ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Kanalga Telegram’da o‘tish
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Ko'proq ko'rsatish2 937
Obunachilar
-324 soatlar
+3667 kun
+38130 kun
Postlar arxiv
ሰበር ዜና!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ 24ኛ ክፍለጦርና እና 35ኛ ክፍለጦር በጋራ ታላቅ ጀብድ በመፈፀም ድል ተቀዳጁ።
የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ከ104ኛ ኮር 24 ክፍለጦር እና ከ101ኛ ኮር 35 ከወልዲያ ፣ ከመርሳ : ከሳንቃ እንዲሁም ከዕዜት ስርዐቱ በብዛት አግተልትሎ ወደ ደቡብ ወሎ ዞን አምባሰል ወረዳ 015 ቀበሌ ልዩ ቦታው ወፉጮና ቋሆ ወደ ተባለ ቦታ ዛሬ ሀምሌ 05/2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 2:30 አካባቢ ሲንቀሳቀስ የነበረው ይህ የስርዐቱ ወንበር ጠባቂ ጦር በተጠና እና ውጤታማ በሆነ ደፈጣ በ35ኛ ክፍለጦር እና በ24 ክፍለጦር በርመጠበቂያ እየተባለ በሚጠራ ቦታ ላይ በመደምሠስ ድል ተጎናፀፉ።
በዚህ አውደ ውጊያ ዛሬ ሀምሌ 05/2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 2:30 ጀምሮ በተደረገ ተጋድሎ የስርዐቱን ጦር በተጠና ደፈጣ ጥቃት ከ75 በላይ መደምሰስ ሲቻል ከ30 በላይ በማቁሰል ድል መጎናፀፍ ሲቻል ፣ይህ ከተለያየ ቦታ በገፍ ተሰባስቦ የመጣ ሀይል ነፍስ አውጭኝ በማለት ወደ መጣበት እየተበታተነ ተመልሷል።
በዚህ የተበሳጨው የጥላት ሀይል ከመርሳ እና ከጀነቶ ጀኔራል መድፎችን ከጥዋቱ 4:00 ጀምሮ በዘፈቀደ ወደ ህዝባችን ያለ ማቋረጥ እሰከ ቀኑ 9:30 ድረስ ሙትና ቁስለኛውን ለማውጣት እየወረወረ ወይም እያስወነጨፈ ውሏል።በመጨረሻም በአራት ኦራል ሙትና ቁስለኛውን ወደ መርጦና ወልዲያ እያጓጓዘ አመሸቶ ፣ በከባድ መሳሪያ ሽፉን እየሰጠ እያግተለተለ ያመጣውን ቅጥረኛ ሰራዊት ወደ ዕዜት ና መርጦ ጀግኖቹና ነበልባሎቹ 24ኛ እና 35ኛ ክፍለጦር መልሰውታል ሲል የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ የ24ኛ ክፍለጦር ቃል አቀባይ ፉኖ አሉላ ዮሀንስ መረጃውን ልኮልናል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!
ሀምሌ 05 /2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት እና በወሎ ቤተ-አማራ የተመዘገቡ ወታደራዊ ድሎች
ሐምሌ 04 ቀን 2018 ዓ.ም።
1. የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ግንባሮች
ሀ. በመርሐቤቴ አውራጃ፦
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሥር የሚገኘው አፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር በናደው ክፍለ ጦር ጠላት ተደመሰሰ።
ኮላሽ ተራራማ ስፍራ እና አለም ከተማ ዙሪያ (በልዩ ስሙ ዘይታና አከያ መስክ) በተባለ ቦታ ላይ ከሌሊቱ 10:00 ጀምሮ በተወሰደ መብረቃዊ ጥቃት የጠላት ምሽግ ሙሉ በሙሉ ተሰብሯል። አንድ የጠላት ኃይል የጫነ 'ኦራል' ተሽከርካሪ በቦንብ ተመቶ ወድሟል። የኮላሹን ኃይል ለመታደግ ከፌጥራ እስከ አለም ከተማ የተንቀሳቀሰው ኃይል በደፈጣ ተመቷል።
በጠላት ላይ የደረሰ ኪሳራ፦
3 የኮማንዶ አመራሮች ተማርከዋል።
1 ብሬን፣ 7 ክላሽንኮቭ፣ 3 መውዜር፣ 2 ሬዲዮ መገናኛ፣ 2 ኤፍ-1 ቦንብ እና 360 ጥይቶችን ጨምሮ በርካታ ትጥቆች ተማርከዋል።
በሽንፈቱ የተበሳጨው የአገዛዙ ኃይል በዙ-23 እና ሞርተር በንፁሃን አርሶ አደሮች ላይ የበቀል ጥቃት እየሰነዘረ ይገኛል።
ለ. በደገም ወረዳ ግንባር፦ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሥር የሚገኘው አፄ አምደጽዮን ኮር በራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር - 2ኛ አሊ ሻለቃ
ልዩ ቦታው ሀሮ እና አቦ ለሊሳ (ግራሪያ/ፍቸ ሰላሌ) ላይ ከንጋቱ 12:00 እስከ ቀኑ 5:00 ድረስ በተወሰደ እርምጃ ህዝብን፣ ብሔርና ሃይማኖት ሳይለይ ሲዘርፍ በነበረው የሸኔ ቡድን ላይ የማያዳግም እርምጃ ተወስዷል።
በዚህም የጠላት ካምፕ ተሰብሮ በርካታ የቡድኑ አባላት ተደምስሰዋል። 7 የጦር መሣሪያዎች ሲማረኩ፣ ከተዘረፉት ውስጥ 9 የቀንድ ከብቶች እና 15 በግና ፍየሎች ተመልሰው ለአርሶ አደሩ ተሰጥተዋል።
ሐ. በመንዝ አውራጃ ግንባር፦ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሥር የሚገኘው አፄ አምደ ፅዮን ኮር በአፄ ምኒልክ ክፍለ ጦር ሞላሌ ከተማ (መንዝ ማማ ክላስተር) ላይ በሌሊት በተደረገ ሰርጎ የመግባት ኦፕሬሽን እና በአባት አርበኞች በተወሰደ አጸፋዊ እርምጃ የብልጽግና አገዛዝ ታጣቂዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።
በዚህም የወረዳው የሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ (አቶ ችላባለው) እና የሚሊሻ መቶ መሪው (ኃይሉ ከፈለውን) ጨምሮ ሌሎች አባላት ተደምስሰዋል። በርካታ የቆሰሉ የጠላት ኃይሎች በሞላሌ ሆስፒታል ይገኛሉ።
2. የወሎ ቤተ-አማራ ግንባር
ሀ. በላሊበላና አካባቢው ግንባር፦ የአፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሥር የሚገኘው 303ኛ አሳምነው ኮር (በ21ኛ ተከዜ ክፍለ ጦር እና 16ኛ ነብሮ ተወርዋሪ ኮማንዶ ክፍለ ጦር) አማካኝነት መነሻውን ኩልመስክና ላሊበላ አድርጎ ወደ ገነተማርያም በተንቀሳቀሰው ኃይል ላይ በተወሰደ እርምጃ በዙ-23 እና በ107 የተደገፈውን የጁላ ሰራዊት ስቦ በማስገባት እና በመቁረጥ ከፍተኛ ኪሳራ ማድረስ ተችሏል።
በዚህም ከ55 በላይ ጠላት ሲደመሰስ፣ ከ30 በላይ ቆስሏል። 42 ጥቁር ክላሽንኮቭ፣ 1 ሬዲዮ መገናኛ፣ 27 የደረትና የወገብ ትጥቆች እንዲሁም 36 ሻንጣዎች ተማርከዋል።
ልዩ መረጃ፦ አንድ የአገዛዙ ሰራዊት አባል 1 ጥቁር ስናይፐር እና 1 ጥቁር ክላሽ ይዞ 16ኛ ነብሮ ተወርዋሪ ኮማንዶ ክፍለ ጦርን በራሱ ፍቃድ ተቀላቅሏል። ይቀጥላል.....
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አበበ ሙላት
የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ
ጀግና አይሞትም፤ ታሪክ ሁሌም ያዘክረዋል!
ቀን፦ ሐምሌ 05/2018 ዓ.ም
ክብር እና መፅናናት ለአርበኛ ፀጋው ታፈሰ እና ለቀኝአዝማች አቡ አሳመረው ቤተሰቦች፣ ጓዶችና ለመላው የአማራ ህዝብ!
ታሪክ ራሱን በጀግኖች ደምና አጥንት ይፅፋል። ትናንት በመርሐቤቴ አውራጃ፣ ላይ ቤት ወረዳ በኮላሽ ተራራማ ስፍራ በነበረው ታላቅ ፍልሚያ፤ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርዓያዕቆብ ኮር ናደው ክፍለ ጦር ባደረገው የላቀ ጀግንነት የአገዛዙ ትልቅ የቁም ምሽግ ሲሰባበር፣ የጠላት ዋይታ በየጉድጓዱ አንባርቋል። የአገዛዙን ቅልብ ኮማንዶ በያለበት ክፉኛ በመምታት፣ ለወሬ ነጋሪ እንኳ ሳይተርፉ በርካታ የጠላት ኃይሎችን በመደምሰስ የክብር ሰማዕትነት የተቀበሉት አርበኛ ፀጋው ታፈሰ እና ቀኝአዝማች አቡ አሳመረው ለሕዝባቸው ያላቸውን ፍቅር እና የገቡለትን ቃል በአንድያ ነፍሳቸው በተግባር አስመስክረዋል።
እነዚህ የቁርጥ ቀን ጀግኖች በፋኖ ማዕቀፍ ውስጥ በመሆን ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ለአማራ ሕዝብ ህልውና፣ ክብርና መብት ሲሉ በግንባር ቀደምትነት የተሰለፉ፣ ያዋጉ፣ የተዋጉና ሕዝብን በማደራጀት ረገድ የተዋጣላቸው የትግሉ አብሪ ኮከቦች ነበሩ። ዛሬም እንደ ትናንቱ በኮላሽ ጠንካራ የቁም ምሽግ ላይ ታሪክ ዘላለም ሲዘክረው የሚኖር የጀግንነት ሥራ ሠርተው አልፈዋል።
• አርበኛ ፀጋው ታፈሰ፦ መርሐቤቴ ሰራዊት በማደራጀት እስከ ምስራቅ አማራ ድረስ በግንባር ቀደምትነት የተሰለፈ፣ የታገለና ያታገለ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው።
• ቀኝአዝማች አቡ አሳመረው፦ የመጀመሪያውን የአጣዬና የደራን የጠላት ከበባ ከሰበሩ አብሪ የትግል መሪዎች አንዱ ሲሆን፤ ይመራው የነበረውንም ሰራዊት ለአማራ ሕዝብ ህልውና ሲባል "ምርጫችን ወይ ሞት ወይ ማሸነፍ!" በሚል መርህ ያታገለ ጀግና ነበር።
እነዚህ የሸንቁጥ ልጆች፣ አባቶቻቸው ከፋሺስት ጣሊያን ጦር ጋር ታሪክ በሠሩበት በታሪካዊቷ ላይ ቤት ወረዳ ኮላሽ ሰንሰለታማ ተራራ ላይ የብልፅግናን ሰራዊት ለወሬ ነጋሪ ሳይተርፍ ካረገፉ በኋላ፣ ውድ ሕይወታቸውን በጀግንነት ለአማራ ሕዝብ ህልውና ሲሉ ሰውተዋል።
በዕለቱ የነበረው ተጋድሎ ወደር የሌለው ነበረ፤ ጀግኖቹ ሙሉ አንድ ሻለቃ የጠላት አየር ወለድን ያንበረከኩ፣ በጀግንነት መሃል ገብተው የቦምብ ናዳ በማውረድ ታሪክ የሠሩ ብርቅዬዎች ነበሩ። ምንም እንኳ እነዚህ የቁርጥ ቀን ልጆች ሙሉ ድሉ ከመጠናቀቁ በፊት ቢሰዉም፣ ያፈሯቸው ሺህ ጀግኖች ግን ዓላማቸውን አንግበው ተልዕኮውን ፈጽመዋል። የጀግኖቹ ደም በከንቱ አልቀረም፤ የጀመሩት እና የመሩት ውጊያ በተተኪዎቹ የናደው ክፍለ ጦር አናብስት በተቀጣጠለ ወኔና ልዩ የመዋጋት ጥበብ ቀጥሎ፣ በጠላት ላይ ሙሉ በሙሉ በደረሰ የድምሰሳ ፍጻሜ ተጠናቋል። የጀግኖቹም ደም በድል ተክሷል። በዕለቱም ማትያስ ማድቦ ሲመራው የነበረ ጦር በጀግኖቹ ምት በኮላሽ ተራራ ተቀብሮ የብልፅግና ሹማምንቶችን ሀዘን ያስቀመጠ ክስተት ሆኖ አልፏል።
"ጀግና ቢወድቅም የጀመረው ዓላማና የለኮሰው የነጻነት እሳት መቼም ቢሆን አይጠፋም።"
• ለተከበሩ ቤተሰቦቻቸው፦ በእንዲህ ዓይነት የቁርጥ ቀን የህልውና ዋስትና የሆኑ ጀግኖችን ለአማራ ሕዝብ ያበረከታችሁ የጀግና ወላጆችና ቤተሰቦች፤ ሐዘናችሁ የሁላችንም ሐዘን ቢሆንም ማኅፀናችሁ በኩራትና በክብር ሊመሰገን ይገባዋል። ፈጣሪ ጽናቱንና መጽናናቱን ይስጣችሁ።
• ለትግል ጓዶቻቸው፦ የአብሮነት፣ የደምና የዓላማ ጓዶቻቸው የሆናችሁ የነጻነት ታጋዮች፤ የጀግኖቹ መውደቅ የትግል ወኔያችሁን የሚያጠነክር፣ የተረከባችሁትን አደራ በድል ለማጠናቀቅ ጉልበት የሚሆን ነው። የአማራ ሕዝብ ህልውና የሚረጋገጠው በጀግኖች መስዋዕትነት እና ጠላትን በየቦታው በመቅበር በመሆኑ፣ ከትናንቱ ነገ ይበልጥ እንድትጠነክሩ ያደርጋችኋል። ጀግንነታችሁ ይቀጥል!
• ለመላው የአማራ ሕዝብ፦ ሕዝባችን እንደነዚህ ያሉ ውድ ልጆቹን ለነጻነቱና ለህልውናው ሲል መስዋዕት አድርጓል። ታሪክ የማይረሳቸው እነዚህ ሰማዕታት የቁጭትና የድል አርማዎቻችን ናቸው።
የጀግኖቹ የአርበኛ ፀጋው ታፈሰ እና የቀኝአዝማች አቡ አሳመረው ስምና ታሪክ በትውልድ ልብ ውስጥ ለዘላለም ሕያው ሆኖ ይኖራል!
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! ፈጣሪ ለቤተሰቦቻቸውና ለጓዶቻቸው መፅናናትን ይስጥ!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ጀግና አይሞትም፤ ታሪክ ሁሌም ያዘክረዋል!
ቀን፦ ሐምሌ 05/2018 ዓ.ም
ክብር እና መፅናናት ለአርበኛ ፀጋው ታፈሰ እና ለቀኝአዝማች አቡ አሳመረው ቤተሰቦች፣ ጓዶችና ለመላው የአማራ ህዝብ!
ታሪክ ራሱን በጀግኖች ደምና አጥንት ይፅፋል። ትናንት በመርሐቤቴ አውራጃ፣ ላይ ቤት ወረዳ በኮላሽ ተራራማ ስፍራ በነበረው ታላቅ ፍልሚያ፤ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርዓያዕቆብ ኮር ናደው ክፍለ ጦር ባደረገው የላቀ ጀግንነት የአገዛዙ ትልቅ የቁም ምሽግ ሲሰባበር፣ የጠላት ዋይታ በየጉድጓዱ አንባርቋል። የአገዛዙን ቅልብ ኮማንዶ በያለበት ክፉኛ በመምታት፣ ለወሬ ነጋሪ እንኳ ሳይተርፉ በርካታ የጠላት ኃይሎችን በመደምሰስ የክብር ሰማዕትነት የተቀበሉት አርበኛ ፀጋው ታፈሰ እና ቀኝአዝማች አቡ አሳመረው ለሕዝባቸው ያላቸውን ፍቅር እና የገቡለትን ቃል በአንድያ ነፍሳቸው በተግባር አስመስክረዋል።
እነዚህ የቁርጥ ቀን ጀግኖች በፋኖ ማዕቀፍ ውስጥ በመሆን ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ለአማራ ሕዝብ ህልውና፣ ክብርና መብት ሲሉ በግንባር ቀደምትነት የተሰለፉ፣ ያዋጉ፣ የተዋጉና ሕዝብን በማደራጀት ረገድ የተዋጣላቸው የትግሉ አብሪ ኮከቦች ነበሩ። ዛሬም እንደ ትናንቱ በኮላሽ ጠንካራ የቁም ምሽግ ላይ ታሪክ ዘላለም ሲዘክረው የሚኖር የጀግንነት ሥራ ሠርተው አልፈዋል።
• አርበኛ ፀጋው ታፈሰ፦ መርሐቤቴ ሰራዊት በማደራጀት እስከ ምስራቅ አማራ ድረስ በግንባር ቀደምትነት የተሰለፈ፣ የታገለና ያታገለ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው።
• ቀኝአዝማች አቡ አሳመረው፦ የመጀመሪያውን የአጣዬና የደራን የጠላት ከበባ ከሰበሩ አብሪ የትግል መሪዎች አንዱ ሲሆን፤ ይመራው የነበረውንም ሰራዊት ለአማራ ሕዝብ ህልውና ሲባል "ምርጫችን ወይ ሞት ወይ ማሸነፍ!" በሚል መርህ ያታገለ ጀግና ነበር።
እነዚህ የሸንቁጥ ልጆች፣ አባቶቻቸው ከፋሺስት ጣሊያን ጦር ጋር ታሪክ በሠሩበት በታሪካዊቷ ላይ ቤት ወረዳ ኮላሽ ሰንሰለታማ ተራራ ላይ የብልፅግናን ሰራዊት ለወሬ ነጋሪ ሳይተርፍ ካረገፉ በኋላ፣ ውድ ሕይወታቸውን በጀግንነት ለአማራ ሕዝብ ህልውና ሲሉ ሰውተዋል።
በዕለቱ የነበረው ተጋድሎ ወደር የሌለው ነበረ፤ ጀግኖቹ ሙሉ አንድ ሻለቃ የጠላት አየር ወለድን ያንበረከኩ፣ በጀግንነት መሃል ገብተው የቦምብ ናዳ በማውረድ ታሪክ የሠሩ ብርቅዬዎች ነበሩ። ምንም እንኳ እነዚህ የቁርጥ ቀን ልጆች ሙሉ ድሉ ከመጠናቀቁ በፊት ቢሰዉም፣ ያፈሯቸው ሺህ ጀግኖች ግን ዓላማቸውን አንግበው ተልዕኮውን ፈጽመዋል። የጀግኖቹ ደም በከንቱ አልቀረም፤ የጀመሩት እና የመሩት ውጊያ በተተኪዎቹ የናደው ክፍለ ጦር አናብስት በተቀጣጠለ ወኔና ልዩ የመዋጋት ጥበብ ቀጥሎ፣ በጠላት ላይ ሙሉ በሙሉ በደረሰ የድምሰሳ ፍጻሜ ተጠናቋል። የጀግኖቹም ደም በድል ተክሷል። በዕለቱም ማትያስ ማድቦ ሲመራው የነበረ ጦር በጀግኖቹ ምት በኮላሽ ተራራ ተቀብሮ የብልፅግና ሹማምንቶችን ሀዘን ያስቀመጠ ክስተት ሆኖ አልፏል።
"ጀግና ቢወድቅም የጀመረው ዓላማና የለኮሰው የነጻነት እሳት መቼም ቢሆን አይጠፋም።"
• ለተከበሩ ቤተሰቦቻቸው፦ በእንዲህ ዓይነት የቁርጥ ቀን የህልውና ዋስትና የሆኑ ጀግኖችን ለአማራ ሕዝብ ያበረከታችሁ የጀግና ወላጆችና ቤተሰቦች፤ ሐዘናችሁ የሁላችንም ሐዘን ቢሆንም ማኅፀናችሁ በኩራትና በክብር ሊመሰገን ይገባዋል። ፈጣሪ ጽናቱንና መጽናናቱን ይስጣችሁ።
• ለትግል ጓዶቻቸው፦ የአብሮነት፣ የደምና የዓላማ ጓዶቻቸው የሆናችሁ የነጻነት ታጋዮች፤ የጀግኖቹ መውደቅ የትግል ወኔያችሁን የሚያጠነክር፣ የተረከባችሁትን አደራ በድል ለማጠናቀቅ ጉልበት የሚሆን ነው። የአማራ ሕዝብ ህልውና የሚረጋገጠው በጀግኖች መስዋዕትነት እና ጠላትን በየቦታው በመቅበር በመሆኑ፣ ከትናንቱ ነገ ይበልጥ እንድትጠነክሩ ያደርጋችኋል። ጀግንነታችሁ ይቀጥል!
• ለመላው የአማራ ሕዝብ፦ ሕዝባችን እንደነዚህ ያሉ ውድ ልጆቹን ለነጻነቱና ለህልውናው ሲል መስዋዕት አድርጓል። ታሪክ የማይረሳቸው እነዚህ ሰማዕታት የቁጭትና የድል አርማዎቻችን ናቸው።
የጀግኖቹ የአርበኛ ፀጋው ታፈሰ እና የቀኝአዝማች አቡ አሳመረው ስምና ታሪክ በትውልድ ልብ ውስጥ ለዘላለም ሕያው ሆኖ ይኖራል!
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! ፈጣሪ ለቤተሰቦቻቸውና ለጓዶቻቸው መፅናናትን ይስጥ!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
በሸበል በረንታ የሚሊሻ መዋቅር እየፈራረሰ ነው!!
ሀምሌ 05/2018 ዓ.ም
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
በ64ኛ ክ/ጦር ቀጠና ሸበል በረታ ወረዳ የድውሃ ከተማ የሚገኘው የአገዛዙ ቅጥረኛ የሚሊሻ ሰራዊት አባላት አገዛዙ በትግራይ ክልል ግዳጅ መስጠቱን ተከትሉ ለአገዛዙ ቅጥረኛ ሆኖ የቆዩ የሚሊሻ ሰራዊት አባላት በዛሬው እለት ሀምሌ 05/2018 ዓ.ም ብርቁ አየለ የተባለ የፖራ ኮማንዶ አባል አንድ ኮሪያ ክላሽ በመያዝ አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ተቀላቅሏል።
የውሸት ማዕበል በጥበብ ምድር፦ የአማራነት ስም ራሱ የክብር፣ የውበትና የልዕልና መገለጫ በሆነባት በዚያች ጥንታዊት ምድር ላይ፣ ዛሬ የክህደት ጭጋግ ዙሪያውን ከቧታል። ታሪክ በአንበሶች ደም በተጻፈባት አገር፣ ዛሬ ግን ሆዳቸውን እንደ አምላክ የሚያመልኩ፣ ለጥቅማቸው ሲሉ ወገኖቻቸውን አሳልፈው የሚሰጡ "የውስጥ አሳማዎች" በዝተዋል።
በቤተ-መንግስቱ ወንበር ላይ ከተቀመጠውና አገርን እንደ ህፃናት መጫወቻ ከሚያይ ጨቅላ መሪ ጀምሮ፣ እስከ ታችኛው ካድሬ ድረስ የሚነፋው የፕሮፓጋንዳ ጥሩምባ ህዝብን ለማደንዘዝ ይጮኻል። በዚህ ዘመን እኮ በኢትዮጵያ ምድር ተምሮ መመረቅ ማለት ትርጉሙ ተቀይሯል፤ የትናንቱ ታላቅ የዕውቀት ማዕረግ ዛሬ ክብሩ ረክሶ፣ ማስተርስና ዲግሪው የድሮዋን የአስራ ስድስት ሉክ ደብተር ያህል እንኳ ዋጋ የሌለው ባዶ ወረቀት ሆኗል። በዚህ የወረቀት ክምርና የውሸት ድግስ መሃል ታዲያ፣ የብልፅግና ልሳኖች "አንድ ታላቅ ታጋይ ተመረቀ!" እያሉ ከበሮ ይደልቃሉ።
"የአንበሳ ቆዳ የለበሰ ሁሉ አንበሳ አይሆንም፤ አንዳንዱ ቆዳውን የሚለብሰው የበጎቹን መንጋ በቅርብ ሆኖ ለመበላት ነውና።"
የካፒቴኑ ቲያትር እና የተገለጠው ገመና የዚህ የተቀነባበረ ተውኔት ዋና ተዋናይ ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ ይባላል። በህዝቡ ዘንድ "የፋኖ አመራር ነበር" እየተባለ ስሙ በከንቱ ቢገነባም፣ እውነታው ግን የዚህን ተቃራኒ ነበር። ማስረሻ በልብሱ ውስጥ የፋኖን ስም፣ በልቡ ውስጥ ግን የብልፅግናን ፍቅር የያዘ፣ ከስርአቱ ጋር በምስጢር እየሰራ ህዝቡን ሲያታልል የኖረ የጥቅም ምርኮኛ ነበር።
ያ ሁሉ የትናንቱ "ትግል" እና "የድርድር" ድራማ፣ ዛሬ ለደረሰበት የጥቅም ማማ አስቀድሞ የተሰራ የካሜራ ጀርባ ቲያትር እንጂ ሌላ አልነበረም። ከግጭቱ በፊት ጀምሮ ከጌቶቹ ጋር ሲያሴርበት የነበረውን መንገድ ዛሬ ፍፃሜው ላይ አድርሷል።
ዛሬ በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ አደባባይ የክብር ካባ ተደርጎለት፣ በ"ሰላምና ደህንነት" (Peace and Security) የትምህርት ዘርፍ በማስተርስ ዲግሪ ተቀዳጀ ተብሎ ሲወራለት፣ የውስጥ አዋቂዎች ግን በምልከታቸው ይሳለቁ ነበር። ለመሆኑ እርሱ ያጠናው ሰላም የማንን ደህንነት ለመጠበቅ ነው? የራሱን ወይስ የጌቶቹን?
የማይሸሸገው እውነት ካፒቴኑ የክብር ቆብ ቢደፋም፣ የተመረቀበት ወረቀት ግን የሆዳምነቱንና የክህደቱን ታሪክ ሊሸሽግለት አልቻለም። የብልፅግና ካድሬዎች "ታጋዩ በድርድር ወደ ሰላም ገባ" እያሉ ታሪክ ለመቀየር ቢውተረተሩም፣ የዋዛው ህዝብ ግን ጭንብል አውላቂዎችን ጠንቅቆ ያውቃል። በትግል ስም የሚነግዱትና በሰላም ስም ጥቅማቸውን የሚያድኑት ሲያልፉ፣ እውነተኛው የነጻነትና የክብር ጉዞ ግን በፅኑ መሠረት ላይ ይቀጥላል። Dave Amhara
የፅናትና የክብር ተምሳሌቶች የነፃነት አባት ራስ አርበኛ ዘመነ ካሴ፥በቀኖቹ መከራና በጨለማው ዘመን፣ የአማራ ህዝብ ታሪክና ማንነት አደጋ ላይ ሲወድቅ፣ የቁርጥ ቀን ልጆቹ ዳር ቆመው አልተመለከቱም። እውነተኛው ፋኖ ማለት የጥንታውያኑ አባቶች የአርበኝነት መንፈስና የጀግንነት ደም በውስጡ የሚፈላ፣ ለህዝቡ ነጻነትና ክብር ሲል ነፍሱን በደረት ኪሱ ይዞ የተነሳ የቁርጥ ቀን ጀግና ነው።
እነዚህ ጀግኖች እንደ ዱር አራዊትና እንደ ሆድ አምላኪዎች ለጥቅምና ለስልጣን አይሮጡም፤ መኝታቸውን በበረሃው ድንጋይ፣ ትራሳቸውን በጠመንጃቸው አድርገው፣ በቁርና በሃሩር የሚጋደሉት ለአንድ እና ለአንድ ዓላማ ብቻ ነው የአማራ ህዝብ በገዛ ምድሩ ላይ አንገቱን ቀና አድርጎ፣ በነጻነትና በክብር ይኖር ዘንድ!
የፋኖ ጀግንነት መገለጫዎች የመንፈስ ልዕልና እና ፍርሃት-አልባነት፦ እውነተኛ ፋኖዎች ከፊት ለፊታቸው የሚመጣውን ዘመናዊ የጦር መሣሪያ ሳይሆን ከጀርባታቸው ያለውን የህዝብ ሰቆቃና እንባ የሚያዩ ናቸው። የጠላት ብዛትና የኃይል ሚዛን አያስፈራቸውም፤ በልባቸው ውስጥ ያለው ፍቅርና እምነት ከማንኛውም የብረት ጋሻ ይበልጣል ረቂቅ ነው።
የህዝብ ጋሻና አለኝታነት፦ ፋኖ ለህዝቡ እረኛ፣ ለጠላት ግን መብረቅ ነው። በሄዱበት ምድር ሁሉ የሴቶች ረዳት፣ የህፃናት ዋስትና፣ የአረጋውያን ምርኩዝ በመሆን የሞራል ልዕልናቸውን ያስመሰክራሉ። የእነሱ ጀግንነት የሚለካው በጦር ግንባር በሚያስመዘግቡት ድል ብቻ ሳይሆን፣ ለህዝባቸው በሚያሳዩት ፍፁም ትህትናና ታማኝነት ጭምር ነው።
የታሪክና የማንነት ጠባቂዎች፦ የአማራን ህዝብ ታሪክ ለመበረዝ፣ ባህሉን ለማርከስና ህልውናውን ለማጥፋት ለሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ሁሉ የቆሙ የማይናወጡ የዓለት ምሶሶዎች ናቸው። የትናንቱን የአባቶቻቸውን የአርበኝነት ታሪክ ዛሬም በደማቸው እያደሱት ይገኛሉ። የልብ ፅናት "ጀግንነት ማለት ታጥቆ መፎከር ብቻ አይደለም፤ ጀግንነት ማለት ህዝብ በተጨነቀበት ቀን፣ ሁሉም በፈራበትና በከዳበት ሰዓት፣ 'እኔ አለሁልሽ!' ብሎ ለፍትህና ለክብር መሰዋት ነው።
እውነተኛ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች (ፋኖዎች) በታሪክ መዝገብ ላይ በወርቅ ቀለም የሚጻፉ፣ የትውልድ ኩራትና የነጻነት መብራቶች ናቸው። ስማቸው በጭቃ ሊለሰን፣ ታሪካቸው በከንቱ ፕሮፓጋንዳ ሊጠለሽ አይችልም፤ ምክንያቱም የእነሱ ጀግንነት የተገነባው በሆድና በጥቅም ሳይሆን፣ በማይበገረው የአማራ ህዝብ የልብ ትርታ ላይ ነው! Dave Amhara
+1
201ኛ ክር 74ኛ ክ/ጦር የአባይ ሸለቆ ተርቦች ዲቦ ከተማ የመሸገው ጠላት ላይ ድንቅ ስራ ሰርተዋል።
➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺
...ሐምሌ 05/2018 ዓ/ም
የብልፅግናውን እንክርዳድ ሰራዊትን ሐምሌ 04/2018 ዓ.ም ምሽት 10:00 ሰአት ላይ ከዲቦ ንዑስ ወረዳ ዲቦ ከተማ ተከማችቶ የነበረው ሚሊሻ ከካምፕ ወጥቶ እነብሬ ቀበሌ ተንቀሳቅሶ የነበረውን የሸለቆው አዳኞች ባልጠበቀው መልኩ ድንገተኛ ጥቃት በመፈፀም ሙትና ቁስለኛ አድርገውታል።
በዚህም 05 ሚሊሻና ፖሊስ አድማ በትን ወደ ላይኛው ሲሸኝ ሌላው እግሩ ወደመራው ሲበታተን በርካታው ቆስሎ ሆስፒታል የገባ ሲሆን የብሬን እና የክላሽ ተተኳሾችንም መማረክ ችለዋል።
በእለቱ ከተሸኙት የአብይ አገልጋዮች ውስጥም፦
1ኛ.ተመስገን ይርጋ
2ኛ.ትልቅ አወቀ ብሬን ተኳሹ ጥቂቶቹ ሲሆኑ አብርሃም ወሎየው ፖሊስ በከባድ ከቆሰሉት ውስጥይገኙበታል።
በመጨረሻም አሁንም አልረፈደም ጠብ አጫሪው አብይ አህመድ በሚጠራው የጦርነት ድግስ ውስጥ እየገባችሁ የምትማገዱ የብልፅግና አገልጋዮች ኑ የአማራ ፋኖ ይቅር ባይ ነውና በይቅርታ ወደ ቤተሰባችሁ ተቀላቀሉ በማለት ጥሪያችን እናስተላልፋለን
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
ካራማራ ክፍለ ጦር ለወራት ሲያሰለጥን የቆየውን እግረኛ ሠራዊት በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ
በአፋብን በላይ ዘለቀ ዕዝ መይሳው ካሳ ኮር ሥር የሚንቀሳቀሰው ካራማራ ክፍለ ጦር፡ ለወራት በወታደራዊ እና በፖለቲካዊ ትምህርቶች ሲያሰለጥን የቆየውን ሠራዊት በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አስመርቋል።
ካራማራ ክፍለ ጦር በዘንድሮው ዓመት በአገዛዙ ጥምር ሠራዊት ላይ በተደጋጋሚ በማያቋርጥ ኦፕሬሽን ከፍተኛ ድሎችን በማስመዝገብ የበላይነቱን ሲያሳይ የቆየ ታላቅ አደረጃጀት ነው።
ክፍለ ጦሩ ከወታደራዊ ተጋድሎ ጎን ለጎን፣ ወቅቱን የተረዳ፣ ጠንካራ ሥነ-ልቦና እና ጥልቅ የፖለቲካ ግንዛቤ ያለው ሠራዊት በመገንባት ረገድ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል።
አዲስ የተመረቁት ሠራዊት በክፍለ ጦሩ የተሰዉ ጓዶቻቸውን እና እንደ አርበኛ ፈንታሁን ገበየሁ ያሉ ጀግና አመራሮችን በማስታወስ ቃል ኪዳን ገብተዋል።
ሠራዊቱ በትግሉ ሂደት የጀግኖች አባቶቻቸውን አደራ በመቀበል፣ በደምና በአጥንት ዋጋ የሀገሪቱን የዘንዶ ሥርዓት በማስወገድ፣ በምትኩ ፍትሐዊ እና መልካም ሥርዓትን ለትውልድ ለማስረከብ እስከ ድል ድረስ እንደሚታገል በታላቅ ቃል ኪዳን አረጋግጠዋል።
ይህ የሠራዊት ምልመላ እና ስልጠና የፋኖን ድርጅታዊ አቅም በማሳደግ፡ ትግሉን ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር እና የጠላትን ኃይል ሙሉ በሙሉ ለመደምሰስ የሚያስችል ወሳኝ ምዕራፍ ተደርጎ ተወስዷል።
የጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 47ኛ ክ/ጦር አትሮንስ ሻለቃ ደፈጣ በመጣል በአገዛዙ ሰራዊት ላይ የማያዳግም እርምጃ ወሰደች!
አፋብን ወሎ ቤተ_አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 47ኛ ክ/ጦር የአትሮንስ_ሻለቃ ተናዳፊ ተርቦች በኦህዴድ/ብልፅግና ወንጀለኛ ቡድን ሥልጣን ጠባቂ ቅጥረኛ ኃይል ላይ ደፈጣ በመጣል የክ/ጦርና የሻለቃ አመራሮችን ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ከፍተኛ ሰብዓዊ ኪሳራ አድርሰውበታል።
04/11/2018 ዓ.ም በአምሓራ ሳይንት ሰማይ ስር እፁብ ድንቅ ተብሎ በተመሰገነውና ድንገተኝነትን ባተረፈው የደፈጣ ጥቃት ከደንሳ ከተማ ወደ በለጩማ በ 7 መኪና ሲጓጓዝ የነበረ ወራሪ ኃይል ልዩ ቦታው ወጀድ መገንጠያና ጎዴል በተባሉ ስትራቴጅክ ቦታዎች ላይ የአትሮንስ ሻለቃ ትንታጎች አከርካሪውን በማድቀቅ አሽመድምደውታል።
በዚህ አስደናቂ ጥቃት ክ/ጦር ዘመቻ ኃላፊ ሻለቃ ወልደ ጊዮርጊስና የሻንበል ማዕረግተኛ የሆነው አስራት ከባድ ቁስለኛ ሲሆኑ ሌላኛው ማዕረጉ ለጊዜው ያልታወቀ መስመራዊ መኮነን እስከ አጃቢው ለዘላለም ማሸለቡ ታውቋል።
አመራሮቹን አጅበው በፓትሮልና በካሶኒ ታጭቀው ሲጓዙ ከነበሩት በአልታሰበና ድንገተኛ የቦንብና የጥይት ጥቃት ተጋላጭ በመሆናቸው አያሌ ቁጥር ያላቸው መሠረታዊ ወታደሮች ለኦህዴድ/ብልፅግና ወንጀለኛ ቡድን ሥልጣን ለመጠበቅ ሲባል የመስዋዕት በግ ሆነው ወደከርሰ_መቃብር በመውረድ በአፍንጫቸው አፈር ፈሷል።
የክ/ጦር ዘመቻ ኃላፊው ሻለቃ ወልደ ጊዮርጊስ አጃቢ መሠረታዊ ወታደር ከድር ጀማል ከቀናት በፊት ወደ ፋኖ መኮብለሉ የሚታወቅ ነው። ዛሬ ደግሞ ሻለቃ ወልደ ጊዮርጊስና ሌሎች የክ/ጦርና የሻለቃ አመራሮች በከፍተኛ አጀብ ተከበው ለመንቀሳቀስ ቢሞክሩም እነሆ ከመቅሰፍቶቹ የጥይት ሀሩር ግን ማምለጥ አልቻሉም።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!!
ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ_አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!
05/11/2018 ዓ.ም
