅናና ክብር እንዲኖራቸው የሚያስችል የታሪክ ምዕራፍ ነው ተብሏል። ይህ ስምምነት ኢትዮጵያ በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን ለምትጀምረው "የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የግዴታ የማስተማር አገልግሎት" á‹ˆáˆłáŠ ሚና ይኖረዋል። ተማሪዎች የሚያከናውኑት የማስተማር አገልግሎት በአህጉር ደረጃ ዕውቅና ያለው የምስክር ወረቀት እንዲያገኙና በቀጣይ የስራ ዘመናቸው ትልቅ ዋጋ እንዲኖረው ያደርጋል። የአሁኑ ስምምነት የመምህራንን ስነ-ልቦናዊ ዝግጁነት እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ብቃት ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። ምንጭ፦ áŠ ááˆŞáŠŤ ህብረት / የትምህርት ሚኒስቴር @universityidea

የ12ኛ ክፍል ዲጂታል ፈተና ዝግጅት መጠናቀቂያ ገደብ ተቀመጠ! የመሠረተ-ልማት መጠናቀቅ (Infrastructure) ባለከፍተኛ ፍጥነት ኢንተርኔት፦ ፈተናው በሚሰጥባቸው ትምህርት ቤቶች ሁሉ የኢንተርኔ
የ12ኛ ክፍል ዲጂታል ፈተና ዝግጅት መጠናቀቂያ ገደብ ተቀመጠ!             የመሠረተ-ልማት መጠናቀቅ (Infrastructure) ባለከፍተኛ ፍጥነት ኢንተርኔት፦ ፈተናው በሚሰጥባቸው ትምህርት ቤቶች ሁሉ የኢንተርኔት መቆራረጥ እንዳይኖር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመቀናጀት ልዩ መሾመር ተዘርግቷል። ተተኪ የኤሌክትሪክ ኃይል፦ በፈተና ወቅት መብራት ቢጠፋ እንኳ ፈተናው እንዳይቋረጥ እያንዳንዱ የፈተና ማዕከል የራሱ የሆነ ጄነሬተር እንዲኖረው ተደርጓል። የጊዜ ገደብ፦ እነዚህ ዝግጅቶች እስከ መጋቢት 20/2018 ዓ.ም (እሁድ) ድረስ ተጠናቀው ለአገልግሎት ዝግጁ ይሆናሉ።         ለተማሪዎች የቀረበ የልምምድ ጥሪ የሙከራ ፈተና (Mock Exam)፦ ተማሪዎች በትምህርት ቤቶቻቸው የተገጠሙትን ኮምፒውተሮች በመጠቀም በ result.eaes.et በኩል የኦንላይን ፈተናውን ድባብ እንዲለማመዱ ተመክሯል። የዲጂታል ካልኩሌተር አጠቃቀም፦ በወረቀት ፈተና ላይ እንደምንጠቀመው ካልኩሌተር ሳይሆን፣ በስክሪኑ ላይ የሚገኘውን ካልኩሌተር በፍጥነት መጠቀም መለማመድ ጊዜ ለመቆጠብ እጅግ ይረዳል።                የተማሪዎች  የቤት ሾል መሠረተ-ልማቱ ስለተሟላ ብቻ ውጤት አይመጣም። ተማሪዎች አሁን ትኩረት ማድረግ ያለባቸው በቴክኖሎጂው አጠቃቀምና በንባባቸው ላይ ነው።       በተለይ ኮምፒውተርን በመጠቀም ጥያቄዎችን በፍጥነት ማንበብና መመለስን (Digital Reading Habits) ማዳበር ይጠበቅባቸዋል። @universityidea