ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Kanalga Telegram’da o‘tish
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Ko'proq ko'rsatish2 951
Obunachilar
+1424 soatlar
+247 kun
+38330 kun
Postlar arxiv
ዐማራው ራሱን እንደ “ጥቂት”፣ “ተበዳይ” ወይም “ተከላካይ” አድርጎ መሳሉን አቁሞ፣ የቀጣናውን ፖለቲካዊ መዋቅር የመለወጥ አቅም እንዳለው ታላቅ ሕዝብ (Major Hegemonic Force) ማሰብ እንዲጀምር ከአደረጉት ድሮን ዐማራዎች መካከል አንዱ ‼️
ድሮን ነው በራሱ ‼️
ይድነቃቸው ሸዋንግዛው በክንድህ
+4
ጤናው ተሾመ፣ ስመኘው ጥላሁን፣ ታደሰ ደረሰ፣ ሰለሞን ገዛ፣ ተረፈ ተገፉ የተባሉ 5 የአገዛዙ ሰራዊቶች በዛሬው ዕለት 206ኛ ኮርን ተቀላቀሉ።
ሰኔ 7/2018 ዓ.ም
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ጤናው ተሾመ ----ፓራ ኮማንዶ
ስመኘው ጥላሁን --- ሚኒሻ ከየጁቤ በመውጣት 34ኛ ክ/ጦር አብራጂት ሻለቃን ሲቀላቀሉ።
ታደሰ ደረሰ--ከሉማሜ ከተማ
ተረፈ ተጋፉ-- ከአምበር ከተማ
ሰለምን ገዛ--- ከየጁቤ ከተማ በመውጣት 34ኛ ክ/ጦር ተድላ ጓሉ ሻለቃን ተቀላቅለዋል።
በሁለት ቀናት ብቻ 11 የአገዛዙ ወታደሮች 206ኛ ኮርን የተቀላቀሉ ሲሆን ከደብረ ማርቆስ፣ ረቡዕ ገበያ፣ አምበር፣ የጁቤ ፣ሉማሜና ቁይ ወጠው ወደ 14ኛ፣ 24ኛ እና 34ኛ ክ/ጦሮች ሲደርሱ የጀግና አቀባበል ተደርጎላቸዋል ።
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ!
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
+1
ግፍን የተቃዎሙ የአገዛዙ ወታደሮች ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ከስምሪት ቀጠናቸው በመጥፋት ፋኖ በገፍ መቀላቀላቸውን ቀጥለዋል‼️
ወታደሮቹ፦
1, ስናይፐር እና ~ 220 የስናይፐር ተተኳሽ
2, ጥቁር ክላሽ ~ 220 የክላሽ ተተኳሽ
2, ቦምብ በመያዝ ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው በምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 33ኛ ክፍለጦርን ተቀላቅለዋል ሲል የክፍለጦሩ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል አስታውቋል።
ስቦ ማስከዳቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል!
07/10/2018 ዓ.ም
303ኛ አሳምነው ኮር ከአውደ ውጊያ ጎን ለጎን ከማህበረሰቡ ጋር ውይይቶችን አጠናክሮ ቀጥሏል!!
በሰሜን ወሎ አስተዳደር ዞን ላስታ ወረዳ 025 ቀበሌ ድብኮ ክላስተር ከፍተኛ የኮርና የወረዳው ጊዚያዊ ሲቪል መዋቅር አመራሮች በተገኙበት በወቅታዊ ጉዳዮች እንዲሁም ጥልቅ የሆነ የስራ ግምገማ እና የቀጣይ አቅጣጫ ተልዕኮን ጨምሮ ህዝባዊ ውይይትን አካሂደዋል።
ህዝባዊ ውይይቱ ሰኔ 07 ቀን 2018 ዓ/ም ሲካሔድ የ025 ቀበሌ ድብኮ ከተማ ነዋሪዎች በነቂስ በመውጣት ውይይቱ ላይ የተሳተፉ ሲሆን ስለወቅታዊ የሀገሪቱ ሁኔታ፣ ስለ ሰባተኛው የብልፅግና የጨረባ ድህረ ምርጫ፣ ስለ ፋኖ ወቅታዊ አቋም፣ ስለመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችና ሌሎች አጀንዳወችን በማንሳት በብስለትና በጥልቀት ፋኖ ደጀን ከሆነው ህዝቡ ጋር በእልፍኙ መክሯል።
በውይይቱም በሳልና ገንቢ አስተያየቶችና ምክረ ሃሳቦች የተነሱ ሲሆን ድብኮ ከተማ የሚገኙ የሙስሊሙ ማህበረሰቦች አርሲ ላይ የተካሄደው የክርስቲያን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕመናኖች ላይ የተደረገው ዘግናኝ ጭፍጨፋ እጅግ ማዘናቸውንና የድርጊቱ ፈፃሚዎች የኢትዮጵያን መፍረስ የሚፈልጉና በሐይማኖት ሽፋን ሌላ ድብቅ እኩይ ሴራቸውን የሚያራምዱ ስውር እጆች ድርጊት እንጅ ለዘመናት ከሌሎች ሐይማኖቶች ጋር ተቻችሎ የሚኖርን የአባቶቻችን የእነ ሼህ ሁሴን ጅብሪል ሐይማኖት የሆነውን እስልምናን እንደማይወክል ተናግረዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎችም አያይዘው ሰባተኛው የብልፅግና የጨረባ ምርጫ እንደ ላስታ ወረዳ የትኛውም ቀበሌ እንዳልተካሄደ እናውቃለን፣ ሀሰት ሲደጋገም እውነት ነው እንዲሉ በማናውቀው ብልፅግና ተመርጫለሁ ቢል የቁራ ጩኸት መሆኑን ነውና ፋኖዎች የአብራካችን ልጆች እውነተኛ ታጋዮቻችን መሆናችሁን በግልፅ ተረድተናል ከዚህ በኋላ ህዝቡ ከጎናችሁ ነው ሲሉ የመድረኩ ተሳታፊዎች በአንክሮ ተናግረዋል።
በተጨማሪም በትጥቅ ትግል ላይ ብትሆኑም ህዝቡንም እያስተዳደራችሁት የምትገኙት እናንተ በመሆናችሁ አልፎ አልፎ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መቅረፍና ማስተካከል ብትችሉ እንዲሁም ትግሉን በከፍተኛ ግለት ብታስቀጥሉትና ተስፋፊና የውጭ ተላላኪ ከሆነው ብልፅግና በቶሎ እንድታላቁን ሲሉ ተወያዮቹ አስተያየታቸውን ችረዋል።
በመጨረሻም ከህዝቡ የተነሱትን በሳል ምክረ ሃሳቦችንና ጥቆማዎችን በመቀበልና የቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስረፅ ማህበረሰቡ ከፋኖ ጎን መሆን በእጅጉ እንዳስደሰታቸውና ትግሉን በማሳጠር የአማራን ህዝብ ለመካስ ታሪካዊ ኃላፊነት ተሸክመው እንደሚሰሩ ለህዝብ ቃል በመግባትና የቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የኮሩ ከፍተኛ አመራሮችና የፖለቲካ መምሪያ ኃላፊው አርበኛ በሪሁን ደምሌ እንዲሁም የላስታ ወረዳ አመራሮች መድረኩን አጠናቀዋል።
መዳረሻው ድል እና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የ303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት አርበኛ ቢሆነኝ ቢያበይን መረጃውን አድርሷል ።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ!!
ግንቦት 7/2018ዓ.ም
+3
በእነብሴ ሳርምድር ወረዳ ከዞባር ይቋንዳ ቀበሌ ነዋሪወች ጋር ህዝባዊ ውይይቶች እንደቀጠሉ ናቸው
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
.........ሰኔ 7/2018 ዓ.ም
በውይይቱም ላይ አመራሮቹ በቅድሚያ የትግሉን አሁናዊ ቁመና እና የድርጅቱን አቅም በማስረዳት አሁን ላይ ከጠላት የተሻለ ድፕሎማሲያዊ ቅቡልነትን በመፍጠሩ ቀጠናዊና አለማቀፋዊ ተቀባይነቱም በመጨመሩ በርካታ አጋር ሀይሎችንም በማፍራቱ በአጭር ጊዜ ድል ማድረግ እንደሚችል አብራርተዋል፤ በማህበረሰቡም በኩልም ለተነሱ ጥያቄወች በአመራሮቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
በቀበሌው ውስጥ በሚያገለግሉ የቀበሌ ጊዚያዊ አመራሮች ላይ ሰፊ የሆነ ሀሳቦችን በመስጠት ግንባታ የሚያስፈልጋቸውን በመለየት በቀጣይ በጥያቄዎች መሰረት የማስተካከል ስራ በመስራት በቀጣይ መመሪያና የስራ አቅጣጫ ተሰጥቷቸዋል።
የአማራ ህዝብ የትግሉ ባለቤት በመሆኑ በየጊዜው በመገኘት የማህበረሰብ ችግሮችን እያወያዩ በመለየት አስቸኳይ መፍትሄዎችን የመስጠት ሂደቱንም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በአፅኖት ተናግረዋል።
የእነብሴ ሳርምድር ወረዳ ጊዜያዊ መንግስት ኮምንኬሽን
+3
ቢቡኝ ወረዳ ደብረሲና አስማረ ቀበሌ ህዝባዊ ውይይት ተካሔደ
"""""""""“""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""" """"""
ሰኔ 07/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር የቢቡኝ ወረዳ ጊዜያዊ መንግስት አስተዳር መልካም አስተዳደር በአደረጃጀት በማፅናት በአፋብን የአደረጃጀት መምሪያ ቅፅ መሰረት ሁሉንም ቀበሌ አደራጅቶ እየመራ ሲሆን በደብረ_ሲና አስማረ ቀበሌ የህዝብ መድረክ ማካሄድ ተችሏል።
የደብረሲና አስማረ ቀበሌ መልካም አስተዳደር ና ፀጥታና ደህንነት በመገምገም የፍትህ አሰራርን ማዘመን መኖር የአማራን ህዝብ በትናንት ማንነቱና ታሪኩ እንዲቀጥል በየዘርፉ ማህበረሰቡን ማገልገል ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጥቷል።
በቢቡኝ ወረዳ ወይንዉሃ ንዑስ ከተማ የአማራን የህልዉና ትግል ችቦ ለኳሽ እንደመሆኑ ታራኩን የሚያውቅና በታሪኩ የሚኮራ ማህበረሰብ ፤ የህልዉና ትግል ቡራኬ ተቋዳሽ እንደነበር በማስረዳት ትግላቸዉን ማስቀጠልና የነገ እጣ ፈንታ በእጃችን እንደሚፃፍ ሰፊ ስራ ተሰርቷል።
አዲስ ትውልድ፣አዲስ ተስፋ፣ አደስ አስተሳሰብ
አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር የቢቡኝ ወረዳ ጊዚያዊ መንግስት ሚዲያና ግንኙነት
+4
የቢቡኝ ወረዳ ጊዜኣዊ መንግስት በፍትህ ዘርፉ ላሉ የቀበሌ ፍርድ ሸንጎ አመራሮች ስልጠና ተሰጠ።
^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^
ሰኔ 7/2018ዓ.ም
የቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክፍለ ጦር የቢቡኝ ወረዳ ጊዜአዊ መንግስት የፍትህ አካላትን አቅም ከፍ ለማድረግ በማስብ፣እንዲሁም የአማራ ህዝብ ለብዙ ዘመናት አጥቶ የነበረዉን የፍትህ አገልግሎት ለማሳለጥ ኮሩ ባስቀመጠዉ አቅጣጫ መሰረት በወረዳዉ ዉስጥ ላሉ ከሁሉም ቀበሌዎች የማህበራዊ የፍትህ አገልግሎት ሰጭዎች ስልጠና ሰጠ።
በመድረኩ የ54ኛ ክፍለ ጦር የህግ ክፍል ሰብሳቢ ፣የቢቡኝ ወረዳ ጊዜአዊ መንግስት ሰብሳቢ።የቢቡኝ ወረዳ ጊዜአዊ መንግስት የፍትህ ክፍል ተጠሪ ተገኝተዋል።በመልዕክታቸዉም ለህዝባችን በቅንነት የፍትህ አገልግሎት መስጠትና በቀጠናው የህዝብ አስተዳደር ፤ የፍትህ መመሪያዎችን ከህግ አንፃር መተግርና መፈፀም እንዳለባቸው መልዕክት ተላልፏል።
አማራዊ ህግ አዋቂነት፤ አማራዊ የሽምግልና እሴት ብሎም የትናንት ሀገረ መስራችነትን ሳንረሳ ስለሀገር(ስለህዝብ) እንመክራለን፤ እንሰራለን።
አዲስ ትውልድ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ!
አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር
የቢቡኝ ወረዳ ጊ/መንግስት
የጀግናው አማር ታዘዘ የፊስቡክ አካውንት ነው ይወዳጁት!!
https://www.facebook.com/profile.php?id=61590766434419
"ከአይናችን ይልቅ አንተን በስስት እንጠብቃለን"
የአማራ ህዝብ አንድ የሚተማመንበት ኃይል ቢኖር መሪያችን አርበኛ ዘመነ ካሴ ትግሉ ነው። ጅረት፣ ወንዝ ፣ተራራ፣ ሸለቆ፣ አውራጃና መንደር በሱ ፊት እጅግ ፀያፍ ምልከታዎች ናቸው በርግጥ ይህ ለእኛም እጅግ አስነዋሪ አመለካከት ነው።
እጅግ ብዙ ስራ አለብን፤ ፋታ የማይሰጡ ተደራራቢ ኃላፊነትም ተሸክመናል፤ የትኛውንም ተልዕኮ ተቀብለን በቁርጠኝነት የምንደክመው የመሪያችንን ራዕይና የድርጅታችንን ግዳጅ ጫፍ ለማድረስ ነው ። በዚህ ሒደት ጠላት ከጀርባችን የሚጎነጉናቸውን የተንኮል ሹርባዎችን በጥበብ እያፍታታን ትግሉ በሚፈልገው ልክ አስቀምጠናቸዋል።
የኛስ የኛ ነው ! በመሪያችን ላይ የሚደረገው ዘመቻ ግን አይናችንን በሜንጦ የማውጣት ያክል እጅግ አደገኛ አካሔድ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፤ ከጠላት የደህንነት ክንፍ እስከ ሚዲያ ግሪሳ የሚታየው መንቀዣቀዥ ዓላማው ይታወቃል ።
ለጠላትም ለወገንም "ጆከር" ሁኖ መቀጠል አይቻልም። ትግሉ ስክነትን፣ ፅናትን እና አንድነትን ይፈልጋል የውሾችም የግመሎችም ሀብል በእጃችን ነው በሶስት አመት የትግል ሒደት አይናችንን ጨፍነን አናውቅም አንቀላፍተን ያለፈን ጉዳይም የለም ።
ትግል ያለ ህዝብ፤ ህዝብ ያለ ድርጅት፤ ድርጅት ያለ መሪ ከንቱ ነው።
መሪያችንን አርበኛ ዘመነ ካሴን መጠበቅ የትግላችን ዶግማ ሁኖ ይቀጥላል።
የሸዋው ነበልባል፡ የዲሽቃው ንጉስ ፋኖ አርበኛ እሸቱ በቀል!!
የቀድሞው የአማራ ልዩ ሀይል አባል የአሳምነው ቀኝ እጅ የዛረው የሰባት ለሰባ ክፍለጦር ከፍተኛ አመራር በታሪክ ማህደር ውስጥ አንዳንዶቹ ስማቸው በቀለም ሳይሆን በጀግንነት ደምና በነፃነት አሻራ ይፃፋል። ከእነዚህ ታሪካዊ ክስተቶች መካከል የክብር ስሙ የሚነሳው ፋኖ አርበኛ እሸቱ ነው!
ይህ አይበገሬ ታጋይ፣ የአባቶቹን የጀግንነት ታሪክ በአዲስ ምዕራፍ እየደገመ የሚገኘው በታሪካዊቷ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት በአሳምነው ዕዝ ስር በሚንቀሳቀሰው በዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር የሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር ውስጥ ነው። የትውልድ ሃረጉ ደግሞ የማይደፈሩ ጀግኖች ማህፀን ከሆነችውና አንገቷን ለባዕድና ለወራሪ ካልደፋችው ከኤፍራታ ግድም ወረዳ ይመዘዛል።
የኤፍራታው አንበሳ አርበኛ እሸቱ በቀለ በኤፍራታ ግድም ወረዳ ተራሮችና ሸለቆዎች መሃል ሲያድግ፣ ከማንኛውም ነገር በላይ የኮራው በአባቶቹ የነፃነት አየርና የፈረስ ኮቴ ድምፅ ነው። ሀገርና ወገን ታሪካዊ ፈተና ውስጥ ወድቀው፣ ህልውና ሲደፈር ግን ይህ ወጣት የቁርጥ ቀን ልጅ ዝምታን አልመረጠም ይልቁኑ መረር ያለውን የትግል መንገድ መረጠ። ዛሬ እሸቱ ግንባር ላይ ተራ ተዋጊ አይደለም፤ የከባድ መሳሪያው የዲሽቃ ንጉስና እውነተኛ መሃንዲስ ነው እንጂ! እሸቱና የዲሽቃው ምት የማይነጣጠሉ አንድ አካል ሆነዋል። እርሱ የዲሽቃውን ቀስቅስት አቅንቶ፣ ወደ ጠላት ምሽግ ሲያነጣጥር፣ የጠላት ምሽግ እንደሚናድ፣ የጋሻ ጃግሬው ሰራዊት ደግሞ የድል ስነ-ልቦናው ሰማይ እንደሚነካ የታመነ ነው። እርሱ ሲተኩስ የዲሽቃው ድምፅ ለጠላት መርዶ፣ ለወገን ደግሞ የነፃነት ዜማ ነው።
የአብይ አህመድ ወራሪና አየር ወለድ ሰራዊት የንፁሃንን መንደር ረግጦ በገባበትና ጦርነት በጫረበት ስፍራ ሁሉ፣ አርበኛ እሸቱ እንደ እሳት ነበልባል ቀድሞ ይገኛል። "ጠላት በገባበት ገብቶ መምታት፤ ምሽግ በሰራበት ቆፍሮ መቅበር" የእርሱና የክፍለ ጦሩ የማይታጠፍ መመሪያ ነው። የጠላት አየር ወለድ ሰራዊት በትጥቅ ብዛትና በልዩ ስልጠና ተመክቶ ቢመጣም፣ በአርበኛ እሸቱ የዲሽቃ እሳት ግንባር ግንባሩን እየተመታ ስልቱና ሃይሉ እንደ ጉም በኖ ቀርቷል።
የሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር የሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር አባላት በኩራት እንደሚመሰክሩት፣ እሸቱ ዲሽቃውን ይዞ አውድማውን መምራት ሲጀምር የጠላት አየር ወለድ ሰራዊት መሸሸጊያ ያጣል። በገባበት እየገባ፣ ምሽጉን እየሰበረና የተደራጀውን የጠላት ሃይል በመበተን የሰራቸው ጀብዱዎች በኤፍራታ ግድም ሸለቆዎችና በሸዋ ምድር ላይ ዛሬም በክብር ይነገራሉ።
የማይበገረው የነፃነት ፋና አርበኛ እሸቱ የኤፍራታ ግድም ወረዳ ለአሳምነው ዕዝ ያበረከተችው፣ በታሪክ የሚታወስ ድንቅ የቁርጥ ቀን የቁርጥ ልጅ ነው። የእርሱ ቆራጥነት፣ የማያወለውል ጀግንነትና በዲሽቃ መሳሪያ የሚሰራው ተአምር ለፋኖ ታጋዮች ታላቅ ብርታት፣ ለጠላት ደግሞ መርዶና የፍርሃት ምንጭ ሆኖ ቀጥሏል። ይህ ጀግና ዛሬም በጦር ግንባር ላይ ታሪክ እየሰራ፣ የነፃነትና የክብር ምልክት ሆኖ የአባቶቹን አደራ እየጠበቀ ይገኛል።
አማራ ታዘዘ የዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር ህዝብ ግኑኝነት ኃላፊ
የሸዋው ነበልባል፡ የዲሽቃው ንጉስ ፋኖ አርበኛ እሸቱ በቀል!!
የቀድሞው የአማራ ልዩ ሀይል አባል የአሳምነው ቀኝ እጅ የዛረው የሰባት ለሰባ ክፍለጦር ከፍተኛ አመራር በታሪክ ማህደር ውስጥ አንዳንዶቹ ስማቸው በቀለም ሳይሆን በጀግንነት ደምና በነፃነት አሻራ ይፃፋል። ከእነዚህ ታሪካዊ ክስተቶች መካከል የክብር ስሙ የሚነሳው ፋኖ አርበኛ እሸቱ ነው!
ይህ አይበገሬ ታጋይ፣ የአባቶቹን የጀግንነት ታሪክ በአዲስ ምዕራፍ እየደገመ የሚገኘው በታሪካዊቷ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት በአሳምነው ዕዝ ስር በሚንቀሳቀሰው በዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር የሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር ውስጥ ነው። የትውልድ ሃረጉ ደግሞ የማይደፈሩ ጀግኖች ማህፀን ከሆነችውና አንገቷን ለባዕድና ለወራሪ ካልደፋችው ከኤፍራታ ግድም ወረዳ ይመዘዛል።
የኤፍራታው አንበሳ አርበኛ እሸቱ በቀለ በኤፍራታ ግድም ወረዳ ተራሮችና ሸለቆዎች መሃል ሲያድግ፣ ከማንኛውም ነገር በላይ የኮራው በአባቶቹ የነፃነት አየርና የፈረስ ኮቴ ድምፅ ነው። ሀገርና ወገን ታሪካዊ ፈተና ውስጥ ወድቀው፣ ህልውና ሲደፈር ግን ይህ ወጣት የቁርጥ ቀን ልጅ ዝምታን አልመረጠም ይልቁኑ መረር ያለውን የትግል መንገድ መረጠ። ዛሬ እሸቱ ግንባር ላይ ተራ ተዋጊ አይደለም፤ የከባድ መሳሪያው የዲሽቃ ንጉስና እውነተኛ መሃንዲስ ነው እንጂ! እሸቱና የዲሽቃው ምት የማይነጣጠሉ አንድ አካል ሆነዋል። እርሱ የዲሽቃውን ቀስቅስት አቅንቶ፣ ወደ ጠላት ምሽግ ሲያነጣጥር፣ የጠላት ምሽግ እንደሚናድ፣ የጋሻ ጃግሬው ሰራዊት ደግሞ የድል ስነ-ልቦናው ሰማይ እንደሚነካ የታመነ ነው። እርሱ ሲተኩስ የዲሽቃው ድምፅ ለጠላት መርዶ፣ ለወገን ደግሞ የነፃነት ዜማ ነው።
የአብይ አህመድ ወራሪና አየር ወለድ ሰራዊት የንፁሃንን መንደር ረግጦ በገባበትና ጦርነት በጫረበት ስፍራ ሁሉ፣ አርበኛ እሸቱ እንደ እሳት ነበልባል ቀድሞ ይገኛል። "ጠላት በገባበት ገብቶ መምታት፤ ምሽግ በሰራበት ቆፍሮ መቅበር" የእርሱና የክፍለ ጦሩ የማይታጠፍ መመሪያ ነው። የጠላት አየር ወለድ ሰራዊት በትጥቅ ብዛትና በልዩ ስልጠና ተመክቶ ቢመጣም፣ በአርበኛ እሸቱ የዲሽቃ እሳት ግንባር ግንባሩን እየተመታ ስልቱና ሃይሉ እንደ ጉም በኖ ቀርቷል።
የሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር የሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር አባላት በኩራት እንደሚመሰክሩት፣ እሸቱ ዲሽቃውን ይዞ አውድማውን መምራት ሲጀምር የጠላት አየር ወለድ ሰራዊት መሸሸጊያ ያጣል። በገባበት እየገባ፣ ምሽጉን እየሰበረና የተደራጀውን የጠላት ሃይል በመበተን የሰራቸው ጀብዱዎች በኤፍራታ ግድም ሸለቆዎችና በሸዋ ምድር ላይ ዛሬም በክብር ይነገራሉ።
የማይበገረው የነፃነት ፋና አርበኛ እሸቱ የኤፍራታ ግድም ወረዳ ለአሳምነው ዕዝ ያበረከተችው፣ በታሪክ የሚታወስ ድንቅ የቁርጥ ቀን የቁርጥ ልጅ ነው። የእርሱ ቆራጥነት፣ የማያወለውል ጀግንነትና በዲሽቃ መሳሪያ የሚሰራው ተአምር ለፋኖ ታጋዮች ታላቅ ብርታት፣ ለጠላት ደግሞ መርዶና የፍርሃት ምንጭ ሆኖ ቀጥሏል። ይህ ጀግና ዛሬም በጦር ግንባር ላይ ታሪክ እየሰራ፣ የነፃነትና የክብር ምልክት ሆኖ የአባቶቹን አደራ እየጠበቀ ይገኛል።
አማራ ታዘዘ የዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር ህዝብ ግኑኝነት ኃላፊ
+3
ከደብረ ማርቆስ ወደ ስናን ሬሽን ለማቀበል በተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ላይ 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ስናን አባ ጅሜ ሻለቃ ባደረገው ማጥቃት 20 የአረመኔው ሰራዊት ሲደመሰሱ 12 የሚደርሱ ከባድ ቁስለኛ ሁነው 3 ክላሽ ፣ 1050 ጥይት ተማርኳል።
(አፋብን 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ) ሰኔ 7/2018 ዓ.ም
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
የአረመኔው ሰራዊት የ6ኛ ዕዝ 602ኛ ኮር 75ኛ ክ/ጦር ከደብረ ማርቆስ ተነስቶ ወደ ስናን ረዕቡ ገበያ ሬሽን ለማቀበል እየተንቀሳቀሰ ባለበት 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ስናን አባ ጅሜ ሻለቃ ባደረገው ማጥቃት 20 የጠላት ወታደሮች ሲደመሰሱ 12 የሚደርሱት ቁስለኛ ሁነዋል።
በተፈፀመው ፈጣን ጥቃት የጠላት መስመራዊ መኮንኖች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን ፻ አለቃ ታሪኩ በቀለ ባቲሳ የሻለቃ አዛዥ ይገኝበታል።
ጠላት በአልጠበቀው ስዓት በተከፈተበት ተኩስ አስክሬን ሳያነሳ ፈርጥጦ 3 ክላሽ፣ 1050 ጥይት ትጥቆችና ወታደራዊ ቦርሳዎች ተማርኳል።
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ!
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት
የምራብ ጎጃም ዞን ፍ/ሰላም ጃቢ ጠህናን በውስጡ 7 ወረዳዎች እና 44 የገጠር ቀበሌዎች ያሉት ሲሆን
ተወካይ ያስፈልገናል ስንል በምክንያት ነው !!
⏭ ከ6000ሽ በላይ የአባት አርበኞች ያሉበት
⏭ ጠንካራ የቀበሌ መዋቅር የተዘረጋበት
⏭ ፍትህ የነገሰበት ህግና ስነስርአት የሚሰጥበት
⏭ የአርበኞች ልጆች ልበ ሙሉ ___ፋኖዎች ያሉት
መርህና መሪ አክባሪ ፤
መሬት የወረደ ስራ ሰሪ፤
ባህልና እምነቱን አክባሪ፤
እሴትና ወጉን ሰሪ፤
አናት አባቱን ጧሪ ።
እሪዎትና አላማውን ሰንቆ ፤
ጥቅምን ስልጣን ንቆ ።
ማህበረሰቡን ጠብቆ ባቆየ እንዴት ተወካይ ይጣ?
ይድረስ ለሚመለከተው ሁሉ:- ምነው ሰው አጣችሁ?
1,ገብረ መድህን እንየው የእውነት ሰው ሀገርን ከነታሪኩ፣ባህልን ከነ አኗኗሩ፣ አባትነትን ከነ ጥበቃው፣ ትንቢት ተንብየው ቀድመው አንቅተው፣ እውቀትን ሰንደው ፅፈው ያነቁትን ያፈራች ሀገር
2,ጋሽ አለማየሁ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ስልጠናወችና ልምዶችን የሰጡ
የተሻለ የረጅም ጊዜ የፖለቲካ ልምድ ያላቸው በዚህ እድሜያቸው የቀሰቀሱ ያማከሩ ያበረቱ የመነቁ
3, አታላይ ሞሴን
ከአባልነት ሻለቃ ብርጌድ ክፍለጦር እዝ በሂደት የተገኘ ሰፊ ሀሳብ ያለው የሀገር ባለውለታ
4,ዶ/ር ጌታቸው የጦሩ ቀኝ እጅ ባለውታ እግዚአብሔር የሰጠን ቅን አገልጋይ!!
ለዚህ ደግሞ ህዝብ ምስክር ነው ።
ለታመመም ሁሉ እውቀቱንና ሙያውን ጨለማና ብርደድ ሳየገድበው ያከመ።
አቅዶ የህክምናን መስመር የዘረጋ
⏭ ድልነሳ መኮነን- ኢንጂነሩ ጦረኛ
⏭ አበረ ምናሉ - የደፈጣው አጥቂ
⏭ ግርማ ስማቸው -ጀብደኛው ተዋጊ
⏭ አንዷምላክ አወቀ - የአቢወት መሪ
⏭ የሽዋስ ምህረቴ - ታጋሹ ጦር ጠበብት
⏭ ፲ አለቃ አብርሀም በላይ - የጦሩ መሀንዲስ
⏭ ፲አለቃ ይታይህ - የጦሩ መቅጫ
⏭ ዳዊት አስማረ - ዝምተኛው ገዳይ
⏭ መዝገብ የሮም- አልሞ ተኳሹ
⏭ ፍስሀ አደራው - የብዕር ባለቤት
⏭ ክብሮም አማረ - የተግባርና የመርህ ሰው
⏭ አንዳርጌ የእቅዱ ዶክተር
⏭ ደርብ አላዩ ጥበቀኛ መሪ
⏭መንግስቱ አለማየሁ ድበር አስጠባቂ የአቢዮቱ ቀስቃሽ
⏭ ሰሎሞን ፀጋየ- ደጀንንና ደህንነት አስጠባቂ
እንዴው ድከሙ ቢለን ዘርዝረን ላንጨርስ
ብዙ የደበቅናቸው የጭንቅ ቀን ደራሾችን ቢኖሩም
በሙያዊ ጥበብ
በመሪነት ጥበብ
ተዋግቶ በማዋጋት
ማርኮ በማስታጠቅ
ኩሩ የሆኑ የተማሩ የህዝብ አገልጋይና ጠባቂ በሞላበት ሀገር
ስራ አስፈፃሚ ተወካይ ያስፈልጋታል ስንል በምክንያት ነው ። የግል ጥቅምና አፈንጋጭ ለማስታገስ የሚሰራን ስራ እንቃወማለን። እንብለጥ አንልም ግን ሁሉን አቀፍ የሆነ ስራ እንዲሰራ እንፈልጋለን ሰማዓት ለሆኑ ወድሞች
እደሀገርም ሊጠቅምና ሊበጅ ሚችል ሀሳብ ነው።
⏭ አርበኛ ምናሉ መንገሻ ሀገር
⏭ የአርበኛ ነብዩ ጌትነት ሀገር ፍኖተ ሠላም!!
የዓላማ ጽናት ድል፦
አንድ ሰው እንዴት ተራራን እንደናደው….
እውነተኛ ጥንካሬና ጽናት የሚወለደው ከጥልቅ መከራና ከባድ ፈተናዎች ውስጥ ነው። በህንድ ግዛት በቢሃር (Bihar)፣ በጋያ ወረዳ (Gaya district) ልዩ ስሟ ጌህላውር (Gehlaur) በሚትባል መንደር ውስጥ፣ ዳሽራት ማንጂ (Dashrath Manjhi) የተባለ ፈጹም ደሀ ገበሬ የማይገመት ትልቅ አሳዛኝ አደጋ ገጠመው።
ለዓመታት ባለቤቱ ፋልጉኒ ዴቪ (Falguni Devi) በእርሻ ቦታ ላይ ምሳ ልታደርስለት በየቀኑ አደገኛና ድንጋያማ የሆነውን የተራራ ሸንተረር ትወጣ ነበር። ነገር ግን፣ በአንድ በጎዶሎ ቀን ተራራውን ስትወጣ ተንሸራታ ወደቀች። በቅጽበት ከተራራው ግርጌ ተገኘች። በጣምም ጉዳት ደረሰባት። በአቅራቢያው የነበረው ሐኪም ከዚያ ግዙፍ የድንጋይ ግንብ ጀርባ ከ55 ኪሜ በላይ ርቆ በመገኘቱ ምክንያት፣ የህክምና እርዳታ በሰዓቱ ሳይደርስላት ህይወቷ አለፈ።
በሀዘን ክፉኛ የደቀቀው ዳሽራት ማንጂ ከእንግዲህ ማንም ሰው በእንደዚህ ዓይነት መሰናክል ምክንያት ተመሳሳይ ዕጣ ፈንታ ሊደርስበት አይገባም በማለት ቆረጠ። ምንም ዓይነት ገንዘብ፣ ዘመናዊ ማሽነሪ ወይም የውጭ አካል ድጋፍ ሳይኖረው፣ የቤተሰቡን ብቸኛ ንብረት የነበሩትን ሶስት ፍየሎች በመሸጥ መዶሻ፣ ቺዝል (የድንጋይ መውቂያ) እና የብረት ማንሻ ዘንግ ገዛ። ዓይኖቹን ወደ ተራራው አማተረ። በክንዶቹ ልከፍላቸው ወሰነ። ወደ ተራራውም በፍጹም ቁጭት ተንደረደረ።
ዳሽራት ማንጂ ለዚህ ቅዱስ ዓላማ ራሱ ስያጭ ከገንዘብ እጦት በላይ ፈተና የነበረበት ማህበራዊ ጫናው ነበር። የአካባቢው ሰዎች የእሱን ፍላጎትና ታላቅ ህልም እንደ እብድነት በመቁጠር በግልፅ ፈረጁት። ሌላው ቀርቶ የገዛ አባቱ የማይሳካ ህልም ላይ ህይወቱን በከንቱ እያባከነ እንደሆነ በማመን አጥብቆ በአደባባይ ወቀሰው።
በዚህ ሁሉ ሳይበገር፣ የቀን አድካሚውን የእርሻ ስራ ከሌሊቱ የማይታክት የድንጋይ መውቀጥ ስራ ጋር እያቀናጀ፣ አካላዊ ድካም ሙሉ በሙሉ እስኪያሸንፈው ድረስ ተራራውን መናዱን ጀመረ። በመጨረሻም፣ ቤተሰቡ ከባድ የኢኮኖሚ ችግር ውስጥ ቢወድቅም እንኳ፣ የእርሻ ስራውን ሙሉ በሙሉ ትቶ በተራራው ላይ ብቻ ሙሉ ጊዜውን ለመስጠት ወሰነ።
ከባድ ድርቅ አካባቢውን መትቶ መላው የመንደሩ ህዝብ ንብረቱን ጠቅልሎ እንዲሰደድ ባስገደደው ጊዜ እንኳ፣ እሱ ግን የተረከበውን ታላቅ ተልዕኮ ለመተው አልፈቀደም። በዚያ ምድረ በዳ ውስጥ ብቻውን ሆኖ፣ በከፍተኛ ጫና ውስጥ አዳዲስ ዘዴዎችን ፈጠረ። በድንጋዩ ላይ ማገዶ በማቃጠል እና ቀዝቃዛ ውሃ በመርጨት የሙቀት ልዩነትን (Thermal Shock) በመጠቀም ግትር የሆነውን የድንጋይ አካል እንዲሰነጠቅ አደረገ። ፍርስራሹንም በየቁርጥራጩ ሙሉ በሙሉ በእጁ አስወገደ።
ሃያ ሁለት ዓመታትን ሙሉ በሙሉ ለእዚህ ዓላማ መገዛቱና የማይናወጥ ጽናቱ በመጨረሻ ታላቅ ታሪካዊ ድል አስገኘለት። በተራራው ውስጥ በቀጥታ 110 ሜትር ርዝመት እና 9.1 ሜትር ስፋት ያለውን መንገድ በተሳካ ሁኔታ ጠረገ።
ይህ አቋራጭ መንገድ ከመሰራቱ በፊት ነዋሪዎቹ ወደ አቅራቢያ ወዳለው ከተማ ለመድረስ ከተራራው ጌርጌ ታክኮ የተሰራውን ጠመዝማዛውን የ55 ኪሎሜትር መንገድ ይጓዙ ነበር። እሱ በሠራው መንገድ ምክንያት ግን አጠቃላይ የጉዞ ርቀቱ ወደ 15 ኪሎሜትር ብቻ ዝቅ ሊል ችሏል። ይህም ማለት ዳሽራት ማንጂ የሰዎችን የጉዞ ርቀት በ40 ኪሎሜትር በማሳጠር፣ ሰዓታት ይፈጅ የነበረውን አድካሚ መንገድ ወደ ጥቂት ደቂቃዎች ቀይሮታል። በአንድ ወቅት «እብድ ነው» ብለው ያጣጣሉት እነዚያው ተቺዎች፣ በመጨረሻ የእሱን አስደናቂና ታላቅ መንፈስ በመገንዘብ «ባባ» (ቅዱስ ሰው) የሚል የክብር ስም ሰጥተውታል።
እናማ ወዳጆቼ የአማራ ህልውና ትግል፣ የእያንዳንዱ የፋኖ ተጋድሎ ልክ እንደዚህ ጀግና የህይወት ምዕራፍ ታርክ ነው። ሀገሩ በክፉ ሰው እጅ ሁና ሙታበት፣ የአማራ ማህበረሰብ ማህበራዊ ዕረፍት ተነፍጎ እና ለህልውና ስጋት ተጋልጦበት፣ ሰሚ ስጠፋ ልክ እንደ ዳሽራት ማንጂ በሀዘን ክፉኛ ብደቅም ያለውን ይዞ ሆ ብሎ ከቤቱ ወጣ። ተራራ አክሎ የኖረውን የጠላት ኃይል እየናደው አጋመሶታል። ክብር ለሰማይታት። ትግሉም ይቀጥላል። በድልም ይጠናቀቃል።
