ru
Feedback
🎓University's

🎓University's

Открыть в Telegram

ሀገራዊና አለም አቀፍ ዚዩኒቚርሲቲዎቜ መሚጃዎቜ እንዳያመልጊ! ‎አስተማማኝ እና እውነተኛ  ዜናዎቜን ለማግኘት ዛሬውኑ ተቀላቀሉ#university #ministry of education # Ethiopian university # GATExam #ExitExam

БПльше
951
ППЎпОсчОкО
-124 часа
-77 ЎМей
-2630 ЎеМь
АрхОв пПстПв
ውጀትዎን ይመልኚቱ! ኹሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም ዹተሰጠው ዹ2018 ዓ.ም ዹኹፍተኛ ትምህርት ዚመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጀት መታዚት ጀምሯል። ውጀትዎን ለማዚት 👇 https://result.
ውጀትዎን ይመልኚቱ! ኹሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም ዹተሰጠው ዹ2018 ዓ.ም ዹኹፍተኛ ትምህርት ዚመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጀት መታዚት ጀምሯል። ውጀትዎን ለማዚት 👇 https://result.ethernet.edu.et ሊንኩን ኚተጫኑ በኋላ 'Exit Examination' ላይ 'View Results' ዹሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጀትዎን ይመልኚቱ @universityidea

ኹሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም ዹተሰጠው ሀገር አቀፍ ዚቅድመ-ምሹቃ ትምህርት ዚመውጫ ፈተና መጠናቀቁን ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት አሳውቋል። ዹ2018 ዓ.ም ዚመውጫ ፈተና አኃዛዊ መሚጃዎቜ
ኹሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም ዹተሰጠው ሀገር አቀፍ ዚቅድመ-ምሹቃ ትምህርት ዚመውጫ ፈተና መጠናቀቁን ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት አሳውቋል።   ዹ2018 ዓ.ም ዚመውጫ ፈተና አኃዛዊ መሚጃዎቜፊ   224,234 ➫ ፈተናውን ዚወሰዱ ተፈታኞቜ 287 ➫ ዚቅድመ-ምሹቃ ዹፈተና ዓይነቶቜ 47 ➫ ዹቮክኒክና ሙያ ስልጠና ዹፈተና ዓይነቶቜ 88 ➫ ዹፈተና ማዕኚላት >5000 ➫ ዹፈተና አስፈጻሚዎቜ

#ቅሬታ ትናንት ሰኔ 10/2018 ዓ.ም በተሰጠው ዚፋርማሲ ትምህርት ዚመውጫ ፈተና ላይ ስርቆት ተፈፅሟል ሲሉ በርካታ ተፈታኝ ተማሪዎቜ ቅሬታ቞ውን እያቀሚቡ ነው፡፡ "ዚፋርማሲ ትምህርት ዚመውጫ ፈተና
#ቅሬታ ትናንት ሰኔ 10/2018 ዓ.ም በተሰጠው ዚፋርማሲ ትምህርት ዚመውጫ ፈተና ላይ ስርቆት ተፈፅሟል ሲሉ በርካታ ተፈታኝ ተማሪዎቜ ቅሬታ቞ውን እያቀሚቡ ነው፡፡ "ዚፋርማሲ ትምህርት ዚመውጫ ፈተና አስቀድሞ ተሰርቋል" ያሉት ቅሬታ አቅራቢ ተማሪዎቹፀ ዹሚመለኹተው ዚመንግሥት አካል ማብራሪያ እንዲሰጥም ጠይቀዋል። ለፈተናው ዝግጅት ሲያደርጉ ቢቆዩም፣ ኃላፊነት በማይሰማቾው አካላት አማካኝነት ፈተናው ቀድሞ ወጥቶ መሰራጚቱን ዚሚያሳዩ መሚጃዎቜ እንደደሚሷ቞ው ቅሬታ አቅራቢ ተማሪዎቹ ገልፀዋል። ይህ መሆኑም በኹፍተኛ ጥሚትና በራሳ቞ው ልፋት ዹተፈተኑ ተማሪዎቜን ስነ-ልቩና በእጅጉ ዚጎዳና ፍትሃዊነትን ዹጎደለው ተግባር መሆኑን ጠቁመዋል። ጉዳዩ በትምህርት ሚኒስ቎ር፣ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት እንዲሁም በኢትዮጵያ ፋርማሲስቶቜ ማኅበር በኩል በአስ቞ኳይ ታይቶ፣ አስፈላጊው ማጣሪያ እንዲደሚግና ተገቢው ምላሜ እንዲሰጣ቞ው ተፈታኞቹ ጠይቀዋል። ቲክቫህ ዩኒቚርሲቲ ኚተፈታኝ ተማሪዎቜ ዹቀሹበውን ይህንን ቅሬታ መነሻ በማድሚግ፣ በጉዳዩ ላይ ኚሚመለኚታ቞ው ዚመንግሥት ሥራ ኃላፊዎቜ ማብራሪያ ለማግኘት ያደሚገው ሙኚራ አልተሳካም። ተጚማሪ ማብራሪያ እንዳገኘን ዚምናደርሳቜሁ ይሆናል። ምስልፊ ተፈታኝ ተማሪዎቜ ወጥቷበማለት ያጋሩን ዚመልስ ማውጫ @universityidea

ዹኹፍተኛ ትምህርት ተማሪዎቜ ዚመውጫ ፈተና (Exit Exam) መሰጠት ጀምሯል፡፡ ፈተናው ኚዛሬ ሰኔ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሰባት ቀናት (ቅዳሜ እና እሑድ ሳይጚምር) በኩንላይን ይሰጣል፡፡ ለመጀመ
ዹኹፍተኛ ትምህርት ተማሪዎቜ ዚመውጫ ፈተና (Exit Exam) መሰጠት ጀምሯል፡፡   ፈተናው ኚዛሬ ሰኔ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሰባት ቀናት (ቅዳሜ እና እሑድ ሳይጚምር) በኩንላይን ይሰጣል፡፡   ለመጀመሪያ ጊዜ እና በድጋሜ ለመውጫ ፈተናው ዚሚቀመጡ በመቶ ሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ዚመንግሥት እና ዹግል ተፈታኞቜ ፈተናውን ይወስዳሉ፡፡   ተፈታኞቜ ስለፈተናው አጠቃላይ ገለጻ ዛሬ ጠዋት ዚተሰጣ቞ው ሲሆንፀ በዛሬው ዚመጀመሪያ ቀን ዹፈተና ውሎ በጠዋት እና ኚሰዓት መርሐግብር (ኹ5፡00-7፡00 እና ኹ8፡30-11፡00) ዹ62 ትምህርት አይነት ፈተናዎቜ እንደሚሰጡ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ዚወጣው መርሐግብር ያሳያል፡፡   ዹኹፍተኛ ትምህርት ዚመውጫ ፈተና ኹ2015 ዓ.ም ጀምሮ እዚተሰጠ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ ምስልፊ ዓዲግራት ዩኒቚርሲቲ፣ ወልድያ ዩኒቚርሲቲ እና ወራቀ ዩኒቚርሲቲ

ዹ2018 ዓ.ም ዚዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ ዚመውጫ ፈተና መርሐግብር (Exit Exam Schedule) ዚቅድመ-ምሹቃ ዚመውጫ ፈተና ኹሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል። @universityidea

ዹ2018 ዓ.ም ዹኹፍተኛ ትምህርት ብሔራዊ ፈተናዎቜ ዹጊዜ ሰሌዳ ትምህርት ሚኒስ቎ር ለተማሪዎቜ እና ለሚመለኚታ቞ው አካላት ይፋ ባደሚገው መርሃ-ግብር መሰሚትፊ ዚማጠናኚሪያ (Remedial) ፕሮግራም
ዹ2018 ዓ.ም ዹኹፍተኛ ትምህርት ብሔራዊ ፈተናዎቜ ዹጊዜ ሰሌዳ ትምህርት ሚኒስ቎ር ለተማሪዎቜ እና ለሚመለኚታ቞ው አካላት ይፋ ባደሚገው መርሃ-ግብር መሰሚትፊ ዚማጠናኚሪያ (Remedial) ፕሮግራም ብሔራዊ ፈተና፩ ኚግንቊት 17 እስኚ ግንቊት 20 ቀን 2018 ዓ.ም (May 25 – 28, 2026) ይሰጣል። ዚመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎቜ ዚመውጫ ፈተና (Exit Exam)ፊ ኹሰኔ 2 እስኚ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም (June 9 – 19, 2026) ይሰጣል። ዹ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና (ESSLCE)ፊ ኹሰኔ 24 እስኚ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም (July 1 – 24, 2026) ይሰጣል። ዚድህሚ-ምሹቃ መግቢያ ፈተና (NGAT)ፊ ኹነሐሮ 1 እስኚ ነሐሮ 2 ቀን 2018 ዓ.ም (August 6 – 7, 2026) ይሰጣል። ለተማሪዎቜ በሙሉ መልካም ዚዝግጅት ጊዜ ይሁንላቾው

በኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ዚሚታዚውን ዚተሜኚርካሪዎቜ እጥሚት ለመቅሹፍ በኪራይ ለመሾፈን መደሹጉ ለኹፍተኛ ዚሀብት ብክነትና ለመልካም አስተዳደር ቜግር ምክንያት መሆኑ ተገለጞ። መንግሥት ልዩ ት
በኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ዚሚታዚውን ዚተሜኚርካሪዎቜ እጥሚት ለመቅሹፍ በኪራይ ለመሾፈን መደሹጉ ለኹፍተኛ ዚሀብት ብክነትና ለመልካም አስተዳደር ቜግር ምክንያት መሆኑ ተገለጞ። መንግሥት ልዩ ትኩሚት ሰጥቶ ግዢ ሊፈፀም እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል። በሕ/ተ/ም/ቀት ዹሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቮክኖሎጂ ጉዳዮቜ ቋሚ ኮሚ቎ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በተለይ “ዚአራተኛ ትውልድ ዩኒቚርሲቲዎቜ ለመኪና ኪራይ ብቻ ኹ70-100 ሚሊዮን ብር በዓመት እያወጡ ይገኛሉ” ብለዋል። ይህ ዚኪራይ ወጪ ለአንድ ዩኒቚርሲቲ መኪና ለመግዛት ኚሚያስፈልገው በጀት ጋር ዚሚቀራሚብ ቢሆንም፣ በውጭ ምንዛሬ እጥሚት ምክንያት ግዢው ሳይፈጞም ሚዥም ጊዜ መቆዚቱን አንስተዋል። ለቜግሩ መፍትሔ እንዲሰጥ በ2016 ዓ.ም ደብዳቀ መጻፉን አስታውሰዋል። ጉዳዩ በሚኒስትሮቜ ምክር ቀት ደሹጃ አጀንዳ ሆኖ መቅሚብ እንዳለበትም አሳስበዋል። 1,265 መኪኖቜ እንዲገዙ ቢታዘዝም እስካሁን ድሚስ እንዳልተገዙ ዚትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) አንስተዋል። በሚኒስ቎ሩ ዹኹፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዲኀታ ኮራ ጡሜኔ በበኩላ቞ው ኚአንድ ዓመት በፊት በተደሹገ ጥናት መሠሚት ዩኒቚርሲቲዎቜ በዓመት ኹ600 ሚሊዮን ብር በላይ ለተሜኚርካሪ ኪራይ ዚሚያወጡ መሆኑን ተናግሚዋል። አሁን ላይ በተቋማቱ ዹሚገኙ መኪኖቜ 15 ዓመትና በላይ እድሜ ዹሞላቾው በመሆኑ፣ ለነዳጅና ለጥገና ዚሚጠይቁት ወጪ እጅግ ኹፍተኛና ለሥራ ውጀታማ ያልሆኑ ናቾው ብለዋል። ቜግሩን ለመፍታት ምን አይነትና ስንት መኪናዎቜ መገዛት እንዳለባ቞ው ዚሚያሳይ ዝርዝር ጥናት ተጠናቅቆ ለገንዘብ ሚኒስ቎ር መቅሚቡንና ውጀቱንም እዚተጠባበቁ መሆኑን ሚኒስትር ዲኀታው ገልፀዋል።

ትምህርት ሚኒስ቎ር በመንግሥት ዩኒቚርሲቲዎቜ ዚተማሪዎቜ ወጥ ዚክፍያ ማዕቀፍ ሊያዘጋጅ ነው፡፡ ማዕቀፉ በመንግሥት ዩኒቚርሲቲዎቜ ኹፍለው ዚሚማሩ ተማሪዎቜ በፈለጉት ሳይሆን፣ ወጥ ዚክፍያ ሥርዓት ገደብ
ትምህርት ሚኒስ቎ር በመንግሥት ዩኒቚርሲቲዎቜ ዚተማሪዎቜ ወጥ ዚክፍያ ማዕቀፍ ሊያዘጋጅ ነው፡፡ ማዕቀፉ በመንግሥት ዩኒቚርሲቲዎቜ ኹፍለው ዚሚማሩ ተማሪዎቜ በፈለጉት ሳይሆን፣ ወጥ ዚክፍያ ሥርዓት ገደብ ተቀምጊለት እንዲመራ ዚሚያስቜል መሆኑ ተገልጿል። ዚክፍያ ማዕቀፉ በዋናነት ዚዩኒቚርሲቲዎቜ ዚክፍያ ሥርዓት እንዎት መመራት እንደሚኖርበት ዹሚጠቁም መሆኑን በትምህርት ሚኒስ቎ር ዹኹፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ደኀታ  ኮራ ጡሹኔ ገልፀዋል፡፡ ማዕቀፉ አንድ ዩኒቚርሲቲ ዚክፍያ ተመን ሲያወጣ ዚገበያ ሁኔታ ብቻ አይቶ ሳይሆን፣ ዚተማሪዎቜን ዹመክፈል አቅምና አካታቜነት ማዚት እንደሚኖርበት አክለዋል፡፡ በዚህም ዚተቋማቱን ወቅታዊ ዹመማር ማስተማር ሁኔታ ያገናዘበ ክፍያ እንዲኖር ማዕቀፉ ያስቜላል ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ኮራ ተናግሚዋል፡፡ ዹሁሉም ዩኒቚርሲቲዎቜ ክፍያ ተመሳሳይ ይሆናል ማለት እንዳልሆነ ስሚዱት ሚኒስትር ደኀታውፀ ለአብነትም በአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ እና በአሶሳ ዩኒቚርሲቲ ለመማር ዹሚፈጾም ክፍያ ተመሳሳይ ሊሆን እንደማይቜል አስገንዝበዋል፡፡ ማዕቀፉ ዚመንግሥት ዩኒቚርሲቲዎቜን ብቻ ዚሚመለኚት እንደሚሆን፣ ይህ ማለት ግን ወደፊት ዹግል ኹፍተኛ ተቋማት ጉዳይ አይታይም ማለት እንዳልሆነ ተናግሚዋል፡፡

photo content

#RemedialExam ዹ2018 ዓ.ም ዚሪሚዲያል ተማሪዎቜ ዚማጠቃለያ ፈተና ኚቀጣይ ሳምንት ጀምሮ በዩኒቚርሲቲዎቜ እንደሚሰጥ ይጠበቃል፡፡ በትምህርት ሚኒስ቎ር ዹሚሰጠው ዚሪሚዲያል ተማሪዎቜ ዚማጠቃለያ
+1
#RemedialExam ዹ2018 ዓ.ም ዚሪሚዲያል ተማሪዎቜ ዚማጠቃለያ ፈተና ኚቀጣይ ሳምንት ጀምሮ በዩኒቚርሲቲዎቜ እንደሚሰጥ ይጠበቃል፡፡ በትምህርት ሚኒስ቎ር ዹሚሰጠው ዚሪሚዲያል ተማሪዎቜ ዚማጠቃለያ ፈተና ደግሞ በግንቊት ወር አጋማሜ እንደሚሆን መሚጃዎቜ ያሳያሉ፡፡ ዋቾሞ ዩኒቚርሲቲ ዚሪሚዲያል ተማሪዎቜ ዚማጠቃለያ ፈተናን አስመልክቶ ያጋራው መርሐግብር ፈተናው በኩንላይን እንደሚሰጥ ጠቁሟል (ምስሉ ኹላይ ተያይዟል)፡፡ ትምህርት ሚኒስ቎ር እስካሁን ዚሪሚዲያል ተማሪዎቜ ዚማጠቃለያ ፈተና መቌ እንደሚሰጥ በይፋ ያወጣው መሹጃ ዚለም፡፡ ዹ2018 ዓ.ም ዚሪሚዲያል ተማሪዎቜ ኚህዳር አጋማሜ ጀምሮ በትምህርት ላይ እንደሚገኙ ይታወቃል።

#ጥቆማ ዚኢትዮጵያ አቪዬሜን ዩኒቚርሲቲ በአቪዬሜን ማኔጅመንትና ኊፐሬሜንስ ዲግሪ ትምህርት (BSc in Aviation Management and Operations) አመልካ቟ቜ ምዝገባ እያደሚገ ነው። ትም
#ጥቆማ ዚኢትዮጵያ አቪዬሜን ዩኒቚርሲቲ በአቪዬሜን ማኔጅመንትና ኊፐሬሜንስ ዲግሪ ትምህርት (BSc in Aviation Management and Operations) አመልካ቟ቜ ምዝገባ እያደሚገ ነው። ትምህርቱ ኀርፖርቶቜን ለመምራት እና አዹር መንገዶቜን ለማስተዳደር ዚሚያስፈልግዎን እውቀትና ክህሎት ዚሚያገኙበት ነው። ለማመልኚት 👉 https://eau.edu.et ለበለጠ መሹጃ፩ Email: etauinfo@ethiopianairlines.com | eaainfo@ethiopianairlines.com Phone: +251115174600 / +251115178598 @universityidea

ተራዝሟል! በፌዎራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደሹጃ ትምህርት ቀቶቜ በሁለተኛው ሲሚስ቎ር ተጚማሪ ተማሪዎቜን ለመቀበል ባወጣው ማስታወቂያ ለመማር ተመዝግባቜሁ በመጠባበቅ ላይ ያላቜሁ ተማሪዎቜ ሪፖርት አድርጉ
ተራዝሟል! በፌዎራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደሹጃ ትምህርት ቀቶቜ በሁለተኛው ሲሚስ቎ር ተጚማሪ ተማሪዎቜን ለመቀበል ባወጣው ማስታወቂያ ለመማር ተመዝግባቜሁ በመጠባበቅ ላይ ያላቜሁ ተማሪዎቜ ሪፖርት አድርጉ ተብሏል። ተመዝግባቜሁ ዚመግቢያ ፈተናውን ለመውሰድ ፈቃደኛ ዚሆናቜሁ ተማሪዎቜ በተመዘገባቜሁበት ሊንክ በመግባት በድጋሜ እንድትመዘገቡ ትምህርት ሚኒስ቎ር ጠይቋል። በተሰጠው ዚመመዝገቢያ ጊዜ በርካታ ተማሪዎቜ ያልተመዘገቡ በመሆናቾው ምዝገባውን መራዘሙን ሚኒስ቎ሩ አሳውቋል። በመሆኑም ያልተመዘገባቜሁ ተማሪዎቜ እስኚ አርብ መጋቢት 25/2018 ዓ.ም ድሚስ ምዝገባው ዚተራዘመ በመሆኑ እንድትመዘገቡ ሚኒስ቎ሩ አሳስቧል።

አስ቞ኳይ ማስጠንቀቂያ፡ 52 ዹግል ኹፍተኛ ዚትምህርት ተቋማት እንዲዘጉ ታዘዘ!    ዚኢትዮጵያ ዚትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን (ETA) በመላ ሀገሪቱ ዹሚገኙ 52 ዹግል ኮሌጆቜና ዩኒቚርሲቲዎቜ á‰ áŠ á‹áŒ£áŠ እንዲዘጉ ለክልል መንግስታትና ለጞጥታ አካላት ጥብቅ መመሪያ አስተላልፏል።     ለምን ተዘጉ? እነዚህ ተቋማት እንዲዘጉ ዚተወሰነባ቞ው ዋና ዋና ምክንያቶቜፊ ዚፈቃድ መታደስፊ á‹šá‰°á‰€áˆ˜áŒ á‹áŠ• ዚጥራት መስፈርት አሟልተው በድጋሚ ባለመመዝገባ቞ው። ዚጥራት ጉድለትፊ á‰ 2017 ዓ.ም (2025 G.C) ዹ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካለፉት ተማሪዎቜ መካኚል 8.4% á‰¥á‰» መሆናቾው በትምህርት ጥራት ላይ ኹፍተኛ ጥያቄ አስነስቷል። ህጋዊ እውቅናፊ á‰°á‰‹áˆ›á‰± ዚመንግስትን ዚቁጥጥር መመሪያዎቜ ባለማክበራ቞ው ዚነበራ቞ው ዚስራ ፈቃድ ተሰርዟል።   ለተማሪዎቜና ለወላጆቜ ዹተሰጠ ምክር፩ ምዝገባ ኹመፈጾምዎ በፊትፊ áˆ›áŠ•áŠ›á‹áˆ ተማሪ ወደ ግል ኮሌጅ ኚመግባቱ በፊት ዹተቋሙ ፈቃድ መታደሱንና ህጋዊ መሆኑን በባለስልጣኑ ድሚ-ገጜ ወይም በአካል ማሚጋገጥ እንዳለበት ተመክሯል። ዚተመዘገቡ ተማሪዎቜፊ á‰ áŠ¥áŠá‹šáˆ… ተቋማት ውስጥ ትምህርት ዚጀመሩ ተማሪዎቜ እጣ ፈንታ ምን እንደሚሆን ባለስልጣኑ በቀጣይ ዝርዝር መመሪያ እንደሚሰጥ ይጠበቃል። ምንጭ፩ á‹šá‰µáˆáˆ…ርትና ስልጠና ባለስልጣን (ETA) @universityidea

#ETA በትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዚተላለፈባ቞ውን ውሳኔ ተግባራዊ ባላደሚጉና በኹፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ተሰማርተው በሚገኙ 52 ተቋማት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ባለሥልጣኑ ጠዚቀ፡፡ ባለሥልጣኑ በቀ
+1
#ETA በትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዚተላለፈባ቞ውን ውሳኔ ተግባራዊ ባላደሚጉና በኹፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ተሰማርተው በሚገኙ 52 ተቋማት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ባለሥልጣኑ ጠዚቀ፡፡ ባለሥልጣኑ በቀን 16/07/2018 ዓ.ም ለሁሉም ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር ጜ/ቀቶቜ፣ ለአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ኚንቲባ ጜ/ቀት፣ ለድሬዳዋ ኹተማ አስተዳደር ኚንቲባ ጜ/ቀት፣ ለሁሉም ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና ኹተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮዎቜ፣ ለሁሉም ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና ኹተማ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሜን ጜ/ቀቶቜ እና ኹተማ አስተዳደር ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሜን ጜ/ቀቶቜ እንዲሁም ለሁሉም ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና ኹተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮዎቜ በጻፈው ደብዳቀ በተቋማቱ ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቋል፡፡ ኹፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ዚዳግም ምዝገባ ስርዓት ውስጥ ባለመግባታ቞ው ምክንያት ኹኹፍተኛ ትምህርት ሮክተር እንዲወጡ ዚታዘዙ መሆናቾው ተገልጿል፡፡ ተቋማቱ አራት ጊዜ በስልክ እንዲሁም አንድ ጊዜ በአካል ቀርበው እንዲያስሚዱ ጥሪ ዹቀሹበላቾው ቢሆንም ዚሚጠበቅባ቞ውን መስፈርት እና ሒደት በማሟላት ኚትምህርት ሮክተር ያልወጡ መሆኑን ደብዳቀው ያስሚዳል፡፡ በመሆኑም "ተቋማቱ ዹተላለፈውን ውሳኔ ተግባራዊ ባለማድሚጋ቞ው ህጋዊነታ቞ው ዹተቋሹጠ ሰለሆነ በኹፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ተሰማርተው ዜጎቜ ላይ ጉዳት እንዳያደርሱ ዹኹፍተኛ ትምህርት አገልግሎት መስጠት እንዲያቆሙ እንድታደርጉ እንዲሁም እስካሁን ያደሚሱት ጉዳት ካለ በመፈተሜ አስፈላጊ ዹህግ እርምት እርምጃ እንዲወሰድባ቞ው" ዚተቋማቱን ስም ዝርዝር በማያያዝ ባለሥልጣኑ ጠይቋል፡፡ (ዚተቋማቱ ስም ዝርዝር ኹላይ ተያይዟል፡፡) @universityidea

ዚትምህርት አብዮት በአዲስ አበባፊ 12 አዳዲስ መተግበሪያዎቜ ለተማሪዎቜ! በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚዹም እዚተካሄደ ባለው ዚኀድ቎ክ (EdTech) ሳምንት፣ ዚኢትዮጵያን ዚትምህርት ስርዓት ወደ ዲጂታል
ዚትምህርት አብዮት በአዲስ አበባፊ 12 አዳዲስ መተግበሪያዎቜ ለተማሪዎቜ! በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚዹም እዚተካሄደ ባለው ዚኀድ቎ክ (EdTech) ሳምንት፣ ዚኢትዮጵያን ዚትምህርት ስርዓት ወደ ዲጂታል ዹሚቀይር ትልቅ ስምምነት ዛሬ ተፈርሟል። በማስተር ካርድ ፋውንዎሜን ዹሚደገፉ 12 ዹሀገር በቀል ዹቮክኖሎጂ ውጀቶቜ áŠšá‰µáˆáˆ…áˆ­á‰µ ሚኒስ቎ር ይፋዊ ዚጥናት ፖርታል (study.moe.gov.et) ጋር እንዲቀናጁ ተወስኗል።            ተማሪዎቜ ዚትምህርት ሚኒስ቎ር ድሚ-ገጜን በመጠቀም እነዚህን 12 ዘመናዊ መተግበሪያዎቜ በነጻ ማግኘት ይቜላሉ።               ትምህርቶቜ በቪዲዮ፣ በጚዋታ መልክ (Gamification) እና በይነ-ተግባራዊ (Interactive) በሆነ መንገድ ዚቀሚቡ በመሆናቾው ተማሪዎቜ ሳይሰለቹ እንዲማሩ ይሚዳሉ።      áŠ á‰¥á‹›áŠžá‰¹ መተግበሪያዎቜ አንዮ ኚተጫኑ በኋላ ያለ ኢንተርኔት መስራት ዚሚቜሉ በመሆናቾው ለገጠሩ ዚሀገሪቱ ክፍል ትልቅ ተስፋ ሆኗል። ዚፖሊሲ አውጭዎቜና ዹቮክኖሎጂ ባለሙያዎቜ ዛሬ ባደሚጉት ውይይት፣ ይህ እርምጃ ኢትዮጵያ በ2026 ዹ12ኛ ክፍል ፈተናን በኩንላይን ለመስጠት ለያዘቜው ግብ እንደ ትልቅ ስኬት እንደሚቆጠር ገልጾዋል @universityidea

ዚአፍሪካ መምህራን ጉባኀ በአዲስ አበባ በስኬት ተጠናቀቀ! ላለፉት ሶስት ቀናት በአፍሪካ ህብሚት ዋና መሥሪያ ቀት ሲካሄድ ዹቆዹው አህጉራዊ ዚመምህራን ልማት ጉባኀ ዛሬ መጋቢት 18/2018 ዓ.ም ተጠ
ዚአፍሪካ መምህራን ጉባኀ በአዲስ አበባ በስኬት ተጠናቀቀ! ላለፉት ሶስት ቀናት በአፍሪካ ህብሚት ዋና መሥሪያ ቀት ሲካሄድ ዹቆዹው አህጉራዊ ዚመምህራን ልማት ጉባኀ ዛሬ መጋቢት 18/2018 ዓ.ም ተጠናቋል። ጉባኀው በመምህራን ብቃትና ማበሚታቻ ዙሪያ አዲስ á‹šáŠ ááˆªáŠ« መምህራን ዚብቃት ማዕቀፍ (Continental Teachers Qualification Framework) áˆ‹á‹­ መግባባት ላይ ደርሷል። ይህ ማዕቀፍ መምህራን በመላው አፍሪካ እኩል ዕውቅናና ክብር እንዲኖራ቞ው ዚሚያስቜል ዚታሪክ ምዕራፍ ነው ተብሏል። ይህ ስምምነት ኢትዮጵያ በሚቀጥለው ዚትምህርት ዘመን ለምትጀምሚው "ዚዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ ዚግዎታ ዚማስተማር አገልግሎት" á‹ˆáˆ³áŠ ሚና ይኖሚዋል። ተማሪዎቜ ዚሚያኚናውኑት ዚማስተማር አገልግሎት በአህጉር ደሹጃ ዕውቅና ያለው ዚምስክር ወሚቀት እንዲያገኙና በቀጣይ ዚስራ ዘመናቾው ትልቅ ዋጋ እንዲኖሚው ያደርጋል። ዹአሁኑ ስምምነት ዚመምህራንን ስነ-ልቩናዊ ዝግጁነት እና ዹቮክኖሎጂ አጠቃቀም ብቃት ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። ምንጭ፩ áŠ ááˆªáŠ« ህብሚት / ዚትምህርት ሚኒስ቎ር @universityidea

ዹ12ኛ ክፍል ዲጂታል ፈተና ዝግጅት መጠናቀቂያ ገደብ ተቀመጠ! ዹመሠሹተ-ልማት መጠናቀቅ (Infrastructure) ባለኚፍተኛ ፍጥነት ኢንተርኔትፊ ፈተናው በሚሰጥባ቞ው ትምህርት ቀቶቜ ሁሉ ዚኢንተርኔ
ዹ12ኛ ክፍል ዲጂታል ፈተና ዝግጅት መጠናቀቂያ ገደብ ተቀመጠ!             ዹመሠሹተ-ልማት መጠናቀቅ (Infrastructure) ባለኚፍተኛ ፍጥነት ኢንተርኔትፊ ፈተናው በሚሰጥባ቞ው ትምህርት ቀቶቜ ሁሉ ዚኢንተርኔት መቆራሚጥ እንዳይኖር ኚኢትዮ ቎ሌኮም ጋር በመቀናጀት ልዩ መስመር ተዘርግቷል። ተተኪ ዚኀሌክትሪክ ኃይል፩ በፈተና ወቅት መብራት ቢጠፋ እንኳ ፈተናው እንዳይቋሚጥ እያንዳንዱ ዹፈተና ማዕኹል ዚራሱ ዹሆነ ጄነሬተር እንዲኖሚው ተደርጓል። ዹጊዜ ገደብፊ እነዚህ ዝግጅቶቜ እስኚ መጋቢት 20/2018 ዓ.ም (እሁድ) ድሚስ ተጠናቀው ለአገልግሎት ዝግጁ ይሆናሉ።         ለተማሪዎቜ ዹቀሹበ ዚልምምድ ጥሪ ዚሙኚራ ፈተና (Mock Exam)ፊ ተማሪዎቜ በትምህርት ቀቶቻ቞ው ዚተገጠሙትን ኮምፒውተሮቜ በመጠቀም በ result.eaes.et በኩል ዹኩንላይን ፈተናውን ድባብ እንዲለማመዱ ተመክሯል። ዚዲጂታል ካልኩሌተር አጠቃቀም፩ በወሚቀት ፈተና ላይ እንደምንጠቀመው ካልኩሌተር ሳይሆን፣ በስክሪኑ ላይ ዹሚገኘውን ካልኩሌተር በፍጥነት መጠቀም መለማመድ ጊዜ ለመቆጠብ እጅግ ይሚዳል።                ዚተማሪዎቜ  ዚቀት ስራ መሠሹተ-ልማቱ ስለተሟላ ብቻ ውጀት አይመጣም። ተማሪዎቜ አሁን ትኩሚት ማድሚግ ያለባ቞ው በቮክኖሎጂው አጠቃቀምና በንባባ቞ው ላይ ነው።       በተለይ ኮምፒውተርን በመጠቀም ጥያቄዎቜን በፍጥነት ማንበብና መመለስን (Digital Reading Habits) ማዳበር ይጠበቅባ቞ዋል። @universityidea

🏆 ዹ2026 ዚኢትዮጵያ ምርጥ 10 ዩኒቚርሲቲዎቜ ዝርዝር ይፋ ሆነ! እንደ QS World University Rankings እና UNIRANKS ዹ2026 ዚቅርብ ጊዜ መሚጃዎቜ መሠሚት፣ ዚኢትዮጵያ ኹፍተ
🏆 ዹ2026 ዚኢትዮጵያ ምርጥ 10 ዩኒቚርሲቲዎቜ ዝርዝር ይፋ ሆነ! እንደ QS World University Rankings áŠ¥áŠ“ UNIRANKS á‹š2026 ዚቅርብ ጊዜ መሚጃዎቜ መሠሚት፣ ዚኢትዮጵያ ኹፍተኛ ዚትምህርት ተቋማት በዓለም አቀፍ ደሹጃ ያላ቞ው ደሹጃ በኹፍተኛ ሁኔታ አሻሜለዋል። ዹደሹጃ ሰንጠሚዡ እንደሚኚተለው ቀርቧል፩ አዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ (AAU)ፊ á‰ áŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« 1ኛ፣ በምስራቅ አፍሪካ á‰€á‹³áˆš áŠ¥áŠ•á‹²áˆáˆ በሰሃራ በታቜ ባሉ አገራት 13ኛ á‹°áˆšáŒƒáŠ• በመያዝ ክብሩን አስጠብቋል። ጅማ ዩኒቚርሲቲ (JU)ፊ á‰ áŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« 2ኛ áˆ²áˆ†áŠ•á£ በምርምር ስራዎቹ ጥራት በአፍሪካ 42ኛ á‹°áˆšáŒƒ ላይ ተቀምጧል። ባህር ዳር ዩኒቚርሲቲ (BDU)ፊ á‰ áŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« 3ኛ á‹°áˆšáŒƒáŠ• ዚያዘ ሲሆን፣ በዲጂታል ትምህርት ዘርፍ ግንባር ቀደም ተጠቃሜ ነው። ጎንደር ዩኒቚርሲቲ (UoG)ፊ á‰ áŒ€áŠ“ ሳይንስ ምርምር ውጀቶቹ በሀገር አቀፍ ደሹጃ 4ኛ áˆ†áŠ—áˆá¢ ሐሮማያ ዩኒቚርሲቲ (HU)ፊ á‰ áŒá‰¥áˆ­áŠ“ ሳይንስ ባለው ታሪካዊ ጥንካሬ 5ኛ á‹°áˆšáŒƒáŠ• ይዟል። መቀሌ ዩኒቚርሲቲ (MU)ፊ á‰ áŠ¢áŠ•áŒ‚áŠáˆªáŠ•áŒáŠ“ ቮክኖሎጂ ዘርፍ ባለው ብቃት 6ኛ á‹°áˆšáŒƒ ላይ ይገኛል። ሀዋሳ ዩኒቚርሲቲ (HU)ፊ á‰ á‰¢á‹áŠáˆµáŠ“ አካባቢ ጥበቃ ትምህርቶቜ 7ኛ á‹°áˆšáŒƒáŠ• ይዟል። አርባ ምንጭ ዩኒቚርሲቲ (AMU)ፊ á‰ á‹áˆƒ ቮክኖሎጂ ዚታወቀው ይህ ዩኒቚርሲቲ 8ኛ á‹°áˆšáŒƒ ላይ ተቀምጧል። አዳማ ሳይንስና ቮክኖሎጂ ዩኒቚርሲቲ (ASTU)ፊ á‰ áŠ¢áŠ–á‰¬áˆœáŠ•áŠ“ ቮክኖሎጂ ውጀቶቹ 9ኛ áˆ†áŠ—áˆá¢ ደብሚ ማርቆስ ዩኒቚርሲቲ (DMU)ፊ á‰ áˆáˆ­áˆáˆ­ ውጀቶቹ እድገት በማሳዚት ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ áˆáˆ­áŒ¥ 10 á‰°á‰€áˆ‹á‰…ሏል። ዚዘንድሮው ደሹጃ አሰጣጥ በዋናነት ትኩሚት ያደሚገው በምርምር ስራዎቜ ጥራት፣ በዲጂታል ዝግጁነት እና በተመራቂዎቜ ዚሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ላይ ነው። @universityidea

አሁኑኑ ይመዝገቡ! ዹ2028 ዓ.ም ዹ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ ነገ መጋቢት 15/2018 ዓ.ም ኹቀኑ 11:30 ላይ ይጠናቀቃል። በተሰጠው ጊዜ ያልተመዘገበ ተማሪ ለፈተናው መቀመጥ አይቜል
አሁኑኑ ይመዝገቡ! ዹ2028 ዓ.ም ዹ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ ነገ መጋቢት 15/2018 ዓ.ም ኹቀኑ 11:30 ላይ ይጠናቀቃል። በተሰጠው ጊዜ ያልተመዘገበ ተማሪ ለፈተናው መቀመጥ አይቜልም። ያልተመዘገበ ተማሪ በቀጣይ ዓመት ዹሚፈተን መሆኑን ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ገልጿል። ለምዝገባ ዚሚያስፈልጉፊ ➫ ኹ9-11 ክፍል ዚተማሩበት ውጀት ➫ አሁን ላይ ዹ12ኛ ክፍል ተማሪ መሆን በድጋሜ ተፈታኝ ኹሆኑ https://register.eaes.et ላይ ኹዚህ በፊት ዚተፈተኑበትን አድሚሜን ካርድ በማስገባትና 750 ብር ክፍያ በመፈጾም መመዝገብ ይቜላሉ። ተፈታኞቜ በመሚጡበት ዹፈተና ማዕኹል መፈተን እንደሚቜሉ ተገልጿል።

ለተመራቂ ተማሪዎቜፊ ኹምሹቃው ባሻገር ያለው ዝግጅትና ዹሀዘን መግለጫ ለምሹቃ ለደሚሳቜሁ ተማሪዎቜ በሙሉፀ ዩኒቚርሲቲዎቜ ኹምሹቃው ስነ-ስርዓት ጎን ለጎን ተማሪዎቜን ለስራ ዓለም ዚሚያዘጋጁ ስራዎቜን
ለተመራቂ ተማሪዎቜፊ ኹምሹቃው ባሻገር ያለው ዝግጅትና ዹሀዘን መግለጫ      ለምሹቃ ለደሚሳቜሁ ተማሪዎቜ በሙሉፀ ዩኒቚርሲቲዎቜ ኹምሹቃው ስነ-ስርዓት ጎን ለጎን ተማሪዎቜን ለስራ ዓለም ዚሚያዘጋጁ ስራዎቜን እያኚናወኑ ይገኛሉ።     ዚስራ ዕድልና ዚክህሎት ዝግጅት (Job Fairs): ባህር ዳርና ሐዋሳ ዩኒቚርሲቲዎቜፊ á‰ áˆáˆšá‰ƒá‹ ዋዜማ ታላላቅ ዹ"ስራ ትርኢት" (Job Fair) በማዘጋጀት ተማሪዎቜን በቀጥታ ኚአሰሪ ድርጅቶቜ ጋር እያገናኙ ነው። ዚሲቪ (CV) ዝግጅት ስልጠናፊ á‰°áˆ˜áˆ«á‰‚ዎቜ ዚሙያ ማመልኚቻ ደብዳቀና ሲቪ እንዎት እንደሚዘጋጅ በዩኒቚርሲቲዎቹ ዚሙያ ማበልጞጊያ ማዕኚላት (Career Centers) በኩል ዚሚሰጡ ስልጠናዎቜን እንዲኚታተሉ ጥሪ ቀርቧል። ይህ ተማሪዎቜ ኹተመሹቁ በኋላ ወዲያውኑ ወደ ስራ እንዲገቡ ትልቅ ድልድይ ይሆናል።       ዹሀዘንና ዚክብር መግለጫ (Gamo Zone Tribute): በደቡብ ኢትዮጵያ በጋሞ ዞን በደሹሰው አሳዛኝ ዚመሬት መንሞራተት አደጋ ምክንያት፣ በክልሉ ዹሚገኙ ዩኒቚርሲቲዎቜ (በተለይም áŠ áˆ­á‰£ ምንጭ ዩኒቚርሲቲ) ዹምሹቃ ስነ-ስርዓታ቞ውን በሀዘን መግለጫና በጞሎት ዚታጀበ እንዲሆን ወስነዋል። በአደጋው ህይወታ቞ውን ያጡ ተማሪዎቜንና ወላጆቜን ለማሰብ በምሹቃው እለት ልዩ ዚዝምታ ጊዜና ዚሻማ ማብራት ስነ-ስርዓት እንደሚካሄድም ታውቋል። ምሹቃ ዚደስታ ብቻ ሳይሆን ዚሀላፊነትም ቀን ነው። ዚስራ ዕድል መሚጃዎቜን በንቃት በመኚታተልና በአደጋው ዚተጎዱ ወገኖቻቜንን በማሰብ ይህን ታሪካዊ ቀን በክብር እንድታሳልፉ እንመክራለን። ለተመራቂዎቜ በሙሉ ብሩህ ዚስራ ዘመን እንዲሆንላቜሁ እንመኛለን    @universityidea