cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

⚖Ethiopian law by Daniel Fikadu Law office⚖

ዳንኤል ፍቃዱ ተስፋዬ በሁሉም የፌደራል ፍርድ ቤቶች ጠበቃና የህግ አማካሪ ስልክ - 0913158507 ወይም 0978554559 Daniel Fikadu Tesfaye Certified Attorney of law at all Federal Courts of Ethiopia. Email- nurotekore@gmail. Com ⚖️⚖️Ethiopian Law by Daniel Fikadu channel ⚖️⚖️⚖️

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
8 710
Obunachilar
+2024 soatlar
+1777 kunlar
+65630 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

“የሜሪት እና የደመወዝ ቦርድ” የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ ቦርድ፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰብሳቢነት የሚመራ ይሆናል። ቦርዱ ሰብሳቢውን ጨምሮ ስምንት አባላት ያሉት ሲሆን የፕላን እና ልማት እንዲሁም የገንዘብ ሚኒስትሮች አባል እንደሚሆኑ የቦርዱን መቋቋም በሚያትተው የረቂቁ ክፍል ላይ ተዘርዝሯል። ከቦርዱ ኃላፊነቶች ውስጥ አንዱ፤ “የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ ስኬል ማስተካከያ፣ የደመወዝ ጭማሪ፣ የክፍያና ጥቅማ ጥቅም እና ማትጊያ ወይም ማበረታቻ ጥናትን ተመልክቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት መቅረብ ያለበትን የኮሚሽኑን ውሳኔ ሀሳብ ያረጋግጣል” የሚል ነው። የመንግስት ሰራተኞች “ከተሰማሩበት ሙያ ምድብ አንጻር መክፈል ያለባቸውን ተስማሚ፣ ተመጣጣኝ ደሞዝ እና ጥቅማ ጥቅምን“ የሚመለከት የኮሚሽኑ የውሳኔ ሀሳብም “ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ” የሚቀርበውም በቦርዱ አማካኝት እንደሆነ ረቂቁ ላይ ሰፍሯል። በአፈጻጸም ግንባር ቀደም የሆኑ የመንግስት መስሪያ ቤቶች እና የመንግስት ሠራተኞች የሚሸለሙበትን “የአመታዊ አገልጋይነት ቀን ሽልማት ሥርዓት” መዘርጋትም ከቦርዱ ኃላፊነቶች መካከል ነው። t.me/ayulaw
Hammasini ko'rsatish...
Ayu

👍 3👎 1
ሁለት ጊዜ ምዘና ያላለፉ ሰራተኞችን የሚያሰናብተው አዲሱ የፌደራል መንግሥት ሠራተኞች ረቂቅ አዋጅ ምን ዝርዝር ይዟል? በስድስት ወር ውስጥ ሁለት ጊዜ የብቃት ምዘና ፈተናን ያላለፉ ነባር ሰራተኞች ይሰናበታሉ አዲስ አዋጅ ሲዘጋጅ ለማሳካት ከታቀዱ ዓላማዎች ውስጥ አንዱ “በመንግሥት መስሪያ ቤት የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማስፈፀም ብቃት ያላቸውን ባለሙያዎች ለማግኘት እና በሥራ ላይ ያሉትንም ለማቆየት” የሚለው አንዱ እንደሆነ በረቂቁ መግቢያ ላይ ተጠቅሷል። ለዚህም፤ “የመንግስት ሠራተኞች የብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ሥርዓትን መዘርጋት” አስፈላጊ እንደሆነ ይህ የረቂቁ ክፍል ያስረዳል። በስራ ላይ ባለው የፌደራል መንግስት ሠራተኞች አዋጅ ላይም የተደነገገው የስራ አፈጻጸም ምዘና በረቂቅ አዋጁ ላይ የጊዜ ገደብ ተቀምጦለታል። በረቂቅ አዋጁ መሰረት ማንኛውም የመንግስት መስሪያ ቤት የሰራተኞቹን “የብቃት ክፍተት” ለመለየት እና ለሰራተኞቹ “የብቃት ዳሰሳ እንዲደረግ” የመከታተል ኃላፊነት ተጥሎበታል። መስሪያ ቤቶች “ለሥራ ብቁ የሆነን ሠራተኛ በብቃት መመዘኛ መስፈርቶቹ አማካይነት የማረጋገጥ” ስራ እንደሚያከናውኑ የሚገልጸው ረቂቁ፤ የመንግስት ተቋማቱ በስራ ላይ የሚመድቡት “በብቃት ምዘናው ዝቅተኛ ማለፊያ ውጤት ያገኘ ሠራተኛን” እንደሚሆን አስፍሯል። “የሥራ ብቃት ክፍተት” ያለባቸው ሰራተኞች “አጭር ሥራ ተኮር ወይም ሞጅላር ስልጠና ወይም በመደበኛ ብቃት ማሟያ ረጅም ጊዜ ትምህርት” እንደሚያገኙ እንደሚደረግ በረቂቁ አዋጅ ላይ ተጠቅሷል። “ክፍተት” የታየባቸው ሰራተኞች እነዚህን ስልጠናዎች ከወሰዱ በኋላ “የብቃት ምዘና” እንደሚወስዱ በረቂቁ ላይ ያሰፈረ ሲሆን መስሪያ ቤቶች “ከሥልጠናው በኋላ በብቃት ምዘናው አነስተኛ ማለፊያ ውጤት ያገኘውን ሠራተኛ በሥራ ላይ” እንደሚመድቡ አስቀምጧል። ረቂቅ አዋጁ፤ “የብቃት ክፍተት ማሟያ ሥልጠና ተሰጥቶት በስድስት ወር ለሁለት ጊዜ የብቃት ምዘና አነስተኛ የማለፊያ ውጤት ያላገኘ ሠራተኛ” ይህ ረቂቅ አዋጁ ባሰፈረው መሰረት “መብቱ ተጠብቆ አገልግሎትን ስለማቋረጥ የተደነገገው ተፈጻሚ ይደረጋል” ሲል ፈተናውን ያላለፉ ሰራተኞች እጣ ፋንታ ይገልጻል። መስሪያ ቤቶች በሚያከናውኑት የብቃት ምዘና ውጤትን መሰረት ያደረገ ምደባ መሰረት “በሥራ ላይ ለመመደብ ፍላጎት የሌለው ነባር ሰራተኛ” ላይም ከስራ የመሰናበት ተፈጻሚ እንደሚሆን ተቀምጧል። በዚህ አይነት መልኩ የሚሰናበት ነባር የመንግስት ሰራተኛ ጡረታ ለመውጣት እድሜው ያልደረሰ ከሆነ የሁለት ዓመት የተጣራ ደመወዙ “በአንድ ጊዜ” እንደሚከፈለው ረቂቅ አዋጁ ያስረዳል። የሚሰናበት ሰራተኛ ከመስሪያ ቤቱ የሚያገኘው ይህ ክፍያ ከ12 ሺህ ብር ማነስ እንደሌለበት ተጠቅሷል። ሰራተኛ ለመቅጠር የሚደረግ ምልመላ እና መረጣ በቀጣሪዎቹ መስሪያ ቤቶቹ አይከናወንም የመንግስት መስሪያ ቤቶች በስራ ላይ ባለው አዋጅ የተሰጣቸውን ሰራተኛ ለመቅጠር ማስታወቂያ የማውጣት፣ የመመልመል እና የመምረጥ ኃላፊነት በረቂቁ የፌዴራል መንግስት ሠራተኞች አዋጅ ይነጠቃሉ። በረቂቁ መሰረት ይህ ኃላፊነት የሚሰጠው እንደ አዲስ በሚቋቋመው “የኢትዮጵያ የሥራ ብቃትና አመራር ኢንስቲትዩት” ነው። በአጼ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግስት ተቋቁሞ እስካሁን ድረስ በስራ ላይ ያለውን “የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት” የሚተካው አዲሱ ተቋም፤ በዚህ ረቂቅ በተለይ በመንግስት ሰራተኞች ቅጥር ላይ ወሳኝ ሚና ተሰጥቶታል። በረቂቅ አዋጁ መሰረት የመንግስት መስሪያ ቤቶች ክፍት የስራ መደብ ሲኖራቸው የሚያስታውቁት ለአዲሱ የኢትዮጵያ የሥራ ብቃትና አመራር ኢንስቲትዩት ነው። ኢንስቲትዩቱም፤ “ማስታወቂያ በማውጣት አዲስ አመልካች እና ነባር መንግሥት ሠራተኛ እንዲመዘገብ” የማድረግ ኃላፊነት ተሰጥቶታል። ኢንስቲትዩቱ ከተመዘገቡ ስራ ፈላጊዎች ውስጥ “አወዳድሮ አብላጫ ውጤት ያመጡትን ከቅጥር በፊት የቴክኒካል እና የባህርያዊ ብቃት ሥልጠና” እንደሚሰጥ በረቂቁ ላይ ሰፍሯል። ከዚህ ስልጠና በኋላ ስራ ፈላጊው ግለሰብ “በመንግስት መስሪያ ቤት ለመቀጠር በኢንስቲትዩቱ የሚሰጠውን የቴክኒካል እና የባህርያዊ ብቃት ምዘና አነስተኛ የማለፊያ ውጤት ማግኘት አለበት” ሲል ረቂቅ አዋጁ ቀጣዩን የቅጥር ሂደት ያስረዳል። ይህንን ውጤት ያስመዘገቡ ሰልጣኞች የኢንስቲትዩቱን የብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት እንደሚያገኙ ያሰፈረው ረቂቅ፤ ይህ የምስክር ወረቀት የሌለው ግለሰብ “በመንግስት መስሪያ ቤት ለመቀጠር አይችልም” ሲል ቅድመ ሁኔታ መሆኑን ያስቀምጣል። “የነባር ሠራተኛ ወይም የዝግጁነት ሰልጣኝ የሥራ ቅጥር አመልካች ተፈላጊ ችሎታ ማሟላታቸውን እና የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ያላቸው መሆኑን በማረጋገጥ እና በማወዳደር ኢንስቲትዩቱ ቅጥር መፈጸም አለበት” ሲል ቅጥሩን መስሪያ ቤቶቹ እንዳማይፈጽሙ ይጠቁማል። ረቂቁ እንደሚያስረዳው፤ በዚህ መልኩ የተቀጠረ የመንግስት ሰራተኛ ለስድስት ወራት በሙከራ ጊዜ ላይ የሚቆይ ሲሆን ይህ ጊዜ ሲሞላ “የሥራ አፈጻጸም ምዘና ውጤቱ ከመካከለኛ በታች ሆኖ ከተገኘ የሙከራ ጊዜው ለተጨማሪ ሦስት ወር ሊራዘም ይችላል።” ረቂቁ፤ “በተራዘመው የሙከራ ጊዜ ውስጥ ሠራተኛው መካከለኛ ወይም ከዚያ በላይ የተጠቃለለ የሥራ አፈጻጸም ምዘና ውጤት ካላገኘ ከሥራ ይሰናበታል” ሲል አዲስ ሰራተኞች በቅጥር ለመቀጠል የሚያስፈልጋቸው ማለፊያ እንደ ነባር ሰራተኞች “አነስተኛ ማለፊያ ውጤት” አለመሆኑን ይጠቁማል። የደመወዝ ስኬል ማስተካከያ በየአራት ዓመቱ እየተጠና፣ ይወሰናል ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው የፌደራል መንግስት ሰራተኞች ረቂቅ አዋጅ ከሚያስተዋውቃቸው ለውጦች ውስጥ አንዱ የደመወዝ ስኬል ማስተካከያ በምን ያህል ጊዜ እንደሚደረግ ማስቀመጡ ነው። በስራ ላይ ያለው አዋጅ የመንግስት ሰራተኞች የደመወዝ ስኬል “የመንግስትን የፋይናንስ አቅም፣ የህዝቡን አጠቃላይ የኑሮ ሁኔታ፣ የዋጋ ደረጃዎች እና አግባብነት ያላቸውን ሌሎች ሁኔታዎች ባገናዘበ መንገድ” እየተጠና እንደሚወሰን ይደነግጋል። ይሁንና አዋጁ “በየጊዜው እየተጠና የሚወሰን ይሆናል” እንዲሁም “አስፈላጊ ሆኖ” ሲገኝ የደመወዝ ስኬል ተጠንቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት እንደሚቀርብ ከመደንገግ ውጪ ይህ ጥናት በምን ያህል ጊዜ እንደሚደረግ አያስቀምጥም። አዲሱ ረቂቅ አዋጅ በአንጻሩ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን “የሥራ ደረጃ መነሻ ዝቅተኛ ደመወዝ እና ከፍተኛ ደመወዝ ጣሪያ በየአራት አመቱ አጥንቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት አቅርቦ” እንደሚያስወስን እንዲሁም አፈጻጸሙን እንደሚቆጣጠር ያስቀምጣል። ኮሚሽኑ የሚያደርገው የአበል ማስተካከያም በተመሳሳይ የጊዜ ገደብ ተቀምጦለታል። በረቂቅ አዋጁ፤ “የመንግስት ሠራተኛ ወጪን መሸፈን የሚያስችል ልዩ ልዩ የአበል አይነቶች እና የቀን ውሎ አበል ማስተካከያ በየሁለት አመት ኮሚሽኑ ይወስናል” ሲል በየስንት ጊዜው ማስተካከያ እንደሚደረግ ይወስናል። የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የደመወዝ ስኬልን ለማስተካከል በየአራት ዓመቱ የሚያደርገውን ጥናት ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ከማቅረቡ አስቀድሞ ግን ማረጋገጫ የመስጠት ኃላፊነት ያለው አዲስ ቦርድ በረቂቅ አዋጁ ተዋውቋል።
Hammasini ko'rsatish...
👍 3
የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ በተለያዮ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ የተለያዮ ውሳኔዎችን ሰጠ፡፡ ››››››››››››››››››››››››››››››››››››››››››› ጉባኤው ዛሬ ግንቦት 07 ቀን 2016 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የተለያዮ ሹመቶችን እና የዲሲፕሊን ክሶችን መርምሮ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት 1ኛ) ዘጠኝ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሬጅስትራሮች እና 2ኛ) በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ድሬድዋን ጨምሮ ለሶስቱም ደረጃ የፌደራል ሸሪያ ፍርድ ቤቶች ተመልምለው የቀረቡ 10 ዳኞችን ሹመት መርምሮ አጽድቋል፡፡ 3ኛ) ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍርድ ቤቶች ዳኝነት ተወዳድረው መስፈርቱን ባሟሉ 9 ዕጩ ዳኞች ላይ አስተያየት ተሰጥቷል፡፡ በሌላ በኩል የፌደራል ዳኞች የስነ-ምግባርና ዲሲፕሊን ኮሚቴ መርምሮ ባቀረባቸው የውሳኔ ሃሳቦች ላይ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ በዚህም መሰረት አንድ ተከላካይ ጠበቃና አንድ የከፍተኛ ፍርድ ቤት ሬጅስተራር በበፈጸሙት ከባድ የዲሲፕሊን ጥሰት ጉባኤው ከስራ እንዲሰናበቱ የወሰነ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ አንድ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትና አንድ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ረዳት ዳኞች የቀረበባቸው የዲሲፕሊን ክስ ታይቶ ውሳኔ እስኪሰጣቸው ድረስ ከስራና ደመወዛቸው ታግደው እንዲቆዩ ወስኗል፡፡
Hammasini ko'rsatish...
👍 3
Sent with Xodo
Hammasini ko'rsatish...
👍 6 1
ክፍት የስራ ማስታወቂያ‼️ አስቸኳይ ክፍት የስራ ቦታ ከAron‼️ የሚያበቃበት ቀን ግንቦት 14 Aron S.C invites qualified and energetic candidates for the following positions.   የሚያስፈልገው የ ት/ት ድርጃ ☑️ Bachelor’s degree in Law,  Additional certification in law, banking, finance or similar fields is an added advantage ❇️  Qualifications2: bachelors degree marketing, accounting, management and relate field 🔻 Salary & Benefits: 18,000 + transport allowance    ☘ሌሎችም ተጨማሪ ስራዎች ስላሉ            በመደወልና በአካል መተዉ ያናግሩን  🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹 🇪🇹ለበለጠ መረጃ 🇪🇹👇👇👇👇 📌አድራሻ:-  መገናኛ ለም ሆቴል ማትያስ ህንፃ ሲደርሱ ይደውሉልን ለበለጠ መረጃ 👇👇👇👇👇           ☎️ 0942771288             ☎️ 0940771200
Hammasini ko'rsatish...
👍 8
Repost from Ethiopia Insider
የብሔር ብሔረሰቦች “ብዙሃነት እና አካታችነት” ስርዓት፤ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ተግባራዊ እንዲደረግ የሚደነግግ አዋጅ ለፓርላማ ቀረበ ማንኛውም የመንግስት መስሪያ ቤት “ኢትዮጵያን የሚመስል የሰራተኞች ስብጥር መኖሩን የሚያረጋግጥ”፣ “የብሔር ብሔረሰቦችን ብዙሃነት እና አካታችነት” ያገናዘበ ስርዓት ተግባራዊ ማድረግ እንዳለበት የሚደነግግ የአዋጅ ረቂቅ ለፓርላማ ቀረበ። በመንግስት መስሪያ ቤት ውስጥ የሚፈጸም የሰራተኛ ስምሪት፤ የብሔር ብሔረሰቦችን እና ህዝቦችን “ሚዛናዊ ተጽዕኖ” ለማሳደግ በሚያስችል መልኩ መፈጸም እንዳለበትም የአዋጅ ረቂቁ ያዝዛል። እነዚህን ድንጋጌዎች ያካተተው አዲሱ የህግ ማዕቀፍ፤ በ2010 ዓ.ም. የጸደቀውን እና እስካሁን በስራ ላይ የቆየውን “የፌደራል መንግስት ሰራተኞች አዋጅ” የሚተካ ነው። በአስራ ሰባት ክፍሎች እና በ160 አንቀጾች የተዋቀረው ይህ የአዋጅ ረቂቅ፤ የደመወዝ ጭማሪ፣ የደመወዝ እርከን፣ የመንግስት ሰራተኞች ክፍያ እና ጥቅም ጥቅም፣ የማትጊያ ወይም ማበረታቻ ስርዓት፣ የሰራተኞች ብቃት ምዘና እና ማረጋገጫ፣ የስልጠና አሰጣጥ እና ስራ ስምሪትን የተመለከቱ ድንጋጌዎች በዝርዝር የቀረቡበት ነው። በነባሩ አዋጅ ያልተካተቱ “ነጻ ገለልተኛ ስርዓት መገንባት”፣ “ሁሉ አቀፍ ብዝሃነት፣ አካታችነት እና ተጨማሪ የድጋፍ እርምጃ አፈጻጸምን” የተመለከቱ ድንጋጌዎችንም አዲሱ የአዋጅ ረቂቅ በውስጡ ይዟል። የአዋጅ ረቂቁ ዛሬ ማክሰኞ በተካሄደው የተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ በቀረበበት ወቅት፤ አዲሱ የህግ ማዕቀፉ እንዲዘጋጅ ካስፈለገበት ምክንያቶች ውስጥ የ“ህብረ ብሔራዊነትን” ጉዳይ አንዱ መሆኑን በፓርላማ የመንግስት ተጠሪው ተስፋዬ በልጅጌ ተናግረዋል። 🔴 ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2024/13041/ @EthiopiaInsiderNews
Hammasini ko'rsatish...
👎 6👍 3 2
Job Title: Legal and Compliance Specialist Job Type: On-site - Contractual Job Sector: #Project_management_and_administration Work Location: Addis Ababa, Ethiopia Education Qualification: Bachelor's Degree Experience Level: Expert Salary/Compensation: Monthly Deadline: May 24th, 2024 Description: Overview: We are looking for a highly skilled and experienced Legal and Compliance Specialist to join our team. The ideal candidate will have a strong background in law, business administration, or a related field, along with a passion for ensuring legal and regulatory compliance within the coffee industry. The individual should be between the ages of 25 and 45 and possess a minimum of 8 years of relevant experience in the field. Responsibilities: - Conducting legal research and analysis to ensure compliance with local, state, and federal regulations within the coffee industry - Developing and implementing compliance policies and procedures to mitigate legal risks - Collaborating with internal teams to provide legal guidance on business operations, contracts, and transactions - Reviewing and drafting legal documents, including contracts, agreements, and regulatory filings - Monitoring changes in laws and regulations affecting the coffee industry and advising on necessary adaptations - Conducting internal audits to assess compliance with legal requirements and recommending corrective actions - Providing education and training to employees on legal and compliance matters related to the coffee industry - Serving as a liaison with external legal counsel and regulatory authorities as needed Qualifications: - Bachelor's degree in Law, Business Administration, or a related field (Master's degree preferred) - Minimum of 8 years of experience in legal and compliance roles within the coffee industry or related sectors - In-depth knowledge of applicable laws, regulations, and industry standards in the coffee sector - Strong analytical skills and attention to detail - Excellent communication and interpersonal skills - Ability to work independently and as part of a team - Certification in compliance or related field is a plus If you meet the qualifications and requirements for this position, we encourage you to apply to join our dynamic team and contribute to ensuring legal and regulatory compliance in the exciting world of coffee. To Apply Please Use This Link https://forms.gle/hTh3bMn6J26SiVE7A __________________ Purpose Black Eth Trading s.c [Verified Company ✅] 301 Jobs Posted From: @freelance_ethio | @freelanceethbot For our Amharic Channel, Join @afriworkamharic
Hammasini ko'rsatish...
👍 4
ምክር ቤቱ አምስት ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች መራ ---------------------------- (ዜና ፓርላማ) ግንቦት 6 ቀን፣ 2016 ዓ.ም፤ አዲስ አበባ፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 26ተኛ መደበኛ ስብሰባው አምስት ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች መርቷል፡፡ ከተመሩት ረቂቅ አዋጆች መካከል የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ የሁለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች የስራ ስንብትን አስመልክቶ የቀረበው የውሳኔ ሀሳብ አንዱ ሲሆን የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ የውሳኔ ሀሳቡን አቅርበዋል፡፡ የውሳኔ ሀሳቡም ቁጥር 2/2016 ሆኖ ለዝርዝር እይታ ለህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምጽ ተመርቷል፡፡ የፌደራል መንግስት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 1064/2010ን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር የተከበሩ አቶ ተስፋዬ በልጅጌ ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት አዋጁ በስራ ላይ ከዋለ ስድስት አመት ያስቆጠረ መሆኑንና አሁን ካሉ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ እንዲሁም ነባሩ አዋጅ ስራ ላይ ከዋለ በኋላ በትግበራ ወቅት የታዩ ችግሮችን በመፍታት የመንግስትን የመፈጸም ብቃት በማጎልበት የዜጎችን ፍላጎት የሚያረካ አገለግሎት ለመስጠት የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት አስፈላጊ በመሆኑ ነው ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል የመንግስት ሰራተኞች የሰው ሀይል ምልመላና መረጣ ግልጽነት ባለው ውድድርና ብቃት ላይ የተመሰረተ ሆኖ ሁሉንም ባካተተና ብዝሀነትን በጠበቀ መልኩ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ስርአት መዘርጋት በማስፈለጉ ረቂቅ አዋጁ መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡ በረቂቅ አዋጁ ማሻሻያ ከተደረገባቸው ጉዳዮች ውስጥ የደሞዝ ጭማሪ፣ የደሞዝ እርከን፣ ክፍያና ጥቅማጥቅሞች ማትጊያና ማበረታቻ ስርአት እንዲሁም የሰራተኞች ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ስልጠና አሰጣጥ ስራ ስምሪት እና ነጻ ገለልተኛ ስርአት መገንባት፣ የመንግስት ሰራተኛነት ውል ማቋረጥና ማራዘም የሚሉት እና ሌሎችም እንደሚገኙበት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር የተከበሩ አቶ ተስፋዬ ገልጸዋል፡፡ የምክር ቤት አባላትም ረቂቅ አዋጁ መዘጋጀቱ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው ብቃትን መሰረት አደረጎ ለብሔር ብሔረሰቦች እኩል ዕድል ለመስጠት አስፈላጊ መሆኑን፣ አዋጁ የፌደራል ተቋማት ኢትዮጵያን እንዲመስሉ እንደሚያግዝ እና ሌሎች መታየት አለባቸው ያሏቸውን አስተያየቶች ሰጥተዋል፡፡ ረቂቅ አዋጁም አዋጅ ቁጥር 13/2016 ሆኖ በሙሉ ደምጽ ለሰው ሀብት ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተመርቷል፡፡ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ደረጃዎች ረቂቅ አዋጅ እና የሕጋዊ ስነ ልክ ረቂቅ አዋጅን የሚመለከቱ የውሳኔ ሀሳቦችን የተከበሩ አቶ ተስፋዬ በልጅጌ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል፡፡ ምክር ቤቱ ረቂቅ አዋጆቹን መርምሮ አዋጅ ቁጥር 14/2016 እና15/2016 ሆነው በሙሉ ድምጽ ለንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተመርተዋል፡፡ በመጨረሻም የተጨማሪ እሴት ታክስ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የተከበሩ አቶ ተስፋዬ በልጅጌ ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት አዋጁ ከወጣ ወዲህ የተደረጉ ለውጦቸን፣ የኤሌክትሮኒክስ ግብየትና በአለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያላቸውን አዳዲስ እሳቤዎችን በሀገራቸን የህግ ማዕቀፎች በማካተት ታክሱ ለኢኮኖሚ ዕድገት የሚፈለገውን እገዛ እንዲያደርግ ማስቻል ተገቢ ሆኖ መገኘቱን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ግልጽነት በጎደላቸው አንቀጾች ምክንያት በታክስ ከፋዩና በታክስ ሰብሳቢው መካከል ሲፈጠር የነበረውን ያለመግባባት በማስወገድ ምቹ የሆነ የታክስ አስተዳደር እንዲኖር ያግዛልም ብለዋል፡፡ ምክር ቤቱ ረቂቀ አዋጁን መርምሮ ለፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አዋጅ ቁጥር 16/2016 አድርጎ በሙሉ ድምጽ መርቷል፡፡ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡- በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament በዩቲዩብ https://www.youtube.com/@FDREHOPR በቴሌግራም https://t.me/ParlamaNews በትዊተር http://twitter.com/fdrehopr በዌብሳይት www.hopr.gov.et ይከታተሉ።
Hammasini ko'rsatish...
Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

👍 6
#Vaccancy for Lawyers
Hammasini ko'rsatish...
👍 3