ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Kanalga Telegram’da o‘tish
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Ko'proq ko'rsatish2 923
Obunachilar
+3224 soatlar
+3727 kun
+36630 kun
Postlar arxiv
በፖሊት ቢሮው ማስጠንቀቂያ ከተሰጠው በኋላ ነው ዛሬ በግልጽ ወጥቶ ኦሕዴድን መቀላቀሉን የገለጸው።
የበረኸኛው ቀስተ ደመና ብርጌድ ለወራት ያሰለጠናቸውን የፋኖ የሠራዊት አባላትን በዛሬው ዕለት በደመቀ ሁኔታ አስመርቋል‼️
==================
በሕዝባችን ትከሻ ላይ የወደቀውን የባርነት ቀንበር አሽቀንጥሮ በመጣል የተጋረጠበትን የሕልውና አደጋ ለመቀልበስ በሚደረገው እልህ አስጨራሽ ትግል ውስጥ የኃይል ግምባታ ተቀዳሚው ትኩረት የሚሻ ጉዳይ ነው።
እንደ ቀስተ ደመና ፋኖም ባሳለፍናቸው 3 የትግል ዓመታት ውስጥ እጅግ ፈታኝና ውስብስብ የትግል ጎዳናዎችን በማለፍ ሁለንተናዊ የትግል እምርታዎችን አስመዝግቧል፤ አመርቂ የለውጥ ደረጃዎችንም አልፏል።
ከዚህ መካከልም የስልጠናና የኃይል ጎምባታ ሥራው ትኩረት ተሰጥቶት የተሰራበት ተግባር ነው።
በዛሬው ዕለትም ለወራት ያሰለጠናቸውን አራተኛ ዙር ሰልጣኞች በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል። ሰልጣኞቹም በቆይታቸው በርካታ ወታደራዊ፣ ፖለቲካዊና ስነ ልቡናዊ እውቀቶችን በማካበት ቀጣይ የሚጣልባቸውን ግዳጅ በብቃት ለመወጣት የሚያስችል አቅም ፈጥረዋል።
በምረቃ መርሐ ግብሩ የብርጌድ፣ የሻለቆችና የቀበሌ አመራሮች፤ የሃይማኖት አባቶች፣ የሃገር ሽማግሌዎች የበረኸኛው ቀስተ ደመና ብርጌድ የሠራዊት አባላት የጓይና አካባቢው ማሕበረሰብና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን ለተመራቂዎቹ የእንኳን ደስ አላችሁና የአደራ መልዕክት በአመራሩ ተላልፏል።
ቀድም ሲል በዚህ ብርጌድ ሲታገልና ሲያታግል የክብር መስዋዕትነትን በተቀበለው ሰማዕት አርበኛ ተመስገን ተስፋየ የተሰየሙት ሰልጣኞችም በዕለቱ ወታደራዊ ትርዒቶችን በማሳየት መርሐ ግብሩን ድምቅ አድርገውት ውለዋል።
ማሰልጠን፣ኃይል ግንባታ የሕዝብ አስተዳደር፣ ጠላትን መደምሰስና የጠላትን ተቋም ማፍረስ የትኩረት ነጥቦቻችን ናቸው።
ለሕዝባችን ሕልውና አስተማማኝ ዋስትና ለመስጠት የጠላትን አደረጃጀቶች ከማፈራረስ ባለፈ የሕዝባችን የነገ አለኝታ የሚሆን ተቋም ግንባታ ላይ አበክረን እንሰራለን።
ድል ለአማራ ፋኖ!
ክብር ለሰማዕታቱ!
ነሐሴ 18/12/2018 ዓ.ም
18/12/2018 ዓ.ም
ሚኪ አማራ
√ ከወለጋ የስቃይ ማዕበል እስከ አማራ የህልውና ትግል !!
ዛሬ ላይ ሆኖ ወለጋን ማየት ማለት የሰብአዊነት መቁሰልን፣ የፖለቲካ ሸፍጥን እና የዘመናት ግፍ መዘዝን በአንድ ላይ መመልከት ማለት ነው። ለዓመታት በወለጋ ምድር ላይ በአማራው ሕዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው ግፍ፣ መፈናቀል እና ስልታዊ ጭፍጨፋ ከምድር ሲኦል ጋር የሚስተካከል ነው። ይህ ሁሉ ግፍ የተጠነሰሰው በጠባብ ፖለቲካዊ ቅንጅቶች እና በስልጣን ጥም በሰከሩ አካላት ሲሆን የወለጋን ሕዝብ የፖለቲካ የቁማር ካርድ አድርጎ በመጠቀም የሕዝባችንን ደም እንደ ውኃ ሲያፈሱ ኖረዋል።
የጃዋር መሐመድ እና የሽመልስ አብዲሳ ፖለቲካዊ ቁማር ማሳያ የሆነው ይህ መዋቅር ለሕዝባችን የሲኦል ምድር ፈጥሮ ቆይቷል።
ይሁን እንጂ፣ የጨለማው ዘመን ማብቂያ ጅምር ታይቷል። ዛሬ በአማራ ፋኖ አደረጃጀት በወለጋ መሬት መጎልበት እና መጠናከር የጠላትን እንቅልፍ ነስቶታል። የሴራው ፖለቲካ ባለቤቶች የሆኑት አካላት የፖለቲካ ቁማር ማብቂያው ሰዓት ላይ ደርሰዋል። ፋኖ ለወለጋ አማራ የሰጠው የትግል ተስፋ እና የራስን በራስ የመከላከል አቅም የዚህ ስብራት ማብቂያ ነው።
ይህንን ታሪካዊ ሂደት ስንመለከት ታሪካዊ እና ወታደራዊ ትምህርቶችን መውሰድ ተገቢ ነው። ታሪክ እንደሚያስተምረን ሕዝብን ያለ ሠራዊት እና ያለ ራስን የመከላከል አቋም ማቆየት ራስን ለአስገዳጅ እልቂት አሳልፎ መስጠት ነው። ወለጋ ከማዕከላዊው የአማራ ክልል ርቆ የሚገኝ በመሆኑ፣ ጠላት ሐሳቡን በቀላሉ በመበታተን ሕዝቡን አቅመ ቢስ ለማድረግ ሞክሯል። ነገር ግን ፋኖ በወለጋ መደራጀቱ የጠላትን የከፋፍለህ ግዛ ስልት ሰባብሮታል። ወታደራዊ ጥንካሬ የሌለው ፖለቲካ ከንቱ እንደሆነ ሁሉ ሕዝብን ከጥቃት የሚታደገው የታጠቀ የጸና ክንድ ብቻ ነው። የፋኖ መረብ መተሳሰሩ ለወለጋ አማራዎች ታሪካዊ የህልውና ዋስትና ሆኗል።
ለዚህም ስኬት ፖለቲካዊ መፍትሔዎችና የስትራቴጂ ለውጥ ማምጣት ያስፈልጋል። የወለጋን ሕዝብ ለምርጫና ለስልጣን መለወጫ ማድረጉን ማስቆም፣ የጃዋር እና የሽመልስ አብዲሳ የፖለቲካ ቁማር በሕዝብ የጋራ ንቃት እና በፋኖ ጽኑ አቋም መዳከም አለበት። የትግሉ ማዕከል የጥላቻ ፖለቲካን ሳይሆን ከሌሎች ሰላም ፈላጊ ሕዝቦች ጋር በመተባበር አራጁን ሥርዓት ማስወገድ መሆን ይገባዋል።
ስለዚህ መላው አማራ ለወለጋ ማድረግ የሚገባው ተግባር ግልጽ ነው። የወለጋ ፋኖ እና ሕዝብ በብቸኛነታቸው የሚዋጉ ሳይሆን ከመላው የአማራ ሕዝብ የሚደረግላቸው የቁሳቁስ፣ የሞራል እና የዲፕሎማሲ ድጋፍ ሊጠናከር ይገባል። እያንዳንዱ አማራዊና አማርኛ ተናጋሪ ማህበረሰብ የራሱን ደህንነት በንቃት የሚጠብቅበትን የአካባቢ ጥበቃ ሥርዓት ማጠናከር አለበት። የወለጋ ትግል የመላው አማራ የህልውና ፈተና በመሆኑ ትኩረታችን በዘላቂ ሰላም እና በጠላት መዋቅር ማክሰም ላይ መሆን አለበት።
ይህ የሲኦል ምድር የሚበቃው በጋራ ጽናት፣ በወታደራዊ ጥንካሬ እና በፖለቲካዊ ንቃት ብቻ ነው። የየወለጋ አማራ ቁማር ካርድነት ዘመን አብቅቷል::
እናሽንፋለን!!
አንድነትን የማጽናትና ወንድምነትን ከፍ ያደረገ የከፍታ ውሎ ከቋራ!
ነሐሴ 18/2018ዓ.ም
ከጎንደር አንድነትና ከሰማዕታት አንድነት ጉባኤ በድርኳዜ ሐምሌ 05/2018 ዓ.ም በኋላ የአፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ተቋማዊ ግዳጆችን በመውሰድ በሁሉም ቀጠናዎች አንድነትን የማጽናት ሥራዎችን እያከናዎነ ይገኛል።
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ በተለይም ፀረ-አንድነት ግለሰቦች በሚነዙት የልዩነት ሀሳብ ውስጥ የነበሩ ወንድማማቾች ላይ ግንዛቤ በመፍጠር፣ መርህን፣ ህግንና ተቋማዊ አንድነትን ማረጋገጥ ላይ ትኩረት አድርጎ በቁርጠኝነት በመስራት የአቃፊነት ስራዎቹን በማከናዎን ላይ ነው።
በዚሁ መሠረት በቋራ ቀጠና በተካሄደው ታሪካዊ ውሎ፣ የዕዙ ምክትል ወታደራዊ አዛዥ ለወታደራዊ ጉዳዮች ኃላፊ አርበኛ ሸጋ ጌታቸው፣ የዕዙ ምክትል አደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ አርበኛ ብርሃኑ ነጋ እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ውይይት ተካሂዷል።
በዚህ መድረክ የ2ኛ መይሳው ካሳ ኮር ዋና ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ በሊሁን ጌታቸው፣ የኮርና የክፍለ ጦር አመራሮች እንዲሁም አባላት ተሳትፈዋል። በፀረ-አንድነቶች ሴራ ምክንያት በተለያዩ ውዥንብሮች ውስጥ እንዲያልፍ ሲሰሩበት የነበረው 2ኛ መይሳው ካሳ ኮር፣ በዛሬው ዕለት ከዕዙ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት በማድረግ የነበሩ ልዩነቶችን መፍታት ተችሏል። በቀጣይ በስሩ ያሉ ሁሉንም ክፍለ ጦሮች አካቶ ሰፊ ግንዛቤና የአንድነት ማጽናት ስራዎችን መስራት በሚያስችሉ ሁነቶች ላይ አቅጣጫ አስቀምጧል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!
በየዕድውሃ ከተማ መሽጎ የሚገኘው የአገዛዙ ሰራዊት አባላት ሙትና ቁስለኛ ሲሆን 1የአገዛዙ ቅጥርኛ ሚሊሻ በቁጥጥር ስር ውሏል 5 የሚሊሻ አባላት አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር ተቀላቅለዋል።
~~~~
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር ነሀሴ 15/2018 ዓ.ም በሸበል በረንታ የዕድውሃ ከተማ ከንጋቱ 11:00 እስከ ጥዋት 2:00 ሰዓት በመግባት የሽፈራው ገረባው ልጆች ከባድ ውጊያ አካሂዶል። በዚህ አውደ ውጊያ በየዕዱውሃ ከተማ መሽጎ የሚገኘው አገዛዙ ሰራዊት አባላት ሙትና ቁስለኛ ሆነዋል።
ሀምሌ18/2018 ዓ.ም ሀብታሙ ደጉ የተባለ የአገዛዙ የሚሊሻ ሰራዊት አባላት በሸበል በረንታ መረገጭ ንዑስ ከተማ የሚሊሻ አባል ሲሆን በክ/ጦሩ በተሰጠው መረጃ መሰረት ከፍተኛ ክትትል በማድርግ በቁጥጥር ስር ውሏል።
በሌላ መረጃ በእነማይ ወረዳ የሚገኘው የአገዛዙ የሚሊሻ ሰራዊት አባላት በታላቁ ዲማ ጊዮርጊስ፣ ደብረ ፅሞና ቀበሌ ላይ በእምነት ተቋማትና የንፁሀን ሀብት ንብረት ላይ በተፈፀመው ዘረፋና ውድመት በመቃወም አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር ተቀላቀሉ።
1ኛ. ሚሊሻ ማሩ ምረት ስር እየሱስ ቀበሌ
2ኛ.ሚሊሻ ሀብታሙ ነገሠ ጋታንስ ቀበሌ
3ኛ.ሚሊሻ ሙሉሠው ተሻለ የቀበሀና ቀበሌ
4ኛ.ሚሊሻ መልካም ጤና ጋታንስ ቀበሌ
5ኛ.ሚሊሻ መኳንት ያለው እንደሽኝት ቀበሌ ተወላጅ ሲሆኑ ነሀሴ 18/2018 ዓ.ም የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር ተቀላቅለዋል።
አዲስ ትውልድ ፣አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
ነሀሴ 18/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
የብልፅግና ሥርዓት ዐቢይ አሕመድ አስተዳደር ማኒፌስቶና እቅድ ቀርፆ የአማራን ሕዝብ ከምድር ገጽ ለማጥፋት እየሠራ መሆኑ የሚገባህ፣ በዚሁ ሥርዓት የሚደርሰውን መገፋት፣ መገደል፣ መፈናቀልና መሰቃየት በገዛ ራስህ ላይ ሲደርስና መከራውን ስትቀምስ ብቻ ነው።
ለዚህም ነው ዛሬ ልዩነቶችን ወደ ጎን በመተው 'አንድ ሆነን ይህን ሥርዓት እንታገል' በማለት አጥብቄ ጥሪ የማቀርበው። እኔ ራሴ በዚህ ሥርዓት በደልና ግፍ ከተፈጸመባቸው፣ ከተረገጡት የአማራ ልጆች መካከል አንዱ ነኝ። ሆኖም ግን ይህንን በደል፣ ግፍና ጨቋኝ ሥርዓት ድል ማድረግና መብታችንን ማስከበር የምንችለው መበታተንን አስወግደን በአንድነትና በጽናት አብረን ስንሰለፍ ብቻ ነው።"
የአማራን ግፍ የአማራን ስቃይ የሚያቃት እንደዚህ ወንድሜ ሲበደል ብቻ ነው!! ያኔ ነው አማራ መሆንህ የሚገባህ ሆዳም አማራዎች በግዜ መፍትሔ ከእራሳችሁ ይመጣል ደም በደም ይጠራልና #Dave #Amhara
…እግሩን ተመትቶ የቆሰለን ይህን የትግሬ ወታደር ዓለምአቀፍ የጦርነት ሕግን በተላለፈ በዚህ መልኩ በሚያሰቅቅ ሆኔታ የረሸነን የአቢይ አሕመድ፣ የብርሃኑ ጁላ፣ የአበባው ታደሰና የባጫ ደበሌን የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት ማንም ይሁኑ ማን በሕግ መጠየቅ ለፍርድም መቅረብ አለባቸው። ይሄ የጸና አቋሜ ነው።
"…ይህ የምታዩት የትግሬ ወታደር ቆስሏል። የተመታው እግሩን ነው። በሕጉ መሠረት ምርኮኛ መያዝ ያለበት በሕግ አግባብ ነው። ነገር ግን በኢትዮጵያ ወገንም በወያኔም በኩል የተፈጸሙት ከሕግ ውጪ ነው። በአፋርና በዐማራ ክልል የተጨፈጨፉ ምስኪን ዜጎች ሳይቆጠሩ በትግራይ ብቻ ከ2 ሚልዮን በላይ ዜጎች በጦርነቱም፣ ከጦርነቱም ውጪ የዘር ማጥፋት ወንጀል ተፈጽሞባቸዋል።
"…እኔ ግን በጦርነቱ ወቅት ከተገደሉ ወታደሮችና ከጦርነቱ መልስ ስልካቸው ጠፍቶባቸው፣ አንዳንዶቹም ስልካቸውን ሽጠውት ከተገኙ አሰቃቂ የአቢይ ብርሃኑ ጁላ የዘር ጭፍጨፋ የሚያሳይ ዘግናኝ ዘግናኙን መርጬ አሳያችኋለሁና ጨከን ብላችሁ ለማየት ተዘጋጁ።
"…ሲጠቃለል እናንተ የጦርነቱም ጊዜ ቀስቃሽ ማጋጅ፣ ጨፍጫፊ አስጨፍጫፊ፣ በሰላሙም ጊዜ መልሳችሁ እናንተው የሰላም ሰባኪ፣ የሰላም ሐዋርያ መሆን አትችሉም። ሰላም የሚረጋገጠው በፍትሕ ነው። ሕዝብ ያልተሳተፈበት ሰላም ደግሞ አይጸናም። እናንተ ጃኬት እየለዋወጣችሁማ አታጃጅሉንም። ማየት ባትፈልጉም እንኳ እኔ ግን የሚሰቀጥጥ የእናንተን የወንጀል ቪድዮዎች መልቀቄን እቀጥላለሁ። #Dave #Amhara
የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ አፄ ዘርያዓቆብ ፩ ኮር ናደው ክፍለ ጦር አስደናቂ ጀብድ ፈፅሟል !!
ነሐሴ 18/2018 ዓ ም
የአገዛዙ 101ኛ አየር ወለድ ኮማንዶ በሆድ አደሩ ሚሊሻ መንገድ መሪነት በ ቀን 17/12/2018 ዓ.ም መነሻውን ከመርሐቤቴ ፌጥራ ከተማ በማድረግ ፋኖ ይንቀሳቀስበታል ብሎ ወደገመተው ታችቤት ቀጣና ጥቃት ለመፈፀም እየተግተለተለ በሦስት አቅጣጫ የተንቀሳቀሰ ቢሆንም የናደው ክፍለ ጦር የውጊያ ጠበብቶችና ፈጣን ተዋጊዎች ጠላት ያሰበበት ቦታ ሳይደርስ ፈጣን ጥቃት በመፈፀሙ ለቀናት የተሰናዳበት ዕቅድ ከሸፈ።
የጠላትን ዕቅድ ቀድሞ የደረሳቸው የናደው ክፍለ ጦር ቃኝዎች ወደ ፌጥራ ከተማ ልዩ ስሙ ጉራንባ የተባለ ቦታ ላይ የመሸገውን የጠላት ኃይል ላይ ከቀኑ 8:00 ሰአት ላይ ተኩስ በመክፈት አመርቂ ድል ተጎናፅፈዋል። በነበረው አውደ ውጊያ በወገን ኃይል የበላይነት የጠላት ኃይል በርካታ ሙት እና ቁስለኛ ሲሆን የቀረው የጠላት ኃይል በውር ድንብር ለማፈግፈግ ሲሞክር በተኩስ ጫና የገደል ሲሳይ ሆኗል።
በእዚህ የተደናገጠው የጠላት ሀይል ማጥቃት የሚለው የህልም እንጀራ ከሽፎበት ቀሪውን ኃይሉን ለማትረፍ በፍጥነት ኃይል ጨምሮ ወደ አንድ አቅጣጫ ማለትም ወደ ፌጥራ ከተማ ተግተልትሎ በመግባት የተለመደውን የፈሪ ብትሩን በፌጥራ ከተማ ንፁሃን ወጣቶች እና ከተማ ውስጥ በተገኙ አዛውንቶች ላይ በድብደባና በማሰር የማይረባ ድርጊቱን ሲፈፅም አምሽቷል ሲል የግንባር መረጃችን ገልጿል።
በሌላ በኩል ከትናንት በስተያ የናደው ክፍለጦር በቀንደኛ ሁለት ባንዳዎች ላይ የማያዳግም እርምጃ መውሰዱን ገልጿል።የክ/ጦሩ ተንቀሳቃሽ ቃኝዎች ለስራ በተሰማሩበት በመርሐቤቴ ላይቤት ወረዳ ከአለም ከተማ በቅርብ ርቀት በምትገኝ ልዩ ስሟ እራስመስክ ቀበሌ ከቀኑ 9:30 ላይ በመከላከያ ተልዕኮ ሰጭነት የፋኖን እንቅስቃሴ ለስለላ እና ከተሰጣቸው ተልዕኮ ጉን ለጎን የፋኖን ስም ለማስጠልሸት በከተማ ቅርብ ርቀት እየዘረፉ ባሉበት እርምጃው ተወስዷል ተብሏል። በዚህም :-
1) አቶ አባወይ አየለና 2) አቶ አስፈራ ቡችሌ ላይ ኦፕሬሽን በመስራት ህዝባችንን ከዘረፋ የገላገለና የአገዛዙን የስለላ መረብ የመበጠሰ ስራ ተሰርቷል ። በእነዚህ ግለሰቦች ላይ በተበደለው ህዝባችን ጥቆማ በፋኖ ጠንካራ መረጃ ማጣራትና ትብብር እርምጃው የተወሰደ ሲሆን አቶ አባወይ አየለ የተባለው ባንዳ ከዚህ ቀደም የናደው ክፍለ ጦር አባል የነበረ እና መሳሪያ ይዞ ከድቶ ለአገዛዙ ያደረና እና ህዝቡን በመካድ የጠላት መንገድ መሪ ሆኖ ሲያገለግል የነበረ በመሆኑ እና ተደጋጋሚ ምክር የተሰጠው ቢሆንም ከጥፋቱ ባለመታረሙ ከእነ ግብረ አበሩ አቶ አስፈራ ቡችሌ የማያዳግም እርምጃ ተወስዶበታል። ክፍለጦሩም ሌሎች ባንዳና የሚሊሻ አባላት ከዚህ በመማር ከእኩይ ድርጊታችሁ ተቆጥባችሁ ወደመደበኛ ሂይወታችሁ ተመለሱ ያለ ሲሆን፤ ለዘረፋ ሲጠቀሙበት የነበረው የጦር መሳሪያም ወደ ክ/ጦሩ ገቢ ተደርጓል ሲል ኮሩ በላከው መረጃ አክሎ ገልጿል።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
አፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ጉና ክፍለ ጦር ገብረ መስቀል ብርጌድ እና ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክፍለ ጦር ለተከታታይ 3 ቀን በጠላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ አድርሰዋል።
ነሐሴ 17/2018 ዓ.ም
የአገዛዙ ኃይል ከነሐሴ 15/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 3 ቀናት በሜጀር ጀኔራል ውባተ አባተ ፩ ኛ ኮር ሁሉም ክፍለ ጦሮች ቀጣና ላይ እንቅስቃሴ ለማድረግ ሞክሮ በርካታ ኃይሉ ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ደርሶበታል።
በዛሬው ዕለትም ነሐሴ 17/2018 ዓ.ም በጉና ክፍለ ጦር ገብረ መስቀል ብርጌድ እና በሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክፍለ ጦር ድንቅ ቅንጅት ከደብረ ታቦር ከተማ በቅርብ እርቀት ቁስቋም፣መድሃኔዓለም ፣ ወርቄ ፣ ቀፎ ቤት እና ወርቅ አጠና ላይ ከፍተኛ ምት አርፎበት 11 አባላቱ ሲደመሰሱ ከ 20 በላይ ደግሞ ከቀላል እስከ ከባድ ቁስለኛ አስተናግዷል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
የሸዋ አማራ የአሳምነው ፋኖ፦ ከደምና ከነፍስ የተሰራ የጽናት ተራራ! በተጋደለ ምድር፣ በነጎድጓዳም ተራራዎችና በሰፊው የሸዋ ሜዳ ላይ ቆሞ የቆሰለውን ልብ የሚያናፍስ ፋኖ የህዝብ ብረት፣ የነፃነት ህያው ጋሻ ነው!
የሸዋ ህዝብ በታሪኩ ለፍትህ፣ ለክብሩና ለአንድነቱ ሲል ህይወቱን አሳልፎ ለመስጠት አንድም ቀን አላመነታም። ይህ የተቀደሰ ህዝባዊ ማዕበል "በአንድ ድምፅና በአንድ አካል" ሲነሳ የተራራው ቁልቁለት በፍቅርና በወኔ ይንቀጠቀጣል፤ ታሪክም የጀግኖችን ስም በወርቅ ብዕር፣ በህዝቡ ልብ ውስጥ ለመጻፍ ይገደዳል።
የህዝብ አለኝታ፦ የደምና የነፍስ ወንድምነት የአንድነት ብረት፦ "በአንድ ድምፅ፣ በአንድ አካል!" የተሳሰሩት የሸዋ ፋኖዎች፣ የህዝባቸውን አለኝታነትና እውነተኛ አባትነት በተግባር አስመስክረዋል።
የተራራዎች ምሽግ፦ ከግርማዊው መንዝ እስከ ሸዋ ሮቢት፣ ከይፋት እስከ ቡልጋ ባሉት ተራራዎችና ሸለቆዎች ውስጥ አደራቸውን በነፍሳቸው ጠብቀው፣ የህዝባቸውን ህልውና በደማቸው ያስከብራሉ።
የማይበገስ ወኔ፦ ለህዝብ ክብርና ለትውልድ ነፃነት ሲሉ መከራንና እንግልትን እንደ ውድ ጌጥ ይቆጥሩታል፤ የጋራ ህልማቸው የህዝብን ፍቅርና ክብር ማስከበር ብቻ ነው። በልብ የሚያስቀረው የጽናት ስንኝ፦ የአማራ ልጅ ጀግና በአንድ ድምፅ በአንድ አካል፣
ሸዋ መከረ ሀገር ጠነከረ!
የህዝቡ አለኝታ የነፃነት ጋሻ፣ ለክብሩ የሚቆም የጽናት መንሻ!"
ይህ የሸዋ አማራ የአሳምነው ፋኖዎች ከወገኖቻቸው ጋር ያላቸውን የማይበጠስ የደም ቁርኝት፣ ጥልቅ ፍቅርና ለሀገር ክብር ያላቸውን ዘላለማዊ ህያውነት ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
ለህዝብ ህልውናና ለሀገር ክብር የቆመ ጽናት መቼም አይወድቅም! #Dave #Amhara
