uz
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Kanalga Telegram’da o‘tish

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Ko'proq ko'rsatish
2 929
Obunachilar
+224 soatlar
+3727 kun
+36730 kun
Postlar arxiv
የ7ለ70 ክፍለ ጦር ደመላሽ ሻለቃ ቃኚዎች በኤፍራታ ግድም ወርዳ ፈረድ ውሃ ቀበሌ በመግባት መብረቃዊ ጥቃት ፈጸሙ!! ነሐሴ 4/2018 ዓ.ም የመብረቃዊና የደፈጣ ባለሙያዎቹ 7ለ70 ክፍለ ጦር ደመላሽ ሻለቃ ቃኚዎች ፣ ከአጣዬ ቅርብ ርቀት ፈረድ ውሃቀበሌ ፈጣን እርምጃ በመውሰድ በገዢው ስርዓት ጠባቂዎች ላይ ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ በማድረስ ድል አስመዝግበዋል። የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ 7/ለ70 ክፍለ ጦር ደመላሽ ሻለቃ ቃኚዎች ለሊት 12፡00 ሰዓት ላይ ከአጣዬ ከተማ 3 ኪሎ ሜትር ብቻ እርቀት ላይ በሚገኘው ፈረድ ውሃ ቀበሌ ዘልቆ በመግባት፣ ተመሸገው በነበሩ የአገዛዙ ጥምር ኃይሎች ላይ ድንገተኛ የማጥቃት እርምጃ ፈፅመዋል። በተደረገው ወታደራዊ እርምጃ አራት(4) የስርዓቱ ጠባቂዎች ተደምስሰዋል። ✔ ጋሻውበዛ ለገሰ – የፈረድ ውሃ ቀበሌ ሚሊሻ ✔በግዱ ተጫኔ – የላየኛዉ አጣዬ ቀበሌ ሚሊሻ ✔ደምስ ፍስሃ – የአላላ ቀበሌ ሚሊሻ ✔ስሙ ያልተለየ – አንድ ተጨማሪ የሚሊሻ አባል ሲደመሰሱ፤ በተጨማሪም የስርዓቱ ልዩ የጦር ክንፍ በሆነው በ104ኛ አየር ወለድ ኮማንዶ ላይ በውጊያው 1 የኮማንዶ አባል ሲገደል 2 አባላት ደግሞ በፅኑ ቆስለው በህክምና ላይ እደሚገኙ ተረጋግጧል። የደመላሽ ሻለቃ ቃኚዎች የተጣለባቸውን ተልዕኮ በድል አድራጊነት ካጠናቀቁ በኋላ የጠላትን የጦር መሳሪያዎች በማረክ ለትግሉ ገቢ አድርገዋል። ✔ 2 ክላሽንኮፍ መሳሪያ ✔ 1 ጂ-3 (G3) መሳሪያ " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ከእናንተ ጋር ያሳለፍኳቸው እያንዳንዱ የነፃነት አፍታዎች የሕይወቴ ትልቁ ስጦታዎች ናቸው… በልቤ መዝገብ ውስጥ ለዘላለም የማይጠፉ፣ በደም፣ በወዳጅነትና በፍቅር የተቀረጹ የውበት ማስታወሻዎች። ​ሆኖም ግን መንገዳችን እጅጉን የከበደ፣ መከራው እስከ አጥንት የሚዘልቅ፣ ህመሙም ልብን የሚሰብቅ ነበር። በእየረገጥንበት ምድር ላይ ሁሉ በሆዳሞችና በባንዳዎች የታለሙ እልፍ የሴራ እሾሆች ተዘርግተውብኝ ብዙህ አሳልፊለሁ፤ የወደቁ ወንድሞቻችን ደም፣ የእናቶቻችን እንባ እና የሕዝባችን ስቃይ ልባችንን በሐዘን እያደማን እንድንጓዝ አድርጎናል። ነገር ግን በዚያ ሁሉ ጨለማ፣ ውርጭና የሕመም ማዕበል ውስጥ እኔን ደግፎ ያቆመኝ፣ ተስፋ እንዳልቆርጥና እንዳላብድ ያደረገኝ የእናንተ አብሮነት ብቻ ነበር… የእናንተ መኖር በዚያ ጨለማ ውስጥ ብቸኛው የተስፋዬ ብርሃን ሆኖልኛል። ​ዛሬም ቢሆን በሕመም የተሰበረችው፣ በቁስል የተሞላችው ነፍሴ የምትተንፈሰው በአንድ ነገር ብቻ ነው ነገ የታገደው ፍትህ የሚነግስበት፣ ታሪካዊ ጠላቶቻችንን በድል አፈር አልብሰን በወደቁት አበበዎቻችን ደም የተለወሰው የመከራ ዘመን የሚያበቃበት ቀን ይመጣል ብዬ ሳስብ ነው! በይቅርታ፣ በፍጹም ወንድማማችነትና በአንድነት አዲሷን ኢትዮጵያ በነጻነት የምንቀበልበት ያ ታላቅ የታሪክ ምዕራፍ እውን እንደሚሆን እርግጠኛ ነኝ። ​ያንን የድል፣ የነጻነትና የእንባ ማበሻ ታላቅ ማለዳ በሕሊናዬ ስሳል… ነፍሴ በሕመሟ ውስጥ ሆና በስሱ እያለቀሰች፣ ግን ደግሞ በሚያንበርክክ ታላቅ ሐሴት፣ ተስፋና ደስታ ትሞላለች! #Dave #Amhara

ከአውደ ውጊያ ጎን ለጎን በሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ ሀናመኳት ንዑስ ወረዳ ምኒልክ ዕዝ ታላቅ ህዝባዊ ምክክር አካሄደ! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ከብልፅግናው አገዛዝ ነፃ ካወጣቸው ወረዳዎች መካከል አንዱ የሆነዉ መቄት ወረዳ በሀና መኳት ንዑስ ወረዳ የጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ታላቅ ህዝባዊ መድረክ ተካሂዷል። በዚህ ህዝባዊ መድረክም የአማራ ህዝብ የህልዉና ትግል አላማና መዳረሻ ግብ፣ አሁናዊ ትግሉ ያለበትን ደረጃ እና ከማህበረሰቡ የሚጠበቅ ወቅታዊ አቋም፣ ሰለ ጊዜያዊ የመንግስት አስተዳደር ምንነተና አስፈላጊነት እንዲሁም በሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ማብራሪያ በሚኒልክ ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች ተሰጥቷል። በዚህ ህዝባዊ ዉይይት በማህበረሰቡ የተለያዩ ጥያቄዎችን እና ሃሳቦችን የተነሱ ሲሆን ለተነሱት ጥያቄወች እና ሃሳቦች የምኒልክ ዕዝ አመራሮች መልስ ሰጥተዋል። ማህበረሰቡም ለጠየቋቸዉ ጥያቄወች ፈጣንና ግልጽ ምላሽ በመሰጠታቸዉ እንደተደሰቱ የገለፁ ሲሆን አገዛዙን ነቅሎ ለመጣል ከመቸውም ጊዜ በላይ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በዚህ ህዝባዊ መድረክ የምኒልክ ዕዝ አደረጃጀት መምሪ ኋላፊ አርበኛ አሰፋ መሰለ(አሳምነው)፣ የምኒልክ ዕዝ የእቅድ ዝግጅትና ግምገማ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ኢ/ር አራጋው ያለው፣ የምኒልክ ዕዝ ምክትል ህዝብ አስተዳደር መምሪያ ሃላፊ አርበኛ ጋሻው ሙሉጌታ፣ የመቄት ወረዳ ጊዜያዊ ሲቨል አስተዳደር አመራሮች እንዲሁም የ16ኛ ኮር 22ኛ ክፍለጦርና 13ኛ ኮር 81ኛ ክፍለጦር አመራሮች ተገኝተዋል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ ነሐሴ 04/2018 ዓ.ም

ስቦ ማስከዳቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል። #_የሻለቃ_ዘመቻ_መሪው_50አለቃ_ከፍያለው_አምሳሉ_እና_5የሚሊሻ_አባላት ከግንደወይን እና ከዋበር ከተማ በመውጣት ፋኖን ተቀላቅለዋል። ========================== .....ነሐሴ 04/12/2018 ዓ.ም በዛሬው እለት ከግንደወይን እና ከዋበር ከተማ ወጥተው 201ኛ ኮር 74ኛ እና 54ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉ ሲሆን፦ 1.50 አለቃ ከፍያለው አምሳሉ ..የሻለቃ ዘመቻው ክላሽ 3ካዝና ሙሉ ተተኳሽ እና 1መገናኛ ሬዲዮ በመያዝ ወደ 54ክ/ጦር 2.ይበልጣል የስጋት...ሚሊሻ74ኛክ/ጦር 3.ውጣባቸው ጌታውአንተ....ሚሊሻ 4.ሙጨው ፀጋ............ሚሊሻ 5.ብርሀኑ አበረ............ሚሊሻ 6.ሙሉቀን ጌታው.......ሚሊሻ ሲሆኑ ለሌላ እልቂት ትሄዳላቹህ በማለት እያስጨነቁት ሲሆን ሁሉም የብልፅግና ሰራዊት አባላት የመዋጋት ስነ ልቦና የሌለው መሆኑን እና ለመውጣት ሁኔታወችን እየተጠባበቁ እንደሆነ የገለፁ ሲሆን አሁንም ቢሆን አልረፈደም ወደ ወንድሞቻቹህ ተመለሱ ኑ በክብር እንቀበላቹሀለን በማለት ጥሪያችን እናስተላልፋለን። የአፋብን ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

የብልፅግና መከላከያ ሠራዊት ከገዳ ኮማንዶ ጋር በመቀናጀት በጉሙዝ ሕዝብ ላይ ጭፍጨፋ ከፈተ! ከብልፅግና መከላከያ ሠራዊት፣ ከገዳ ኮማንዶና ከሚኒሻ የተወጣጣ ጥምር ወታደራዊ ኃይል፡ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ ዞን ሚዚጋ ወረዳ(በቀድሞው በለውጅጋንፎይ ወረዳ) ሜጢ ቀበሌ ላይ ከቀናት በፊት ጀምሮ በከባድ መሣሪያ የታገዘ ጥቃት ከፍቶ በርካታ ንፁኋን የጉሙዝ ብሔረሰብ አባላትን መግደሉን የመረብ ሚዲያ ምንጮች ገልፀዋል። በጥቃቱ ከተገደሉት በተጨማሪ በርካታ ንፁኋኖች የቆሰሉ ሲሆን፡ ሃብት ንብረታቸው ወድሟል፣ ቀሪዎቹ ሕይወታቸውን ለማትረፍ በሽሽት ላይ ናቸው። አከባቢውን ወደ ኦሮሚያ ክልል ለማካለል ያለመ ነው በተባለው በዚህ ጥቃት በመከላከያ ሠራዊቱ ፈቃድ ከጥምር ጦሩ ጋር ተሰልፎ ሀብት ንብረት እየዘረፈ በተሽከርካሪ ጭኖ የሚወስድ ቡድን መኖሩንና ከቀንድ ከብት ጀምሮ የቤት ጣራና ግርግዳ ጭምር እየነቀለ ዘርፎ የሊሙ ወረዳ ዋና ማዕከል ወደሆነችው ገሊላ ከተማ እየወሰደ መሆኑን ነው የመረብ ሚዲያ ምንጮች የገለፁት። የብልፅግናው መከላከያ ሠራዊት ከኦሮሚያ ክልል ታጣቂዎች ጋር በመቀናጀት ምንም አይነት መሣሪያ ባልታጠቁ ንፁኋኖች ላይ ነው በሞርታርና በዙ23 ጭምር የታገዘ ጥቃት የከፈተው ያሉት ምንጮቻችን፡ ጥቃቱ ተባብሶ መቀጠሉንና የሟቾችን አስከሬን መቅበር አለመቻሉን ገልፀዋል።

የጄኔራሎችን ዘመቻ ድባቅ የመታው የሉማሜ ከተማ ጀብድ! ነሐሴ 4/ 2018 ዓ.ም =================================== ጅባራው ብርሃኑ ጥላሁን የ6ኛ ዕዝ አዛዥ፣ ጄኔራል ሶፊያ በክሪ የ602ኛ ኮር አዛዥ፣ ኮሎኔል አለምሰገድ ተስፋየ የ32ኛ ክ/ጦር አዛዥ በአለፍቱ ቀናት የጎጃምን ታጋይ ወደ ተራ ሽፍትነት ቀይረነዋል የሚል ትልቅ ዘመቻ በጮቄ ተራራ አድርገናል እያሉ ሲያቅራሩ የተመለከተው 34ኛ ክ/ጦር ሉማሜ ከተማን በመቆጣጠር ጀብድ ሰርቷል። ሉማሜ ከተማን ካርታ ላይ በማስፈር የተጠና እቅድ በማቀድ የተጀመረው ልዩ ኦፕሬሽ የጦር አመራሩ ሰራዊቱን የግዳጅ አፈፃፀሙን በሚገባ እንዲረዳ አድርገዋል። ከሌሊቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ በጀግኖች የተመራው 34ኛ ክ/ጦር ሉማሜን በመቆጣጠር የጠላትን ሰራዊት ድባቅ መምታት ጀምረዋል። የጠላት የሰራዊት አቀማመጥ ቤተ ክርስቲያንን ከለላ ያደረገ ቢሆንም የወገን ኃይል በተጠና መልኩ ሰራዊቱን በማናጠል ደምስሰዋል። የሉማሜ ከተማ ሰላምና ደህንነት ኃላፊ ተመስገን ምስክር በብልፅግና ቢሮ በር ላይ በ34ኛ ክ/ጦር ተደምስሷል። አቶ ናቃቸው ጫኔ በሉማሜ ከተማ የገቢዮች ጽ/ቤት ግብር ሰብሳቢ ቡድን መሪ የነበረው ህዝብን በከፍተኛ ግብር በማሰቃየት እንዲሰደዱ ያደረገ ዋና የብልፅግና ጨካኝ ሰው በማህበረሰቡ ጥቆማ ተማርኳል። በሉማሜ ከተማ የመሸገውን የጠላት ኃይል በመደምሰስ የጄኔራሎች ጩኸት ባዶ ያስቀረው 34ኛ ክ/ጦር ከፍተኛ ወታደራዊ ድል አስመዝግቧል ። በነበረው ውጊያ 4 ፓትሮል፣3 አምቡላንስ የጠላት ኃይል ቁስለኛ ሁኗል ከ25 በላይ ተደምስሷል፤ ክላሾች ተማርከዋል። ከቀናት በፊት አስደማሚ የኮማንዶ ሰራዊት ያስመረቀው 34ኛ ክ/ጦር በተከታታይ አቅዶ በተዋጋባቸው ውጊያዎች ድል ማስመዝገቡ ቀጥሏል። አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ! የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

ከወታደራዊ ግዳጆች ጎን ለጎን ህዝባዊ ውይይቶች ቀጥለዋል!! ነሐሴ 04/2010ዓ.ም ​የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ከቅርብ ጊዜው የአንድነት ምስረታ ማግስት ጀምሮ በስምሪት ላይ የሚገኝ ሲሆን ፣ ከወቅታዊ ወታደራዊ ግዳጆቹ ጎን ለጎን በሁሉም ቀጠናዎች ከሕዝብ ጋር የሚደረጉ ውይይቶችን አጠናክሮ ቀጥሏል። የዕዙ ሥራ አስፈጻሚ በሁሉም ቀጠናዎች ውይይቶችን እያካሄደ የሚገኝ ሲሆን፣ለጎንደር አንድነት የተከፈለውን ውድ ዋጋ ለህዝባችንና ለሰራዊታችን ግልጽ ስለማድረግ፣ የሕዝብ ግንኙነት ሥራዎችን ለማስፋት ያለመ እና በፖለቲካ መር ትጥቅ ትግል ውስጥ የህዝባችንን ሚና ምን መምሰል አለበት በሚሉ አንኳር ነጥቦች ላይ ትኩረት ያደረገ ነበር። በእብናት ወረዳ ወርጋጃ ላይ በተካሄደው መድረክ የዕዙ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ጀኔራል ተሾመ አበባው እና ሌሎች የዕዝና የክፍለ ጦር አመራሮች በተገኙበት ዕዙ አንድነቱን ለማምጣት የደረሰበትን ውጤት ፣ የሰራዊቱንና የህዝባችን ሁለተናዊ ትስስር ፣ ለማይቀረው የአሸናፊነት ጉዞ የአንድነታችን ብስራት የውዴታ ግዴታ መሆኑንና ህዝባችን ባለፉት 3 ዓመታት ላደረገው አይተኬ ድጋፍን በተመለከተ ለተሳታፊዎች ማብራሪያ ሰጥቶበታል ። ​በተጨማሪም በመድረኩ የወደፊት ወታደራዊና ሕዝባዊ የጋራ አቅጣጫዎች ላይ ጥልቅ ውይይት የተደረገ ሲሆን ፣ በተለይም የአንድነትንና የመተባበርን አስፈላጊነት፣ የተቀናጀ ሕዝባዊ ድጋፍን ማጠናከር እንደሚገባ እንዲሁም ጠንካራ ሕዝባዊ ወገንተኝነት ያለው ጦር በመገንባት ሂደት ዙሪያ ባሉ ዋና ዋና ነጥቦች ላይ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን ! አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!

ፋኖ በአማራ ሕዝብ ታሪክ፣ ባህልና ማኅበራዊ መዋቅር ውስጥ ጥልቅ ቦታ ያለውና ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የኖረ የነጻነትና የራስን የመከላከል ምልክት ነው። ​የአማራ ልጅ ሲወለድ አንድ ዲግሪ አለው» የሚባለው በአማራ ማኅበረሰብ ዘንድ ገና ከሕፃንነቱ ጀምሮ የሚኮተኮተውን የመታገል፣ የአገር ፍቅር፣ የጀግንነት እና የራስን ክብር የማስጠበቅ እሴት ያመለክታል። ትምህርት ቤት ሳይገባ ወይም ዘመናዊ ሳይንስ ሳይማር፣ በባህሉና በታሪኩ ውስጥ የነጻነትንና የጀግንነትን ትምህርት አብሮት ይዞ የሚያድግ መሆኑ ው። ​ሁሉን አቀፍ ተሳትፎ (ከሌቅ እስከ ደቂቅ) የፋኖነት እሴት የወሰነ የዕድሜ፣ የጾታ ወይም የማኅበራዊ ደረጃ ገደብ የለውም። «ከሌቅ እስከ ደቂቅ» እንደሚለው፣ ሽማግሌው፣ ወጣቱ፣ አባወራው፣ እናቱም ሆነ ሕፃኑ በየፊናቸውና በየአቅማቸው ለማኅበረሰቡ ደህንነትና ለነጻነቱ ጥበቃ የየራሳቸውን አስተዋጽኦ የሚያደርጉበት ባህላዊ መዋቅር አለው። ​ትውልድ ተሻጋሪነት ፋኖነት ለአንድ ወቅት ወይም ለአንድ ዘመን ብቻ ተከስቶ የሚያልፍ ሳይሆን፣ ትውልድ ከአባቶቹ ተቀብሎ ለቀጣዩ የሚያስተላልፈው ዘላቂ የማንነትና የባህል አካል ነው። ታሪክን፣ ባህልን፣ ተረትንና ጀግንነትን የማስታወስ ሂደት እንደመሆኑ መጠን ከትውልድ ወደ ትውልድ ይተላለፋል። ​የመደጋገፍና የማኅበራዊ ቁርኝት ምሳሌ ፋኖ በጦርነትና በችግር ጊዜ ብቻ ሳይሆን፣ በማኅበራዊ ህይወት ውስጥም ለፍትሕ፣ ለእውነት እና ለመደጋገፍ የሚቆም ማኅበረሰባዊ ምሰሶ እንደሆነ ይቆጠራል። #Dave #Amhara

በሸዋ ጠቅላይ ግዛት የ«ኮሉ ብርጌድ» ደጀን አርበኞች ጦር እየተደራጀ ይገኛል!! ነሐሴ 04/2018 ዓ.ም በትጥቅ ትግሉ ስትራቴጂካዊ ምህዳር ውስጥ ጉልህ ስፍራ የሚይዘው የሸዋ ምድር፣ የትግሉን ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሚዛን መልክ የሚቀይር አዲስ የሃይል አደረጃጀት እየተደራጀ ይገኛል። በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ በሚዳና ሬማ ክላስተር፣ በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ በአፄ ዓምደ ጽዮን ኮር አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በሚቀሳቀስበት ቀጠና «ኮሉ ብርጌድ» የተሰኘ ግዙፍ የአርበኞች ጦር ሰራዊት በይፋ መመስረቱ ታውቋል። ከውስጣዊ ፈተና ወደ ወታደራዊ የበላይነት የተሸጋገረው ማሕበረሰብ በፖለቲካ ውስብስብ ጉዳዮች እየተፈተነ የህልውና አደጋ ይታይበት የነበረና ለጠላት ሃይሎች መፈንጫ ሆኖ የቆየ ስትራቴጂካዊ ቀጠና እንደሆነ ይታወቃል። ሆኖም የትግሉን ሚዛን ማስጠበቅ አስፈላጊ መሆኑን የተረዱት የቀጠናው ቁርጠኛ ታጋዮች፣ በጥቂት ቀናት ውስጥ የተካሄደውን የተናበበ የመልሶ ማደራጀት ስራ ተከትሎ ከመደበኛው የፋኖ ሰራዊት ውጭ ሁለት ግዙፍ የአርበኞች ጦር ብርጌድ «ካራምሽግ» እና «ኮሉ» ብርጌዶችን ማደራጀት ተችሏል። ከፍተኛ የአሳምነው ዕዝ እና የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር አመራሮች፣ የየቀበሌ አስተዳደሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በተካሄደው የዚሁ ምስረታ ስነ-ስርዓት ላይ፣ ለሰራዊቱ ሰፊ የፖለቲካና የወታደራዊ ስትራቴጂ/ግንባታ ትምህርቶች ተሰጥተዋል። የብርጌዱን አወቃቀር በተጠናከረ መልኩ ከመደራጀቱም በላይ፣ አመራሮችና አባላት ህዝባቸውንና ቀጠናቸውን በፍፁም ታማኝነት፣ በፍትሃዊነትና በጽናት ለማገልገል በህዝብ ፊት ቃለ-መሃላ ፈጽመዋል። አደረጃጀቱም የወታደራዊ ደጀንነቱን በቁርጠኝነት በማገዝ በአገዛዙ ሃይሎች ላይ ለሚሰነዘረው የማጥቃት ስምሪት ይበልጥ የተቀናጀ እንደሚያደርገው በመድረኩ የተገኙት የዕዝ አመራሮቹ ገልፀዋል ሲል ኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አስታውቋል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

በዚገም ወረዳ ሰፍሮ ማሕበረሰቡን ሲዘርፍና ሲያሳድድ በነበረው የሚኒሻ ኃይል ላይ በተወሰደ ከባድ የቆረጣ እርምጃ ከ20 በላይ የሚኒሻ አባላት ሲገደሉ 12 ክላሽንኮፍ መሣሪያ በፋኖ ቁጥጥር ስር ውሏል።
በዚገም ወረዳ ሰፍሮ ማሕበረሰቡን ሲዘርፍና ሲያሳድድ በነበረው የሚኒሻ ኃይል ላይ በተወሰደ ከባድ የቆረጣ እርምጃ ከ20 በላይ የሚኒሻ አባላት ሲገደሉ 12 ክላሽንኮፍ መሣሪያ በፋኖ ቁጥጥር ስር ውሏል። የፋኖ የቆረጣ ታክቲክ ከማጥቃት ፍጥነት ጋር ተዳምሮ የጠላትን ጦር ባሽመደመደበት በዚህ ተጋድሎ፡ በዚገም ወረዳ ዚገም ፊለም፣ ጉሀ፣ አሀቲ፣ ኮሸይ፣ ዳዳን ቲትም የተባሉ አከባቢዎች ሙሉ በሙሉ በፋኖ ቁጥጥር ስር ውለዋል።

በሰሜን ወሎ ዞን ዳዉንት ወረዳ ታልቅ ህዝባዊ መድረክ ተካሂደ!! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ በስሩ ከሚያስተዳድራቸዉ ወረዳዎች መካከል አንዱ የሆነዉ በሰሜን ወሎ ዞን ዉስጥ ዳዉንት ወረዳ አንዱ ሲሆን በዚህም በዛሬዉ ዕለት ማለትም በቀን 03/12/2018 ዓ.ም የጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ታላቅ ህዝባዊ መድረክ ተካሂዷል። በዚህ ህዝባዊ መድረክም የአማራ ህዝብ የህልዉና ትግል መነሻ፣ አሁናዊ ትግሉ ያለበትን ደረጃ፣ ሰለ አጋርነት እና ትብብር እና በሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ማብራሪያ በሚኒልክ ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች ተሰጥቷል። በዚህ ህዝባዊ ዉይይት በማህበረሰቡ የተለያዩ ጥያቄዎችን እና ሃሳቦችን የተነሱ ሲሆን ለተነሱት ጥያቄወች እና ሃሳቦች የሚመለከታቸዉ አካላት በዘርፉ መልስ ሰጥተዋል:: ማህበረሰቡም ለጠየቋቸዉ ጥያቄወች ፈጣንና ግልጽ ምላሽ በመሰጠታቸዉ እንደተደሰቱ ገልፀዉ "ካሁን በኋላ ከፋኖ ጋር በጋራ ሁነን ይህን የብልፅግና ስርዓት ለመጣል" ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በዚህ ህዝባዊ መድረክ የምኒልክ ዕዝ ም/ትል ሰብሳቢ አርበኛ ረዳ ዉበቱ(ቀኝ አዝማች)፣ የምኒልክ ዕዝ ፖለቲካ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ሞገስ አባራዉ፣ የምኒልክ ዕዝ ዘመቻ መምሪያ አርበኛ በለጠ ሸጋዉ(ድሮን)፣ የምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ አርበኛ ብርሃን አርጋ እና የምኒልክ ዕዝ 16ኛ ኮር አመራር እና የክፍለ ጦር አመራሮች ተገኝተዋል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!! ነሀሴ :- 03/ 2018 ዓ/ም