uz
Feedback
Legal Insights Network ⚖

Legal Insights Network ⚖

Kanalga Telegram’da o‘tish

ቻናሉ የተለያዩ ሕጎችን እና የፍ/ቤት ዉሳኔዎችን እንዲሁም አጫጭር የሕግ ማብራሪያዎችን ያጋራል።

Ko'proq ko'rsatish
1 122
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+137 kunlar
+5330 kunlar
Postlar arxiv
+5
መመሪያ_ቁጥር_34_2018_ዓ_ም_በአማራ_ብሄራዊ_ክልላዊ_መንግስት_ትራንስፖርት_እና_ሎጀስቲክስ_ባለስልጣን.pdf1.38 MB

+9
መመሪያ_ቁጥር_22_2018_ዓ_ም_በአማራ_ብሔራዊ_ክልላዊ_መንግሥት_የልማት_ዕቅድ_አዘገጃጀት_መመሪያ.pdf1.03 MB

+9
መመሪያ_ቁጥር_12_2018_ዓ_ም_በአብክመ_የህዝብ_ትራንስፖርት_መናኸሪያ_የውስጥ_ገቢ_አሰባሰብና_አጠቃቀም.pdf3.84 KB

+9
በአብክመ በ2018ዓ/ም የወጡ ልዩ ልዩ መመሪያዎች!!!

ፍርድ ከተፈፀመ በኋላ በፍርዱ መብቴ ተነክቷል የሚል ሰው በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 358 መሠረት ፍርዱን መቃወም የማይችል በመሆኑ አዲስ ክስ ለፍ/ቤት ማቅረብ ይችላል። "አመልካች ክስ ያቀረቡበት አከራካሪ የሆነው ይዞታ አመልካች ተከራካሪ ባልሆኑበት መዝገብ ውሳኔ አግኝቶ አፈፃጸሙ ተጠናቅቆ ተጠሪ ይዞታውን በተረከቡበት ሁኔታ አመልካች በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 358 መሠረት ፍርዱን ሊቃወሙ የሚችሉበት አግባብም አይኖርም፡፡ በመሆኑም ጉዳዩ የቀረበለት የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመልካች አስቀድሞ የተሰጠው ፍርድ መብታቸውን የሚነካው ከሆነ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 358 መሠረት መቃወሚያ ከሚያቀርቡ በቀር አዲስ ክስ ማቅረብ አይችሉም በማለት የሰጠው ወሳኔ የድንጋጌውን ይዘት እና ዓላማ ያላገናዘበ እና መሠረታዊ የሆነ የሕግ ስሕተት የተፈጸመበት ሆኖ አግኝተነዋል፡፡" የሰ/መ/ቁ 210420 https://t.me/insights89

ፍርድ ከተፈፀመ በኋላ በፍርዱ መብቴ ተነክቷል የሚል ሰው በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 358 መሠረት ፍርዱን መቃወም የማይችል በመሆኑ አዲስ ክስ ለፍ/ቤት ማቅረብ ይችላል። "አመልካች ክስ ያቀረቡበት አከራካሪ የሆነው ይዞታ አመልካች ተከራካሪ ባልሆኑበት መዝገብ ውሳኔ አግኝቶ አፈፃጸሙ ተጠናቅቆ ተጠሪ ይዞታውን በተረከቡበት ሁኔታ አመልካች በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 358 መሠረት ፍርዱን ሊቃወሙ የሚችሉበት አግባብም አይኖርም፡፡ በመሆኑም ጉዳዩ የቀረበለት የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመልካች አስቀድሞ የተሰጠው ፍርድ መብታቸውን የሚነካው ከሆነ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 358 መሠረት መቃወሚያ ከሚያቀርቡ በቀር አዲስ ክስ ማቅረብ አይችሉም በማለት የሰጠው ወሳኔ የድንጋጌውን ይዘት እና ዓላማ ያላገናዘበ እና መሠረታዊ የሆነ የሕግ ስሕተት የተፈጸመበት ሆኖ አግኝተነዋል፡፡" የሰበር መ/ቁ 210420 #የTellegram ቻናላችን👇👇👇👇 https://t.me/GetachewandBedrulawoffice በዚህ ገፅ ላይ አስፈላጊ የሆኑ ሕጎችንና የፍ/ቤት ዉሳኔዎችን ያገኛሉ ። በተጨማሪም የሕግ ማብራሪያዎችንና የምክር አገልግሎቶችን ማግኘት ይችላሉ። https://t.me/insights89

Repost from Ethiopian Law
ከሪል እስቴት አልሚዎች አልያም ከግለሰቦች ንብረት ገዝተዋል? ይህ አስቸኳይ ጥሪ ለዕርሶ ነው !!!! ****ከሪል እስቴት አልሚዎች (Real Estate Developers) ወይም ከግለሰቦች ላይ የመኖሪያ ቤት፣ የንግድ ቤት ወይም የጋራ ህንፃ (Apartment) የገዙ ሰዎችን በሙሉ የሚመለከት ነው። ዋና ዓላማው የንብረት ባለቤትነት መብትን በህጋዊ መንገድ ማስከበርና ማስተካከል ነው። ዋና ዋና ዝርዝር ነጥቦች የስም ዝውውር (Title Transfer) ማጠናቀቅ፦ ብዙ ገዢዎች ውል ከተዋዋሉ ወይም ክፍያ ከፈጸሙ በኋላ በይዞታ ማረጋገጫ (ካርታ) ላይ የስም ዝውውር ሳያደርጉ ለረጅም ጊዜ ይቆያሉ። ቢሮው ማንኛውም ገዢ ህጋዊ ባለቤትነቱን ለማረጋገጥ አስቸኳይ የስም ዝውውር መፈጸም እንዳለበት እያሳሰበ ይገኛል። የሰነዶች ህጋዊነት ማረጋገጥ፦ የተገዛው ንብረት የተገነባበት መሬት ህጋዊ ፈቃድ ያለው መሆኑን፣ ከዕገዳ ነፃ መሆኑን እና ከአልሚው ጋር የተደረገው ውል በውልና ማስረጃ (Documents Authentication and Registration Agency) የተመዘገበ መሆኑን ማረጋገጥ ያስፈልጋል። አልሚዎች ላይ የተሰጠ ማሳሰቢያ፦ በሌላ በኩል የሪል እስቴት አልሚዎች የወሰዱትን መሬት በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት አልምተው ማጠናቀቅና ለገዢዎች ማስረከብ እንዳለባቸው፣ ካልሆነ ግን አስተዳደሩ እርምጃ እንደሚወስድ ይገልጻል። ለገዢዎች የሚመከሩ ጥንቃቄዎችና መሟላት ያለባቸው ነገሮች የካርታ ሁኔታን ማረጋገጥ፦ አልሚው ድርጅት ወይም ግለሰቡ ለቦታው ትክክለኛና ህጋዊ ካርታ እንዳለው ማረጋገጥ። የውል ምዝገባ፦ ማንኛውም የቤት ግዢ ስምምነት በከተማው የውልና ማስረጃ ቢሮ ፊት ቀርቦ መፈረምና መጽደቅ አለበት። የመሬት ቢሮ ክትትል፦ ወደ መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ/ክፍለ ከተማ በመሄድ በንብረቱ ላይ ምንም ዓይነት የዕዳ ወይም የፍርድ ቤት ዕገዳ አለመኖሩን ማረጋገጥ።

ሐምሌ 8/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የቀረቡ ስምንት አጀንዳዎች በዝርዝር:- አጀንዳ ቁጥር 1 1. የሀገር ግንባታ 1.1 የማንነት እና የሀገር ባለቤትነት ጉዳዮች 2. ታሪክ እና ማንነት 3. የጋራ ሀገራዊ ማንነት እና እሴቶች (እሴቶችንም የሚመለከቱ ጉዳዮች) 4. ሀገር ግንባታና ብዝሀነት አስተዳደር ጉዳዮች 5. የቋንቋ ጉዳዮች 1.6 የባህል፣ታሪክና ቅርስ ጥበቃ ጉዳዮች እንዲሁም ሌሎችም በርካታ ጉዳዮች አጀንዳ ቁጥር 2 2. የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም የፖለቲካ ስርአት፣የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ስርአት 2.1 የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ 2.1.1 የመንግስት አደረጃጀት፣አስተዳደር ስርአት አይነት 2.1.2 የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት (በቅንፍ ውስጥ ሲቲዝንሺፕ ዜግነት) ህዝባዊ...አንድ 2.1.3 የብሄር ብሄረሰቦች ትርጓሜ (አንቀጽ 39 ንኡስ አንቀጽ 5 ህገ መንግስቱ) 2.1.4 የፌደራል መንግስት እና የክልል መንግስታት መሪዎች የስልጣን ዘመን 2.1.5 የፌደራልና የክልል መንግስታት ግንኙነት። የስልጣን ክፍፍል፣የፌደራልና የክልል መንግስት። የፊሲካል ፌደራሊዝምና የሀብት ክፍፍል 2.1.6 የክልል አስተዳደር እና ወሰኖች፤ የአዳዲስ ክልሎች አመሰራረት። የክልል አስተዳደራዊ ወሰኖች 2.1.7 የህግ አውጪው አካል ወይም ፓርላማ አወቃቀርና ሚና 2.1.8 ህገ መንግስትን የመተርጎም ስልጣን 2.1.9 የህገ መንግስት ማሻሻያ ስርአት (አንቀጽ 104ና 105) 2.2 የፖለቲካ ውክልናና የምርጫ ስርአት ጉዳዮች 2.2.1 የሀገሪቱ የምርጫ ስርአት 2.2.2 የመድብለ ፓርቲ ስርአት 2.2.3 የፖለቲካ ፓርቲ አደረጃጀት 2.2.4 የመንግስትና የገዢ ፓርቲ ሚና መለያየት 2.2.5 የምርጫ ክልሎች አወቃቀር 2.2.6 የፖለቲካ ፓርቲዎች የመንግስት ሀብት አጠቃቀም አጀንዳ ቁጥር 3 3. የፌደራል ከተሞች (አዲስ አበባና ድሬዳዋ) 3.1 የአዲስ አበባ ጉዳይ 3.1.1 የአዲስ አበባ ህጋዊ አቋም። አዲስ አበባ ከኦሮሚያ ክልል ጋር ያለው ግንኙነት የአዲስ አበባ ከተማ የበጀት ድርሻ ጉዳይ 3.1.2 የፌደራል ዋና ከተማ ጉዳይ 3.1.3 የአዲስ አበባ ፖሊስና ፍ/ቤት ጉዳይ 3.1.4 የአዲስ አበባ ወሰንና የቦታዎች ስያሜዎች 3.1.5 የአዲስ አበባ የስራ ቋንቋ 3.1.6 የአዲስ አበባ ታሪካዊ ቅርሶች፣አካታችነት ጉዳይ 3.2 የድሬዳዋ ጉዳይ 3.2.1 የድሬዳዋ ህጋዊ አቋም 3.2.2 የድሬዳዋ የወደፊት አስተዳደራዊ ሁኔታ፣የህዝቦቿ ውክልናና ከኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልሎች ጋር ያላት ግንኙነት 3.2.3 የድሬዳዋ በፌደራል መንግስት ውክልና። ድሬዳዋ በፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚኖራት ውክልና ጉዳይ አጀንዳ ቁጥር 4 4. የሃይማኖት ጉዳዮች፣ታሪካዊ ቅሬታዎች እና እርቅን የሚመለከቱ ጉዳዮች 4.1.1 በሴኪውላሪዝምና በሃይማኖት ነጻነት መካከል ጤናማ ሚዛን መጠበቅ 4.1.2 የሃይማኖት ነጻነትና ገደቦቹ 4.1.3 አናሳ የተከታይ ቁጥር ያላቸው ሃይማኖት ተቋማት ጥበቃ 4.1.4 ከባህል እና ከሃይማኖታዊ እሴቶች ጋር የሚጋጩ ድርጊቶች ጉዳይ 4.2 ታሪካዊ ቅሬታዎችና እርቅን የሚመለከቱ ጉዳዮች 4.2.1 ታሪካዊ መገለል እና ልዩ ተጠቃሚነት 4.2.2 የእርቅና እውቅና የመስጠት ሂደት 4.3 በሃይማኖቶች መካከል ስላለው ግንኙነት እና አብሮ መኖርን በተመለከተ 4.3.1 በሃይማኖቶች መካከል ያሉ ውጥረቶችና መፍትሄዎቻቸው 4.3.2 በሃይማኖቶች መካከል የውይይት እና ምክክር ዘዴዎችን ማጠናከር 4.4 ሃይማኖት በህዝብ ህይወት እና ማህበራዊ ግንኙነቶች ውስጥ ያለውን መስተጋብር በተመለከተ 4.4.1 በህዝብ ተቋማት ውስጥ የሃይማኖት ሚና 4.4.2 የሃይማኖት መድረኮች፣ሚዲያና ህዝባዊ ውይይቶች 4.4.3 የሃይማኖት ተቋማት የድምጽ አጠቃቀም እና የህብረተሰብ መብት አጀንዳ ቁጥር 5 5. የተቋማት ግንባታ፣ የህግ የበላይነትና ሰብአዊ መብቶች 5.1 የሰብአዊ መብቶች 5.1.1 ህገ መንግስታዊ እና ህጋዊ ማእቀፍ ለሰብአዊ መብቶች ጥበቃ 5.1.2 በሀገር ውስጥ የተፈናቀሉ ሰዎች መብቶች 5.1.3 አካል ጉዳት፣ተጋላጭና የተገለሉ ቡድኖች መብቶች 5.1.4 የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ በግጭት እና በጸጥታ ሁኔታዎች ውስጥ 5.1.5 ለሰብአዊ መብት ጥበቃ ተቋማዊ ማእቀፎች የማጠናከር ጉዳይ 5.1.6 በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጉዳይ (ዳያስፖራ)። የጥምር ዜግነት መብት እውቅና እና ሌሎች ጉዳዮች 5.2 የህግ የበላይነት 5.2.1 የህግ የበላይነት (ህጋዊነት) 5.2.2 በህግ ፊት እኩልነት 5.2.3 ተጠያቂነት 5.2.4 የፍትህ ተደራሽነት 5.3 የተቋማት ግንባታ 5.3.1 የዲሞክራሲያዊ ተቋማት ገለልተኝነት፣ ነጻነትና ተደራሽነት 5.3.2 የፍትህ ተቋማት ነጻነትና ተጠያቂነት 5.3.3 የጸጥታና ደህንነት ተቋማት ነጻነት፣ ገለልተኝነትና አደረጃጀት 5.3.4 የሶስቱ የመንግስት አካላት ሚዛን፣ ነጻነት እና ተጠያቂነት 5.3.5 የመገናኛ ብዙሃን ተቋማዊ ገለልተኝነት፣ ነጻነት እና ተጠያቂነት 5.3.6 የሲቪል ማህበራት ነጻነት፣ ሚናና ተጠያቂነት አጀንዳ ቁጥር 6 6. ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች 6.1 ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች 6.1.1 የሴቶች ጉዳይ እና ተያይዘው የቀረቡ ጥያቄዎች 6.1.2 የሀብት አስተዳደር እና ፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል 6.1.3 የመሬት ይዞታና ባለቤትነት 6.1.4. የህዝብ ቆጠራ ውክልና እና አካታች አስተዳደር 6.1.5 ማህበራዊ አገልግሎቶች (ጤና፣ ትምህርትና የኑሮ ደረጃ) 6.1.6 የሰራተኛ መብቶች እና ፍትሀዊ የስራ ሁኔታ 6.1.7 ዘላቂ ልማትና የአካባቢ ጥበቃ። 6.1.8 የተፈጥሮ ሀብት መብቶችና ጥቅም መጋራት 6.1.9 አካታች ኢኮኖሚ፣ኢንቨስትመንት እና ምርታማነት 6.1.10 ማህበራዊ ደህንነትና የስራ እድል 6.2. የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳይ 6.2.1 የአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ተሳትፎና እኩልነት ተጠቃሚነትን የማሳደግ ጉዳይ 6.2.2 የግብርና ግብአቶች ወቅታዊና ፍትሀዊ ተደራሽነትን በተመለከተ። 6.2.3 የህገ መንግስቱ አንቀጽ 40 ንኡስ አንቀጽ 5ና አንቀጽ 41 ንኡስ አንቀጽ 8 ላይ የተጠቀሰውን 'ዘላን' የሚለውን ስያሜ ማስተካከል 6.2.4 ነጻ የገበያ እድልና የገበያ ትስስር መፍጠር 6.2.5 የአርሶ አደርና አርብቶ አደር ማህበረሰቦች የጋራ መልማትና ኢኮኖሚያዊ ድጋፍ 6.2.6 የአርብቶ አደሮች የኑሮ ዘይቤያቸውን ያማከለ የልማት ፖሊሲ አጀንዳ ቁጥር 7 7. ሙስና እና መልካም አስተዳደር 7.1 የመልካም አስተዳደር ችግር እና የሙስና ጉዳዮች። 7.2 የጸረ-ሙስና ስርአት ግንባታ 7.3 የመልካም አስተዳደር ስርአት ግንባታ 7.4 ፍትሀዊ ፓብሊክ ሰርቪስ 7.4.1ፍትሀዊና አካታች ፓብሊክ ሰርቪስ 7.4.2 በብቃት ላይ የተመሰረተ የሰው ሀብት አመዳደብ እና ቅጥር አጀንዳ ቁጥር 8 8. ሰላም ግንባታ 8.1የግጭት መንስኤዎች እና አፈታት መንገዶች ግጭቶችንና መሳሪያ ያነሱ አካላትን በሚመለከቱ 8.3 የዘላቂ ሰላም መሰረቶች 8.4 ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎች እውቅና፣ ማጠናከር እና ዘመናዊ ውህደት 8.4.1 ባህላዊ እውቅና እና ህጋዊ ማእቀፍ 8.4.2 የእርቅና ይቅርታ ጉዳይ 8.4.3 የተኩስ አቁም እና የሰላም ስምምነቶች 8.4.4 የሽግግር ፍትህ 8.5. ሃይማኖት ተቋማት ሚና በሰላም ግንባታ ሂደት ውስጥ ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ/ም

ክስ ቀርቦብኝ ከዚህ ቀደም ጉዳዩ በእርቅ ስምምነት መዝገቡ ተዘግቶ ነበር የሚለው መከራከሪያ በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት ባይነሳም በፍሬ ነገር ክርክር ላይ በእርቅ ስምምነት መዝገቡ ስለመዘጋቱ መከራ
+3
ክስ ቀርቦብኝ ከዚህ ቀደም ጉዳዩ በእርቅ ስምምነት መዝገቡ ተዘግቶ ነበር የሚለው መከራከሪያ በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት ባይነሳም በፍሬ ነገር ክርክር ላይ በእርቅ ስምምነት መዝገቡ ስለመዘጋቱ መከራከሪያ እስከተነሳ ድረስ ፍ/ቤቱ እንደ መጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ወስዶ በቅድሚያ እልባት ሊሰጠው የሚገባ እና ፍ/ቤቱ እንደመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አስቀድሞ ሊመለከተው የሚገባ ስለመሆኑ የፌደራል ሰበር ሰሚ ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 222041 ጥቅምት 15 ቀን 2015 የተሰጠ

የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የተሻሻለው የመንግስት ሠራተኞችን አዋጅ ለመደንገግ የወጣ አዋጅ ቁጥር 309/2018

‎ምክር ቤቱ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶችን ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አፀደቀ ‎ ‎የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሔደው 28ኛ መደበኛ ጉባኤው የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አጽድቋል። ‎ ‎የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ እፀገነት መንግስቱ የፌዴራል የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ በዝርዝር አቅርበዋል። ‎ ‎ረቂቅ አዋጁ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት በአንቀጽ 34 ንዑስ አንቀጽ (5) መሠረት እንዲሁም አንቀጽ 78 (5) መሠረት የግል እና የቤተሰብ የሕግ ጉዳዮችን አስመልክቶ የሚነሱ አለመግባባቶችን በፈቃደኝነት ላይ በተመሰረተ ሁኔታ በሃይማኖታዊ ሕጐች ለመዳኘት የሚያስችል መሆኑን ገልፀዋል። ‎ ‎ሰብሳቢዋ አክለውም፣ ረቂቅ አዋጁ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች እንደ አንድ የሀገራችን የፍትህ አካል የዳኝነት ነጻነታቸው ተጠብቆና ተጠያቂነት የሰፈነበት አሰራር የሚያሰፍን ቀልጣፋና ተደራሽነት ያለው የዳኝነት አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን አንስተዋል። ‎ ‎ረቂቅ አዋጁ ሃይማኖታዊ እሴቶችን የሚያከብር፣ ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግሥት ጋር የማይቃረን እና ረቂቅ አዋጁ የፍርድ ቤቶቹን ተጠሪነት፣ አደረጃጀት እና የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች አስተዳደር ጉባዔን የሚያቋቁም እንደሆነ ጨምረው አንስተዋል። ‎ ‎የምክር ቤት አባላት በበኩላቸው፣ ረቂቅ አዋጁን ለማዳበር የተዘጋጁት መድረኮች አሳታፊ እንደነበሩ አስተያየት ሰጥተዋል። ‎ ‎በመጨረሻም፣ ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጁ ላይ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ፣ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ፣ አዋጅ ቁጥር 1428/2018 አድርጎ በሙሉ ድምፅ አጽድቆታል። ‎ ‎መረጃው የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው።

ከጋብቻ በፊት የነበረ ቤት በትዳር ውስጥ ቢሻሻልም የጋራ ንብረት አይሆንም! የፌዴሬሽን ምክር ቤት በመስከረም 28/2017 ዓ.ም. የሰጠው አስፈላጊ ውሳኔ በቤተሰብ ህግ ውስጥ የነበረን ክርክር ግልጽ አድርጎ አብቅቷል። #አንድ ሰው ከጋብቻ በፊት በግሉ የያዘው ቤት በትዳር ውስጥ #ከፍተኛ_ወጪ ተደርጎ ከታደሰ፣ ከተስፋፋ ወይም እሴቱ በእጅጉ ከጨመረ፣ ያ ቤት የባልና ሚስት የጋራ ንብረት ይሆናልን? የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ. 215860 የሰጠው ውሳኔ፣ "መሰረታዊ የሆነ እድሳት ወይም ከፍተኛ ማሻሻያ ከተደረገ ቤቱ የጋራ ንብረት ሊሆን ይችላል" የሚል አቋም ወስዶ ነበር። የፌዴሬሽን ምክር ቤት ግን ይህ አቋም ሕገ መንግስቱን ይቃረናል በሚል የሕገ መንግስት ትርጉም ተጠይቆ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሰበር ሰሚ ችሎቱን ውሳኔ ሽሮታል። ምክር ቤቱ የሰጠው መርህ ግልጽ ነው፦ "ከጋብቻ በፊት በግል የተያዘ ንብረት፣ በጋብቻ ውስጥ ቢሻሻል፣ ቢስፋፋ ወይም በከፍተኛ ወጪ ቢታደስም የግልነት ባህሪውን አያጣም።" ለምን? ምክንያቱም የንብረቱ መነሻ (source of ownership) የግል ነው። የተደረገው ማሻሻያ በንብረቱ ላይ እሴት ሊጨምር ይችላል፤ ነገር ግን የባለቤትነት ባህሪውን አይቀይርም። ታዲያ በጋራ የወጣው ወጪ ምን ይሆናል? ይህ ውሳኔ ወጪውን ችላ አላለም። ቤቱን ለማስፋፋት፣ ለማሻሻል ወይም ለማደስ ከባልና ሚስት የጋራ ሀብት ወይም ጥረት የወጣ ከሆነ፣ የወጣው ወጪ ተጣርቶ በህግ አግባብ ሊካፈል ይችላል። የውሳኔው ቁም ነገር"የግል ንብረት በማሻሻያ ምክንያት የጋራ ንብረት አይለወጥም፤ ነገር ግን ለማሻሻያው የወጣው የጋራ ወጪ ግን የሂሳብ መብት ይፈጥራል።" ይህ ውሳኔ ከጋብቻ በፊት የነበሩ የግል ንብረቶች በትዳር ውስጥ ስለሚደረግባቸው ማሻሻያ የተነሳ የባለቤትነት መብታቸው እንዳይለወጥ የሚያረጋግጥ ጠቃሚ የሕገ መንግስት ትርጉም ነው። https://t.me/insights89

#የሰራተኞችድምጽ በአማራ ክልል የሚገኙ ዓቃቢያነ ህግ የፌደራል መንግስት ያደረገው ሀገራዊ የደመወዝ ማሻሻያ እስካሁን ተግባራዊ አልተደረገልንም ሲሉ ቅሬታ አቅርበዋል። " በአንድ የፍትህ ሥርአት ውስጥ ለዳኞች የደሞዝ ማሻሻያው ተተግብሮ ለዓቃቢያነ ህግ መቅረቱ አግባብ ያልሆነና በፍትህ ስርዓቱ ላይ ጫና የሚያሳድር ጉዳይ ነው " - የክልሉ ፍትሕ ቢሮ በአማራ ክልል ውስጥ በማገልገል ላይ የሚገኙ ዓቃቢያነ ህግ፣ የፌደራል መንግስት ያደረገው ሀገራዊ የደመወዝ ማሻሻያ እስካሁን ተግባራዊ እንዳልተደረገላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን ገልጸዋል። ዓቃቢያነ ህጉ፥ የ2018 በጀት ዓመት የደመወዝ ማሻሻያ መመሪያ ቁጥር 1110/2018 እነሱንም የሚያካትት ቢሆንም፣ የበጀት ዓመቱ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ብቻ እስኪቀሩት ድረስ ምንም ዓይነት ጭማሪ እንዳልተደረገላቸው ገልጸዋል። የፌደራል ዓቃቢያነ ህግ የማሻሻያው ተጠቃሚ በሆኑበት ሁኔታ፣ የክልሉ ባለሙያዎች ተነጥለው መቅረታቸው አግባብ እንዳልሆነና አሳሳቢ የህልውና ጥያቄ በመሆኑ በአስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ የባለሙያዎቹን ቅሬታ ይዞ የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ዋና ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ጎሽምን በስልክ አነጋግሯል። የክልሉ ፍትህ ቢሮ ዋና ኃላፊ በዝርዝር ምን አሉ ? የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ ሀገራዊ የደሞዝ ጭማሪው ከመታወጁ በፊት በክልሉ የዓቃቢያነ ህግ የደረጃ ማሻሻያ ተደርጎ እንደነበር አንስተዋል። " ከፌደራል የደሞዝ ጭማሪ መጥቷል ሲባል የክልሉ መንግስት ያደረገውን የደረጃ እድገት ማስተካከያን መነሻ ያደረገ ሪፖርት ለፌደራል መንግስት ልከናህ። ይሁን እንጂ ሀገራዊው የደሞዝ ስኬል ማሻሻያ ግን ለክልሉ ዓቃቢያነ ህግ እስካሁን አልተላከም። ለምንድነው እስካሁን ያልመጣው? የሚለው የኛም ጥያቄ ነው። የፌደራል ፍትህ ሚኒስቴሯን ሰብሳቢ ያደረገ ኮሚቴ ተቋቁሟል። የገንዘብ ሚኒስቴር እና ለሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለጉዳዩ መፍትሄ እንዲሰጡም ጥረት እየተደረገ ነው። የዳኞች የደሞዝ ማሻሻያ በቅርቡ በዚህ አንድ ወር ውስጥ ተግባራዊ ተደርጓል። በአንድ የፍትህ ስርዓት ውስጥ ለዳኞች የደሞዝ ማሻሻያው ተተግብሮ ለዓቃቢያነ ህግ መቅረቱ አግባብ ያልሆነና በፍትህ ስርዓቱ ላይ ጫና የሚያሳድር ጉዳይ ነው። የእኛም አቋም ሀገራዊ ጭማሪው ለዓቃቤ ህግም መምጣት አለበት የሚል ነው " ሲሉ ነግረውናል። የዐቃቢያነ ህግ ጥያቄ የደሞዝ ጭማሪው እስከ ውዝፍ ክፍያው ይከፈለን የሚል መሆኑን ለኃላፊው ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሀገራዊ የደሞዝ ማሸሻያው መመሪያ መስከረም ላይ እንደወጣ አስታውሰው እንደ አማራ ክልል ከመስከረም ጀምሮ ውዝፉም አብሮ ይሰጠን የሚል ጥያቄ ለፌደራል መቅረቡን አሳውቀዋል። በመጨረሻም የፌደራል መንግስት ውሳኔውን አሳልፎ በጀቱን ሲለቅ፣ የክልሉ ፍትህ ቢሮ የዚህን በጀት ዓመት ውዝፍ ክፍያ በቀጥታ ለባለሙያዎቹ ተደራሽ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አቶ ብርሃኑ ጠቁመዋል። የጊዜ ጉዳይ እንጂ መፍትሄ ማግኘቱ የማይቀር መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፣ የፍትህ ሚኒስቴር ማኔጅመንትም በትናንትናው እለት በጉዳዩ ላይ ውይይት ማድረጉንና በቀጣይም ከገንዘብ ሚኒስቴር እና ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ጋር የሚደረገውን ንግግር ኮሚቴው አጥብቆ እንደሚከታተለው ተናግረዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

የአብክመ_ቴምብር_ቀረጥ_አዋጅ_ቁጥር_3072018.pdf2.11 MB

መገደብ አይደለም፡፡ የሽያጭ ውሉ ባልተመዘገበበት እና በሌላ ሁኔታ 1ኛ ተጠሪ ስለሽያጭውሉ መደረግ አወኩ ካሉበት ጊዜ በፊት ስለማወቃቸው በአመልካች የቀረበ ክርክር የሌለ ከመሆኑም በላይ 1ኛ ተጠሪ ውሉ አውቀዋል ወይም ማወቅ ነበረባቸው ተብሎ የሚገመተው ውሉ የተመዘገበ ቢሆን ኖሮ ነበር፡፡ ይህ ባልሆነበት ውሉ በተደረገበት በ2 ዓመት ውስጥ ክስ ማቅረብ ነበረባቸው የሚለው የአመልካች ክርክር የቤተሰብ ህጉን አንቀጽ 69 አላማ እና መንፈስ ያላገናዘበ ከመሆኑም በተጨማሪ ከተጋቢዎች አንዱ የሌላኛውን ፍቃድ ሳያገኝ ውል እየተዋዋለ የ2 ዓመት የይርጋ ጊዜ እስኪያልፍ ደብቆ በማቆየት በውሉ ላይ ፍቃደኝነቱን ያልገለጸውን ተዋዋይ ወገን ውሉ እንዲፈርስ የመጠየቅ መብቱን አላግባብ እንዲያጣ የሚያደርግ ነው፡፡ በማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ የሚደረጉ ውሎች በሚመለከተው አካል እስካልተመዘገቡ ድረስ የውል ይፍረስልኝ ክስ ማቅረቢያ የ2 ዓመት የይርጋ ጊዜ መቆጠር መጀመር ያለበት በውሉ ላይ ስምምነቱን ያልሰጠው ተጋቢ የውሉን መደረግ ካወቀበት ጊዜ ጀምሮ ሊሆን ይገባል፡፡ ይህም ማለት በቤተሰብ ህጉ አንቀጽ 69 በማንኛውም ሁኔታ ውሉ ከተደረገበት ጀምሮ በሁለት ዓመት ውስጥ የውል ይፍረስልኝ ክስ መቅረብ አለበት የሚለው ድንዳዴ ተፈጻሚ መሆን ያለበት እንዲፈርስ የሚጠየቀው ውል በሚመለከተው የመንግስት አካል የተመዘገበ ከሆነ ወይም ባይመዘገብ እንኳን በሌላ አግባብ ስለውሉ መደረግ በሚያውቅ ተጋቢ ላይ ሊሆን ይገባል፡፡ በመሆኑም በተያዘው ጉዳይ በቤተሰብ ሕጉ አንቀፅ 69 ላይ የተመለከተው የይርጋ ጊዜ መቆጠር መጀመር ያለበት 1ኛ ተጠሪ ውሉ መደረጉን ካወቁበት ህዳር 23 ቀን 2007 ዓ.ም ጀምሮ መሆን ስለሚገባው እና 1ኛ ተጠሪም የሽያጭ ውሉ መደረጉን ካወቁበት ጀምሮ ክስ እስከ መሰረቱበት ግንቦት 21 ቀን 2007 ዓ.ም 6 ወር ሳይሞላው ክስ የመሰረቱ በመሆኑ በአመልካች እና በ2ኛ ተጠሪ በኩል የተነሳው የይርጋ መከራከሪያ መታለፉ መሰረታዊ የሕግ ስህት የተፈፀመበት አይደለም፡፡ በመቀጠልም የሽያጭ ውሉ እንዲፈርስ የተሰጠውን ውሳኔ አግባብነት ስንመለከት አመልካች አከራካሪውን ቤት ከ1ኛ ተጠሪ ጋር በጋራ ያፈሩት መሆኑን ሳይክዱ ሰኔ 12 ቀን 2002 ዓ.ም በተደረገ የክፍፍል ስምምነት የአመልካች ንብረት እንዲሆን 1ኛ ተጠሪ የተስማሙ በመሆኑ የሽያጭ ውሉ እንዲፈርስ መወሰኑ አግባብ አይደለም በማለት ተከራክረዋል፡፡ ነግር ግን ሰኔ 12 ቀን 2012 ዓ.ም የንብረት ክፍፍል ተደርጎበታል በተባለው ሰነድ ላይ 1ኛ ተጠሪ አለመፈረማቸው እና አመልካች ሰነዱን በሐሰት ያዘጋጁት መሆኑ ተረጋግጦ አመልካች በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት በወ/መ/ቁ 161234 በወንጀል የተቀጡ ሲሆን ይህ የጥፋተኝነት ውሳኔም በፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በይ/መ/ቁ 164836 በተሰጠ ውሳኔ ፀንቷል፡፡ ይህ የወንጀል ውሳኔ በፍትሐብሔር ጉዳዮች ላይ እንዳለ ተቀባይነት ያለው ማስረጃ (Conclusive Evidence) በመሆኑ አመልካች በስር ፍ/በት ፊርማው በፎረንሲክ ሳይመረመርየተሰጠው ውሳኔ ተገቢ አይደለም በማለት የሚያነሱት መከራከሪያ ተቀባይነት የለውም፡፡ በመሆኑም ሰኔ 12 ቀን 2002 ዓ.ም ተደረገ የተባለው የንብረት ክፍፍል ስምምነት በሀሰት የተዘጋጀ በመሆኑ እንዲሁም በሽያጭ ውሉ 1ኛ ተጠሪ ፍቃዳቸውን ያልሰጡ መሆኑ በመረጋገጡ የሽያጭ ውሉ እንዲፈርስ በስር ፍ/ቤቶች የተሰጠው ውሳኔ ላይ የተፈፀመ የሕግ ስህተት የለም፡፡ አመልካች በይዞታው ላይ ከሽያጭ ውሉ በኋላ በ2ኛ ተጠሪ ተጨማሪ ግንባታ መደረጉን በመግለፅ ተዋዋዮችን ወደ ነበርንበት መመለስ አይቻልም፤ ውሉ እንዲፈርስ ሲወሰንም አንደኛው ወገን ያለአግባበብ የሚበለፀግ መሆን አለመሆኑ ከግምት ውስጥ ሳይገባ መወሰኑ ተገቢ አይደለም በማለት የሚከራከሩ ቢሆንም ይህ መከራከሪያ ሊቀርብ የሚገባው በ2ኛ ተጠሪ በመሆኑ እና 2ኛ ተጠሪ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤቱ በሰጠው ውሳኔ ይግባኝ ስለማቅረባቸው ወይም በዚህ ሰበር ሰሚ ችሎት በተደረገው ክርክር መጥሪያ የደረሳቸው ቢሆንም ቀርበው ይህን ገልፀው ያቀረቡት መከራከሪያ እና የመስቀለኛ የሰበር አቤቱታ ስለሌለ የአመልካች ክርክርተቀባይነት የለውም በማለት ተከታዩን ወስነናል፡፡ሰ/መ/ቁጥር 190729 የካቲት 24 ቀን 2013 ዓ/ም https://t.me/insights89

የጋራ የሆነን የማይንቀሳቀስ ንብረት ለመሸጥ ለመለወጥ፣ ለማከራየት፣ በመያዣነት ለመስጠት ወይም በሌላ በማንኛውም ሁኔታ ሌሎች ሰዎች በንብረቱ ላይ መብት እንዲያገኙ ለማድረግ የተጋቢዎቹ የጋራ ስምምነት እንደሚያስፈልግ፤ ከዚህ በተቃራኒ አንደኛው ተጋቢ የውል ግዴታ የገባ እንደሆነ ፍቃዱን ያልሰጠው ተጋቢ ግዴታው መገባቱን ካወቀበት ግዜ ጀምሮ በ6 ወርውሰጥ ወይም በማንኛውም ሁኔታ ግዴታው በተገባ በ2 ዓመት ውስጥ ግዴታው እንዲፈርስ ሊጠይቅ እንደሚችል በፌደራል የቤተሰብ ሕግ አንቀፅ 68(1) እና 69 ላይ ተመላክቷል፡፡ ከክርክሩ ሒደት መገንዘብ እንደቻልነው አከራካሪ የሆነውን ቤት አመልካች እና 1ኛ ተጠሪ እንደ ባልና ሚስት አብረው ሲኖሩ በ1993 ዓ.ም በጋራ የገዙት ሲሆን አመልካችም ይህ ንብረት ከመነሻውም የጋራ ንብረት አይደለም በማለት የሚያቀርቡት መከራከሪያ የለም፡፡ አመልካች አጥብቀው የሚከራከሩት ሰኔ 12 ቀን 2002 ዓ.ም ከተጠሪ ጋር የንብረት ክፍፍል ማድረጋቸውን በዚህም መነሻነት ቤቱ የአመልካች ድርሻ እንዲሆን ተስማምተው የሽያጭ ውሉ ሰኔ 5 ቀን 2003 ዓ.ም ከተደረገ በኋላ በ2007 ዓ.ም ውሉ እንዲፈርስ የቀረበው ክስ በይርጋ ቀሪ ይሆናል በማለት ነው፡፡ 1ኛ ተጠሪ የሽያጭ ውል መኖሩን ያወቁት ጉዳዩን በመጀመሪያ ደረጃ በተመለከተው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በአመልካች ላይ የጋራ ንብረት ክፍፍል ክስ በኮ/መ/ቁ 90444 መስርተው ክርክር ላይ እያሉ ሕዳር 23 ቀን 2007 ዓ.ም 2ኛ ተጠሪ የሽያጭውሉን መሰረት አድርገው በክርክሩ ጣልቃ ለመግባት ካቀረቡት አቤቱታ መሆኑን ገልፀው የሚከራከሩ ሲሆን አመልካችም ሆነ 2ኛ ተጠሪ ይህን በመቃወም ያቀረቡት መከራከሪያ የለም፡፡ ከዚህም ሌላ 1ኛ ተጠሪ የሽያጭ ውለ አለመመዝገቡን ጠቅሰው ክርክር አቅርበዋል፡፡ አመልካችም ሆነ 2ኛ ተጠሪ የሽያጭ ውሉ መመዝገቡን ገልጸው ያቀረቡት መከራከሪያ የለም፡፡ ይልቁኑም 2ኛ ተጠሪ የሽያጭ ውሉ ያልተመዘገበው አመልካች እና 1ኛ ተጠሪ ቤቱን በ1993 ዓ.ም የገዙት ባልተመዘገበ ውል በመሆኑ ከአመልካች ጋር ያደረጉት የሽያጭ ውልም ያለመመዝገቡን ገልፀው ተከራክረዋል፡፡ ይህም የሽያጭ ውሉ በማይንቀሳቀስ ንብረት ላይየተፈፀመ እንደመሆኑ የፍ/ሕ/ቁጥር 1723 በሚደነግገው አግባብ ስልጣን ባለው ሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ ፅ/ቤት አለመመዝገቡን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ እንዲሁም በፍ/ሕ/ቁጥር2878 መሰረት ውሉ ለክርክሩ መሰረት የሆነው ቤት በሚገኝበት አከባቢ በሚገኝ የማይንቀሳቀስ ንብረት መመዝገቢያ የባህር መዝገብ ላይ አለመመዝገቡን ያሳያል፡፡ የማይንቀሳቀስ ንብረትን የሚመለከቱ ውሎች ምዝገባ አላማም በተዋዋዮች መካከል ውሉን የተመለከቱ አከራካሪ ሁኔታዎች ቢነሱ ጉዳዩን በቀላሉ እልባት ለመስጠት ለማስቻል እንዲሁም በንብረቱ ሽያጭ ላይመብት ጠያቂ ሶስተኛ ወገኖች ካሉ ውሉ ስለመደረጉ አውቀው ተገቢውን መፈጸም እንዲችሉ ለማስቻል ነው፡፡ አመልካች እና 2ኛ ተጠሪ ውሉን መዋዋላቸው ባይካካዱም ይሕ የሽያጭ ውል በፍ/ሕ/ቁጥር 1723 እና 2878 መሰረት ስልጣን ባለው አካል ያልተመዘገበ በመሆኑ 1ኛ ተጠሪ በቤቱ ላይ የተደረገውን የሽያጭ ውል አውቀው መቃወሚያ ሊያቀርቡበት የሚችሉበት አግባብ የለም፡፡ በአንፃሩ 1ኛ ተጠሪ ይህ የሽያጭ ውል መኖሩን ያወቁት ህዳር 23 ቀን 2007 ዓ.ም መሆኑ እና ውሉ እንዲፈርስ በፍ/ቤት ክስ የመሰረቱት ግንቦት 21 ቀን 2007 ዓ.ም መሆኑ ተረጋግጧል፡፡ እንደሚታወቀው የይርጋ ድንጋጌዎች አላማ መብቱን የሚጎዳ ነገር መፈጸሙን እያወቀ በመብቱ ሳይሰራ የሚቆይን ከሳሽ ክስ የማቅረብ መብት መገደብ እንጂ መብቱ ስለመነካቱ የማያውቅ ወይም ማወቅ የሚችልበት እድል የሌለውን ከሳሽ ክስ የማቅረብ መብት

ስለመሆኑ ይህ ሰበር ችሎት ከዚህ ቀደም በተለያዩ መዝገቦች ላይ ከሰጠዉ ፍርድ ይዘት መገንዘብ ይቻላል፡፡በዚህ ረገድ በሰበርመ/ቁ/37105 29861:47551:49660 እና ሌሎች ተመሳሳይ ጉዳዮች ላይ የሰጠዉን ዉሳኔ መመልከት ይቻላል፡፡በዚህም ጉዳይ የቼክ ክስ የተመራበት አግባብ ከዚሁ አኳያ መታየት አለበት፡፡ ከላይ እንደተጠቀሰዉ በአጭር ስነስርዓት ክስ የሚቀረብባቸዉ ጉዳዩች በባህይርያቸዉ ተከሳሽ መከራከሪያ ሊያቀርብባቸዉ የማይችል እና በይዘታቸዉ አከራከሪ ያልሆኑ ናቸዉ ብሎ ህጉ ግምት የወሰደባቸዉ ቢሆንም ተከሳሽ ወገን በቂ መከራከሪያና መከላከያ ምክንያቶች እንዳሉት ማሳየት ከቻለ ደግሞ ወደ መደበኛ ክርክር ተገብቶ ጉዳዩ በማስረጃ ነጥሮ እንዲወሰን የማድረግ ሃላፊነት ለፍርድ ቤቱ የተተወ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ስ/ስ/ህግ ቁ/287 289 እና 290 ድንጋጌዎች ይዘት ያስገነዝባል፡፡ ሲጠቃለል ለዚህ አቤቱታ መሰረት የሆነዉ የቼክ ክስ ተጠሪ እንዲከላከል ፍርድ ቤቱ ከፈቀደለበት በኋላ ተጠሪ እንደክርክሩ አቀራረብ ማስረዳት አለማስረዳቱን ሳያረጋገጥ ከሳሽ የሆነዉ አመልካች ቼኩን ያገኘበትን ዉል አላስረዳም በማለት ክሱን ዉድቅ ማድረጉ በቀዳሚነት የማስረዳት ሽክም የማነዉ የሚለዉን ባለመለየት የማስረዳት ሸክም ያለአግባብ ወደ ከሳሽ (አመልካች) ማዞሩን ስለሚያሣይ ክርክሩን የመራበት አግባብ ስህተት ነዉ፡፡

በመሠረቱ ቼክ የተወሰነ ገንዘብ ለመክፈል ሀተታ የሌለበት ትዕዛዝ የያዘና ቼኩም እንደቀረበ የሚከፈል መሆኑ በን/ህ/ቁ. 827/ሀ/ እና 854ሥር የተመለከተ በመሆኑ ቼኩ የታዘዘለት ሰው /አምጪው/ ቼኩን ይዞ እንደቀረበ ሊከፈል ይገባዋል፡፡ቼኩን ይዞ ለቀረበ ሰዉ ክፍያ ካልተፈጸመለት ቼክ አውጪውም ሆነ የጀርባ ፈራሚዎቹ ለቼኩ አከፋፈል ኃላፊዎች ስለመሆናቸው የን/ህ/ቁ.840 እና 868(ሐ) መሰረት ተጠያቂዎች ናቸዉ፡፡ቼክ በባህሪዉ ገንዘብን ተክቶ በቀላሉ ሊተላለፍ የሚችል በመሆኑ የቼክ አከፋፈል ላይ በመርህ ደረጃ መከራከሪያ ሊቀርብ አይችልም፡፡በሌላ ሁኔታ ሕጉ ለይቶ ባስቀመጣቸው ጉዳዮች ካልሆነ የቼክ ክፍያ በማንኛውም ምክንያት ሊቆምና ሊታገድ አይችልም፡፡ነገር ግን የተወሰኑ ሁኔታዎች ባጋጠሙ ጊዜ አውጪው ወይም ፈራሚዎቹ ቼክ ሊከፈል የማይገባበትን መቃወሚያ ያነሱ ይችላሉ፡፡በመሆኑም አግባብነት ያላቸው የንግድ ህግ ድንጋጌዎች በመቃወሚያነት እንዲቀርቡ የፈቀዷዋቸውን እና የከለከለዋቸውን ጉዳዮች በመለየት ይህ ሰበር ችሎት በሰበር መ/ቁ/24435 እና ሌሎችም መዝገቦች አስገዳጅነት ያለዉ የህግ ትርጉም የሰጠበት ጉዳይ ነዉ፡፡ በተጠቃሹ የሰበር መዝገብ እና ሌሎችም መዝገቦች ላይ በተሰጠዉ ፍርድ እንደተገለጸዉ በቼክ ላይየሚቀርቡት መቃወሚያዎች ሁለት ገጽታ ያላቸዉ መሆናቸዉን ያሣያል፡፡ በአንድ በኩል ማንኛውም በቼክ የተከሰሰ ሰው ሊያነሳቸው የሚችል፣ አምጪውም ቢሆን እነዚህ መቃወሚያዎች አንተን የሚመለከቱ አይደሉም ሊል የማይችልባቸው በመሆናቸው ሰነዱን ተከትለው የሚሄድ በሌሎች የሕግ ሥርዓቶች እና የሕግ ጽንሰ ሃሣብ /real defense/ በመባል የሚታወቁ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ሰነዱ ይመለከታቸዋል ከሚባሉ ሰዎች መካከል የተወሰኑ ሰዎች ብቻ ካልሆኑ በቀር ሌሎቹ እንዲያነሱዋቸው የማይፈቀድ ብ ሕግ ሳይንስ እና ብ ሌሎች የ ሕግ ስርዓቶች /Personal defense /in personal defense/በመባል የሚታወቁ መቃወሚያዎች ናቸው፡፡መቃወሚያዎችን /defense/ ብቻ ሳይሆን መብቶችን Personal እና Real ወይም rights in personal እና rights in rem/ ብሎ መከፋፈል በሁለም የሕግ ሥርዓቶች ያለ በኛም የሕግ ሥርዓት በተለያዩ ሁኔታዎች የተካተተ መሆኑን የሚያሳይ ነዉ፡፡በንግድ ህጉ በተለይም በአንቀጽ 717፣ 752 እንዲሁም 850 ላይ የተደነገገው እና የግል ግንኙነትን የሚመለከተው መቃወሚያ ሊታይ የሚገባው ከዚህ አንፃር እንደሆነ ያስገነዝባል፡፡ስለዚህም ቼክ አምጪ በፍ/ብ/ስ/ስ/ህግ ቁጥር 284 መሰረት በማድረግ በቼክ የተመለከተዉ ገንዘብ ክፍያ እንዲወሰንለት ሲጠይቅ በቼኩ ላይ የተመለከተዉ ገንዘብ የማይከፈልበትን ምክንያት የማስረዳት ሸክም የተከሳሹ መሆኑን ያስገነዝባል፡፡በዚህ ረገድ ሰበር ችሎቱ በተለያዩ መዝገቦች በሰጠዉ ዉሳኔ እንዳመለካተዉ ተከሳሽ የሆነ ወገን መቃወሚያዉን በማቅረብ በቼኩ ክፍያ የማይገደድ ስለመሆኑ ህጋዊ ምክንያቶችን አቅርቦ ማስረዳት የሚጠበቅበት መሆኑን አስገዳጅ ትርጉም ሰጥቶበታል፡፡ ሰበርመ/ቁ/24435፣170068፣213749 እና ሌሎች መሰል መዝገቦችን ይመለከታል፡፡ በመሆኑም በቼክ ክስ ላይተከሳሹ የመከላከያ ክርክሩን ሳያሰረዳ ከሳሹ ወገን ለቼኩ መዉጣት ምክንያት የሆነዉን ግንኙነት የማስረዳት ግዴታ በህግ አልተጣለበትም ማለት ነዉ፡፡ በተያዘዉ ጉዳይ ተጠሪ ክስ የቀረበበትን ቼክ ለአመልካች መስጠቱን አልካደም፡፡ይልቁንም ቼኩን መስጠቱን በግልጽ አምኖ ቼኩን የሰጠሁት ለመተማመኛ ነዉ በማለት መከራከሩን ያሣያል፡፡ ከዚህም መገንዘብ የሚቻለዉ ተጠሪ በቼኩ (ሰነዱ) ሀጋዊነት ላይ /real defense/ መከራከሪያ ያላቀረበ መሆኑን ይልቁንም ለቼኩ መዉጣት ምክንያት ነዉ የሚለዉን የግል ግንኙነትን መሰረት በማድረግ ክፍያ እንደማይገደድ የተከራከረ መሆኑን የሚያሳይ ነዉ፡፡ይህ ከሆነ ደግሞ ቼኩ ክፍያ የማይፈጸምበትን ህጋዊ ምክንያት ስለመኖሩ በቀዳሚነት የማስረዳት ሸክም (ግዴታ) የተጠሪ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ከዚህ አኳያ ሲታይ ፍርድ ቤቱ በቀዳሚነት መመርመር የሚገባዉ ጉዳይ ተጠሪ ለቼኩ መዉጣት ምክንያት ነዉ ያለዉንና ክፍያ የማይፈጸምበት ምክንያት መኖር አለመኖሩን በተገቢዉ ማስረጃ ማስረዳት መቻል አለመቻሉን መለየት ነዉ፡፡ተጠሪ እንደክርክሩ አቀራርብ ማስረዳቱ ሳይረጋገጥ አመልካች ለቼኩ መዉጣት ምክንያት የሚለዉን ዉል መኖሩን አላስረዳም የሚለዉ የስር ፍርድ ቤት ድምዳሜ የማስረዳት ሽክምን ያለአግባብ ወደ ከሳሽ ያዞረ መሆኑን ያስገነዝባል፡፡ከዚህ አኳያ ፍርድ ቤቱ ክርክሩን የመራበት እና የደረሰበት ድምዳሜ ላይ የተፈጸመ መሰረታዊ ስህተት መኖር አለመኖሩን መመርመር ተገቢ ነዉ፡፡ የሰበር ችሎቱ ስልጣን የመጨረሻ ዉሳኔ በተሰጠባቸዉ ጉዳዮች ላይ መሰረታዊ የህግ ስህተት ተፈጽሞ ሲገኝ ይህንኑ በማረም ላይ የተገደበ መሆኑን ከሰበር ስርዓት መሰረታዊ ዓላማ የምንገነዘበዉ ጉዳይ ነዉ፡ የኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 80/3/ሀ ይዘትና መንፈስ ይህንኑ የሚያመለከት ሲሆን ቀደም ሲል ሰበር ችሎቱ በተለያዩ መዝገቦች መሰረታዊ የህግ ስህተት ምንነት አመላካች ዉሳኔዎች መስጠቱ የሚታወቅ ሲሆን ጥር 13 ቀን 2013ዓ.ም የጸደቀዉ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 በሰበር ሊታረም የሚገባ መሰረታዊ የህግ ስህተት ማለት ምን ማለት ነዉ ወይም የመጨረሻ ዉሳኔ ላይመሰረታዊ ህግ ስሀተት ተፈጽሟል የሚያሰኙት ሁኔታዎች ምንድናቸዉ ለሚለዉ ትርጉም ሰጥቷል (አንቀጽ2/4/ይመለከታል)፡፡በአዋጁ አንቀጽ 4 ስር እንደተዘረዘረዉ በሰበር ችሎቱ ሊታይ የሚችል የመጨረሻ ዉሳኔ፣ ፍርድ፡ ብይን ወይም ትእዛዝ ላይ የህገ መንግስቱን ድንጋጌዎች የሚቃረን፣ ህግን አለ አግባብ የሚተረጉም ወይም ለጉዳዩ አግባብነት የሌለዉን ህግ የሚጠቅስ፤ለክርክሩ አግባብነት ያለዉ ጭብጥ ሳይያዝ ወይም ከክርክሩ ጋር የማይዛመድ አግባብነት የሌለዉ ጭብጥ ተይዞ የተወሰነ፣ በዳኝነት ታይቶ ሊወሰን የሚገባዉን ጉዳይ ዉድቅ በማድረግ የተወሰነ፣ በፍርድ አፈጻጸም ሂደት ከዋና ፍርድ ጋር የማይገናኝ ትእዛዝ የተሰጠበት፡ጉዳዩን አይቶ የመወሰን የዳኝነት ስልጣን ሳይኖር የተወሰነ የአስተዳደር አካል ወይም ተቋም ከህግ ዉጭ የሰጠዉ ዉሳኔ ወይም የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎትን አስገዳጅ ዉሳኔ በመቃረን የተወሰነ ዉሳኔ ጉዳይ ስለመሆኑ ተደንግጓል፡፡እነዚህኑ ልዩ ሁኔታዎች ማለትም በአዋጁ አንቀጽ 10(1/ሐ) ላይ የተመለከቱትን ድንጋጌዎች ከግምት ዉስጥ የማስገባት ኃላፊነት ይኖርበታል፡፡ ይሁንና በክርክር አመራር፣ጭብጥ አመሰራረት እንዲሁም በማስረጃ አቀባበል እና ምዘና ረገድ የተፈጸመ ስህተት ካለ ሰበር ችሎቱ ሊያርም እንደሚችል በተለያዩ መዝገቦች አሰገዳጅ ዉሳኔ የተሰጠበት መሆኑን ልብ ይለዋል፡፡በፍርዱ ላይ የክርክር አመራር ወይም የማስረጃ አቀባበልና ምዘና ስህተት ተፈጽሟል ለማለት የሚቻለዉ ተገቢዉ ጭብጥ ሳይያዝ ወይም በተከራካሪ ወገኖች የተቆጠረ ማስረጃ ያለበቂ ምክንያት ሳይሰማ ሲታለፍ በማስረጃ አቀባበል ረገድ የተከራካሪ ወገኖች እኩል የመደመጥ መብት አለማከበር፣የማስረዳት ሸክም የማነዉ የሚለዉን አለመለየት ወይም የማስረጃ ተገቢነት /relevancey/: ተቀባይነት /admissibillity/ እና ክብደት ምዘና ረገድ /weight of evidence/ አግባብነት ያለዉን መርህ ባለመከተል እንዲሁም በመሰረታዊ ህግ ወይም በስነስርዓት እና ማስረጃ ደንብ ቅቡልነት ያላቸዉን የማስረጃ ህግ መርሆዎችን ባለመጠበቅ የሚሰጡ ዉሳኔዎችን የሚያጠቃልል

ተጠሪ በአዲስ አበባ ከተማ በኮዬ ፈጬ ሳይት ቁጥር አንድ ፣ ብሎክ 194 ፣ የቤት ቁጥር 09 1ኛ ፎቅ በአመልካች ስም ተመዝግቦ የሚገኝ ባለአንድ መኝታ ኮንዶሚኒየም ቤት የግራቀኙ የጋራ ሀብት በመሆኑ እኩል ሊካፈል ይገባል በማለት ላቀረቡት ክስ አመልች በሰጡት መልስ ለኮንዶሚኒየም ቤት የተመዘገቡት ከግራቀኙ ጋብቻ በፊት በ1997 ዓ/ም መሆኑን ፣ ዕጣው የደረሳቸው ህዳር 27 ቀን 2011 ዓ/ም ሆኖ እቅደመ ክፍያም የፈፀሙት ተጠሪ ታህሳስ 2 ቀን 2013 ዓ/ም ጥሏቸው ከቤት ከወጡ በኋላ ጥር 1 ቀን 2013 ዓ/ም በመሆኑ ተጠሪ ቤቱን ሊካፈሉ አይገባም በማለት ተከራክረዋል፡፡ አመልካች ለኮኒዶሚኒየም የተመዘገቡት በ1997 ዓ/ም መሆኑ ፤ ከቤቶች ኤጀንሲ ጋር ውል የፈፀሙት ህዳር 08 ቀን 2013 ዓ/ም መሆኑ እንዲሁም ግራቀኙ በጋብቻ ውስጥ የቆዩት ከሐምሌ 08 ቀን 2011 ዓ/ም እስከ ሰኔ 25 ቀን 2013 ዓ/ም መሆኑ በፍሬ ነገር ደረጃ የተረጋገጠ ሲሆን ፤ የግራቀኙ ጋብቻ ፀንቶ ባለበት አመልካች ታህሳስ 2 ቀን 2013 ዓ/ም ቅደመ ክፍያ ሲፈፅሙ የተጠሪ ከቤት ወጥቶ መሄድ በኮኒዶሚኒየም ቤቱ ላይ ድርሻ እንዳይኖራቸው የሚያደርግ አይደለም፡፡ ምንም እንኳን አመልካች የኮኒዶሚኒየም ቤቱን ለመግዛት የሚስችላቸው ዕጣ ከግራቀኙ ጋብቻ በፊት ህዳር 27 ቀን 2011 ዓ/ም የወጣ ቢሆንም ፤ የአመልካች እና ተጠሪ ጋብቻ ከሐምሌ 08 ቀን 2011 ዓ/ም እስከ ሰኔ 25 ቀን 2013 ዓ/ም ድረስ የዘለቀ በመሆኑ ፧ ታህሳስ 2 ቀን 2013 ዓ/ም ቅደመ ክፍያ ሲከፈል እንዲሁም ህዳር 08 ቀን 2013 ዓ/ም ቤቱ ያተገኘበት የሽያጭ ውል አመልካች ከቤቶች ኤጀንሲ ጋርሲፈፅሙ ግራቀኙ በጋብቻ ውስጥ ስላሉ የቤቱ የባለቤትነት መብት ከቤቶች ኤጀንሲ በሽያጭ ውል በፍትሐ ብሔር ሕጉ ቁጥር 1184 እና 2875 መሠረት ተላልፎ ፤ በፍትሐ ብሔር ሕጉ ቁጥር 1204 መሠረት የኮኒዶሚኒየም ቤቱ የባለሀብትነት መብት የሚያስገኘው የሽያጭ ውል በጋብቻ ውስጥ ስለተደረገ የኮኒዶሚኒየም ቤቱ በግብይት ተገኘ ሊባል የሚችለው የአመልካች እና ተጠሪ ጋብቻ ፀንቶ ባለበት ወቅት በመሆኑ የሽያጭ ውሉን አመልካች ለብቻቸው መፈረማቸው ፣ የኮኒዶሚኒየም ቤት ለማግኘት አመልካች ከትዳር በፊት በ1997 ዓ/ም መመዝገባቸው እና ዕጣው ከጋብቻ በፊት መውጣቱ ኮኒዶሚኒየም ቤቱን የአመልካች የግል ንብረት የሚያሰኝ ባለመሆኑ ፤ በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር 213/1992 አንቀጽ 62(2) ድንጋጌ መሠረት በትዳር ውስጥ በግብይት የተገኘው ኮኒዶሚኒየም ቤት የአመልካች እና የተጠሪ የጋራ ሀብት በመሆኑ ከዚህ አንፃር የሥር ፍርድ ቤት ውሳኔ የሚነቀፍ ሆኖ አልተገኘም፡፡ አመልካች ከተጠሪ ጋር ትዳር ሳይመሰርቱ በ1997 ዓ/ም የኮኒዶሚኒየም ቤት ለማግኘት ተመዝግበው ሲቆጥቡ በመቆየታቸው የዕጣው ተጠቃሚ ለመሆን ዕድል ያገኙ ከመሆኑ አንፃር አመልካች ከተጠሪ ጋርጋብቻ እስከመሰረቱበት ከሐምሌ 08 ቀን 2011 ዓ/ም ድረስ ለብቻቸው የኮኒዶሚኒየም ቤቱን ለማግኘት የቆጠቡት ገንዘብ ተጣርቶ ተጠሪ ግማሹን ለአመልካች እንዲከፍሉ አለመወሰኑ እንዲሁም የኮኒዶሚኒየም ቤቱ በባንክ ብድር የተገዛ በመሆኑ ዕዳው የግራቀኙ የጋራ ነው ተብሎ አለመወሰኑ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ነው :: የሰበር መዝገብ ቁጥር 219471 ሐምሌ 27 ቀን 2014 ዓ/ም https://t.me/insights89

#Lon_Fuller እና ''The Morality of Law'' (የሕግ የሥነ-ምግባር መሠረት) ፉለር በህግ ፍልስፍና አለም ውስጥ “ተፈጥሯዊ የህግ አምላኪ” (Natural Lawyer) ተብሎ ይመደባል፤ ነገር ግን የእሱ አቀራረብ ከቀደሙት የሃይማኖት ወይም የሞራል ምሁራን የተለየ ነው። እሱ የሚያተኩረው በህጉ ይዘት (Substance) ላይ ሳይሆን ህጉ በሚወጣበትና ስራ ላይ በሚውልበት ሂደትና ቅርፅ (Procedure) ላይ ነው። ይህንን ነው “ውስጣዊ ግብረገብነት” የሚለው። ህግጋት ፍትሃዊ፣ ግልጽ እና ሊተገበሩ የሚችሉ ካልሆኑ የህግነት ባህሪያቸውን ያጣሉ። ፉለር ይህንን ሃሳብ ለማስረዳት (King Rex) የተባለውን ምናባዊ ንጉስ ታሪክ እንደ ምሳሌ ያነሳል። ንጉስ ሬክስ ፍጹም መልካም ፍላጎት ቢኖረውም፣ በስምንት ተከታታይ ስህተቶች ምክንያት የተሳካ የህግ ስርዓት መገንባት ሳይችል ቀርቷል። ➨The Eight Principles of Legality አንድ የህግ ስርዓት ህጋዊ ክብርና የሞራል ግዴታን ለመፍጠር ማሟላት ያለበት ስምንት ውስጣዊ መመዘኛዎች አሉት። እነዚህ መርሆች ሲጣሱ ህጉ ይከሽፋል፦ ▶አጠቃላይነት (Generality): ህግ ግለሰባዊ ውሳኔ ሳይሆን፣ በሁሉም ላይ በእኩልነት የሚተገበር አጠቃላይ መመሪያ መሆን አለበት። በግለሰብ ደረጃ የሚሰጡ በየቀኑ የሚቀያየሩ ውሳኔዎች ህግ ሊሆኑ አይችሉም። ▶ይፋዊነት (Promulgation): ህግ ለተፈፃሚዎቹ በግልጽ ሊታወቅና ሊታወጅ ይገባል። ህዝብ የማያውቀው ሚስጥራዊ ህግ የሰዎችን ባህሪ ሊመራ አይችልም። ▶ ወደኋላ የማይመለስ መሆን (Non-Retroactivity): ህግ ወደፊት ለሚፈጸሙ ድርጊቶች እንጂ፣ ትናንት በተደረገ ነገር ላይ ዛሬ ወጥቶ ሰውን ሊቀጣ አይችልም። ይህ የፍትህ መሰረት ነው። ▶ ግልጽነት (Clarity): የህግ ቋንቋ ህዝብ ሊረዳው የሚችል መሆን አለበት። ማንም ሊፈታው የማይችለው ረቂቅና ድብቅ ህግ መኖርና አለመኖሩ አንድ ነው። ▶ አለመቃረን (Non-Contradiction): በአንድ ስርዓት ውስጥ ያሉ ህግጋት እርስ በርሳቸው መጋጨት የለባቸውም። አንዱ ህግ “ፈቅጃለሁ” የሚለውን ሌላው “ከልክያለሁ” ካለ ህዝቡን ግራ ያጋባል። ▶ ሊተገበር የሚችል መሆን (Possibility of Compliance): ህግ ከሰው አቅም በላይ የሆነን ነገር እንዲያደርጉ ማዘዝ የለበትም። ለምሳሌ “ነገ ጠዋት ሁሉም ዜጋ መብረር አለበት” የሚል ህግ ቢወጣ ተፈፃሚነት ስለሌለው ህግ ሊባል አይችልም። ▶ ጽናት ወይም ቀጣይነት (Constancy): ህግ በየቀኑና በየሰዓቱ መለዋወጥ የለበትም። ሰዎች የወደፊት ህይወታቸውንና እቅዳቸውን ሊመሩበት የሚችል አንጻራዊ መረጋጋት ሊኖረው ይገባል። ▶በፅሁፍና በተግባር መካከል ያለው መጣጣም (Congruence): በይፋ የወጣው ህግና ፍርድ ቤቶች ወይም አስፈፃሚ አካላት በተግባር የሚተረጉሙት ህግ አንድ መሆን አለባቸው። ህጉ ወረቀት ላይ ብቻ ቀርቶ መሬት ላይ ሌላ አምባገነናዊ አሰራር ካለ ህጋዊነት የለም። የፉለር ፍልስፍና ዋና ረቂቅነት የሚገለጠው እዚህ ላይ ነው፤ እነዚህ ስምንት መርሆች የህግ መውጫ መንገዶች ብቻ ሳይሆኑ በራሳቸው የፍትህና የግብረገብነት ምሰሶዎች ናቸው። አንድ ገዢ አካል የፈለገውን ያህል ጨካኝ ቢሆን እንኳን፣ እነዚህን ስምንት መርሆች ጠብቆ ህግ ለማውጣት ከተገደደ፣ የስርዓቱ ውስጣዊ የሞራል ጥንካሬ ክፉና አድሏዊ ህግ እንዳይወጣ በራሱ ትልቅ ጋሻ ይሆናል። ህግ የሰዎችን ክብርና ነጻነት የሚጠብቀው ይዘቱ ብቻ ሳይሆን፣ የሚወጣበት ፍጹም ስነ-ስርዓታዊ ጥበብ ጭምር ነው። የህግ ውስጣዊ ሞራል ሲጣስ፣ የህግ ስርዓቱ ይፈርሳል። ህዝቡም ያንን ህግ የመታዘዝ የሞራል ግዴታው አብሮ ያበቃል። ህግ የሃይል መጫኛ ሳይሆን፣ በገዢና በተገዢ መካከል የሚደረግ የጋራ መከባበርና የታማኝነት ውል (reciprocal burden) ነው። https://t.me/insights89