uz
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Kanalga Telegram’da o‘tish

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Ko'proq ko'rsatish
2 935
Obunachilar
-124 soatlar
+3307 kun
+38330 kun
Postlar arxiv
ከአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር የተሰጠ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሀምሌ 04/2018 ዓ.ም ~~~~~ ለእነማይ ወረዳ እና ሸበል በረንታ ወረዳ ለቤቶች ማህበር የቦታ መሬት ተደራጅተው ለሚጠብቁ ለማህበሩ አባላት በሙሉ፤ የአማራ ሕዝብ በገዛ አገሩና ቀዬው ላይ ተፈናቃይ፣ ተሰዳጅ፣ ታጋች፣ ይባስ ብሎ በደመ ነፍስ እንደሚንቀሳቀሱ ከብትና በሬ እየታረደ ብዙ ጊዜ የመከራ ቀንበር ተጭኖበት ከመንግሥታዊ መዋቅር ተገልሎና ተገፍቶ መቆየቱ ይታወቃል። ይሁን እንጂ ይህ የመከራ ጊዜ ፅዋው ሞልቶ ሲፈስ የአማራ ሕዝብ ከሰላማዊ ትግል፣ ከሰልፍ ወደ ሰይፍ የትጥቅ ትግል ከገባ ወደ 3ኛ ዓመቱን ማስቆጠር ችሏል። በዚህ የ3 ዓመት የትጥቅ ትግል ቆይታ ለአገራቸውና ለማንነታቸው ሲሉ ብዙዎች ቆስለዋል፣ ደምተዋል፣ አካላቸውን አጥተዋል። ብዙዎች የሕይወት መስዋዕትነትን ከፍለዋል፣ ዛሬም እየከፈሉ ይገኛሉ። ነገር ግን ይህ እየሆነ ባለበት ሁኔታ፣ ከአገራቸው ማንነት ይልቅ ለራሳቸው ክብርና ጥቅም ያስቀደሙ፣ የአማራን የከፍታ ማማ በተራ ጥቅም የቀየሩና ያዋረዱ፤ በእነማይ ወረዳ ቢቸና ከተማ፣ በሸበል በረንታ ወረዳ የዕድውሃ እና መርገጭ ዙሪያ የምትገኙ የቤቶች ማህበር አባላት ቦታ ለማግኘት እየተሳተፋችሁ የምትገኙ መሆኑን አውቀናል። ስለሆነም 64ኛ ክፍለ ጦር ሠራዊት በትግላችን ብዙ መስዋዕትነት እየከፈለ መሆኑን እያወቃችሁ፣ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ጉዳዮች ጥሶ የተገኘ ግለሰብ፣ ማህበር ወይም ድርጅት ላይ ተቋማዊ እርምጃ የምንወስድ መሆኑን በጥብቅ ማሳሰብ እንወዳለን፦ ከሐምሌ 27/2015 ዓ.ም ጀምሮ በሊዝ ጨረታ የተገዛ挑战፣ የብልፅግና ካቢኔ挑战፣ ሚሊሻ፣ ፖሊስ እና የባንዳ ተንቀሳቃሽም ይሁን ቋሚ ንብረት፤ ከሐምሌ 27/2015 ዓ.ም ጀምሮ የቦታ ምሪት የተመራና የገዛ አካል። ከዚህ ጋር ተያይዞ በእነማይ እና ሸበል በረንታ ወረዳ ላይ አገዛዙ "በቦታ ካሳ ሰበብ" በሚል የገንዘብ መሰባሰቢያ ዘዴ ዘይዶ የአማራን ሕዝብ የህልውና ትግል ለማኮላሸትና የሕዝባችንን የመከራ ጊዜ ለማርዘም እየሠራ እንደሚገኝ ይታወቃል። የአማራ ሕዝብ በህልውና አደጋ ውስጥ ባለበት ጊዜ ለአገዛዙ የጊዜ ማራዘሚያ የሚሆን የቦታ ካሳ ገንዘብ የሚከፍል አካል ካለ፣ የሕዝባችንን የስቃይና የመከራ ጊዜ ማራዘምና አገዛዙን በፋይናንስ እንደመደገፍ ስለሚቆጠር፣ በዚህ ድርጊት የሚሳተፍ ማንኛውም አካል የካሳ ብር እንዳይከፍልና ከዚህ ድርጊት እንድትቆጠቡ በጥብቅ እያሳሰብን፣ በዚህ ድርጊት በሚሳተፉ የትኞቹም አካላት ላይ አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክፍለ ጦር እርምጃ የሚወስድ መሆኑን እንገልጻለን። አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክፍለ ጦር!

መረጃ፤ የአዊ ዞን ፖሊስና ሚኒሻ ጭንቅ ጥብብ ብሎታል። ከሰሞኑ ወደ ግንባር ትዘምታላችሁ መባሉን ተከትሎ በ"ክልሉ" የሚኖሩ የፖሊስና ሚኒሻ አባላት በጠቅላላ ጭንቅ ውስጥ መሆናቸውን በተጨባጭ መረጃ ስንሰማ መቆየታችን ይታወቃል። ይህን ተከትሎም ከየአሃዱ እየጠፋ እየተናደ ይገኛል። ለምሳሌ ያህል በአዊ ዞን ዛሬን ጨምሮ በዚህ ሁለት ሦስት ቀናት ብቻ ከ57 በላይ አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው አሻፈረኝ ብለው አብዛኛዎቹ ፋኖን የተቀላቀሉ ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ ወደ ቤተሰቦቻቸው በሰላም ተሸኝተዋል። ይህ ወደ ወገን የመሠባሰብና አፈሙዝን የጋራ ወደሆነው ጠላት የማዞር ሂደት በተጨባጭ ቀጣይነት የሚኖረው ይሆናል። ዛሬ በደረሰን ተጨባጭ መረጃ መሠረት በአዊ ዞን የሚገኙና ወደ ግንባር እንዲዘምቱ እጣ የደረሳቸው(የወጣባቸው) የፖሊስና የሚኒሻ አባላት መዝመት አንፈልግም ማለታቸውን ተከትሎ "አንዘምትም ካላችሁ ብር ክፈሉና ትቀራላችሁ" ተብለው ከፍተኛ ገንዘብ እየከፈሉ ይገኛሉ። ብር የሌላቸው ፖሊስና እና ሚኒሾች ደግሞ ቤታቸውን በማስያዣነት ተጠቅመው ከአብቁተ(ፀደይ ባንክ) ብር እየተበደሩ እየከፈሉ መሆኑን አረጋግጠናል። እንደ አብነት የአዊ ዞኑን አነሳን እንጂ ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር በሚያስተዳድራቸው ሁሉም ቀጠናዎች ይህ የጠላት መጠቀሚያ የሆነ ኃይል እየፈራረሰ ይገኛል። ምክረ ሀሳብ ÷÷÷÷ በተደጋጋሚ እንደምንለው ትርጉም የሌለው ሞት አትሙቱ። የእስካሁኑ ይበቃችኋል። ለአንድ እብድና ወፈፌ ግለሰብ ስልጣን ብላችሁ አትለቁ። የብአዴን ባለሥልጣንን ጨምሮ ሆቴልና መጋዘን ጠባቂ አለመሆናችሁን በተግባር አሳዩ። ከሕዝባችሁና ከወገናችሁ ጋር ደም አትቃቡ። ሥለሆነም ኑ! እኛ በፍቅር እንቀበላችኋለን። የጋራ ዘረፈጅ ጠላት አለን እሱን እንምታ። ሀገራችንና ሕዝባችን የጋራችን ናቸው። የእኛ ትግል ለእናንተ ነፃነት ጭምር ነው። በእኛ መስዋዕትነት ነፃ የምትወጡት እናንተና ልጆቻችሁ እንዲሁም መላው ቤተሰባችሁ ጭምር ነው። ኑ! በፍቅር እንቀበላችኋለን። በጠላትነት እንድንተያይ እና እርስ በርስ እንድንታኮስ ያደረገን አገዛዙ ነው። እንጅማ ወንድሞቻችን ናችሁ፤ እኛም ወንድሞቻችሁ ነን። ኑ! ድል ለአማራ ሕዝብ! ድል ለፋኖ! አዲስ ትውልድ፤አዲስ አስተሳሰብ፤አዲስ ተስፋ! ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር ሐምሌ 4/2018 ዓ.ም

​🛑 ሰበር ዜና፦ የብልፅግና 102ኛ አየር ወለድ ምክትል አስር አለቃ አና አንድ አባል በመሆን ሙሉ ትጥቃቸዉን በመያዝ ፋኖን ተቀላቀሉ!! ​ሐምሌ 04/11 / 2018 ዓ.ም ​በኤፍራታ ግድም ወረዳ፣
+3
​🛑 ሰበር ዜና፦ የብልፅግና 102ኛ አየር ወለድ ምክትል አስር አለቃ አና አንድ አባል በመሆን ሙሉ ትጥቃቸዉን በመያዝ ፋኖን ተቀላቀሉ!! ​ሐምሌ 04/11 / 2018 ዓ.ም ​በኤፍራታ ግድም ወረዳ፣ በርግብይ አካባቢ ህዝቡን በማንገላታት፣ በማሳቀቅና በመድፈር ላይ የሚገኘው የአብይ አህመድ ስርዓትና የፀጥታ መዋቅር በከፍተኛ ሁኔታ እየፈረሰ መሆኑ ተነገረ። ​ከዚህ መዋቅር ለመውጣት ለብዙ ወራት ሲያቅዱ የቆዩ ሁለት የመከላከያ አባላት፣ የቆዩበትን የአገዛዙን ሰራዊት ጥለው በመውጣት ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር በሰላም ገብተዋል። ​ከተቀላቀሉት የጦር አባላት መካከል የኦሮሚያ ተወላጅ የሆኑ የአብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ 102ኛ ልዩ ዘመቻ አየር ወለድ መከላከያ ክፍለ ጦር ውስጥ የነበረ ምክትል አስር አለቃ እና አንድ አባል ሲሆኑ እነዚህ አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው የፋኖን ትግል ተቀላቅለዋል በሰጡት ቃልም ​"የቆየንበትን የትግል ዘመን በታሪካችን ህዝብ የበደልንበትና የበዳዮች ተባባሪ የሆንበት በመሆኑ ህዝባችን ይቅር ይበለን" በማለት ጥሪያቸውን አቅርበዋል። ​በአሁኑ ወቅት በርካታ የሰራዊቱ አባላት የሁኔታውን አሳሳቢነት በመረዳትና ህይወታቸውን እያተረፉ ወደ ህዝባዊ ትግሉ እየተቀላቀሉ ይገኛሉ። ​አማራነት ያሸንፋል! የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር

ሰበር የድል ዜና ❗❗ ከኮላሽ ተራራማ ስፍራ እስከ አለም ከተማ ጫፍ በናደው ክፍለጦር ታሪክ ሰራ!      ሐምሌ 04 ቀን 2018 ዓ.ም ሸዋ ጠቅላይ ግዛት — አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር ናደው ክፍለ ጦር በመርሐቤቴ አውራጃ በታሪካዊቷ የኮላሽ ተራራማ ስፍራና በአለም ከተማ ዙሪያ ሰፍሮ በነበረው የብልፅግና አገዛዝ ሰራዊት ላይ የናደው ክፍለጦር ጀግኖች መብረቃዊ ጥቃት በመሰንዘር አኩሪ ድል አስመዝግበዋል። ዛሬ ከሌሊቱ 10:00 ጀምሮ በላይ ቤት ኮላሽ ተራራ  ላይ የገባው የክፍለጦሩ ሻለቃ የጠላትን የቁም ምሽግ ሙሉ በሙሉ በመበተን አካባቢውን በቁጥጥሩ ስር በማድረግ ፤ በተጨማሪም በዞማ ዙሪያ እና ከአለም ከተማ መውጫ በአከያ መስክ ላይ የሠፈረውን  የጠላት ኃይል ሌላኛዋ  የክፍለጦሩ ሻለቆች በቅንጅት ተቆልፎ የተያዘ ሲሆን፣ በተደረገው የጨበጣ ውጊያ የጠላት ክፉኛ ተመቷል። በዚህ አስደናቂ ውጊያ አንድ ሙሉ የአገዛዙን ታጣቂ የጫነ ኦራል ተሽከርካሪ ልዩ ስሙ ዘይታ በተባለ ቀበሌ በቦንብ ተመቶ ከነጫነው የሰው ሀይል ወደ አመድነት ተቀይሯል። ሽንፈቱን ተከትሎ ከፌጥራ እስከ አለም ከተማ ያለውን ጥምር ኃይል በማንቀሳቀስ የኮላሹን ኃይል ለመታደግ የሞከረው የጠላት እቅድ፣ በአለም ከተማ አቅራቢያ በተጣለበት አስደንጋጭ ደፈጣ መክኗል። በአሁኑ ሰዓት ጀግኖቹ ቦታቸውን ይበልጥ እያሻሻሉ ሲሆን፣ በጀግኖቹ የአልሞ ገዳይ (ስናይፐር) ቡድን ክፉኛ የተመታውና የተበታተነው የጠላት ኃይል ሙትና ቁስለኛውን ለመሰብሰብ በመወራጨት ላይ ይገኛል። ነገር ግን ከጀግኖቹ ባሩድ የተረፈ የለም። የጠላት ኃይል በኮላሽ ተራራማ ቦታ ከአመራሮቹ ጋር ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የተደመሰሰ ሲሆን፣ የሚከተሉት ወታደራዊ ቁሳቁሶች እና የጠላት ሀይል በጀግኖቹ ቁጥጥር ስር ውለዋል፦ ✔ 03 የኮማንዶ አመራሮች ተማርከዋል ✔.01 ብሬን (ከነሙሉ ሸንሸሉ) ✔.07 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ ✔.03 ማውዘር (መንቶፍ) ✔.02 መገናኛ ራዲዮ ✔.02 ኤፍ-1 ቦንብ ✔.12 ካዝና እና ✔. 07 የደረት ትጥቅ 360 የክላሽ ተተኳሽ ጥይቶችና ሌሎች ልዩ ልዩ ወታደራዊ ቁሳቁሶች መማረክ ተችሏል። የተስፋ መቁረጥ እርምጃ በጀግናው ናደው ክፍለጦር ክንድ የደረሰበትን ከባድ ኪሳራ መቋቋም ያልቻለው የአገዛዙ ኃይል፣ በተለመደው የሽንፈት ባህሪው ዙ-23 እና ሞርተር በመጠቀም በንፁሃን አርሶ አደሮች መኖሪያ ቤቶችና ንብረቶች ላይ የበቀል ጥቃት በመሰንዘር ላይ ይገኛል። ኮሩ ከግንባር ያደረሰው  መረጃ እንደሚያመለክተው፣ አሁን የተጀመረው ስልታዊ ማጥቃት ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን ጠላትን በእያንዳንዱ ምሽግ የመቅበሩ ስራ ይቀጥላል ሲል ገልጿል ።ሌሎች ተያያዢ ዝርዝር መረጃዎችን በሚደርሰን መረጃ ይዘን የምንመለስ ይሆናል። " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

በመንዝ አውራጃ በሞላሌ ከተማ በተሰነዘረ ጥቃት የወረዳው የሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊና የመቶ መሪ መገደላቸው ተገለጠ!! ሐምሌ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በመንዝ ማማ ክላስተር ሞላሌ ከተማ ውስጥ በብልጽግና
+1
በመንዝ አውራጃ በሞላሌ ከተማ በተሰነዘረ ጥቃት የወረዳው የሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊና የመቶ መሪ መገደላቸው ተገለጠ!! ሐምሌ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በመንዝ ማማ ክላስተር ሞላሌ ከተማ ውስጥ በብልጽግና አገዛዝ ሠራዊት ላይ በተሰነዘረ ድንገተኛ ጥቃት፣ የወረዳው የሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ እና የአንድ መቶ መሪ መገደላቸውን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አስታወቀ። የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ባወጣው መረጃ መሠረት፣ ዛሬ ሐምሌ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ሌሊት የአፄ ምኒልክ ክፍለ ጦር ቃኚዎች ወደ ሞላሌ ከተማ ሰርገው በመግባት በወሰዱት የማያዳግም እርምጃ የሚሊሻ መቶ መሪ የሆነውን ኃይሉ ከፈለውን እስከወዲያኛው ሸኝተውታል። በዚሁ ጥቃት በሌሎች የአገዛዙ ሠራዊት ላይም ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ ተገልጧል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የፋኖ ቤተሠብ ከብቶችን ዘርፈው በመሸሽ ላይ በነበሩ የሚሊሻ አባላት ላይ በአካባቢው የሚንቀሳቀሱት የአባት አርበኞች በወሰዱት አጸፋዊ እርምጃ፣ የመንዝ ማማ ወረዳ የሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ችላባለው የተባሉ ግለሰብና ሌሎች የሚሊሻ አባላትም ተገድለዋል። በጥቃቱ የቆሰሉ በርካታ የአገዛዙ ሠራዊቶች በአሁኑ ወቅት በሞላሌ ከተማ ሆስፒታል ገብተው በመታከም ላይ እንደሚገኙ የኮሩ መግለጫ ያመላክታል። " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

የእዙ ከፍተኛ አመራሮች ክፍለጦሩ በተሰማራበት የግዳጅ ቀጠና ላይ በመገኘት የተሳካ ውይይት አደረጉ!!       ሀምሌ -4-2018 ዓ.ም አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አ/ ዕዝ የመሃመድ ቢሆነኝ ኮር የወንዱ አስቻለው ደሴ ክፍለጦር የግዳጅ ቀጠና ላይ ከተሰማሩ የክፍለጦሩ አመራሮችና የሻለቃ አዛዦች ጋር በመንዝና ግሼ አውራጃ ውጤታማ ውይይት ተካሄደ። በውይይቱ ላይ የአሳምነው ዕዝ ከፍተኛ አመራር አርበኛ አዶናይ አበበ፡አርበኛ ዳመን ወርቁን ጨምሮ ሌሎች የእዙ መሪዎች የተገኙ ሲሆን፥ በዋናነት የሸዋ አንድነት፣ ወቅታዊ የትግል ሁኔታ፣ የሀገሪቱን የሀይል አሰላለፍ፣ በሰራዊቱና በህዝቡ መካከል ሊኖር ስለሚገባው ግንኙነት... ሰፊ ውይይቶችን የተደረገ ሲሆን በመጨረሻም የትግሉን አሁናዊ ቁመና በመገምገም በቀጣይ ክፍለጦሩ ማከናወን ስላለበት ዋና ዋና ተግባራት ላይ በጋራ በመምከር ወሳኝ የግዳጅ አቅጣጫዎችን በማውረድ ውይይቱ በስኬት ተቋጭቷል። ክብርና ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት! ድል ለአማራ ህዝብ!! ​ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ​

#3_የሚሊሻ_አባላት ፋኖንየተቀላቀሉ ሲሆን የብልፅግናው ካምፕ እየተናደ አልቋል ። ========================= .....ሐምሌ 4/2018 ዓ.ም ከግንደ ወይን ከተማ በመውጣት 201ኛ ኮር
+1
#3_የሚሊሻ_አባላት ፋኖንየተቀላቀሉ ሲሆን የብልፅግናው ካምፕ እየተናደ አልቋል ። ========================= .....ሐምሌ 4/2018 ዓ.ም ከግንደ ወይን ከተማ በመውጣት 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦርን የተቀላቀሉ፦ 1.መልካሙ ምስጋናው.... ሚሊሻ 2.ይፍረደው አባተ.... ሚሊሻ 3.ክንዱ የሺ.......ሚሊሻ ሲሆን ሁሉም ለመውጣት በዝግጅት ላይ ነው ናቸው ምቹ ሁኔታወችን እየተጠባበቁ እንደሚገኙ ተናግረዋል የመጡትን አባላትም ወንድማዊ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። የክፍለ ጦሩ ህ/ግንኙነት እንደተናገረው ያለምንም መስዋትነት ውጤታማ እና ትርፋማ ሁኖ ያገኘነው ስቦ ማስከዳት ላይ ስለሆነ አጠናክረን የምንሰራበት ነው በማለት አስታውቀዋል። < ከመሞት መሰንበትን የመረጡት እየመጡ ነው > የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

የ21ኛው ክፍለ ዘመን የአማራው አንበሳአርበኛ ኢሳያስ ደመቀ!! ​በታሪክ ምዕራፎች መካከል አንዳንዴ የአንድን ሕዝብ መፃኢ ዕድል የሚቀይሩ፣ የነፃነትን ትርጉም በደማቸው የሚጽፉ ጥቂት የቁርጥ ቀን ልጆች ይወለዳሉ። በታሪካዊቷ የሽዋ ምድር ተወልዶ፣ በኤፍራታ ምድር ማህፀን ያደገውና የፋኖን የህልውና ተጋድሎ የስትራቴጂ ማዕከል ያደረገው አርበኛ ኢሳያስ ደመቀ የዚህ ዘመን ተምሳሌት ነው። ​ይህ ጀግና የአማራ ፋኖን የመጀመሪያ የጋራ መደራጀት አቅምና ወታደራዊ መዋቅር ለመፍጠር፣ ከሽዋ ሰንሰላታማ ተራሮች ተነስቶ እስከ ጎንደር መተማ ጠረፍ ድረስ የነፃነትን መንገድ የጠረገ፣ ውድና ክቡር ህይወቱን ለሕዝቡ ህልውና በነፃነት መሠዊያ ላይ ያቀረበ የጦር ሜዳ ስትራቴጂስት ነው። በተደጋጋሚ የወላድ መካን ልትሆንና ከካርታ ላይ ልትጠፋ የተቃረበችው የታሪካዊቷ የአጣዬ ምድር በወራሪዎች ስትደፈር፣ ደረቱን ለጥይት ሰጥቶ፣ ሞትን ንቆ ከፊት መስመር በመሰለፍ ወገኑን ከባርነትና ከጅምላ ጭፍጨፋ የታደገ የእምዬ ምኒልክ እውነተኛ የደም ወራሽ ነው! ​ኢሳያስ የሰይፍ ብቻ ሳይሆን የረቂቅ ሀሳብና የዲፕሎማሲ መሪ ነው። ልክ እንደ እምቢተኝነቱ ዓለም አቀፍ ተምሳሌት እንደ ራስ አርበኛ ዘመነ ካሴ ሁሉ፣ በሀሳቡ ምላጭነትና በአንደበተ ርቱዕነቱ የብልፅግናን ሹማምንትና የብርሃኑ ጁላን የትዕቢት የካርታ ቤት የሚያፈርስ፣ የቅስም መስበሪያ ስልጡን አርበኛ ነው። በአስተሳሰቡ የበሰለ፣ በንግግሩ ማራኪ፣ በተግባሩ ደግሞ የማይበገር የጦር አምበሳ በመሆኑ፣ ስሙ በዓለም አቀፍ መድረኮች ጭምር በክብርና በግርማ ሞገስ ይነሳል። ​እርሱ ለተጨቆነ ሕዝብ ድምፅ የሆነ፣ ከመንደርተኝነትና ከከፋፋይ የፖለቲካ ሴራ የራቀ መሪ ነው። ለእርሱ ከሽዋ እስከ ወሎ፣ ከጎንደር እስከ ጎጃም ያለው አማራ ሁሉ አንድ ወጥ የሆነ የነፃነት ኃይል ነው። ኢሳያስ የማይሳሳለት፣ የማይወደውና የማይደራደርበት ወገን የለም። እርሱ የጦር አዋጊና ተዋጊ ብቻ አይደለም፤ በአርቆ አሳቢነት፣ በፖለቲካ ብስለትና ባለሙያ አእምሮ የታደለ የክፍለ ዘመናችን የታሪክ አጋዥ እንጂ! ​ ​በአራቱም ማዕዘን ያሉ ጀግኖችና የዓለም ነፃነት ወዳዶች በታላቅ አክብሮት ይመለከቱታል፤ ፊቱን ለማየትና በትግል ሜዳ ከጎኑ ለመሰለፍ የሚናፍቁ፣ የእርሱን ፈვალሲ የነፃነት መንገድ የሚከተሉ ስፍር ቁጥር የሌላቸው ወጣቶች አሉት። እርግጥ ነው፣ ከታሪካዊ ጠላት ጋር ያላቻ ጋብቻ መስርተው፣ ሆዳቸውን ለመሙላትና ስልጣን ለማግኘት ሕዝባቸውንና ታሪካቸውን የሚሸጡ ሆድ አምላኪዎች በአገር ውስጥም በውጭም አይጠፉም፤ ነገር ግን የእነርሱ ጊዜያዊ ክህደት የዚህን ታላቅ ጀግና የነፃነት ታሪክ ከቶ ሊያደበዝዝ አይችልም። ታሪክ ወርቁን ከባንዳው ለይቶ ይጽፋል! ​ራስ አርበኛ ዘመነ ካሴ በአንድ ወቅት፦ "ፎቶዬን የማላይበት (የነፃነት አየር የምንተነፍስበት) የድል ቀን መቼ ይሆን?" እንዳለው ሁሉ፣ ዛሬም እኛ የወንድማችንን የአርበኛ ኢሳያስ ደመቀን በትግል አውድማ ሳይሆን በነፃነት ማግስት፣ በታላላቅ የዓለም አደባባዮች ላይ በክብርና በኩራት የምናይበት ያ የብርሃን ቀን ናፍቆናል፤ እርሱም በጀግኖቹ የአማራ ልጅ ፋኖ ክንድ ነፃነታችን እውን ይሆናል! ​የተጨቆኑ ሕዝቦች አለኝታ፣ የቁርጥ ቀን ብርሃን አርበኛ ኢሳያስ ደመቀ በጀመርከው የፍትህና የነፃነት ጎዳና ላይ ጽና! የጽዮን አምላክ አንተንና ጀግኖቹን ፋኖዎችን ከክፉ ሁሉ ይጠብቃችሁ። Dave Amhara

በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፤ የአፄ ዘርዓ ያዕቆብ ፩ኛ ኮር የአፄ ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር ወታደራዊ ግምገማ አካሔደ!! ቀን 03/11/2018 ዓ.ም የታጠቀ ሕዝባዊ ኃይሎች የትጥቅ ትግል ጉዟቸውን ስኬታማ ለማድረግ ካላቸው ቁልፍ ስትራቴጂዎች አንዱ የውስጥ ጥንካሬን መፈተሽ፣ ድክመቶችን ማረም እና ቀጣይ ወታደራዊ ግዳጆችን በንቃት ማቀድ ነው። ይህንን መርህ መሠረት በማድረግ፣ በዕለቱ 03/11/2018 ዓ.ም በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ስር የሚገኘው የአፄ ዘረያዕቆብ ፩ኛ ኮር፣ አፄ ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር ከፍተኛ ወታደራዊ ግምገማ አካሂዷል። በትጥቅ ትግል ስነ-ልቦና ውስጥ የአዛዦችና የሰራዊቱ መግባባት ለውጊያ ዝግጁነት ወሳኝ ሚና ይጫወታል። በዚህ መድረክ ላይ የኮሩ ወታደራዊ ዋና አዛዥ፣ የክፍለ ጦሩ ዋና መሪ ፣ የክ/ሩ ወታደራዊ አዛዡ፣ የሻለቃ አመራሮች እና ሻምበል መሪዎች ድረስ ያሉ ሁሉም የጦር መኮንኖች በሙሉ ተገኝተዋል። ይህ አይነቱ የተዋረድ መሪዎች ጥምረት በትግሉ መስመር ውስጥ ያለውን የዕዝ ሰንሰለት ለማጠናከር እና መመሪያዎችን እስከ ታችኛው የሰራዊት አባል ድረስ በግልፅ ለማውረድ ትልቅ አቅም ይፈጥራል። መድረኩ በኮሩ ወታደራዊ ዋና አዛዥ መቶ አለቃ ተፈሪ የተመራ ሲሆን በመድረኩ እንደገለፀው፣ የተካሄደው ጥልቅ ወታደራዊ ግምገማ እጅግ አመርቂና ስኬታማ ነበር።ለቀጣይም የተሻለ ቁመና እንድኖረን እና ወትሮም ለድርጅታዊ ተልዕኮ የሚያነሳሳ ግምገማ ነው ። በትጥቅ ትግል ሂደት ውስጥ የሚገጥሙ ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎችን በወታደራዊ ሳይንስ መነጽር የገመገመው ይህ መድረክ፣ ሠራዊቱ ለቀጣይ ተልዕኮዎችና ግዳጆች በአዲስ መንፈስና በላቀ ዝግጁነት እንዲነሳሳ አድርጓል ብሏል። ይህ ግምገማ ክፍለ ጦሩ በስትራቴጂካዊና በታክቲክ ረገድ ያለውን ቁመና ያጠናከረበት ሲሆን፣ መላው የክ/ጦር አመራሮችም ለቀጣዩ የትግል ምዕራፍና ለሚሰጡ ማናቸውም ወታደራዊ ግዳጆች ሙሉ ዝግጁ መሆናቸውን በጽናት አንፀባርቀዋል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

🎯 ምስራቁ፤ እንኳን ተወለድህልን! ​(አዲሱ ደረበ) ​አንዳንድ ሰዎች መሪነታቸውን በሕይወታቸው ተግብረው ሲያሳዩን ይኖራሉ። በትግል እሳት ውስጥ አልፈው፣ ዳገቱ የሚጠይቀውን መከራ ሁሉ ደክመው ግን ደግሞ አንድም ቀን ከሚዛን የማይጎድሉ፣ ልባቸው እንደ ወርቅ የጠራ ጀግኖች ሲኖሩን ትግሉ ራሱ ትርጉም ያገኛል። ዛሬ እንዲህ ያለው ጀግና የምስራቁ አንበሳ፣ የአፋብን አጋርነትና ትብብር መምሪያ ሐላፊ አርበኛ አበበ ፈንታው (ምስራቁ) የተወለደበት ቀን ነው! ​አቤዋ እኮ ሙሉ ዕድሜውን፣ ወጣትነቱን፣ ጉልበቱንና አቅሙን ለአማራነት ክብርና ሕልውና አሳልፎ የሰጠ፣ ከአማራ ወጣቶች ንቅናቄና ትግል ጀምሮ እስከ አፋብን ከፍተኛ አመራርነት ድረስ በጽናትና በማይናወጥ እምነት እየታገለ ያለ እውነተኛ የሕዝብ አለት ነው። የዋርካው ቀኝ እጅ፣ የሰማዕቱ ኮማንዶ ዳንኤል ዓለሙ ታማኝ ወንድም አቤ! እርሱ የአማራነት ትክክለኛ መስፈሪያና ሚዛን ነው ማለት ይቻላል፤ ሠፈርና ጎጥ አያውቅም፣ መቧደንና የአንጃ መቺነት ፖለቲካ በደረሰበት አይደርስም። አእምሮውና ዓላማው ከጠባብነት የጸዳ፣ ሁለንተናው ለአማራ አንድነትና ነፃነት ብቻ የተገዛ ብርቱ ታጋይ ነው። ​ወላጅ አባቱን ሳይቀር በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ውስጥ በፋሽስቱ ወራሪ ኃይል በግፍ የተነጠቀ፣ በግልና በቤተሰብ ደረጃ እጅግ አያሌና ከባድ ዋጋ የከፈለ ጀግና ነው። ነገር ግን ይሄ ሁሉ መከራ ከዓላማው ፍንክች አላደረገውም፤ ይልቁንም ይበልጥ አጽንቶት ከሚዛን የማይጎድል፣ ለሐቅና ለፍትሕ የሚቆም፣ የሕዝባችን ጽኑ ጠበቃ አድርጎታል። ለዚህም ነው አንዳንድ ጊዜ ሳስበው፣ አቤ የሩቅ መሪ ሳይሆን ልክ የእናትና የአባቴ ልጅ፣ የስጋ ወንድሜ ሆኖ የሚሰማኝ! ለወገኑ ጥላ፣ ለጠላትና ለከዳተኞች ደግሞ የማይበርድ ረመጥና እሳት የሆነ መሪ ነው አቤዋ። ​ምስራቁ፦ ዛሬ በተወለድክበት በዚህ ታሪካዊ ቀን፣ መላው የአማራ ሕዝብና አብረውህ ግንባር ላይ የሚዋደቁ ጀግኖች ጓዶችህ እንኳን ተወለድህልን እያሉ በታላቅ ፍቅርና አክብሮት ያቅፉሃል። አንተን የመሰለ በሳል፣ ቅን፣ ታማኝና አለት የሆነ ወንድም በትግላችን ውስጥ ማግኘታችን ትልቅ መታደል ነው። ፈጣሪ አምላክ ዕድሜህንና ጤናህን ያርዝመው፤ ከፊትህ የተደቀነውን የጠላት ግንብ ሰባብረህ ሕዝባችንን ወደ ሙሉ ነፃነቱ በድል እንድታሻግር ጽናቱንና ጥበቡን አብዝቶ ይስጥህ። የወንድምነትህና የመሪነትህ አሻራ በታሪክ መዝገብ ላይ በወርቅ ቀለም ተጽፎ ይኖራል! ​መልካም ልደት አቤዋ! ድል ለአማራ የህልውና ትግል! 🎯

ሶስት የአገዛዙ ቅጥርኛ የሚሊሻ ሰራዊት አባላት 64ኛ ክ/ጦር ተቀላቀሉ!! ~~~~ በ64ኛ ክ/ጦር ቀጠና እነማይ እና ሸበል በረንታ ቢቸና፣ የዕድውሃ፣ መርገጭ፣ የትመን፣ ማህበርብረሃንና ወይራ ጠልማ ቀበሌ ሰፍሮ የሚገኘው የአብይ አህመድ የጥፋት ቡድን መከላከያ፣ አድማ ብተና እና የሚኒሻ የጥፋት ቡድን ከመኖር ወደ አለመኖር ተስፋ በመቁረጥ ሥሜት ውስጥ መሆናቸው ተረጋግጦል። የአብይ አህመድ አገዛዝ ወደ ትግራይ ድንበር ለግዳጅ ስምሪት መስጠቱት ተከትሎ በህዝባችን ላይ ይፋዊ ጭካኔ ሲፈፅሙ የከረሙ፣ ፋኖን በመጥፎ ስያሜ በመተቸት የነበሩ፣ አማራነታቸውን ክደው ለአገዛዙ ኃይል ቅጥርኛ በመሆን ይሰሩ የነበሩ የአገዛዙ የጠላት ኃይሎች መሳሪያ በመሸጥ ወደ አዲስ አበባ ለማምራት መዘጋጀታቸውንና ቀሪዎቹ ደግሞ ወደ ፋኖ እየተቀላቀሉ ይገኛል። በዚህም መሰረት ከሸበል በረንታ የዕድውሃ ከተማ ህዝባቸውን  ይቅርታ ጠይቀው 64ኛ ክ/ጦር የተቀላቀሉ የሚሊሻ አባላት ውስጥ:- 1ኛ.ገረመ ጎሹ አንድ ክላሽ በመያዝ ከየዕድውሃ 2ኛ.ሙሉየ ዋሌ አብራራው መሳሪያ በመያዝ ከየዕድውሃ 3ኛ.ደምሴ ተስፋው ከቢቸና ከተማ አስተዳደር 04 ቀበሌ ሰላም አስከባሪ ሚኒሻ የነበር ለአገዛዙ ቅጥረኛ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩ ቢሆኑም ሀምሌ 3/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው ተቀላቅለዋል። አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!                 ሐምሌ 3/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት